fa
Feedback
Ewnet Media

Ewnet Media

رفتن به کانال در Telegram
812
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-77 روز
-1830 روز
آرشیو پست ها
ኢዜማ በ7ኛዉ ዙር ሀገር አቀፍ ምርጫ 86 መቀመጫዎችን በማግኘት ቀዳሚዉ ተፎካካሪ ፓርቲ ሆኖ ማጠናቀቁን ገለፀ‼️ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማሕበራዊ ፍትሕ ኢዜማ ሀገር አቀፉ ምርጫዉ ከነእንከኖቹም ቢሆን በ
ኢዜማ በ7ኛዉ ዙር ሀገር አቀፍ ምርጫ 86 መቀመጫዎችን በማግኘት ቀዳሚዉ ተፎካካሪ ፓርቲ ሆኖ ማጠናቀቁን ገለፀ‼️ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማሕበራዊ ፍትሕ ኢዜማ ሀገር አቀፉ ምርጫዉ ከነእንከኖቹም ቢሆን በሰላም በመጠናቀቁ ደስተኛ ነኝ ሲል መግለጫ ሰጥቷል፡፡ ይህን ተከትሎም ፓርቲዉ ለውድድር በቀረበባቸው ቦታዎች 13 የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና 73 የክልል እና የከተማ ምክር ቤት ወንበሮችን በድምሩ 86 መቀመጫዎችን በማግኘት በሀገር አቀፍ ደረጃ ቀዳሚው ተፎካካሪ ፓርቲ ሆኖ ማጠናቀቁን አስታዉቋል። ኢዜማ ከቀጣዩ ምርጫ በፊት ባሉት ዓመታት ጠንካራ ጎኖቹን በማስቀጠል እንዲሁም የነበሩበትን ክፍተቶች በስትራቴጂ እና ሌሎች አስፈላጊ ተግባራት በመሙላት ተጨባጭ የተፎካካሪ ፓርቲነት ሚናውን ጊዜ ሳያባክን የሚጀምረው ተግባር መሆኑን ጠቁሟል፡፡ ፓርዉ አክሎም ገዢ ሆኖ እንዲቀጥል ለተመረጠው ብልጽግና ፓርቲ እና ለውድድሩ ተሳታፊዎች የእንኳን ደስያላችሁ መልዕክቱን አሥተላልፏል፡፡ በተጨማሪም አሸናፊው ፓርቲ ከዛሬ ጀምሮ ዴሞክራሲያዊ ተቋማትን ለመገንባትና ፍትሐዊ የፖለቲካ ምህዳርን ለሁሉም እኩል ተደራሽ ለማድረግ በቁርጠኝነት እንዲሠራ፤ አማራጭ ሃሳቦችን እንዲሰማ፤ እንዲሁም ትችቶችን በሆደ ሰፊነት እያስተናገደ የሀገሪቱን ዴሞክራሲ በጋራ ለመገንባት ቁርጠኛ እንዲሆን ጥሪዉን አቅርቧል፡፡

New to LBank? Unlock VIP2 and Trading Rewards VIP2 trial, transfer rewards, and trading bonuses for new users. Offer availabl
New to LBank? Unlock VIP2 and Trading Rewards VIP2 trial, transfer rewards, and trading bonuses for new users. Offer available until June 30. Sponsored By WaybienAds

Unlock LBank New User Benefits Join LBank and access new user benefits, including a 30 day VIP2 trial, transfer rewards up to
Unlock LBank New User Benefits Join LBank and access new user benefits, including a 30 day VIP2 trial, transfer rewards up to 200 USDT, and additional trading bonuses. Sponsored By WaybienAds

LBank New User Rewards Are Live Join and unlock a 30 day VIP2 trial, transfer rewards up to 200 USDT, and additional trading
LBank New User Rewards Are Live Join and unlock a 30 day VIP2 trial, transfer rewards up to 200 USDT, and additional trading bonuses. Limited time offer for new users. Sponsored By WaybienAds

LBank New User Rewards Are Live Join and unlock a 30 day VIP2 trial, transfer rewards up to 200 USDT, and additional trading
LBank New User Rewards Are Live Join and unlock a 30 day VIP2 trial, transfer rewards up to 200 USDT, and additional trading bonuses. Limited time offer for new users. Sponsored By WaybienAds

LBank New User Rewards Are Live Join and unlock a 30 day VIP2 trial, transfer rewards up to 200 USDT, and additional trading
LBank New User Rewards Are Live Join and unlock a 30 day VIP2 trial, transfer rewards up to 200 USDT, and additional trading bonuses. Limited time offer for new users. Sponsored By WaybienAds

LBank New User Rewards Are Live Join and unlock a 30 day VIP2 trial, transfer rewards up to 200 USDT, and additional trading
LBank New User Rewards Are Live Join and unlock a 30 day VIP2 trial, transfer rewards up to 200 USDT, and additional trading bonuses. Limited time offer for new users. Sponsored By WaybienAds

photo content

Prime Coat, ቻክ እና ጂፕሰም ቦርድ የመስራት ልምድ ያላችሁ አናግሩን። @abela1987

የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ ከዛሬ 12 ሰአት ጀምሮ የነዳጅ ዋጋ በድጋሚ ጭማሪ ተደርጓል‼️ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ታህሳስ 20 ቀን 2014 ዓ.ም ባደረገዉ 3ኛ መደበኛ ስብሰባ ባስተላለፈዉ የነዳጅ ዉጤቶች የ
የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ ከዛሬ 12 ሰአት ጀምሮ የነዳጅ ዋጋ በድጋሚ ጭማሪ ተደርጓል‼️ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ታህሳስ 20 ቀን 2014 ዓ.ም ባደረገዉ 3ኛ መደበኛ ስብሰባ ባስተላለፈዉ የነዳጅ ዉጤቶች የዋጋ ግንባታ የአፈፃፀም ዉሳኔ መሠረት የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በየጊዜዉ እየተከለሰ ስራ ላይ እንዲዉል ሲደረግ መቆየቱ ይታወሳል፡፡ በዚሁ መሠረት የአለም የነዳጅ ዋጋን መነሻ በማድረግ ከመጋቢት 23/2018 ዓ.ም ከምሽቱ 12:00 ሠዓት ጀምሮ የሁሉም የነዳጅ ምርቶች የአዲስ አበባ ከተማ የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ከዚህ በታች በተቀመጠው ሠንጠረዥ መሠረት ተግባራዊ እንዲደረግ በመንግሥት የተወሰነ መሆኑን የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር አሳውቋል።

ኢራን በዱባይ የነዳጅ ታንከር ላይ ጥቃት አደረሰች‼️ በሆርሙዝ ሰርጥ ሲጓዝ የነበረው ይህ ታንከር ንብረትነቱ የነጋዴዎች ነው ተብሏል። ኢራን በዚህ ግዙፍ የነዳጅ ታንከር ላይ በአየር እና በባህር የሰ
ኢራን በዱባይ የነዳጅ ታንከር ላይ ጥቃት አደረሰች‼️ በሆርሙዝ ሰርጥ ሲጓዝ የነበረው ይህ ታንከር ንብረትነቱ የነጋዴዎች ነው ተብሏል። ኢራን በዚህ ግዙፍ የነዳጅ ታንከር ላይ በአየር እና በባህር የሰው አልባ አውሮፕላን ጥቃት ማድረሷ ተገልጿል። የደረሰው ጉዳት በዝርዝር አልተገለጸም።  ኢራን ጥቃቱን ያደረሰችው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የሆርሙዝ ሰርጥን እንድትከፍት እያሳሰቡ በሚገኙበት ወቅት ነው። 

የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ለ”ጨረቃ ቤቶች” የባለቤትነት ማረጋገጫ ሊሰጥ ነው‼️ የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት፣ በክልሉ ያሉ ሕገወጥ ወይም በተለምዶ “ጨረቃ ቤት” ተብለው የሚታወቁ ካርታ እና ፕላን የሌላቸውን ቤቶች ባሉበት ሕጋዊ ሊያደርግ እና የባለቤትነት ማረጋገጫ ሰነድ ሊሰጥ መሆኑ ተሰማ።  የክልሉ መንግሥት ምክር ቤት ወይም ጨፌ ኦሮሚያ፣ ባሳለፍነው መጋቢት 10፣ 2018 ዓ፣ም ባካሄደው 6ኛ የሥራ ዘመን፣ 5ኛ ዓመት 3ኛ መደበኛ ጉባኤው፣ መመሪያውን አቅድቆ ለክልሉ መሬት አሥተዳደር ቢሮ መላኩ ታውቋል። እነዚህን ሕገ ወጥ ቤቶች ሕጋዊ የማድረጉ አሰራር ከከተሞች ፕላን እና መሠረት ልማት ጋር ፈጽሞ ሊጻረር በማይችል መልኩ ብቻ እንደሚከወን የሚያትተው መመሪያው፣ በክልሉ ከተሞች የመሬት ሊዝ አዋጅ መሰረት አስፈላጊው ክፍያ ከተፈጸመ በኋላ ሂደቱ እንደሚጀመር ያመለክታል።  ይህን አሰራር የሚከታተሉትና የሚያስፈጽሙት በከተማ አስተዳደሮች ያሉ የመሬት አስተዳደር ጽሕፈት ቤቶች መሆናቸውን የሚደነግገው የኽው መመሪያ፣ አመልካቾች ማመልከቻቸውን የሚያስገቡበትን ቀንም በይፋዊ ማስታወቂያ እንደሚገለጽ ያብራራል።  የከተማ መሬት አሥተዳደር ጽሕፈት ቤቶች በማመልከቻው መሠረት ያዋቀሯቸውን ባለሙያዎች ወደ ስፍራው በመላክ ቤቱ ያለበት ቦታ ከከተማው ፕላን ጋር የሚጣጣም መሆኑን ከተጣራ በኋላ ቤቱን ሕጋዊ የማድረግ እና የባለቤትነት ማረጋገጫ የመስክር ወረቀት የመስጠት ሂደቱ እንደሚጀመር መመሪያው ያዛል።  ሕጋዊ የሚደረገው የመኖሪያ ቤት ቦታ በካሬ ሜትር ተለክቶ ከከተማው የመሬት ሽንሻና ደረጃ ወይም ስታንዳርድ የሚተርፍ ከሆነ፣ መሬቱ ወደ መሬት ባንክ ተመላሽ እንደሚደረግ መመሪያው አትቷል።  እነዚህን ሕገ ወጥ ቤቶች ሕጋዊ የማድረግ ሥራ ሸገር፣ አዳማ እና ቢሾፍቱ ከተሞችን አያካትትም። ክፍያን በተመለከተ በሊዝ ስርዓት በሚተዳደሩ ከተሞች በከተማው የመሬት ደረጃ መሰረት የከተማ መሬት ሊዝ አዋጅ ከጸደቀበት ከጥር 24፣ 2005 ዓ፣ም ጀምሮ ያለውን የሊዝ ውዝፍ ክፍያ  እንዲሁም፣ የጣሪያና ግድግዳ ግብር ክፍያ  አመልካች መክፈል እንደሚኖርበት መመሪያው ይደነግጋል።  በመሬት ሊዝ ስርዓት ስር ባልገቡ ከተሞች የሚገኙ ቤቶች ደግሞ፣ ከጥር 24፣ 2005 ዓ፣ም ጀምሮ በከተማው ደረጃ ተሰልቶ የመሬቱን ኪራይ እንዲሁም የጣሪያ እና ግድግዳ ግብር ክፍያ፣ በተጨማሪም የክፍያውን 30 በመቶ ቅጣት መክፈል ይጠበቅባቸዋል። ክፍያውን በአንድ ጊዜ ከፍለው ማጠናቀቅ ለማይችሉ ሰዎች፣ በሁለት ዓመታት ውስጥ በአራት ጊዜ ክፍያ ከፍለው ማጠናቀቅ እንደሚችሉ የፈቀደው መመሪያው፣ በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ክፍያውን ከፍሎ ያላጠናቀቀ አመልካች ግን መሬቱ ሕጋዊ እንደማይደረግለትና የከፈለውንም ክፍያ መልሱ ብሎ መጠየቅ እንደማይችል አስጠንቅቋል።  መመሪያዎችን በተቀመጠለት የጊዜ ገደብ ያልፈጸመ አካል፣ በመሬቱ ላይ የሰራው ቤት ፈርሶ መሬቱ ወደ መንግሥት የመሬት ባንክ ተመላሽ እንደሚሆን የጠቀሰው መመሪያው፣ መንግሥት ቤቱን በማፍረሱ የሚያስከትለው ኢኮኖሚያዊ ጉዳት ካለ ቤቱ ሳይፈርስ ባለበት እንደሚወርሰው ደንግጓል።  በየትም ቦታ በስሙም ይሁን በሌላ ሰው ስም ከአንድ በላይ ሕጋዊ ያልሆነ መሬት ያለው ግለሰብ መሬቱን ሕጋዊ በማድረግ ሂደት ውስጥ እንደማይስተናገድ የጠቀሰው መመሪያ፣ ይልቁንም መሬቱ በመንግሥት ይወረሳል ብሏል።  በተጨማሪም ከከተማ ፕላን እና መሰረተ ልማት ጋር የማይጣጣሙ ሕጋዊ ያልሆኑ ቤቶችን ማፍረስ እንደሚቀጥል የጠቀሰው ዋዜማ የተመለከተችው መመሪያ፣ ቤቱ የፈረሰባቸው ግለሰቦች የክልሉ መንግሥት በተለያዩ ጊዜያት በሚያደርገው መሬት ሸንሽኖ የመስጠት ሂደት ውስጥ እንደሚካተቱ ደንግጓል።  እነዚህን ሕገወጥ የመኖሪያ ቤቶች ወደ ሕጋዊ መንገደ የመመለስ ሂደቱ በአንድ ዓመት የጊዜ ገደብ ውስጥ ተሰርቶ እንዲጠናቀቅ መመሪያው የሚያዝ ሲሆን፣ ለሚፈጠረው ማንኛውም መዘግየትና መጓተት የወረዳ አሥተዳዳሪዎች፣ የከተማ ከንቲቦች፣ በየደረጃው ያሉ የመንግሥት የመሬት አሥተዳደር መዋቅሮች ተጠያቂ ይሆናሉ ሲል ያስጠነቅቃል።  የኦሮሚያ ክልል የከተሞች ፕላን ኢንስቲትዩት በበኩሉ፣ ከክልሉ መሬት አሥተዳደር ቢሮ ጋር ለሥራው መሳካት በቅንጅት እንዲሰራ ያሳሰበው መመሪያው፣ መመሪያው በአግባቡ ሥራ ላይ መዋል አለመዋሉን እንዲቆጣጠር ጭምር አዟል። ይህን ሥራ በዋናነት ኃላፊነት ወስደው የሚሰሩት የክልሉ የመሬት አሥተዳደር ቢሮ፣ የክልሉ የከተማ ልማትና ቤቶች ቢሮ እንዲሁም የክልሉ የከተሞች ፕላን ኢንስቲትዩት መሆናቸውም ተመላክቷል።  መመሪያውን በየጊዜው በመከታተል ኦዲት የሚያደርጉ የክልሉ የመንግሥት መዋቅሮች በመመሪያው ውስጥ የተዘረዘሩ ሲሆን እነርሱም፣ የፕሬዝዳት ጽሕፈት ቤት፣ የክልሉ ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ቢሮ፣ የክልሉ የገንዘብ ቢሮ፣ የክልሉ የገቢዎች ቢሮ እንዲሁም የክልሉ እቅድ እና ልማት ኮሚሽን ናቸው።  ለአንድ ሰው ከአንድ መሬት በላይ ሕጋዊ ማድረግ፣ ይህ መመሪያ ከወጣ በኋላ አስፈላጊው ማጣራት ሳይደረግና አመልካች የሚጠበቅበትን ክፍያ ሳይፈጽም ሕጋዊ ላልሆኑ ቤቶች የመሬት ባለቤትነት የምስክር ወረቀት መስጠት ከባድ አሥተዳደራዊ እርምጃ እንደሚያስወስድ ተገልጿል::

አርቲስት ሰራዊት ፍቅሬ፣ መንሱር ጀማል፣ ልጅ ካሊድ፣ ዳንኤል ተገኝ( EBS ጋዜጠኛ) ፣ አርቲስት ይገረም ደጀኔ እና አብርሃም ግዛው ከመሸ በፌዴራል ፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን ዘሀበሻ ዘግቧል‼️
አርቲስት ሰራዊት ፍቅሬ፣ መንሱር ጀማል፣ ልጅ ካሊድ፣ ዳንኤል ተገኝ( EBS ጋዜጠኛ) ፣ አርቲስት ይገረም ደጀኔ እና አብርሃም ግዛው ከመሸ በፌዴራል ፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን ዘሀበሻ ዘግቧል‼️ እነዚህ ታዋቂ ግለሰቦች በቁጥጥር ሥር የዋሉት ፊንቴክ ከተባለ ድርጅት ጋር በመሆን መኪና እናስመጣላችኋለን በሚል ማስታወቂያ በመስራት በርካታ ግለሰቦች ገንዘባቸውን እንደተጭበረበሩ እና መኪናም እንዳልመጣላቸው ይገልፃሉ።

የኢራን የመሪዎች ግድያ ቀጥሏል‼️ የኢራን ከፍተኛ ወታደራዊ ቃል አቀባይ በመሆን ሲያገለግሉ የነበሩት አሊ መሀመድ ናይኒ እስራኤል ዛሬ ጠዋት በፈፀመችው የአየር ጥቃት መገደላቸውን አራን አስታውቃለች።
የኢራን የመሪዎች ግድያ ቀጥሏል‼️ የኢራን ከፍተኛ ወታደራዊ ቃል አቀባይ በመሆን ሲያገለግሉ የነበሩት አሊ መሀመድ ናይኒ እስራኤል ዛሬ ጠዋት በፈፀመችው የአየር ጥቃት መገደላቸውን አራን አስታውቃለች። ኢራን በተያዘው ሳምንት ብቻ አምስት ቁልፍ መሪዎቿን አጥታለች።

#BREAKING የዒድ አልፈጥር በዓል አርብ (ጁምዓ) ይውላል። ዛሬ የሸዋል ወር ጨረቃ ባለመታየቷ 1447ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል ከነገ ወዲያ አርብ (ጁምዓ) ተከብሮ ይውላል። ዒድ ሙባረክ ! #Ha
#BREAKING የዒድ አልፈጥር በዓል አርብ (ጁምዓ) ይውላል። ዛሬ የሸዋል ወር ጨረቃ ባለመታየቷ 1447ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል ከነገ ወዲያ አርብ (ጁምዓ) ተከብሮ ይውላል። ዒድ ሙባረክ ! #Haramain መጋቢት 9 ቀን 2018

እስራኤል የኢራን ቁልፍ የደኅንነት ባለሥልጣን የሆኑት አሊ ላሪጃኒን መግደሏን ተናገረች‼️ የኢራን ብሔራዊ የደኅንነት ጠቅላይ ምክር ቤት ዋና ፀሐፊ አሊ ላሪጃኒ በእስራኤል ጥቃት መገደላቸውን የእስራኤ
እስራኤል የኢራን ቁልፍ የደኅንነት ባለሥልጣን የሆኑት አሊ ላሪጃኒን መግደሏን ተናገረች‼️ የኢራን ብሔራዊ የደኅንነት ጠቅላይ ምክር ቤት ዋና ፀሐፊ አሊ ላሪጃኒ በእስራኤል ጥቃት መገደላቸውን የእስራኤል የመከላከያ ሚኒስትር ኢዝራኤል ካትዝ አስታወቁ። ሌሊቱን በተፈጸመ ጥቃት መገደላቸው የተነገረው ላሪጃኒ በኢራን መንግሥት ውስጥ ከፍተኛ ተሰሚነት ከነበራቸው መሪዎች መካከል አንዱ ናቸው። የባለሥልጣኑ በእስራኤል ዒላማ መሆን እየተነገረ በነበረበት ጊዜ ቢያንስ ሁለት የኢራን መገናኛ ብዙኃን ከፍተኛ የደኅንነት ባለሥልጣናትን ጠቅሰው ግለሰቡ በአጭር ጊዜ ውስጥ መግለጫ ይሰጣሉ ብለው ነበር። አንድ የእስራኤል ወታደራዊ ባለሥልጣን አሊ ላሪጃኒ በእስራኤል መከላከያ ዒላማ መደረጋቸውን ለቢቢሲ አረጋግጠዋል። አሊ ላሪጃኒ በኢራን ብሔራዊ የደኅንነት ጠቅላይ ምክር ቤት የሟቹ ጠቅላይ መሪ አያቶላህ አሊ ኻሜኒ ተወካይ እና ዋና ፀሐፊ ሆነው የተሾሙት ባለፈው ዓመት ነሐሴ በፕሬዝዳንት ማሱድ ፔዜሽኪያን ነበር። ለ12 ዓመታት የኢራን ፓርላማ አፈ ጉባዔ የነበሩት ላሪጃኒ “ለዘብተኛ ወግ አጥባቂ” እንደሆኑ ይነገርላቸዋል፤ በተጨማሪም በኢራን መገናኛ ብዙኃን የጠቅላይ መሪው አማካሪ እንደሆኑ ይጠቀሱ ነበር። እስራኤል በፈጸመችው ጥቃት መገደላቸው የተነገረው ታዋቂው ኢራናዊ ፖለቲከኛ የፓርላማው አፈ ጉባዔ ከመሆናቸው በፊት ኢራንን ከምዕራባውያን ጋር እያወዛገበ በሚገኘው የኒውክሌር ድርድር ላይ አገራቸውን ወክለው ተደራዳሪ ነበሩ። በኢራን ፖለቲካ ውስጥ አሊ ላሪጃኒ ብቻ ሳይሆኑ ወንድማቸውም ከፍተኛ ተሰሚነት አላቸው። ወንድማቸው ሴዴጌ ላሪጃኒ በኢራን ሁለት ኃያል ምክር ቤቶች የበላይ አካል የሆነው ጉባዔ ሊቀ መንበር ናቸው።

ነዳጅን ቆጥባችሁ ተጠቀሙ‼️ 🗣️ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ ባስተላለፉት መልዕክት፤በመካከለኛው ምሥራቅ በተፈጠረው ቀውስ የተነሣ ነዳጅ ገዝተው
ነዳጅን ቆጥባችሁ ተጠቀሙ‼️ 🗣️ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ ባስተላለፉት መልዕክት፤በመካከለኛው ምሥራቅ በተፈጠረው ቀውስ የተነሣ ነዳጅ ገዝተው የሚጠቀሙ ሀገሮች እንደልብ ለማግኘት መቸገራውን አንስተዋል፡፡ "በመሆኑም ችግሩ ተፈትቶ ወደ መደበኛው የነዳጅ አቅርቦት ሥርዓት እስክንመለስ ድረስ ነዳጅን በቁጠባና ለመሠረታዊ ነገሮች ቅድሚያ በመስጠት መጠቀም ይኖርብናል" ብለዋል። "የነዳጅ አከፋፋዮች፣ማደያዎች እና ተጠቃሚዎች ነዳጅን በቁጠባ፣ ለመሠረታዊ ነገሮች ቅድሚያ በመስጠት ሁላችንም በሃላፊነት ስሜት እንድንጠቀም ለማሳሰብ እወዳለው።"ሲሉ አሳስበዋል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ቢሮ የትራንስፖርት ታሪፍ ላይ ጭማሪ አደረገ‼️ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ቢሮ በነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ የተደረገውን ጭማ
+1
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ቢሮ የትራንስፖርት ታሪፍ ላይ ጭማሪ አደረገ‼️ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ቢሮ በነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ የተደረገውን ጭማሪ ተከትሎ፣ በከተማ ውስጥ የሕዝብ ትራንስፖርት ላይ አዲስ የታሪፍ ጭማሪ ማድረጉን አስታወቀ።ከነገ መጋቢት 7 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረገው ይህ አዲስ ታሪፍ፤ የሚኒባስ ታክሲ፣ የሃይገር (ሚዲባስ)፣ የከተማ አውቶቡስ እንዲሁም የባጃጅ አገልግሎቶችን ያካተተ ነው። ቢሮው ይፋ ባደረገው መረጃ መሠረት፣ በሚኒባስ ታክሲዎች እስከ 2.5 ኪሎ ሜትር የሚደረግ ጉዞ በ10 ብር ታሪፍ ቢቀጥልም፣ የርቀቱ መጠን እየጨመረ ሲሄድ ዋጋውም ተመጣጣኝ ጭማሪ አሳይቷል። ለምሳሌ እስከ 10 ኪሎ ሜትር የሚጓዙ ተሳፋሪዎች 35 ብር እንዲከፍሉ የተወሰነ ሲሆን፣ ረጅሙ የ20 ኪሎ ሜትር የርቀት ጉዞ ደግሞ 55 ብር እንዲከፈል ተደንግጓል። በሚዲባስ (ሃይገር) በኩልም በተመሳሳይ የዋጋ ጭማሪ የተደረገ ሲሆን፣ እስከ 8 ኪሎ ሜትር የሚደረግ ጉዞ 15 ብር እንዲከፈል ተወስኗል። ከፍ ያለ የጉዞ ርቀት ያላቸው ማለትም ከ20 እስከ 24 ኪሎ ሜትር የሚጓዙ ተሳፋሪዎች 40 ብር እንዲከፍሉ ሲወሰን፣ በዘርፉ ረጅሙ ተብሎ የተለየው የ28 ኪሎ ሜትር ጉዞ ደግሞ 45 ብር ታሪፍ ተቆርጦለታል።

እስራኤል በሊባኖስ ላይ በፈፀመችው ጥቃት 400 የሚጠጉ ሰዎች ተገደሉ ‼️ በሊባኖስ ከእስራኤል ጋር በተፈጠረ ግጭት የሞቱት ሰዎች ቁጥር 394 መድረሱን የመንግስት የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል። ዛሬ እ
እስራኤል በሊባኖስ ላይ በፈፀመችው ጥቃት 400 የሚጠጉ ሰዎች ተገደሉ ‼️ በሊባኖስ ከእስራኤል ጋር በተፈጠረ ግጭት የሞቱት ሰዎች ቁጥር 394 መድረሱን የመንግስት የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል። ዛሬ እሁድ የሊባኖስ ጤና ሚኒስትር ራካን ናሴረዲን በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳሉት አሜሪካ እና እስራኤል ከኢራን ጋር ባደረጉት ጦርነት ሊባኖስ ከተሳተፈችበት ጊዜ አንስቶ 83 ህጻናት እና 42 ሴቶች ከሟቾቹ መካከል ይገኙበታል። ናስረዲን አክለውም ዘጠኝ የነፍስ አድን ሰራተኞችም ሞተዋል። አጠቃላይ የሊባኖስ የሟቾች ቁጥር ከቅዳሜ ጀምሮ በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ እንደሚገኝ የጤና ሚኒስትሩ አክለው ገልፀዋል ።

ኢራን 220 የአሜሪካ ወታደሮች መገደላቸውንና መቁሰላቸውን ኢራን ገለጸች‼️ ​ኢራን ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ በፈጸመችው የአጸፋ ጥቃት 220 የአሜሪካ ወታደሮችና አዛዦች መገደላቸውንና መቁሰላቸውን
ኢራን 220 የአሜሪካ ወታደሮች መገደላቸውንና መቁሰላቸውን ኢራን ገለጸች‼️ ​ኢራን ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ በፈጸመችው የአጸፋ ጥቃት 220 የአሜሪካ ወታደሮችና አዛዦች መገደላቸውንና መቁሰላቸውን አስታወቀች። ፕሬስ ቲቪ እንደዘገበው የኢራን "ኻታም አል-አንቢያ" ማዕከላዊ ቃርያ ቃል አቀባይ ሌተና ኮሎኔል ኢብራሂም ዞልፋጋሪ እንደገለጹት፣ በባህሬን በሚገኘው የአሜሪካ አምስተኛ የባህር ኃይል ክፍለ ጦር ላይ በተፈጸመ ጥቃት 21 ወታደሮች ተገድለዋል። ​በተጨማሪም በአል-ዳፍራ አየር ማረፊያ በሚገኘው የአሜሪካ ወታደራዊ ካምፕ ላይ በደረሰ ጥቃት ወደ 200 የሚጠጉ ወታደሮች መገደላቸውንና መቁሰላቸውን ኢራን ገልጻለች። በፋርስ ባሕረ ሰላጤ ሰሜናዊ ክፍልም የአሜሪካ ንብረት የሆነ የነዳጅ ጫኝ መርከብ ላይ ጥቃት መፈጸሙ ተጠቅሷል። ይሁን እንጂ አሜሪካም ሆነ ገለልተኛ ወገኖች እስካሁን ይህንን መረጃ አላረጋገጡም።