fa
Feedback
Addis Ababa City Manager Office

Addis Ababa City Manager Office

رفتن به کانال در Telegram
1 474
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-37 روز
-2130 روز
آرشیو پست ها
ዛሬ በይፋ መርቀን ስራ ያስጀመርነው የዘዉዲቱ መታሰቢያ ሆስፒታል የላቀ የሕክምና ማዕከል ዓለም አቀፍ ጥራት ደረጃ በጠበቀ መልኩ ተገንብቶ ዘመኑን የዋጀ የህክምና አገልግሎት አሰጣጥን የሚያሟላ ነው። በውጪ ሀገራት ንፁህ እና ዘመናዊ የህክምና መሳሪያ የተሟላላቸዉ የህክምና ማእከላትን ስናይ “ መቼ ይሆን በሃገሬ ይህንን የመሰለ ለባለሙያው፣ ለታካሚው እንዲሁም ለአስታማሚው ጭምር የተመቸ ዘመናዊ የጤና ማዕከል የሚኖረው?” ለሚለው ቀና ቁጭት ምላሽ የሰጠ ነው። ይህ የላቀ የሕክምና ማዕከል የተለያዩ አገልግሎቶች የተካተቱበት ሲሆን ፦ • የተኝቶ ህክምና ህሙማን ክፍሎች (IPD) • የጨረር ህክምና አገልግሎቶች • ኤም አር አይ፣ ሲቲ-ስካንእና ኤክስሬይ • የህፃናት እና የአዋቂዎች ፅኑ ህሙማን ክፍሎች (ICU) • የኦክስጅን ማምረቻ ፕላንት • የቪአይ ፒ አልጋዎች • የኦፒዲ ክፍሎች • የኦፕራሲዮን ክፍሎች(OR) እና የማገገሚያ ክፍሎች እንዲሁም • የድንገተኛ ክፍል አልጋዎች • በየህክምናው አይነትና በየወለሉ ፋርማሲ እና የመድሃኒት ስቶር • ላቦራቶሪ • የአስተዳደር ቢሮዎች • የማብሰያ ክፍሎች፣ ዋና ካፊቴሪያ፣ በየወለሉ ለሚገለግሉ ባለሙያዎች የሚሆኑ ካፊቴሪያዎች • የመሰብሰቢያ አዳራሽ፣ እንዲሁም ሌሎች ተጨማሪ አገልግሎት የሚሰጡ ክፍሎችን ከውብ ምድረ ግቢ ጋር አካቷል፡፡ ይህን ለማሕበረሰባችን ፋይዳው እጅግ የላቀ የጤና ማዕከል ለአገልግሎት እንዲበቃ የበኩላችሁን አስተዋፅዖ ያበረከታችሁ ተቋማት ፣ አመራሮች እና ባለሙያዎችን በተገልጋዩ ሕብረተሰብ እንዲሁም በራሴ እና በከተማ አስተዳደሩ ስም ከልብ አመሰግናለሁ ። በማዕከሉ የምትገኙ ውድ ባለሙያዎች፣ ለህሙማን የምትሰጡትን አገልግሎት የሚያቀልላችሁ የላቀ የሕክምና ማዕከል እንኳን አገኛችሁ እያልኩ በአግባቡ እንትጠቀሙበት እና ከምንጊዜውም በላይ ሙያዊ ስነምግባር እና ርህራሄ እንዳይለያችሁ አደራ እላለሁ። ፈጣሪ ኢትዮዽያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ ከንቲባ አዳነች አቤቤ

እንኳን ደስ አላችሁ !! ዛሬ በአንጋፋው የዘዉዲቱ መታሰቢያ ሆስፒታል አዲስ ሆስፒታልን የሚመጣጠን ማስፋፊያ ገንብተን፤ ዘመናዊ የህክምና መሳሪያ አሟልተን ስራ አስጀምረናል ። በዘውዲቱ መታሰቢያ ሆስፒታል የተገነባው የላቀ የሕክምና ማዕከል፣ በ1 ሺህ 800 ካ.ሜ ስፋት ላይ ያረፈ እና ባለ 10 ወለል ህንፃ ሲሆን ለተኝቶ ታካሚዎች አገልግሎት የሚሰጥ 320 አልጋ አለው። ይህም ላለፉት 91 ዓመታት የነበረውን የዘውዲቱ ሆስፒታል ታካሚ አገልግሎትን በእጥፍ ያሳድገዋል። ሆስፒታሉ ለህክምና ባለሙያው እና ለታካሚው በሚመች መልኩ የተገነባ ሲሆን አሁን ላይ የህክምናው ዘርፍ በደረሰበት ዘመናዊ የህክምና መሳሪያዎች የተደራጀ እና የራሱ ኦክስጂን ማምረቻ ጭምር ያለው ነው። ይህ ሆስፒታል አስተዳደራችን አዲስ አበባን የሜዲካል ቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ ለጀመረው ሥራ ተደማሪ አቅም የሚፈጥር ይሆናል። ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ Baga Gammaddan !! Har'a dursaa Hospitaala yaadannoo Zowdituutti babal'iinsa hospitaala haaraan kan madaalu ijaarree meeshaa yaalaa ammayyaa guutnee hojii eegalchiisneerra. Hospitaala yaadanoo Zowdituutti kan ijaarame giddugalaa yaalaa olaanaa, bal'ina kaaremeetira kuma 1 fi 800 irra kan qubatee fi gamoo abbaa darbii 10 yemmuu ta'u tajaajila ciisanii yaalamuuf siree 320 qaba. Kunis waggoota 91 dabraniif kan ture tajaajila yaalamtoota hospitaala zowdituu dachaan kan guddisuudha. Hospitaalichi ogeessota fayyaafi yaalamtootaaf bifa mijatuun kan ijaarame yemmuu ta'u ammarratti dameen yaalaa kan irra gahe meeshaalee yaalaa ammayyaan kan gurmaa'e fi oomishaa Oksijiinii mataasaas kan qabuudha. Hospitaalli kuni bulchiinsi keenya Finfinnee giddugala tuurizimii meedikaalaa taasisuuf hojii eegaleef humna dabalaataa kan uumu ta'a. Waaqni Itoophiyaa fi Uummata Ishee Haa Eebbisu

መዲናችን አዲስ አበባን እንደ ስሟ ውብ፣ ጽዱና ለነዋሪዎቿ ምቹ በማድረግ ረገድ ባለፉት የለውጥ አመታት የተሰራው ስኬታማ ስራ ከተማችን ትክክለኛ የብልጽግና ተምሳሌትነቷን በተግባር እንድታረጋግጥ አስችሏታል ሲሉ በም/ ከንቲባ ማእረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ ገለጹ። ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ ይህን የገለጹት የዘንድሮው የሀዳር ሲፀዳ የከተማ አቀፍ የጽዳት ንቅናቄ ይፋ ማድረጊያ መርሐግብር"ህዳር ሲፀዳ አካባቢያችን ጤና” በሚል መሪ ቃል በየካ ክፍለከተማ ተገኝተው ባስጀመሩበት ወቅት ነው። ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ አክለውም የአዲስ አበባ ከተማን የስማርት ሲቲ ግንባታ በማፋጠን ሂደት ስማርት ኢንቫይሮንመንትን ማረጋገጥ ወሳኝ ነው ሲሉ ገልጸው ይህን እውን በማድረግ ረገድም ሁሉም የከተማችን ነዋሪዎች ጽዳትን ከእራስ ቤትና ከአካባቢ እንደሚጀመር ተገንዝቦ ሰፊ ተሳትፎ በማድረግ ስልጣኔያችንና ዘመናዊነታችን በተግባር ልናሳይ ይገባል ብለዋል። የመዲናችን ነዋሪዎች ከተማችን ከጊዜ ወደ ጊዜ በጽዳቷና ውበቷ እያሳዬች ያለችውን ፍካት በጋራ ለመጠበቅ ሁሉም የከተማዋ ነዋሪዎች ጽዳትን ባህል እሰኪያደርጉ ድረስ ተከታታይነት ያለውና የተጠናከረ ስራ ሊሰራ እንደሚገባም አስገንዝበዋል። የየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ፍፁም ሀይሌ በበኩላቸው "ፅዳት የስልጣኔና የከተሜነት መገለጫ በመሆኑ ሁሉም ሰው አካባቢውን በማፅዳት ከተማችንን እና አካባቢያችንን ለመኖር ምቹ እና ጽዱ ለማድረግ ፅዳትን ባህል ማድረግ እንደሚገባ አሳስበዋል። ክፍለ ከተማ አስተዳደሩ ሞዴል ብሎኮችን በሁሉም ዘርፍ ለመፍጠር ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን የገለፁት አቶ ፍፁም ሀይሌ ይህ እንቅስቃሴ የከተማዋን መልካም ገጽታ ከመገንባት ባለፈ ለነዋሪዎች ጤናማ ኑሮ ወሳኝ መሆኑን አስረድተዋል። በንቅናቄው ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፅዳት አስተዳደር ኢጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ገዛበኝ ደሲሳ በበኩላቸው አካባቢያችንን በማፅዳት የዜግነት ግዴታችንን በመወጣት ህዳርን በንፅህና ልናሳልፍ ይገባል፤ በአግባቡ የተያዘ ደረቅ ቆሻሻ ሀብት ነው፤ ንፁህ አካባቢ ሲፈጠርም የራሳችንም የአካባቢያችንም ጤና የተጠበቀ ይሆናል ሲሉ መልዕከታቸውን አስተላልፈዋል። ይህ የፅዳት ንቅናቄ የየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደርና ነዋሪዎች ለጋራ ራዕያቸው ያላቸውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ሲሆን ንፁህ፣ ጤናማና ውብ የከተማ ኑሮ ለመፍጠር ትልቅ መነሳሳትን መፍጠሩ በመርሀ ግብሩ ተገልጿል። ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager

የዘንድሮው ህዳር ሲጸዳ መርሐግብር በመዲናችን በጽዳት አጠባበቅ ረገድ የመጡ እምርታዎችንና ለውጦችን በሚያጠናክሩ ሰፊ የማህበረሰብ ተሳትፎና የአመለካከት ለውጥን በሚያጎለብቱ የጽዳት ስራዎች የሚከወንበት እንደሚሆን በም/ከንቲባ ማእረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ አስታወቁ። ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ በዛሬው እለት "ህዳር ሲታጠን" በሚል በልማዳዊ እሳቤ ሲተገበር የቆየውን ባህላዊ የቆሻሻ አወጋገድ ስርአት 'ህዳር ሲጸዳ" በሚል በዘመናዊ የቆሻሻ አስተዳደር ስርአት በመተካት ካለፉት ሰባት አመታት ወዲህ በከተማችን ጽዳት አጠባበቅ ላይና ብክለትን በመቀነስ ረገድ አበረታች ስራዎች መከናወናቸውን አስረድተዋል። ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ በዛሬው እለት የህዳር ወር የጽዳት ንቅናቄ ስራዎች እቅድ ላይ በተካሄደው የውይይት መድረክ ላይ እንደገለጹት ነዘንድሮው የህዳር ሲጸዳ ንቅናቄ በማህበረሰቡ ተሳትፎ ላይ የተመሰረተ ከተማ አቀፍ የፅዳት እንቅስቃሴን በስፋት የሚተዋወቅበትና ተገቢ የሆነ የቆሻሻ አወጋገድ ስርአትንና ደረቅ ቆሻሻ መልሶ ጥቅም ላይ የማዋል ተግባርን የሚበረታታበት ነው ብለዋል። የዘንድሮ ህዳር ወር በፅዳትና በአካባቢ ጥበቃ ላይ የሕብረተሰቡን ግንዛቤ በማጎልበት ፥ዘላቂነት ያለው የቆሻሻ አወጋገድ ስርአት በህብረተሰቡ ውስጥ ባህል ሆኖ እንዲሰርፅ የሚያደርጉ ተከታታይ ድጋፎችን ምንሰጥበት ነው ሲሉ ገልጸው በዚህም የተለያዩ የማህብረሰብ ክፍሎች የጋራ መኖሪያ አካባቢዎች ፅዱና ጤናማ እንዲሆኑ በጋራ በመስራት ሃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል። ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager

የዘንድሮው ህዳር ሲጸዳ መርሐግብር በመዲናችን በጽዳት አጠባበቅ ረገድ የመጡ እምርታዎችንና ለውጦችን በሚያጠናክሩ ሰፊ የማህበረሰብ ተሳትፎና የአመለካከት ለውጥን በሚያጎለብቱ የጽዳት ስራዎች የሚከወንበት እንደሚሆን በም/ከንቲባ ማእረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ አስታወቁ። ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ በዛሬው እለት "ህዳር ሲታጠን" በሚል በልማዳዊ እሳቤ ሲተገበር የቆየውን ባህላዊ የቆሻሻ አወጋገድ ስርአት 'ህዳር ሲጸዳ" በሚል በዘመናዊ የቆሻሻ አስተዳደር ስርአት በመተካት ካለፉት ሰባት አመታት ወዲህ በከተማችን ጽዳት አጠባበቅ ላይና ብክለትን በመቀነስ ረገድ አበረታች ስራዎች መከናወናቸውን አስረድተዋል። ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ በዛሬው እለት የህዳር ወር የጽዳት ንቅናቄ ስራዎች እቅድ ላይ በተካሄደው የውይይት መድረክ ላይ እንደገለጹት ነዘንድሮው የህዳር ሲጸዳ ንቅናቄ በማህበረሰቡ ተሳትፎ ላይ የተመሰረተ ከተማ አቀፍ የፅዳት እንቅስቃሴን በስፋት የሚተዋወቅበትና ተገቢ የሆነ የቆሻሻ አወጋገድ ስርአትንና ደረቅ ቆሻሻ መልሶ ጥቅም ላይ የማዋል ተግባርን የሚበረታታበት ነው ብለዋል። የዘንድሮ ህዳር ወር በፅዳትና በአካባቢ ጥበቃ ላይ የሕብረተሰቡን ግንዛቤ በማጎልበት ፥ዘላቂነት ያለው የቆሻሻ አወጋገድ ስርአት በህብረተሰቡ ውስጥ ባህል ሆኖ እንዲሰርፅ የሚያደርጉ ተከታታይ ድጋፎችን ምንሰጥበት ነው ሲሉ ገልጸው በዚህም የተለያዩ የማህብረሰብ ክፍሎች የጋራ መኖሪያ አካባቢዎች ፅዱና ጤናማ እንዲሆኑ በጋራ በመስራት ሃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል። ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች የዘንድሮው ህዳር ሲጸዳ መርሐግብር በመዲናችን በጽዳት አጠባበቅ ረገድ የመጡ እምርታዎችንና ለውጦችን በሚያጠናክሩ ሰፊ የማህበረሰብ ተሳትፎና የአመለካከት ለውጥን በሚያጎለብቱ የጽዳት ስራዎች የሚከወንበት እንደሚሆን በም/ከንቲባ ማእረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ አስታወቁ። ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ በዛሬው እለት "ህዳር ሲታጠን" በሚል በልማዳዊ እሳቤ ሲተገበር የቆየውን ባህላዊ የቆሻሻ አወጋገድ ስርአት 'ህዳር ሲጸዳ" በሚል በዘመናዊ የቆሻሻ አስተዳደር ስርአት በመተካት ካለፉት ሰባት አመታት ወዲህ በከተማችን ጽዳት አጠባበቅ ላይና ብክለትን በመቀነስ ረገድ አበረታች ስራዎች መከናወናቸውን አስረድተዋል። ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ በዛሬው እለት የህዳር ወር የጽዳት ንቅናቄ ስራዎች እቅድ ላይ በተካሄደው የውይይት መድረክ ላይ እንደገለጹት ነዘንድሮው የህዳር ሲጸዳ ንቅናቄ በማህበረሰቡ ተሳትፎ ላይ የተመሰረተ ከተማ አቀፍ የፅዳት እንቅስቃሴን በስፋት የሚተዋወቅበትና ተገቢ የሆነ የቆሻሻ አወጋገድ ስርአትንና ደረቅ ቆሻሻ መልሶ ጥቅም ላይ የማዋል ተግባርን የሚበረታታበት ነው ብለዋል። የዘንድሮ ህዳር ወር በፅዳትና በአካባቢ ጥበቃ ላይ የሕብረተሰቡን ግንዛቤ በማጎልበት ፥ዘላቂነት ያለው የቆሻሻ አወጋገድ ስርአት በህብረተሰቡ ውስጥ ባህል ሆኖ እንዲሰርፅ የሚያደርጉ ተከታታይ ድጋፎችን ምንሰጥበት ነው ሲሉ ገልጸው በዚህም የተለያዩ የማህብረሰብ ክፍሎች የጋራ መኖሪያ አካባቢዎች ፅዱና ጤናማ እንዲሆኑ በጋራ በመስራት ሃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል። ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች

ዛሬ “በመደመር መንግስት እይታ፣ የዘርፎች እምርታ” በሚል መሪ ሃሳብ ለብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች በተሰጠው ስልጠና ላይ በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችን እና የፓርቲያችን ፕሬዚዳንት ዶክተር ዐቢይ አሕመድ የተቀመጡ ዋና ዋና ግቦችን ወደ እቅድ በመቀየር በከተማችን አዲስ አበባ በላቀ አፈፃፀም እና ውጤታማነት ለመተግበር ከከተማችን አመራሮች ጋር ውይይት አካሂደናል ። እንደ ከተማ የተያዙ ግቦችን ለማሳካት በጠንካራ የአመራር ቁርጠኝነት፣ በፈጠራ እና ፍጥነት መርህ ግቦቹን ለማሳካት የተዘጋጀውን ዝርዝር እቅድ የጋራ አድርገናል። ከተለዩት ዋና ዋና ግቦች መካከል የብሄራዊ መታወቂያ ምዝገባን (የፋይዳ ምዝገባ)፤ የ5 ሚሊዮን ኮደሮችን፤ የተጀመሩ የኮሪደር፣ የወንዝ ዳር ልማት እና ሌሎች ፕሮጀክቶችን፣ ለምርጫ ምቹ ሁኔታን መፍጠር እና የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርም ግቦችን መቶ በመቶ ማሳካት፤ የቱሪስት ስበትን፣ የሌማት ቱርፋትና የኢንዱስሪ ምርቶችን መጨመር፤ የኑሮ ውድነትን መቀነስ፤ ሌብነት፣ ጉቦኝነትንና ብልሹ አሰራርን፣ መንደርተኝነትን፣ በአካባቢዊነት ማሰብና መስራትን እና ጠባቂነትን መቀነስ፤ እንዲሁም ተረጂነትንና ልመናን፣ ለልማት መዋል የሚገባውን መሬት አጥሮ ማስቀመጥ፣ ኮንትሮባንድና ህገወጥ ንግድ እና ሰላማዊ ሁኔታን የሚያውኩ የጥፋት እንቅስቃሴዎችን ሙሉ በሙሉ ማስቀረት የዋና ዋና ግቦች የትኩረት ማዕከል ሆነው የሚፈፀሙ ይሆናል። ግቦቹን ለማሳካትና ለውጤታማነታቸው እንደ ወትሮው ትውልድና ተቋምን እየገነባን በተለወጠ የስራ ባህል 24/7 በትጋት እና በቁርጠኝነት የምንሰራ ይሆናል። ፈጣሪ ኢትዮዽያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ Har'a "Ilaalama Mootummaa Ida’amu Guddina Dameewwaniif" mata duree jedhuun leenjii hooggantoota olaanoo olaanoo paartii Badhaadhinaaf kenname irratti galmoota gugrguddoo kabajamoo ministira muummee fi pireezidaantii paartii keenya Dr.Abiy Ahimadiin kaayame gara kaayyootti jijjiiruun magaalaa keenya Finfinneetti raawwii fi milkaa'ina olaanaan hojjechuuf hooggantoota magaalaa keenyaa waliin marii gaggeessineerra. Akka magaalaatti galmoota qabaman milkeessuuf kutannoo cimaa hooggantootaan galmoota kalaqaa fi ariitii milkeessuuf karoora bal'aa qabame kan waloo taasisneerra. Galmoota gurguddoo adda baafaman keessaa: galmee eenyummaa biyyaalessaa (galmee faayidaa); koodaroota miliyoona 5; hojiiwwan misooma koriidarii, misooma laggeenii fi piroojektoota biroo eegalaman, filannoof haala mijataa uumuu fi galmoota riifoormii siivil sarvisii dhibbaan dhibbatti milkeessuu; hawwattummaa tuuiristii, maaddii gutuu fi oomishaalee industirii dabaluu; qaala'iinsa jireenyaa hir'isuu; hattummaa, malaammaltummaa fi hojimaata badaa, gandummaan, naannummaan yaaduu, hojjechuu fi eeggattummaa hir'isuu; akkasumas gargaarsaa eeggattuumaa fi kadhaa; lafa misoomaaf oolu dallaa ijaaranii kaa'uu; kontiroobaandii fi daldala seeraan alaa fi sosochiilee badii haala nageenyaa booressan guutumaanguututti hambisuun galmoota gurguddoo giddugala xiyyeeffannoo ta'anii kan raawwataman ta'a. Galmoota milkeessuu fi bu'aqabeessummaa isaaniif akkuma barame dhalootaa fi dhaabbilee ijaaraa aadaa hojii jijjiirameen 24/7 ciminaa fi kutannoon kan hojjennu ta'a. Waaqni Itoophiyaa fi Uummata ishee haa eebbisu Yared

“አዲስ አበባ የብልፅግና እድገት ማሳያ”

ተቋማት ተቀናጅተው መስራታቸው ዜጎች የሚያነሱትን የአገልግሎትና የልማት ጥያቄ በተናበበ አቅም ለመመለስ አቅም ይሆናል AMN - ህዳር 04/2018 ዓ.ም ተቋማት ተቀናጅተው መስራታቸው ዜጎች የሚያነሱትን የአገልግሎትና የልማት ጥያቄ በተናበበ አቅም ለመመለስ አቅም እንደሚሆን በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ ተናገሩ፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ የአገልግሎት አሰጣጥን ለማዘመንና ለማቀላጠፍ እንዲሁም የልማት ስራዎችን ተደራሽ ለማድረግ ተቋማት ተቀናጅተው የሚሰሩበትን አደረጃጀት በመፍጠር እየተሰራ ይገኛል፡፡ በትራንስፖርት እና በማዘጋጃ ቤታዊ ዘርፍ አገልግሎት የሚሰጡ 17 ተቋማትም በክላስተር ተደራጅተው በጋራ መስራት የሚያስቻላቸውን ስምምነት አድርገዋል፡፡ ተቋማቱ የሚያከናውኗቸው ተግባራት ዘመናዊ የትራንስፖርት መሰረተ ልማትን መዘርጋት፣ የትራፊክ ድንብ ክትትል እና ቁጥጥርን ማሻሻል፣ የደረቅ ቆሻሻ አያያዝን ማዘመንን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች የሚሰሩ ናቸው፡፡ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ስራ አሰኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ፤ ቅንጅቱ አገልግሎት አሰጣጡን ለማዘመን እንደሚያስችል ገልጸው፤ የተቋማቱ በትብብር መስራት የከተማዋን አቅም ለማቀናጀትና የተቋም ግንባታን ለማጠናከርም አቅም የሚፈጥር እንደሆነም ተናግረዋል፡፡ የተቋማቱ ቅንጅት የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮችን ከመፍታት ባለፈ ተጠያቂነትን ለማስፈን እንደሚያስችልም ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ ገልጸዋል፡፡ ተቋማቱ በክላስተር መደራጀታቸው የከተማዋን ነዋሪዎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ መሆናቸውን የገለጹት የተቋማቱ አመራሮችም ለተግባራዊነቱ የሚጠበቅባቸውን ኀላፊነት እንደሚወጡ ተናግረዋል፡፡ በቴዎድሮስ ይሳ

የአገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻልና የተቋማት ትብብርና ቅንጅትን ለማጎልበት በአስተዳደሩ አዲስ የተደራጀው የክላስተር ቅንጅት አደረጃጀት ተቋም ተሻጋሪ ተግባራትን በውጤታማነት ለመፈጸም ፣የተቋማትን አቅም ለመገንባትና ከተማ አቀፍ ስትራቴጂክ ግቦችን በአጭር ጊዜ ለማሳካት ወሳኝ እድሎች የፈጠረ ነው ሲሉ በም/ከንቲባ ማእረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ አስገነዘቡ። ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ ይህን ያስገነዘቡት በዛሬው እለት በስራ አስኪያጅ አስተባባሪነት የትራንስፖርት እና ማዘጋጃ ቤታዊ ክላስተር ስር የተደራጁ ተቋማት ያዘጋጁት የጋራ እቅዳቸውን መሠረት ያደረገ የግብ ስምምነት ፊርማ በተፈራረሙበት ወቅት ነው። አዲሱ የክላስተር የቅንጅት አሰራር አደረጃጀት የከተማ አስተዳደሩ ተቋማት የጋራ እቅድና ግብ አስቀምጠን ለጋራ ውጤት እንድንተጋ አስችሎናል ያሉት ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ የዚህ ሁሉ ድምር ውጤት ደግሞ የአገልግሎት አሰጣጣችን ጥራት ያለው ቀልጣፋና ከብልሹ አሰራር የጸዳ በማድረግ ህብረተሰባችን ተገቢውን አገልግሎት እንዲያገኝ ማስቻል ነው ብለዋል። በትራንስፖርትና ማዘጋጃ ቤታዊ ክላስተር አደረጃጀት ስር ባሉ ተቋማት በጋራ ለመስራት በቅንጅት የታቀደውና በዛሬው እለት የግብ ስምምነት የተፈረመበት እቅድ የከተማ ጽዳት ዘላቂነትን ማረጋገጥ፣ የአደጋ ቅነሳ ስራዎች፣ የመሠረተ ልማት ጥበቃና የትራንስፖርት መሠረተ ልማት አገልግሎት አሰጣጥ፣ በኮንስትራክሽን ቦታዎች ላይ የሚፈጠር አደጋን በዘላቂነት መከላከል እና ሌሎች አንኳር ተግባራት የተካተቱበት እንደሆነ ተመላክቷል። የግብ ስምምነቱን በትራንስፖርትና ማዘጋጃ ቤታዊ ክላስተር ስር ያሉ ተቋማት በም/ ከንቲባ ማእረግ ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ እና የክላስተሩ ተቋማት አመራሮች በተገኙበት የፊርማ ስነስርአቱ ተከናውኗል። ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager የአገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻልና የተቋማት ትብብርና ቅንጅትን ለማጎልበት በአስተዳደሩ አዲስ የተደራጀው የክላስተር ቅንጅት አደረጃጀት ተቋም ተሻጋሪ ተግባራትን በውጤታማነት ለመፈጸም ፣የተቋማትን አቅም ለመገንባትና ከተማ አቀፍ ስትራቴጂክ ግቦችን በአጭር ጊዜ ለማሳካት ወሳኝ እድሎች የፈጠረ ነው ሲሉ በም/ከንቲባ ማእረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ አስገነዘቡ። ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ ይህን ያስገነዘቡት በዛሬው እለት በስራ አስኪያጅ አስተባባሪነት የትራንስፖርት እና ማዘጋጃ ቤታዊ ክላስተር ስር የተደራጁ ተቋማት ያዘጋጁት የጋራ እቅዳቸውን መሠረት ያደረገ የግብ ስምምነት ፊርማ በተፈራረሙበት ወቅት ነው። አዲሱ የክላስተር የቅንጅት አሰራር አደረጃጀት የከተማ አስተዳደሩ ተቋማት የጋራ እቅድና ግብ አስቀምጠን ለጋራ ውጤት እንድንተጋ አስችሎናል ያሉት ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ የዚህ ሁሉ ድምር ውጤት ደግሞ የአገልግሎት አሰጣጣችን ጥራት ያለው ቀልጣፋና ከብልሹ አሰራር የጸዳ በማድረግ ህብረተሰባችን ተገቢውን አገልግሎት እንዲያገኝ ማስቻል ነው ብለዋል። በትራንስፖርትና ማዘጋጃ ቤታዊ ክላስተር አደረጃጀት ስር ባሉ ተቋማት በጋራ ለመስራት በቅንጅት የታቀደውና በዛሬው እለት የግብ ስምምነት የተፈረመበት እቅድ የከተማ ጽዳት ዘላቂነትን ማረጋገጥ፣ የአደጋ ቅነሳ ስራዎች፣ የመሠረተ ልማት ጥበቃና የትራንስፖርት መሠረተ ልማት አገልግሎት አሰጣጥ፣ በኮንስትራክሽን ቦታዎች ላይ የሚፈጠር አደጋን በዘላቂነት መከላከል እና ሌሎች አንኳር ተግባራት የተካተቱበት እንደሆነ ተመላክቷል። የግብ ስምምነቱን በትራንስፖርትና ማዘጋጃ ቤታዊ ክላስተር ስር ያሉ ተቋማት በም/ ከንቲባ ማእረግ ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ እና የክላስተሩ ተቋማት አመራሮች በተገኙበት የፊርማ ስነስርአቱ ተከናውኗል። ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager የአገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻልና የተቋማት ትብብርና ቅንጅትን ለማጎልበት በአስተዳደሩ አዲስ የተደራጀው የክላስተር ቅንጅት አደረጃጀት ተቋም ተሻጋሪ ተግባራትን በውጤታማነት ለመፈጸም ፣የተቋማትን አቅም ለመገንባትና ከተማ አቀፍ ስትራቴጂክ ግቦችን በአጭር ጊዜ ለማሳካት ወሳኝ እድሎች የፈጠረ ነው ሲሉ በም/ከንቲባ ማእረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ አስገነዘቡ። ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ ይህን ያስገነዘቡት በዛሬው እለት በስራ አስኪያጅ አስተባባሪነት የትራንስፖርት እና ማዘጋጃ ቤታዊ ክላስተር ስር የተደራጁ ተቋማት ያዘጋጁት የጋራ እቅዳቸውን መሠረት ያደረገ የግብ ስምምነት ፊርማ በተፈራረሙበት ወቅት ነው። አዲሱ የክላስተር የቅንጅት አሰራር አደረጃጀት የከተማ አስተዳደሩ ተቋማት የጋራ እቅድና ግብ አስቀምጠን ለጋራ ውጤት እንድንተጋ አስችሎናል ያሉት ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ የዚህ ሁሉ ድምር ውጤት ደግሞ የአገልግሎት አሰጣጣችን ጥራት ያለው ቀልጣፋና ከብልሹ አሰራር የጸዳ በማድረግ ህብረተሰባችን ተገቢውን አገልግሎት እንዲያገኝ ማስቻል ነው ብለዋል። በትራንስፖርትና ማዘጋጃ ቤታዊ ክላስተር አደረጃጀት ስር ባሉ ተቋማት በጋራ ለመስራት በቅንጅት የታቀደውና በዛሬው እለት የግብ ስምምነት የተፈረመበት እቅድ የከተማ ጽዳት ዘላቂነትን ማረጋገጥ፣ የአደጋ ቅነሳ ስራዎች፣ የመሠረተ ልማት ጥበቃና የትራንስፖርት መሠረተ ልማት አገልግሎት አሰጣጥ፣ በኮንስትራክሽን ቦታዎች ላይ የሚፈጠር አደጋን በዘላቂነት መከላከል እና ሌሎች አንኳር ተግባራት የተካተቱበት እንደሆነ ተመላክቷል። የግብ ስምምነቱን በትራንስፖርትና ማዘጋጃ ቤታዊ ክላስተር ስር ያሉ ተቋማት በም/ ከንቲባ ማእረግ ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ እና የክላስተሩ ተቋማት አመራሮች በተገኙበት የፊርማ ስነስርአቱ ተከናውኗል። ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager

አዲስ አበባ ለመኖር ምቹ፣ ፅዱ እና ውብ ከተማ Finfinnee Magaalaa jireenyaaf mijattuu, qulqullooftuu fi miidhagduu