1 474
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-37 روز
-2130 روز
آرشیو پست ها
ዛሬ ወደ የኢትዮ ጅቡቲ ምድር ባቡር አ.ማ ጉብኝት አድርገናል። ጉብኝቱ የሀገራችንን ብሔራዊ የሎጂስቲክስ ክዋኔ ዐቅም ለመገምገም እና የሀገሪቱን እያደገ ያለ የልማት አጀንዳ ለመደገፍ በሎጂስቲክስ ዝግጁነት ላይ ገንቢ ውይይቶችን ለማካሄድ ጠቃሚ ዕድል ሰጥቶናል።
ኢኮኖሚያችን እያደገ ሲሄድ የሎጂስቲክስ ዘርፉ ካልዘመነ ዘላቂ ዕድገትን የሚገድብ ዋና መሰናክል መሆኑን ይቀጥላል። አሁን በተለይ በውስጣዊ እና በራስ ዐቅም የባቡር መንገድ ግንባታ ላይ የተመዘገበው ዕድገት እጅግ የሚያስደንቅ ነው። ይህም የሀገር ውስጥ ዐቅምን ለመገንባት፣ ውጤታማነትን ለማሻሻል እና በባቡር ዘርፍ ውስጥ ረጅም ጊዜ የሚቆይ ዘላቂነትን ለማረጋገጥ ያለንን ጽኑ ቁርጠኝነት ያሳያል።
ሎጂስቲክስ ከባሕር እስከ መጋዘኖች ድረስ ያለውን ሙሉ ሰንሰለት ያካትታል። ይህም ወደቦች፣ የባቡር መንገዶች፣ አውራ ጎዳናዎች፣ የትራንስፖርት አገልግሎቶች እና የማከማቻ ተቋማትን ይጨምራል። በአሁኑ ወቅትም በእጃችን ውስጥ ባሉ መስኮች ላይ እንደ ደረቅ ወደቦች፣ የባቡር መሠረተ ልማት፣ አውራ ጎዳናዎች እና የመጋዘን ግንባታ አስፈላጊ ማሻሻያዎችና ዘመናዊ የማድርግ ሥራዎች በሂደት ላይ ናቸው። እነዚህን ተያያዥ የሎጂስቲክስ ክፍተቶችን በተቀናጀ መንገድ መፍታት የዘርፉን መሰናክሎች ለመሻር እና የሀገሪቱን ሰፊ የልማት ግቦች ለመደገፍ ወሳኝ ይሆናል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
የአብርሆት ቤተ-መጻሕፍትን ወደ ላቀ የዲጂታል ምዕራፍ የሚያሸጋግሩ ሦስት የቴክኖሎጂ ፕሮጀክቶች ይፋ የተደረጉበት ሥነሥርአት
በመዲናዋ በሁሉም የገበያ ማዕከላት እና የሰንበት ገበያዎች እና በባዛሮች በተሠራዉ የቅድመ ዝግጅት ስራ በቂ የምርት አቅርቦት እና ፍትሀዊ የግብይት ስርዓት መኖሩ ተገለፀ
በመዲናችን የገናን በአል ምክንያት በማድረግ በመዲናዋ በሁሉም የገበያ ማዕከላት እና የሰንበት ገበያዎች በተሠራዉ የቅድመ ዝግጅት ስራ በቂ የምርት አቅርቦት እና ፍትሀዊ የግብይት ስርዓት መኖሩ ተገለጿል።
መጭውን የገና በዓል በማስመልከት የህብረተሰቡን የፍጆታ ፍላጎት ለማሟላት እና የዋጋ ንረትን ለመቀነስ የኢንዱስትሪ እና የግብርና ምርት ዉጤቶች በመዲናዋ በ 5ቱ የገበያ ማዕከላት እና ከ220 በላይ ሰንበት ገበያዎች ላይ በስፋትና በጥራት የቀረቡበትና ሸማቹም በተመጣጣኝ ዋጋ የሚገበይበት ፍትሀዊ የግብይት ስርዓት መፈጠሩ በየደረጃዉ ያለዉ የመንግስት አካላት ከአምራቹና ከነጋዴዉ ጋር ተቀናጅቶ በመስራቱ ነዉ ተብሏል።
ይህን ጤናማ የግብይት ስርዓት የበለጠ ለማስቀጠል የህገወጥ ነጋዴዎችንና ደላሎችን አሻጥር እና ህገ ወጥ ተግባር ለመከላከል ከገቢያ ማረጋጋት ግብረ ሃይል እና ከፀጥታ አካሉ ጋር ሁሉም የከተማዋ ማህበረሰብ በኃላፊነት ተቀናጅቶ መስራት እንደሚገባ የተገለፀ ሲሆን ከተማ አስተዳደሩ ከቅድመ ዝግጅት ጀምሮ ከተለያዩ መዋቅሮች ጋር በጋራ እየሠራ ያለዉ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገልጿል።
ከሰንበት ገቢያዎች በተጨማሪ በስፋት ዘይት፣የስንዴ ዱቄት፣ እንቁላል እንዲሁም ስኳር በከተማዋ በሚገኙ የህብረት ስራ ማህበራት በኩል የቀረቡ በመሆኑ ሸማቹ ማህበረሰብ በአቅራቢያው በሚገኙ የገበያ ማዕከላት፣ የሰንበት ገበያዎች እና ኤግዚቪሽንና ባዛር በመሄድ የሚፈልጉትን በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲሸምቱ ጥረ ቀርቧል።
በዓሉን አስመልክቶ የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳያጋጥም እየተሰራ ያለውን ዘርፈ ብዙ ተግባር በማድነቅ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባ በግብይት ወቅት ሲሸምቱ የነበሩ የከተማዋ ነዋሪዎች በሰጡት አስተያየት ገልፀዋል።
ዛሬ የሃባሪ ሜዲካል ፕላዛን መርቀን በይፋ ሥራ አስጀምረናል።
ተቋሙ ለሀገራችን ጥራት ያለው የሕክምና አማራጭ ይዞ የመጣ ማዕከል ነው። ሃባሪ ሜዲካል ፕላዛ ዜጎች ለከፍተኛ ሕክምና ወደ ውጭ ሀገር የሚያደርጉትን ጉዞ በማስቀረት፣ ጥራት ያለው አገልግሎት በሀገር ውስጥ ለማቅረብ የጀመረው ጉዞ ተስፋ ሰጪ ነው።
ተቋሙ አዲስ አበባን የጤና ቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ ለጀመርነው ጉዞ ተጨማሪ አቅም የሚፈጥር በመሆኑ፣ ሁሉን አቀፍ ድጋፋችን አይለያችሁም።
ለዚህ በጎ ጅምር እና ለላቀ አገልግሎታችሁ ያለኝን አድናቆት እየገለጽኩ፤ ለተቋሙ ስኬታማ የሥራ ዘመን እመኛለሁ።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
ለገና እና ለጥምቀት በዓላት በቂ የፍጆታ ምርቶች መቅረባቸው ተገለጸ
ለገና እና ለጥምቀት በዓላት አስፈላጊ የሆኑ የፍጆታ ምርቶች በበቂ ሁኔታ መቅረባቸውን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
ሚኒስትሩ በዓላቱን በማስመልከት በአዲስ አበባ ከተማ በተለያዩ ሥፍራዎች የቀረቡ የግብርና ምርቶችንና የቁም እንስሳት አቅርቦትና ግብይትን ተመልክተዋል።
በአምስቱም የከተማዋ በሮችና የመገበያያ ስፍራዎች ምርቶች በበቂ ሁኔታ መቅረባቸውን የጠቀሱት ሚኒስትሩ፣ ዋጋውም የኅብረተሰቡን የመግዛት አቅም ያገናዘበና የተመጣጠና መሆኑን ተናግረዋል።
ለበዓሉ አስፈላጊ የሆኑ ሁሉም የምርት ዓይነቶች ከስርጭቱ ጀምሮ በበቂ ደረጃ መቅረባቸውን የተናገሩት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሀቢባ ሲራጅ፣ ግብይቱ የተረጋጋ እንዲሆን በሁሉም የግብይት ስፍራዎች የዋጋ ጭማሪ እንዳይኖርም ቁጥጥርና ክትትል እየተደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
ፋይዳ ምን ይፈይዳል?
የዲጂታል መታወቂያ አሁን ባለንበት ዓለም የኢኮኖሚና የማህበራዊ ትስስርን እየቀየረ ያለ የቴክኖሎጂ አብዮት ነዉ፡፡
በኢትዮጵያም "ፋይዳ" መታወቂያ የዚህ ዓለም አቀፋዊ እንቅስቃሴ አንዱ አካል እየሆነ ሲሆን እንደ ስንጋፖር፣ ህንድ እና ኢስቶኒያ ያሉ ሀገራት የዲጂታል መታወቂያን በመጠቀም አብዛኛዎቹን የመንግስት አገልግሎቶች ወደ ዲጂታል በመቀየር የዜጎቻቸውን ሁለንተናዊ አገልግሎት በማዘመን ተጠቃሽ ሀገራት ናቸዉ ፡፡
የጥናት ውጤቶች እንደሚያሳዩት፣ የዲጂታል መታወቂያን ስራ ላይ ማዋል ለሀገር የኢኮኖሚ እድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል።
ፋይዳ ዜጎች ማንነታቸው ታውቆ ሁሉንም ማህበራዊ አገልግሎቶች በእኩልነት እንዲያገኙ ከማድረጉም ባሻገር የባዮሜትሪክ መረጃዎችን በመጠቀም ማንነትን መጭበርበርንና ሀሰተኛ መረጃዎችን ማዘጋጀት የማይቻል በማድረግ የሀገርን ደህንነት በከፍተኛ ደረጃ ያጠናክራል።
ፋይዳ በመንግስትና በዜጎች መካከል የሚገቡ ደላላዎችን በማስቀረት፣ አገልግሎቶች ለታለመላቸው እውነተኛ ዜጎች ብቻ እንዲደርሱ በማድረግ ሙስናንና የሀብት ብክነትን የመከላከል ትልቅ አቅም ያለው ዲጂታል ሥራ ነዉ።"
የአገልግሎቶ አሰጣጥን የምያሳልጥ ይህ ስርዓት፣ ሀገራችን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሆነ የዲጂታል ኢኮኖሚ እንድትገነባ መሰረት ይጥላል።
የፋይዳ መታወቂያ ወረቀትንና የተንዛዛ ቢሮክራሲን በማስቀረት የቴክኖሎጂ፣ የኢኮኖሚ እና የማህበራዊ ዘርፎችን በማቀናጀት ኢትዮጵያ በ2030 ካለመችበት እንድትደርስ የሚያስችላት ትልቅ ብልጽግና ግብ ነዉ፡፡
እያንዳንዱ ዜጋ በዚህ የታሪክ ጉዞ ውስጥ የፋይዳ መታወቂያ በመያዝ፣ ለሀገሪቱ የዲጂታል ሽግግር ስኬትና ለዘመናዊ አሰራር መስፈን መሰረታዊ ሚና መጫወት ይገባል።
FDRE Government Communication Service-በኢፌዴሪ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
አዲስ አበባ ከተማ ስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት አስተባባሪነት የሚመራው የማዘጋጃ ቤታዊና የትራንስፖርት ክላስተር የቴክኒክ ኮሚቴ የሁለት ወር የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ግምገማ አከናወነ።
በግምገማ መድረኩ ከክላስተሩ አባላት መካከል 11 ተቋማት በ2 ወር በቅንጅት ያከናወኗቸውን ተግባራት ሪፖርት ያቀረቡ ሲሆን በሪፖርቱም በአፈፃፀም ሂደት የታዩ ጥንካሬዎች እና ክፍተቶች ላይ ውይይት ተካሂዷል።
በውይይቱ ወቅት ተሳታፊዎች እንደገለፁት ተቋም ተሻጋሪ የሆኑ የአገልግሎት ስራዎችን በተናበበ መልኩ እየተከናወኑ በመሆኑ የፕሮጀክቶች አፈጻጸም ለውጥ እያመጣ እንደሆነ ገልጸው አገልግሎት አሰጣጡ ቀልጣፋና ግልጽ እንዲሆንና በስራ ሂደት የሚያጋጥሙ ችግሮችን ፈጣን ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል ምቹ ሁኔታ ክላስተሩ እንዲፈጠር ማስቻሉን ገልጸዋል ።
የግምገማ መድረኩን የመሩት ዶ/ር ተፈራ ሞላ በቢሮ ሃላፊ ማአረግ የአዲስ አበባ ከተማ ም/ስራ አስኪያጅ እንደተናገሩት በክላስተሩ ተቋማት መካከል የተፈጠረው ቅንጅት ጥራት ያለው እቅድ ከማዘጋጀት ጀምሮ በተግባር ምእራፍ ተቀናጅቶ እና ተናቦ ተግባራትን በውጤታማነት መፈጸም የሚያስችል ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ገልጸው በክላስተሩ ተቋማት በመናበብ፣ በመደጋገፍና የቅንጅታዊ አሰራሩን አጠናክር በማስቀጠል ረገድ የተጀመሩ ስራዎች ይበልጥ መጎልበት እንዳለበት አስገንዝበዋል።
አክለውም የማዘጋጃ ቤታዊና የትራንስፖርት ክላስተር ዘመናዊ የመሠረተ-ልማት፣ ንፁህ፣ ውብና አረንጓዴ የአካባቢ ልማት እና ቀልጣፋ የህዝብ አገልግሎት አሰጣጥን በማሳደግ የተቀናጀ፣ ዘላቂ እና የማይበገር የትራንስፖርትና ማዘጋጃ ቤታዊ ስርዓት ማረጋገጥ እንደሚያስችልም አመልክተዋል ።
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
የአብርሆት ቤተ-መጻሕፍት በመዲናችን የንባብና የምርምር ባህል ማዕከል ሆኖ ስራ ከጀመረ እነሆ አራተኛ ዓመቱን ይዟል።
ዛሬ ማለዳ በቤተ-መጻሕፍቱ በመገኘት፣ ተቋሙን ወደ ላቀ የዲጂታል ምዕራፍ የሚያሸጋግሩ ሦስት ታላላቅ የቴክኖሎጂ ፕሮጀክቶችን በይፋ አስጀምረናል።
በዓመት በአማካይ ለ1.8 ሚሊዮን አንባቢዎች አገልግሎት እየሰጠ የሚገኘውን ይህንን ተቋም ይበልጥ ለማዘመን የሚያስችሉ፦ የተቀናጀ የቤተ-መጻሕፍት አስተዳደር ሥርዓት፣ ዘመናዊ የዲጂታል ቤተ-መጻሕፍት እና ዓለም አቀፍ የምርምር መድረክ (Research Portal) በይፋ ሥራ እንዲጀምሩ ተደርጓል።
እነዚህ አገልግሎቶች አብርሆት በአዲስ አበባ ብቻ የተገደበ እንዳይሆን ምቹ ሁኔታ የሚፈጥሩ ሲሆን፤ ማንኛውም ተማሪም ሆነ ተመራማሪ በየትኛውም የኢትዮጵያ አካባቢ ሆኖ የአብርሆትን የዕውቀት ማዕድ መቋደስ እንዲችል ያደርጋሉ።
በተጨማሪም የታሪክ ሰነዶቻችን በዲጂታል መንገድ ተጠብቀው ለቀጣዩ ትውልድ እንዲተላለፉ ትልቅ እገዛ ይኖራቸዋል።
እነዚህን ቴክኖሎጂዎች በማልማት አስተዋጽኦ ያበረከታችሁ ባለድርሻ አካላትን በሙሉ በራሴና በከተማ አስተዳደሩ ስም ከልብ አመሰግናለሁ።
ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
ፅዳት የዕለት ተዕለት ተግባርና ባህል ሊደረግ የሚገባ ጉዳይ ነው ሲሉ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ ገለፁ።
በዛሬው ዕለት በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ "ተደምረን አዲስ አበባን እንደ ስሟ ፅዱና ውብ በማድረግ የቱሪስት መዳረሻ እናደርጋታለን" በሚል መሪ ሃሳብ በወረዳ ዋዩ ኦሮሚያ ኮንዶሚኒየም አከባቢ የፅዳት ንቅናቄ መርሃ ግብር ተካሂዷል።
በዕለቱ መልዕክት ያስተላለፉት በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ ፅዳት የአንድ ቀንና የአንድ ተቋም ስራ እንዳይደለ ጠቅሰው ነዋሪዎች የዕለት ተለት ተግባርና ባህል ሊያደርጉት የሚገባ ጉዳይ ነው ብለዋል።
የትኛውም መሰረተ ልማት ቢሟላ የከተማው ነዋሪ ከቤቱ ከአከባቢውና ከድርጅቱ የሚወጣውን ቆሻሻ በስርዓትና በተገቢው ማሶገድ ካልቻለ ተጨባጭ ለውጥ እንደማይመጣም አንስተዋል።
የከተማውን ገፅታ የቀየሩ ሰፋፊ የልማት ስራዎች የተሰሩ መሆኑን የገለፁት ዋና ስራ አስኪያጁ የተሰራውን የልማት ስራ የበለጠ የሚያጎላው ፅዳት መሆኑን ተናግረዋል።
የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ ወይዘሮ ካባ መብራቱ አዲስ ከበባን ውብና ፅዱ እንዲሁም ለነዋሪዎቿ ምቹ ለማድረግ እየተሰሩ ካሉ ዘርፈ ብዙ ተግባራት አንዱ ፅዳት መሆኑን አንስተው ዋና መንገዶችንና አስፓልትን ብቻ ሳይሆን ከቤት ጀምሮ በተገቢው ማፅዳት እንደሚገባ ተናግረዋል።
ብሎኮችንና መንደሮችን ለኑሮ አመቺ፣ ውብና ፅዱ ለማድረግ በሚደረገው ጥረት ሁሉም ህብረተሰብ ተሳታፊ ሊሆን ይገባልም ብለዋል።
#LaftoCommunication
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
