fa
Feedback
Addis Ababa City Manager Office

Addis Ababa City Manager Office

رفتن به کانال در Telegram
1 474
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-37 روز
-2130 روز
آرشیو پست ها
ይህንን ያዉቁ ኖሯል? የዘውዲቱ መታሰቢያ ሆስፒታል ከተመሰረተበት 1934 አንስቶ ላለፉት 90 አመታት 261 አልጋ እና 4 የኦፕሬሽን ክፍሎች ብቻ ነበሩት፡፡ በቅርቡ በክብርት ከንቲባ አዳነች አቤቤ እና ሌሎችም ከፍተኛ አመራሮች የተመረቀው የማስፋፊያ ግንባታ አገልግሎቱን በእጥፍ በማላቅ 320 አልጋዎች እና 8 የኦፕሬሽን ክፍሎች ፣ እንዲሁም የራሱ ኦክስጂን ማምረቻ አሉት። ለታካሚዎች ፣ ለአስታማሚዎች እና ለጤና ባለሙያዎች ምቹ ሁኔታ የፈጠረው አዲሱ የማስፋፊያ ግንባታ ዘመኑ የደረሰበትን ቴክኖሎጂዎች የተሟሉላቸው የህክምና ግብዓቶች ጭምር ተሟልተውለታል። ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager

በተባበሩት መንግሥታት የአየርንብረት ለውጥ ማሕቀፍ ኮንቬንሽን መሠረት የኢትዮጵያ የኮፕ 32 አስተናጋጅ ሀገር መሆኗን ተከትሎ የኢትዮጵያ መንግሥት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የሆኑትን ዶክተር ጌዲዮን ጢሞቴዎስን የኮፕ 32 ተወካይ ፕሬዝደንት አድርጎ መመደቡን ሲገልጽ ደስታ ይሰማዋል። ዶክተር ጌዲዮን ከሀገር ውስጥ የሥራ ኃላፊዎች፣ ከተባበሩት መንግሥታት አካላት እና አለምአቀፍ አጋሮች ጋር በመተባበር የኮፕ 32 ዝግጅትን የሚመሩ ይሆናል። የኢትዮጵያ መንግሥት የተባበሩት መንግሥታት የአየርንብረት ለውጥ ማሕቀፍ ኮንቬንሽን አባል ሀገራት ለኢትዮጵያ የማዘጋጀት ኃላፊነት በመስጠታቸው ምስጋናውን እያቀረበ በዶክተር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ አስተባባሪነት ከአለም የአየር ንብረት ጥበቃ ማኅበረሰብ ጋር በቅርበት ለመሥራት ዝግጁ መሆኑን ይገልፃል። #PMOEthiopia

ከተማ የልማት ስራዎች የኢትዮጵያ የመልማት አቅም ማሳያዎች ናቸዉ ፡፡"በጉብኝቱ የተሳተፉ ሰልጣኝ አመራሮች "በመደመር መንግስት እይታ የዘርፎች እመርታ "በሚል መሪ ቃል በሁለተኛ ዙር በአዲስ አበባ ስልጠና ሲከታተሉ የነበሩ የፌዴራል እና የአዲስ አበባ ከተማ የብልፅግና ፓርቲ አመራሮች በአዲስ አበባ ከተማ የተሰሩ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎችን ጎበኙ፡፡ የወንዝ ዳርቻዎች፤አዲስ የመሶብ የአንድ ማእከል ዲጂታል አገልግሎት፤የዘዉዲቱ ሆስፒታል ማስፋፊያ ማእከል፤ልፍቶ ሁለገብ የገበያ ማእከል፤የአንድ ማዕከል አገልግሎት እና ሳይንስ ሙዚየም እና በዘጠኝ ወራት ዉስጥ ተገንብተዉ የተጠናቀቁ የጋራ መኖሪያ ቤቶች በጉብኝቱ የተካተቱ እና እየተጎበኙ የሚገኙ ይገኛሉ ፡፡ ሰልጣኝ አመራሮች እስከ አሁን ባደረጓቸዉ የመስክ ጉብኝቶች እንደተናገሩት የከተማ የልማት ስራዎች የኢትዮጵያ የመልማት አቅም ማሳያዎች መሆናቸው በሰጡት አስተያየት ገልፀዋል፡፡ ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager

የፓርቲያችን ሰው ተኮርነት በተግባር የታየበት ፣ እና ምቹ እና ፅዱ አዲስ አበባን ስሟን እና ግብሯን በሚመጥን ደረጃ የማልማት ተግባር የታየበት የአራዳ ፓርክ..! በመደመር መንግስት እይታ የዘርፎች እመርታ በሚል መሪ ቃል በሁለተኛ ዙር በአዲስ አበባ ስልጠና ሲከታተሉ የነበሩ የፌዴራል እና የአዲስ አበባ ከተማ የብልፅግና ፓርቲ አመራሮች በአዲስ አበባ ከተማ የተሰሩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው!!

በመደመር መንግስት እይታ የዘርፎች እመርታ በሚል መሪ ቃል በሁለተኛ ዙር በአዲስ አበባ ስልጠና ሲከታተሉ የነበሩ የፌዴራል እና የአዲስ አበባ ከተማ የብልፅግና ፓርቲ አመራሮች በአዲስ አበባ ከተማ የተሰሩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው!!

ኢትዮጵያ የጥንታዊ ስልጣኔ ሃገር ናት።በአይበገሬነት የምትታወቅ ሲሆን የወደፊት ተስፋዋም እየተፃፈ ነው።ሕዝባችንም የማይነዋወጥ ማህበረሰብ ገንብቷል። መደመር የመጣው ከዚህ ማህበረሰባዊ ትሩፋት ነው።በተቀናጀ ትብብር ውስጥ ያለ የሚባዛ አቅምና ለሁሉም የሚተርፍ እድገ… See more

አዲስ አበባ እንዴት ነው ያማረባት? የሲንጋፖር ጠቅላይ ሚኒስትር ላውረንስ ዋንግ… See more

በትራንስፖርትና በማዘጋጃ ቤታዊ ክላስተር የማስፈፀሚያ ማኑዋል ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተካሄደ። የአዲስ አበባ ከተማ ስራ አስኪያጅ ፅ/ቤት በትራንስፖርትና ማዘጋጃ ቤታዊ ክላስተር ተቋማት ጋር በቅንጅታዊ አሰራር መሠረት በ2018 በጀት አመት በቅንጅት የሚሰሩ ስራዎችን በተመለከተ ለክፍለ ከተማ የክላስተሩ አባላት በተዘጋጀዉ የማስፈፀሚያ ማኑዋል ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በዛሬዉ እለት አካሂዷል። በመድረኩም እንደተገለፀዉ በትራንስፖርትና ማዘጋጃ ቤታዊ ክላስተር ተቋማት በቅንጅት በከተማችን የተቀናጀ የትራንስፖርት ስርዓት ለመዘርጋት ቅንጅታዊ አሰራርን ተግባራዊ በማድረግ መሰራት መቻሉ እንዲሁም የሚከናወኑ ተግባራት በእቅድ ተይዘዉ ወደ ስራ መገባቱ የተግባር ምዕራፍ ስራዉ ላይ ዉጤት እንዲመዘገብ ማስቻሉ ተመልክቷል። የሚሰጡ አገልግሎቶችን የአሰራር ስርዓትን በመዘርጋት እንዲሁም ተቋማት የተሰጣቸውን ሀላፊነት ተግባራዊ ከማድረግ አንፃርና በከተማዋ የሚሰጠዉን አገልግሎት በይበልጥ ለማዘመን በእቅድ የተያዙ ስራዎችን ጨምሮ ሌሎችም በተቋማት ቅንጅት የአገልግሎት አሰጣጡን ለማሻሻል እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች ተናባቢ በሆነ መንገድ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባም ተገልጿል። በመድረኩም በቀጣይ ቅንጅታዊ አሰራሩን በማጠናከር ረገድ የሚከናወኑ ተግባራት እንዲሁም ከተቋማትና በየደረጃው ካሉ መዋቅሮች የሚጠበቁ አገልግሎቶች ምን መሆን እንዳለበት የሚያሳይ ሰነድ ቀርቦ ዉይይት ተካሂዶበታል። ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት፡- ዛሬ ጠዋት የዩናይትድ ስቴትስ የአፍሪካ እዝ አዘዥ ጄነራል ዳግቪን አር ኤም አንደርሰንን አግኝቼ በቀጠናዊ የጸጥታ እና የበለጠ ትብብር ለማድረግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ውይይት አድርገናል።

የሁለቱ መሪዎች ወግ - በምስል #PMOEthiopia