1 474
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-37 روز
-2130 روز
آرشیو پست ها
በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ ከሳርቤት - ጀርመን አደባባይ- ጋርመንት ፉሪ የሚዘልቀውን የኮሪደር ልማት አስመልክቶ የሰጡት ማብራሪያ:-
በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ ከካዛንቺስ ኮሪደር ቀጥሎ በመዲናዋ ሁለተኛው; ረጅሙ እና ሰፋ ያለ አካባቢ የሚሸፍነዉ ከሳርቤት - ጀርመን አደባባይ- ጋርመንት ፉሪ የሚዘልቀው የኮሪደ… See more
የኮሪደር ልማት የመዲናዋን ዘመናዊነት ከማሳደግ ተሻግሮ የተሻሻለ የኑሮ ዘይቤ ልምምድን እውን አድርጓል ተባለ
የኮሪደር ልማቱ የዜጎችን ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ያረጋገጠና ቃልን በተግባር የቀየረ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
የሳር ቤት - ጀርመን አደባባይ - ጋርመንት እና ፉሪ አካባቢ የኮሪደር ልማት አካታችና የዜጎችን ፍትሃዊ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ቃልን በተግባር የቀየረ ነው ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት ጋር በመሆን የተጠናቀቀውን የሳር ቤት - ጀርመን አደባባይ - ጋርመንት እና ፉሪ አካባቢ የኮሪደር ልማት ሥራ ጎብኝተዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ የኮሪደር ልማቱን በማስመልከት ባደረጉት ገለጻ፤ ሳር ቤት - ጀርመን አደባባይ - ጋርመንት እና ፉሪ የኮሪደር ልማት በከተማዋ በሁለተኛው ዙር ከተከናወኑ የኮሪደር ልማት ስራዎች መካከል አንዱ ነው።
የኮሪደር ልማቱ ከመንገድ መሰረተ ልማት በተጨማሪ በርካታ የከተማ መልሶ ማልማት ስራዎች የተካተቱበት መሆኑንም ጠቁመዋል።
በኮሪደር ልማቱ ዜጎች የስራ እድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ጥረት መደረጉን አመልክተው፤ ለዚህም 1ሺህ 100 ሱቆች የኮሪደር ልማት አካል ሆነው መገንባታቸውን አብራርተዋል።
ይህም ልማቱ የዜጎችን ፍትሃዊ ተጠቃሚነት በተግባር ያረጋገጠ ነው ብለዋል።
በዋናነት ለአካባቢው ነዋሪዎች ብቻ ሳይሆን የከተማዋን ዜጎች ተጠቃሚ ማድረግ የሚያስችል 20 የስፖርት ማዘውተሪያ ሜዳዎችና 20 የህጻናት መጫወቻ ስፍራዎች መገንባታቸውን ገልጸዋል።
የጽዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ አካል የሆኑና ደረጃቸውን የጠበቁ 40 የህዝብ መጸዳጃ ቤቶች ግንባታን ጨምሮ አምስት ነጥብ ሁለት ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የወንዝ ዳርቻ ልማት ስራዎች በኮሪደር ልማቱ ማካተት ተችሏል ነው ያሉት።
ሳርቤት - ጀርመን አደባባይ- ጋርመንት ፉሪ የሚዘልቀው የኮሪደር ልማት ምን ምን አካቷል?
*******************
• እስከ 60 ሜትር የሚሰፋ 16.5 ኪ.ሜ አስፓልት መንገድ (በተጨማሪ 3 .5 ኪ. ሜ የውስጥ ለውስጥ መንገድ) አለው፣
• 33 ኪ.ሜ የእግረኛ መንገድ
• 13.3 ኪ.ሜ የሳይክል መንገድ
• 21 የተለያዩ ፕላዛዎች
• ክረምት ከበጋ ፣ በቀን እና በምሽት አገልግሎት የሚሰጡ 20 የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች
• 20 የልጆች መጫወቻ ቦታዎች
• 5.2 ኪ.ሜ ርዝመት ያለው የወንዝ ዳርቻ ልማት
• 20 የመኪና ማቆሚያ ቦታና ተርሚናሎች ፣ 1 የመኪና ቻርጂንግ ስቴሽን
• በግለሰቦች እና በመንግስት የተገነቡ 1,107 የንግድ ቤቶች
• 50.5 ሄክታር ስፋት ያላቸዉ አረንጓዴ ቦታዎች
• 40 የሕዝብ መፀዳጃ ቤቶች
• 38 የታክሲና አውቶቡስ ቤይ
• 13 ካፌዎች እና 1 ሬስቶራንት እንዲሁም ከ 1 ሄክታር በላይ የነርሰሪ ቦታን በዉስጡ አካትቶ ይዟል።
ከሳር ቤት እስክ ፉሪ የተገነባዉን የኮሪደር ልማት አስመልክቶ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ የሰጡት ማብራሪያ:-… See more
2ኛውን የኢትዮጵያ ወጣቶች ኦሎምፒክ ጫወታዎች ውድድር ዛሬ ማለዳ በአዲስ አበባ ስታዲየም በድምቀት አስጀምረናል።
ከተማችን ይህንን ውድድር በማስተናገዷ ደስታ ይሰማናል። መላው የስፖርት ቤተሰብ በውድድሩ ስፍራዎች በመታደም የነገ ተተኪ ስፖርተኞችን እንዲደግፍ እና እንዲያበረታታ ጥሪዬን አስተላልፋለሁ።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ
Dorgommii Taphoota Olompikii dargaggoota Itoophiyaa 2ffaa har'a ganama istaadiyoomii Finfinneetti bifa hoo'aa ta'een eegalchiisneerra.
Magaalaan teenya dorgommii kana kessummeessuu isheetti gammachuutu nutti dhaga'ama. Maatiin ispoortii magaalaa keenyaa hundi bakkeewwan dorgommichaatti argamuun kanneen ispoortiin boru bakka bu'an akka deeggaruu fi akka jajjabeessu waamicha koon dhiheessa.
Waaqni Itoophiyaa fi Uummata Ishee Haa Eebbisu
በአዲስ አበባ ከተማ የተከናወኑ የኮሪደር ልማት ስራዎች የመዲናዋን አለምዓቀፍ ተመራጭነት ከማሳደግ ባለፈ ጤናማ የከተሜነት እንቅስቃሴ እንዲኖር ያስቻለ ነው ሲሉ በም/ ከንቲባ ማእረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ወንድሙ… See mor
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት ጋር በመሆን የተጠናቀቀውን የሳር ቤት-ጀርመን አደባባይ-ጋርመንት እና ፉሪ አካባቢ የኮሪደር ልማት ሥራ ጉብኝት (በምስል)
