1 474
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-37 روز
-2130 روز
آرشیو پست ها
ዜና ዕረፍት "
የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አምቡላንስ ሾፌር የነበረችው ወ/ሮ አበባ አሠፋ ዛሬ ጥቅምት 26 ቀን 2018 ዓ.ም በስራ ላይ እንዳለች በድንገት ህይወቷ አልፏል።
የቀብር ስነ-ስርዓቷም ነገ ሀሙስ ጥቅምት 27 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 6:00 ሰዓት በእንጦጦ ኪዳነ ምህረት ቤተክርስቲያን ይፈጸማል።
የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አመራርና ሰራተኞች በወ/ሮ አበባ አሠፋ ህልፈት የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ይገልጻሉ ።
በትራንስፖርትና በማዘጋጃ ቤታዊ ክላስተር በቀጣይ የሚሰሩ ስራዎች የጋራ እቅድ ላይ የዉይይት መድረክ ተካሄደ።
በአዲስ አበባ ከተማ ስራ አስኪያጅ ፅ/ቤት አስተባባሪነት በትራንስፖርትና ማዘጋጃ ቤታዊ ክላስተር ተቋማት ጋር በቅንጅታዊ አሰራር መሠረት በ2018 በጀት አመት በቅንጅት የሚሰሩ ስራዎችን በተመለከተ ከሚመለከታቸው ተቋማት ጋር በዛሬው እለት በተዘጋጀዉ የጋራ እቅድ ላይ የዉይይት መድረክ ተካሂዷል።
በመድረኩም በቢሮ ሀላፊ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ስራ አስኪያጅ እና የጥናትና ልማት ትግበራ ዘርፍ ሀላፊ ወ/ሮ ይመኙሻል ታደሰ እንደገለፁት በትራንስፖርትና ማዘጋጃ ቤታዊ ክላስተር ተቋማት በቅንጅት በከተማችን የተቀናጀ የትራንስፖርት ስርዓት ዝርጋታ፣ቀልጣፋ የህዝብ የአገልግሎት አሰጣጡን ከማሳደግ፣ንፁህና አረንጓዴ ከተማን ከማስፋፋት አንፃር በቀጣይም ወደ ተግባር ለመግባት በዚህ ልክ ተገናኝቶ መሰራት መቻሉ እንዲሁም የሚከናወኑ ተግባራት እቅድ መያዛቸዉ በቀጣይ ወደ ተግባር ምዕራፍ ለመግባት የሚያስችል ነዉ ሲሉ ገልጸዋል።
አክለዉም የሚሰጡ አገልግሎቶችን የአሰራር ስርዓትን በመዘርጋት እንዲሁም ተቋማት የተሰጣቸውን ሀላፊነት ተግባራዊ ከማድረግ አነፃርና በከተማዋ የሚሰጠዉን አገልግሎት በይበልጥ ለማዘመንም ጭምር ስራዎችን ተቀናጅቶ እቅዱን ተግባራዊ በማድረግ በትኩረት ሊሰራበት እንደሚገባ ተናግረዋል።
በዉይይት መድረኩ በቀጣይ ቅንጅታዊ አሰራርን በመዘርጋት የሚከናወኑ ተግባራት እንዲሁም ከተቋማት የሚጠበቁ አገልግሎት አሰጣጦች ምን መሆን እንዳለበት የሚያሳይ ሪፖርት ቀርቦ ዉይትት የተካሄደበት ሲሆን በቀጣይ እቅዱን ወደ ተግባር ቀይሮ ወደ ስራ መግባት እንደሚገባም አሳስበዋል።
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
በአዲስ አበባ ከተማ ስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት ስር ባሉ ተጠሪ ተቋማት አገልግሎት ማግኘት ይፈልጋሉ? እንግዲያውስ እነዚህን መረጃዎች ይመልከቱ።… See more
በመዲናችን በተጠናቀቀው የ90 ቀናት ልዩ የንቅናቄ አጀንዳ እቅድ በተቀመጠው የሞዴል ብሎክ መስፈርት መሠረት ህብረተሰቡን በማሳተፍ የተሰሩ የቅድመ አደጋ መከላከል ስራዎች : የመብራት መሠረተ ልማት ዝርጋታዎች:የጽዳትና ውበት ስራዎች እንዲ… See more
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኮሙኒኬሽን ቢሮ በስሩ የሚገኙ የሴክተር ተቋማት የኮሙኒኬሽን ዘርፍ የበጀት ዓመቱን የ 3 ወራት እቅድ አፈፃፀም ስራዎችን ገመገመ
ቢሮዉ የ2018 በጀት የ 1ኛ ሩብ ዓመት የሴክተር ተቋማት የኮሙኒኬሽን ዘርፍ እቅድ አፈፃፀም ተግባራትን ገምግሟል።
በግምገማዉም የሴክተር ተቋማት የኮሙኒኬሽን የዘርፍ ዳይሬክቶሬቶች እና የተቋማት ክላስተር አስተባባሪዎች የበጀት ዓመቱን የ 3 ወራት አበይት እና ቁልፍ ተግባራት እቅድ አፈፃፀም እንዲሁም የተቋማት የመረጃ አጠቃቀም እና ዉጤታማነት ያለበት ደረጃ ላይ ያተኮረ ሪፖርት በዝርዝር አቅርበዋል።
የቢሮዉ ም/ኃላፊ አቶ ሁሴን ዝናብ ከዚህ ጋር ተያይዞ እንደገለፁት በበጀት ዓመቱ ባለፉት ሶስት ወራት በከተማዋ በርካታና ትላልቅ ስራዎች የተከናወኑበት፤ወቅታዊ፤ፈጣንና ጥራታቸዉን የጠበቁ ትክክለኛ መረጃዎች የኮሙኒኬሽን አግባቦችን በመጠቀም በተለያዩ የሚዲያ ፕላት ፎርሞች ተደራሽ የሆኑበት ዉጤታማ ስራዎች መሰራታቸዉን ጠቁመዋል፡፡
ሴክተሮች የማህበራዊ ፕላት ፎርሞችን አማራጭ በማስፋትና በመጠቀም ወቅታዊ መረጃዎችን ለማህበረሰባችን በማድረስ ፤ልምድና ተሞክሮን በማስፋት፤ተቋማት የመረጃ ምንጭ እንዲሆኑ ማድረግና ወደ ተቀራረበ አፈፃፀም ማምጣት ፤የክትትልና ድጋፍ እንዲሁም ስልጠናዎችን ማጠናከር እና የበጀት፤ የሰዉ ሃይል እና የግብዓት ችግሮችን መፍታት በቀጣይ ጊዜያት ሊተኮርባቸዉ የሚገቡ የቀጣይ አቅጣጫዎች ናቸዉ ሲሉ ገልፀዋል፡፡
በየደረጃዉ የሚገኙ የኮሚኒኬሽን መዋቅር አባላት ሙያዊ ብቃትን በመሰነቅ በከተማዋ ሁለተናዊ አጀንዳዎች ላይ ግንዛቤ በመፍጠር በሙሉ ኃላፊነትና ቁርጠኝነት ተልኳቸዉን መወጣት ይጠበቅባቸዋል ያሉት የቢሮዉ ምክትል ኃላፊ አቶ ዘዉዱ ከበደ ይህም የሚረጋገጠዉ ወቅታዊ መረጃዎችን በፍጥነትና በጥራት ተደራሽ የማድረግና የህዝብ እርካታን ማረጋገጥ ሲቻል ነዉ ብለዋል፡፡
አክለዉም ሁሉም ሴክተር በተሰጠዉ ስራ ላይ በሚያስመዘግበዉ ዉጤት መለካት እንዳለበት ገልፀዉ ለተሻለ አፈፃፀም እንደ እነዚህ ያሉ መድረኮችን እና የድጋፍና ክትትል አግባቦችን የበለጠ በማጠናከር ችግሮችን በጋራ መፍታት እንደሚጠበቅ ጠቁመዉ ለዚህም ቢሮዉ አሁንም የበኩሉን ሚና እንደሚወጣና ሁሉም ሴክተሮች የመረጃ ተደራሽነትን ፍጥነትና ብቃት በተሞላበት ወቅታዊ መረጃን የማዳረስና በሁሉም ረገድ በቂ ግንዛቤ የሚገኝበት የመረጃ ምንጭ በመሆን ማህበረሰባችን በቂ ና ሁለንተናዊ መረጃ እንዲኖረው መሰራት ይጠበቃል ብለዋል። በቀጣይም በትኩረት ና በጥምረት መስራት የሚገባቸውን ተግባራት በማስቀመጥ ውይይቱን አጠናቀዋል።
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
የጥገና ሥራ ለማከናወን የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት
ዛሬ ጥቅምት 26 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ስራ ለማከናወን በአዲስ አበባ እና ሸገር አንዳንድ አካባቢዎች ላይ ኃይል የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች :-
👉ከጠዋቱ 2፡30 እስከ 9፡30 በኖህ አደባባይ ፣ ኤፍ 4 ኤፍ-6 ኖክ አደባባይ ፣ካፒታል ሲሚንቶ፣ አየር ጤና ፣ ሳሚ ካፈ ጀርባ ፣ ታቦት ማደሪያ፣ መሐንዲስ ሰፈር፣ ፈመ ሬሲዮ፣ ቴሌ፣ ስልጤ ሰፈር መውጫ፣ ፋኑኤል ቤ/ክ፣ አጃንባ ኮንዶሚኒየም፣
👉ዓለም ገና ፣ ኢንዱስትሪ መንደር ፣ ፉሪ ሬዲዮ ጣቢያ ፣ፉሪ፣ ሃጂ ሪልስቴት አካባቢ፣ ወርዶፋ ሎጅ፣ ዳርፉር ሰፈር፣ ጀሞ 2፣ ጀሞ-3 በከፊል ፣ ፋና ውሃ ስታንድባይ፣ አየይካ አዲስ፣ አይካ ጀርባያሉ ኢንዱስትሪዎች፣ ጀሞነ -2 ኮንዶሚኒየም ፣ የስ ውሃ፣ ዓለምገና ማርስ ብስኩት፣ ካራ መድህንዓለም መውጫ፣ ኢንዱስትሪ መንደር፣ አየር ጤና ት/ቤት፣ አየር ጤና መስጊድ፣ ኪዳነምህረት ቤ/ክ፣ ሱሉልታ ቆዳ ፋብሪካ ፣ ኮሶ በር፣ አቢሲኒያ ሲሚንቶ
👉ሙሎ፣ አሸዋ ሜዳ ኮንዶሚኒየም፣ ዲያስፖራ፣ ፊሊደሮ፣ አንፎ ዓለም ባንክ ጫፍ፣ ኬኬ ብርድ ልብስ ፋብሪካ፣ ቂሊንጦ ኮንዶሚኒየም፣ ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት፣ አስቱ ዩኒቨርስቲ እና ኢንዱስትሪ መንደር፣ ዋልያ ቢራ፣ ሰሚት ኮንዶሚኒየም ሙሉውን እና በአካባቢው ላይ የኃይል አቅርቦት እንደሚቋረጥ Ethiopian Electric Utility -የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታውቋል።፡
ስለሆነም አገልግሎቱ በጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን የጥገና ሥራው ተጠናቆ የኃይል አቅርቦቱ እስኪመለስ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁን በትህትና እንጠይቃለን ብሏል።
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
አዲስ አበባ : የኢትዮዽያ ዘመናዊ ከተማ ልማት ማሳያ !
#ከተሜነት #Urbanization #addisababa #City transformation #green #clean #MAYOR office
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
በአዲስ አበባ ውስጥ የለሙ ፓርኮች፣ ኮሪደሮች፣ መንገዶችና ተጓዳኝ ልማቶች ለከተማችን ጽዳት፣ ውበትና መልካም ገጽታ የላቀ አስተዋጽኦ ያላቸው በመሆኑ ጽዳታቸውን፣ ውበታቸውንና መልካም ገጽታቸውን የሚያበላሹ ተግባራትን ለመከላከል ለመቆጣጠርና አስተዳደራዊ እርምጃ ለመውሰድ የሚያስችል ደንብ ቁጥር 167/2016 ወጥቶ ስራ ላይ መዋሉ ይታወቃል። ይህም ማንኛውም አካል በአካባቢው ደረቅ ቆሻሻን ባልተገባ ቦታ የሚያስወግዱ አካላትን በማስተማርና በመምከር ሳይታረሙ ሲቀሩ የሚወሰድ የማስተካከያ እርምጃ ሲሆን እነዚህንደንቦች ምን ያህል ያውቃሉ?
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
የጥገና ሥራ ለማከናወን የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት
ዛሬ ጥቅምት 25 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ስራ ለማከናወን በአዲስ አበባ እና ሸገር አንዳንድ አካባቢዎች ላይ ኃይል የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች :-
👉ከጠዋቱ 2፡30 እስከ 9፡30 ድረስ በቡራዪ ከተማ ፣ አኔ ዲማ ፣ሳታላይት ጣቢያዎች፣ ታጠቅ ኢንዱስትሪ መንደር በከፊል፣ ድሬ ከአስፋልት በላይ፣ ገፈርሳ ውሀ ግድብ እና አካባቢው፣ መናገሻ፣ ዊጃን ሶል ፋብሪካ፣ ለቡ አርሴማ ፊትለፊት፣ን/ስልክ ፖሊስ፣ ዮበክ ሪልእስቴት፣ ጀርመን ድልድይ፣ አሜሪካ ኤምባሲ
👉ከጠዋቱ 3፡00 እስከ 8፡00 ድረስ በጳውሎስ ሆስፒታል አካባቢ፣ ሩፋኤል ቤ/ክ እና አካባቢ፣ ሰሜን ማዘጋጃ እና በአካባቢው ላይ የኃይል አቅርቦት እንደሚቋረጥ Ethiopian Electric Utility -የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታውቋል፡፡
ስለሆነም አገልግሎቱ በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን የጥገና ሥራው ተጠናቆ የኃይል አቅርቦቱ እስኪመለስ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁን በትህትና እንጠይቃለን ሲል መልእክቱን አስተላልፏል።፡
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
ስሟን በተግባር እየኖረች ያለች ከተማ አዲስ አበባ::
ከሳር ቤት➡️በጀርመን➡️ጋርመንት አደባባይ እስከ ፉሪ አሁናዊ የምሽት ገፅታ::
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
