cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

ትኩስ መረጃ Tekus Mereja

Breaking News Join Us

نمایش بیشتر
کشور مشخص نشده استزبان مشخص نشده استدسته بندی مشخص نشده است
پست‌های تبلیغاتی
500
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

የኩፍኝ፣ ፖሊዮና ቢጫ ወባ ወረርሽኝን ለመከላከል ያለመ የክትባት ሣምንት ሊካሄድ ነው! የኩፍኝ፣ ፖሊዮና ቢጫ ወባ ወረርሽኝን ለመከላከል ያለመ የክትባት ሣምንት ከፊታችን ሰኞ ጀምሮ ሊካሄድ መሆኑን የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ድጉማ በሰጡት መግለጫ ÷ የአፍሪካ የክትባት ሣምንትን ምክንያት በማድረግ የሚከናወነው የክትባት ዘመቻው በተለይም በጸጥታ ችግር ምክንያት ክትባት ባልተሰጠባቸው ቦታዎች ይሰጣል ብለዋል፡፡ የክትባት ሣምንቱ ማህበረሰቡ በክትባት ጠቀሜታ ላይ ትክክለኛውን ግንዛቤ እንዲጨብጥ ለማድረግና የክትባት ተደራሽነትን ለማስፋት መሆኑንም አመላክተዋል፡፡ የክትባት ዘመቻው ዓላማ በወረርሽኝ ደረጃ ሊነሱ ይችላሉ ተብሎ የተሰጉትን ኩፍኝ፣ ፖሊዮ እና ቢጫ ወባን ለመከላከል መሆኑን የጠቆሙት ዶክተር ደረጄ፤ ይህም ተፈናቃይ ዜጎች ባሉባቸው አካባቢዎች በስፋት የሚሰጥ ይሆናል ብለዋል፡፡ ከወረርሽኝ መከላከል ባለፈ ለሕጻናት የአንጀት ተወሃሲያን መከላከያ፣ ቫይታሚን ኤ እና በምግብ እጥረት የተጎዱ ሕጻናትን በመለየት ሕክምና እንደሚሰጥ መናገራቸዉን የኢዜአ ዘገባ ያስረዳል። @YeneTube @FikerAssefa
نمایش همه...
የወልዲያ ከተማ አስተዳዳር ‹‹ሰርጎ ገቦች››ን ለመለየት የነዋሪዎችን መታወቂያ ሊቀይር ነው! የወልዲያ ከተማ አስተዳደር በከተማው ውስጥ የሚገኙ ‹‹ሰርጎ ገቦችን›› ለመለየት እንዲቻል፣ የከተማዋ ነዋሪዎችን በሙሉ መታወቂያ ሊቀር እንደሆነ አስታወቀ፡፡በከተማው ውስጥ ካለው ሁኔታ አንፃር እየተለዩ የሚታሰሩ ግለሰቦች እንዳሉ የገለጸው የከተማ አስተዳደሩ፣ አዲስ መታወቂያ የሚወስዱ ሰዎች ያላቸውን መታወቂያ ከከተማዋ ወሳኝ ኩነት መረጃ ጋር እንደሚያመሳክር ገልጿል፡፡ ለወራት በሕወሓት ቁጥጥር ሥር ከቆየች በኋላ በታኅሳስ ወር ላይ በመንግሥት ቁጥጥር ሥር በሆነችው ወልዲያ፣ ‹‹ሰርጎ ገቦች›› የቀድሞውን መታወቂያ መያዛቸውን ለሪፖርተር የተናገሩት የወልድያ ከተማ ተቀዳሚ ከንቲባ ዳዊት መሰለ (ዶ/ር)፣ በዚህም ምክንያት የከተማው አስተደዳር የከተማዋን ነዋሪዎች መታወቂያ ለመቀየር ውሳኔ ማስተላለፉን ገልጸዋል፡፡ እንደ ዳዊት (ዶ/ር) ገለጻ፣ ከዚህ ቀደም መታወቂያ ሲሰጥ የነበረው መረጃዎችን በመዝገብ ላይ በመጻፍ ብቻ የነበረ ሲሆን፣ ይህም በቀበሌዎች መካከል የሚጣራበት ሁኔታ እንዳይኖር በማድረጉ የተለያዩ ቀበሌዎች ላይ ከአንድ በላይ መታወቂያ ያላቸው ሰዎች አሉ፡፡ ‹‹ሰርጎ ገብ›› የተባሉትን ሰዎች ማንነት አብራርተው ባይገልጹም፣ የከተማዋ ነዋሪዎች መታወቂያ እንዲይዙ የሚያደርጉ የቀበሌ አመራሮች አሉ የሚል ጥርጣሬ እንዳለ አስረድተዋል፡፡ አሁን መታወቂያ የማደስ አገልግሎት እንዲቆም መደረጉን አክለዋል፡፡ Via Reporter @YeneTube @FikerAssefa
نمایش همه...
የጎንደሩን ግድያ የፈፀመዉ ማን እንደሆነ እየተጣራ ነዉ! የአማራ ክልል መንግስት የሰላምና ፀጥታ ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ ደሳለኝ ጣሰው ዛሬ ለዶይቼ ቬለ እንደተናገሩት የፀጥታ ኃይሉ አጥፊ ግለሰቦችንና ቡድኖችን እያደነ እንደሆነም ኃላፊ አመልክተዋል፡፡ ማክሰኞ ዕለት በጎንደር ከተማ በአንድ ታዋቂ አባት መቃብር ላይ የተፈጠረውን የህይወት ማጥፋት፣ የአካል ጉዳትና የንብረት መውደምን ተከትሎ የነበረው አለመረጋጋት እየተሻሻለ መምጣቱን የአማራ ክልል መንግስት አስታውቋል። በጥቃቱ ህይወታቸው ያለፉ ወገኖች የቀብር ሥነ-ስርዓትም እየተከናወነ እንደሆነ ተመልክቷል።አንድ የዓይን እማኝ ዛሬ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ቢከፈቱም አንዳንድ የንግድ ተቋማት እንደተዘጉ ናቸው ብለዋል፡፡የአማራ ክልል የሐይማኖት ተቋማት ጉባኤ ሰሞኑን በጎንደር የተካሄደውን ግድያ አውግዟል፡፡ ማክሰኞ ዕለት በጎንደር ከተማ የአንድ ታላቅ አባት የቀብር ሥነ-ስርዓትን ተከትሎ በንፁሐን ላይ የሞት የአካል ጉዳትና የንብረት ውድመት ተፈፅሟል፣ ያን ተከትሎ በከተማዋ አለመረጋጋት ሰፍኖ መቆየቱን የጎንደር ከተማ ነዋሪዎች ተናግረዋል፡፡ የአማራ ክልል መንግስት የሰላምና ፀጥታ ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ ደሳለኝ ጣሰው ዛሬ ለዶይቼ ቬለ እንደተናገሩት ከሁለቱም የሐይማኖት አባቶች ጋር ውይይቶች ተካሂደው የቀብር ሥነ-ስርዓት እየተካሄደ ነው፡፡የፀጥታ ኃይሉ አጥፊ ግለሰቦችንና ቡድኖችን እያደነ እንደሆነም ኃላፊ አመልክተዋል፡፡ የጉዳቱ መጠን ገና እየተጠና መሆኑን የተናገሩት አቶ ደሳለኝ ጉዳቱ ከሁለቱም ወገን ነው ብለዋል፡፡መንግስቱ የተባሉ የዓይን እማኝ በስልክ እንዳብራሩት ዛሬ በከተማዋ የተረጋጋ ሁኔታ ቢኖርም ሥራ ያልጀመሩ ሱቆችን ተመልክተዋል፡፡መሐመድ የተባሉ ሌላ የዓይን እማኝ “ቀብር አናስቀብርም” የሚል ጥያቄ ያነሱ ወገኖች እንደነበሩ ጠቁመው መጨረሻ ግን በተደረሰ ውይይት ቀብር ተፈፅሟል ነው ያሉት፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ በጎንደር ከተማ የተፈፀመው ድርጊት እንደሚያወግዘው የአማራ ክልል የሐይማኖት ተቋማት ጉባኤ አስታወቋል፡፡ጉባዔው ትናንት ለአገር ውስጥ ብዙኃን መገናኛ ብቻ በሰጠው መግለጫ «በከተማዋ የተፈፀመው ድርጊት የማንንም ሐይማኖት አይወክልም ፣ የሐይማኖቶችን አስተምሮምሆነ እሴት ያልተከተለ ነው» ብሏል፡፡መንግስት አጥፊዎችን ተከታትሎ በአስቸኳይ ለፍርድ እንዲያቀርብ፣ ህዝቡም እንዲተባበር ነው የጉባዔው አባላት ያመለከቱት፡፡ Via DW @YeneTube @FikerAssefa
نمایش همه...
ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር እድሪስ ህዝብን ከህዝብ የሚያጋጩ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አሳሰቡ! ህዝብን ከህዝብ የሚያጋጩ አካላት ከድርጊታቸው መቆጠብ እንዳለባቸው የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር እድሪስ አሳሰቡ። 1 ሺህ 443ኛውን የኢድ በአልና ወቅታዊ ጉዳዮችን አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ የሰጡት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር እድሪስ፤ ያልተረጋገጠ ወሬ ህዝብን ከህዝብ የሚያጋጭ ጉዳይ መሆኑንም አስገንዝበዋል። ከሰሞኑ በተከሰተው ግጭት አሳዛኝ ድርጊት መፈጸሙ የሚወገዝ እና የትኛውንም ሃይማኖት የማይወክል እንደሆነ ገልጸዋል። ለህዝቡ ቅርብ የሆኑና ተሰሚነት ያላቸው አካላት ግጭት አባባሽ መልእክቶችን በማሰራጨት እልቂት እንዲፈጠር እየሠሩ እንደሚገኙ አመልክተው፤ ህዝቡ የተነገረው ሁሉ አምኖ መቀበል ብቻ ሳይሆን መርምሮ ማረጋገጥ እንዳለበት አስረድተዋል። ግጭቱ በተከሰተባቸው አካባቢዎች ያሉ የፀጥታ አካላት እና የመንግስት የስራ ሀላፊዎች ሀላፊነታቸውን መወጣት ላይ ክፍተት እንዳሉባቸው ገልፀው፤ ችግሩ ከዚህ የከፋ ጉዳት ሳያስከትል በቁርጠኝነት እንዲሰሩ አፅንኦት ሰጥተዋል። የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ኮሚቴ በማቋቋም እና ቦታው ድረስ በማቅናት ችግሩን ለመፍታት ጥረት ይደረጋል ማለታቸዉን ኢዜአ ዘግቧል፡፡ @YeneTube @FikerAssefa
نمایش همه...
ሀይማኖትን ሽፋን አድርገው የሚነሱ ግጭቶች በቂ ትኩረት ይሻሉ ሲል የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ አሰሰበ። የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ ከሰሞኑ ጎንደር ላይ የተፈጠረውን ያወገዘ ሲሆን በዚው ዙሪያ መግለጫ አውጥቷል:: ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል። @YeneTube @FikerAssefa
نمایش همه...
የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ስድስት ቅርንጫፎች ሠራተኞች በወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር ዋሉ! በኦሮሚያ ክልል የሚገኙ ስድስት የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ቅርንጫፍ ሠራተኞች በወንጀል ተጠርጥረው በክልሉ የጸጥታ ኃይሎች ዛሬ ሚያዚያ 20 ቀን 2014 ዓም በቁጥጥር ስር ውለው መታሰራቸው ታወቀ። ቅርንጫፍ መስሪያቤቶቹ በአዳማ፣ነቀምት፣ ጅማ፣ጊምቢ፣በደሌ፣መቱ ሲሆኑ ሁሉም መታሸጋቸው ታውቋል።የቅርንጫፍ ሠራተኞቹ በቁጥጥር ስር መዋላቸውንና መታሰራቸውን የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ለሪፖርተር ያረጋገጠ ቢሆንም የታሰሩትን ሠራተኞች ብዛትና የታሰሩበትን ቦታ ከመግለጽ ተቆጥቧል። Via Reporter @YeneTube @FikerAssefa
نمایش همه...
የአማራ ክልል መንግሥት ሽብር በሚፈጠሩ አካላት የማያዳግም እርምጃ እወስዳለው አለ! የአማራ ክልል መንግሥት በጎንደር ከተማ በተፈጠረው ግጭት ተገቢውን ክትትል አድርጎ የማያዳግም እርምጃ እንደሚወስድ አስታወቀ።የአማራ ክልል ርዕሠ መሥተዳድር ይልቃል ከፋለ (ዶ/ር) ፤ እንደ ሀገር ከገጠሙን ችግሮች ሙሉ በሙሉ ሳንላቀቅ ሃይማኖትን ምክንያት በማድረግ የእርስ በርስ ግጭት ለመፍጠር የሚታትሩ እኩይ አካላትን እንደማይታገሱ ተናግረዋል። ርዕሠ መሥተዳድሩ "ክልሉን የትርምስ ቀጣና ለማድረግ የሽብር ድርጊት በሚፈጠሩ አካላት ላይ የማያዳግም እርምጃ እንወስዳለን" ማለታቸውን አሚኮ ዘግቧል፡፡ይህ ሙከራ ኢትዮጵያን ካለችበት ነባራዊ ሁኔታ ለባሰ ቀውስ የሚዳርግ በመሆኑ ድርጊቱ ሊወገዝ ይገባዋል ያሉት ርዕሠ መሥተዳድሩ የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና ወጣቶች ለሰላም ዘብ እንዲቆሙም አሳስበዋል። @YeneTube @FikerAssefa
نمایش همه...
በአዲስ አበባ ከተማ በኤሌክትሪክ ኃይል መቋረጥ የተነሳ በአራት ክፍለ ከተሞች የውሃ አቅርቦት ተቋርጧል! በአዲስ አበባ ከተማ በኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥ የተነሳ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከ 12 ወረዳዎች ፣በቂርቆስ ክፍለ ከተማ 10 ወረዳዎች ፣በቦሌ ክፍለ ከተማ 3 ወረዳዎች እና በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ 5 ወረዳዎች የሚገኙ ደንበኞች ከእሁድ እለት ጀምሮ ውሃ በበቂ ሁኔታ እያገኙ አለመሆኑን የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለሥልጣን የኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰርካለም ጌታቸው በተለይ ለብስራ ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡ በኤሌክትሪክ ኃይል መቋረጥ የተነሳ ከዚህ ቀደም ውሃ በፈረቃ ያገኙ ለነበሩ አካባቢዎች አገልግሎቱን መስጠት መቸገራቸውን ያነሱት ዳይሬክተሯ በተለይ ውሃ በሳምንት አንዴ ያገኙ የነበሩ አካባቢዎች ላይ ችግሩ በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩን ገልፀዋል። ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥ ችግሩን ለመፍታት ከአዲስ አበባ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር በመናበብ በመስራት ላይ መሆናቸውን የሚናገሩት ዳይሬክተሯ በተለይ ከእሁድ ጀምሮ እስከ ድርብ ድረስ ባሉት ቀናት በርካታ ምሶሶዎች መውደቃቸውን ተከትሎ እና መሬት ውስጥ የነበረ ኬብል በመፈንዳቱ ዳግም የመጠገን ስራዎች ላይ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ አሁን ላይ የፈረቃ ሂደቱ በመዛባቱ ባለስልጣኑ ባሉት ቦቲ ተሸከርካሪዎች ውሃ ለማዳረስ እየሰራ ሲሆን ችግሩን በአፋጣኝ ለመፍታት ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልፀዋል። የኤሌክትሪክ ኃይል መቋረጥ የተፈጠረው በቴክኒክ ችግር ምክንያት መሆኑን ለብስራት ሬዲዮ ያስረዱት በአዲስ አበባ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ በቀለ ክፍሌ ሲሆኑ ችግሩን ለመቅረፍ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ [ዳጉ ጆርናል] @YeneTube @FikerAssefa
نمایش همه...
የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ባለሙያዎች ማኅበር መንግሥት የሸቀጥ አቅርቦት እና ዋጋ ንርትን የሚያረጋጋ ጊዜያዊ ቦርድ እንዲያቋቁም ጠይቋል። ማኅበሩን ጥያቄውን ያቀረበው፣ በዋጋ ግሽበት መዋቅራዊ ተግዳሮቶች እና የፖሊሲ አማራጮች ላይ ለ6 ወራት ያስጠናውን ጥናት ይፋ ባደረገበት ወቅት ነው። ቦርዱ ቢቋቋም፣ የአገራዊ ምርትና የገቢ ንግድ አቅርቦት ሚዛንን ማስጠበቅ፣ የዋጋ ግሽበትን የሚቀንስ ግብ ማስቀመጥ፣ በግሽበቱ የሚጎዱ የኅብረተሰብ ክፍሎችን መለየት እና በተለያዩ ኢኮኖሚ ዘርፎች መካከል ቅንጅት ለመፍጠር ይችላል ተብሏል። Via Wazema @YeneTube @FikerAssefa
نمایش همه...
ከትግራይ ዩኒቨርሲቲዎች ለተፈናቀሉ ተማሪዎች ዲግሪ እንደማይሰጥ ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ! ከትግራይ ክልል ዩኒቨርሲቲዎች ተፈናቅለው በአደራ በሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ተምረው ለተመረቁ ተማሪዎች፣ መደበኛ ዲግሪ ሚኒስቴሩ ለመስጠት እንደሚቸገር ተገለጸ፡፡ በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች በትምህርት ሚኒስቴር ዋስትና ገብተው የተመረቁ ከትግራይ ዩኒቨርሲቲዎች የተፈናቀሉ ከ4,000 በላይ ተማሪዎች መደበኛ ዲግሪ ስለተከለከልን ሥራ ለመቀጠርና ለመወዳዳር አልቻልንም ሲሉ ለሪፖርተር ተደጋጋሚ ቅሬታዎችን ሲያሰሙ ቆይተዋል፡፡ የእነዚሁ የተማሪዎች ቅሬታ የቀረበላቸው ትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ (ፕሮፌሰር) እንደተናገሩት፣ ‹‹የተማሪዎቹ ሙሉ መረጃ ሳይገኝ መደበኛ ዲግሪ ለመስጠት እንቸገራለን፡፡ ጦርነቱ ሲቆምና ሰላምና መረጋጋት በሰሜን ኢትዮጵያ በአስተማማኝ ሁኔታ ሲሰፍን ከመጡባቸው ዩኒቨርሲቲዎች ትምህርት ያቆሙበት መረጃ ተሟልቶ ሲቀርብ ዲግሪው ይሰጣቸዋል፡፡ እስከዚያው ግን በተሰጣቸው ውጤታቸውን በሚገልጽ ሰርተፊኬት ሥራ መፈለግ ይችላሉ፤›› ብለዋል፡፡ ሚኒስትሩ ይህን ቢሉም ከትግራይ ክልል ዩኒቨርሲቲዎች በጦርነት ሳቢያ ተፈናቅለው ሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ለመመረቅ የተገደዱ ተማሪዎች ግን፣ ትምህርት ሚኒስቴር በአንድ ሴሚስተር የውጤት መግለጫ ወረቀት (በግሬድ ሪፖርት) አሰናብቶናል ሲሉ ቅሬታ ያሰማሉ፡፡ ይህ ወረቀት ደግሞ በሥራ ዓለም ተወዳዳሪ ሆኖ ለመቀጠር እንደማያስችላቸው በመጥቀስ፣ ትምህርት ሚኒስቴር ዘላቂ መፍትሔ እንዲፈልግላቸው እየጠየቁ ነው፡፡ የትምህርት ሚኒስቴር ግን አሁን ካደረኩት የተለየ አማራጭ የለኝም የሚል ምላሽ ነው የሰጠው፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ: http://bit.ly/36ZDgNi @YeneTube @FikerAssefa
نمایش همه...