2 449
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-147 روز
-10930 روز
آرشیو پست ها
2 449
ኦርቶዶክስ
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
4፥171 እናንተ የመጽሐፉ ሰዎች ሆይ! በሃይማኖታችሁ ወሰንን አትለፉ፡፡ በአላህም ላይ እውነትን እንጅ አትናገሩ፡፡ يَا أَهْلَ الْكِتَابِ لَا تَغْلُوا فِي دِينِكُمْ وَلَا تَقُولُوا عَلَى اللَّهِ إِلَّا الْحَقَّ
"ኦርቶዶክስ" ὀρθόδοξος የሚለው ቃል የሁለት ግሪክ ቃላት ውቅር ነው። "ኦርቶስ" ὀρθός ማለት "ወጥ" "ቀጥተኛ" ማለት ሲሆን "ዶክሳ" δόξᾰ ደግሞ "ክብር" "አመለካከት" ማለት ነው፥ በጥቅሉ "ኦርቶዶክስ" ὀρθόδοξος ማለት "ቀጥተኛ አመለካከት" ማለት ነው።
በተቃራኒው "ሔተሮዶክስ" ἑτερόδοξος የሚለው ቃል የሁለት ግሪክ ቃላት ውቅር ነው። "ሔተሮስ" ἕτερος ማለት "የተዛባ" "የተለያየ" ማለት ሲሆን "ዶክሳ" δόξᾰ ደግሞ "ክብር" "አመለካከት" ማለት ነው፥ በጥቅሉ "ሔተሮዶክስ" ἑτερόδοξος ማለት "የተዛባ አመለካከት" ማለት ነው።
ከአንድ ሃይማኖት ብዙኃኑ ወይም አብላጫው የሚከተለው አንቀጸ-እምነት"creed" ኦርቶዶክስ ይባላል፥ ለምሳሌ በሂንዱ ሃይማኖት ሳናታና ዳርማ ኦርቶዶክስ ሲባል፣ በቡድሃ ሃይማኖት ቴራፋዳ ኦርቶዶክስ ሲባል፣ በአይሁድ ሃይማኖት ማሶሬት ኦርቶዶክስ ሲባል፣ በክርስትና የአራቱ ዓለም ዓቀፍ አንቀጸ-እምነት ኦርቶዶክስ ሲባል፣ በእሥልምና ደግሞ የነቢያችንን"ﷺ" ሡናህ እና የሠለፎችን መንሃጅ ኦርቶዶክስ ይባላል።
በተቃራኒው ከዚያ ውጪ ያሉት ተቃራኒ ወይም የተዛቡ ምንፍቅናዎች ሔተሮዶክስ ይባላሉ፥ ኦርቶዶክስ ሆነ ሔተሮዶክስ በየትኛው ሃይማኖት ቅዱሳን መጽሐፍት ቃሉ የለም።
"ኦርቶዶክስ" የሚለው ቃል ይቅርና "ክርስትና" የሚለው ቃል ባይብል ላይ የለም፥ "ክርስትና" የሚለውን ቃል ለመጀመሪያ ጊዜ ያመጣው የአንጾኪያው ኤጲስ ቆጶስ አግናጥዮስ በ 110 ድኅረ-ልደት ነው።
ክርስቲያኖች በ4ኛ ክፍለ ዘመን በዓለም ዓቀፍ አንቀጸ-እምነት"ecumenical creed" ሦላሴ የሚባለውን እሳቤ በማስገባት በሃይማኖታቸው ወሰን አልፈዋል፦
4፥171 እናንተ የመጽሐፉ ሰዎች ሆይ! በሃይማኖታችሁ ወሰንን አትለፉ፡፡ በአላህም ላይ እውነትን እንጅ አትናገሩ፡፡ يَا أَهْلَ الْكِتَابِ لَا تَغْلُوا فِي دِينِكُمْ وَلَا تَقُولُوا عَلَى اللَّهِ إِلَّا الْحَقَّ
"ዲን" دِين ማለት "ሃይማኖት" "ፍትሕ" "ፍርድ" "ሕግ" "መርሕ"doctrine" ማለት ሲሆን የነቢያት ሆነ የሐዋርያት ፊተኛ እና ታላቁ መርሕ፦ "ጌታ አምላካችን አንድ ጌታ ነው" የሚል ነው፥ በዚህ ሃይማኖታቸው ወሰን በማለፍ፦ "አምላክ ሦስት ነው" ብለዋል፦
4፥171 «ሦስት ነው» አትበሉ! ተከልከሉ! ለእናንተ የተሻለ ይኾናልና፡፡ አላህ አንድ አምላክ ብቻ ነው፡፡ وَلَا تَقُولُوا ثَلَاثَةٌ ۚ انتَهُوا خَيْرًا لَّكُمْ ۚ إِنَّمَا اللَّهُ إِلَـٰهٌ وَاحِدٌ
ሥላሴ ሰው በማመኑ የማይድንበት በመካዱ የማይጠፋበት ሰው ሠራሽ መርሕ ነውና ሥላሴ ከማለት ተከልከሉ! ለእናንተ የተሻለ ይኾናልና፡፡ አሏህ አንድ አምላክ ብቻ ነው፡፡ አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።
✍ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://t.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
2 449
የማንን ክብር?
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።
5፥17 እነዚያ አላህ እርሱ የመርየም ልጅ አልመሲሕ ነው ያሉ በእርግጥ ካዱ፡፡ لَّقَدْ كَفَرَ الَّذِينَ قَالُوا إِنَّ اللَّهَ هُوَ الْمَسِيحُ ابْنُ مَرْيَمَ
ከፈሪሳውያንም ወገን የአይሁድ አለቃ የሆነ ኒቆዲሞስ የሚባል አንድ ሰው በሌሊት ወደ ኢየሱስ መጥቶ ኢየሱስ ምልክቶች የሚያደርገው አምላክ ከእርሱ ጋር ስላለ እንደሆነ እና መምህር ሆኖ የመጣው ከአምላክ ዘንድ እንደሆነ ተናግሯል፦
ዮሐንስ 3፥2 እርሱም በሌሊት ወደ ኢየሱስ መጥቶ፦ መምህር ሆይ! አምላክ ከእርሱ ጋር ከሆነ በቀር አንተ የምታደርጋቸውን እነዚህን ምልክቶች ሊያደርግ የሚችል የለምና፥ መምህር ሆነህ ከአምላክ ዘንድ እንደ መጣህ እናውቃለን" አለው። οὗτος ἦλθεν πρὸς αὐτὸν νυκτὸς καὶ εἶπεν αὐτῷ Ῥαββεί, οἴδαμεν ὅτι ἀπὸ Θεοῦ ἐλήλυθας διδάσκαλος· οὐδεὶς γὰρ δύναται ταῦτα τὰ σημεῖα ποιεῖν ἃ σὺ ποιεῖς, ἐὰν μὴ ᾖ ὁ Θεὸς μετ’ αὐτοῦ.
ይህ ከአምላክ የተላከ መምህር ይህን ያህል ምልክት በአይሁዳውያን ፊት ምንም ቢያደርግ በእርሱ አላመኑም፦
ዮሐንስ 12፥37 ነገር ግን ይህን ያህል ምልክት በፊታቸው ምንም ቢያደርግ በእርሱ አላመኑም። Τοσαῦτα δὲ αὐτοῦ σημεῖα πεποιηκότος ἔμπροσθεν αὐτῶν οὐκ ἐπίστευον εἰς αὐτόν,
የዮሐንስ ጸሐፊ ይህን ያህል ምልክት በፊታቸው ምንም ቢያደርግ በእርሱ ያላመኑበትን ምክንያት በኢሳይያስ ላይ እንደተነገረ ይናገራል፦
ዮሐንስ 12፥38 ነቢዩ ኢሳይያስ፦ "ጌታ ሆይ! ማን ምስክርነታችንን አመነ? የጌታ ክንድ ለማን ተገለጠ? ብሎ የተናገረው ቃል ይፈጸም ዘንድ ነው። ἵνα ὁ λόγος Ἡσαΐου τοῦ προφήτου πληρωθῇ ὃν εἶπεν Κύριε, τίς ἐπίστευσεν τῇ ἀκοῇ ἡμῶν; καὶ ὁ βραχίων Κυρίου τίνι ἀπεκαλύφθη;
እዚህ ዐውድ ላይ "ጌታ ሆይ" እና "ጌታ" የተባለው አብ ሲሆን እንደ ጸሐፊው "የጌታ ክንድ" ደግሞ ወልድ ነው፥ የግሪክ ሰፕቱአጀንት ላይ፦ "ጌታ ሆይ! ማን ምስክርነታችንን አመነ? የጌታ ክንድ ለማን ተገለጠ?" ሲል የዕብራይስጥ ማሶሬት ደግሞ፦ "የሰማነውን ነገር ማን አምኖአል? የያህዌስ ክንድ ለማን ተገልጦአል?" የሚል ነው፦
ኢሳይያስ 53፥1 ጌታ ሆይ! ማን ምስክርነታችንን አመነ? የጌታ ክንድ ለማን ተገለጠ? ΚΥΡΙΕ, τίς ἐπίστευσε τῇ ἀκοῇ ἡμῶν; καὶ ὁ βραχίων Κυρίου τίνι ἀπεκαλύφθη;
ኢሳይያስ 53፥1 የሰማነውን ነገር ማን አምኖአል? የያህዌስ ክንድ ለማን ተገልጦአል? מִ֥י הֶאֱמִ֖ין לִשְׁמֻעָתֵ֑נוּ וּזְרֹ֥ועַ יְהוָ֖ה עַל־מִ֥י נִגְלָֽתָה
የዮሐንስ ጸሐፊ የጠቀሰው ከዕብራይስጥ ማሶሬት ሳይሆን ከግሪክ ሰፕቱአጀንት እንደሆነ ማመሳከር ይቻላል፥ ኢሳይያስ በትክክሉ ያለው የትኛውን ነው? የሚል ጥያቄ የቤት ሥራ ይሁንልኝ! በመቀጠል የዮሐንስ ጸሐፊው ኢሳይያስ አይሁዳውያን ያላመኑበትን ምክንያት እንደተናገረ ይናገራል፦
ዮሐንስ 12፥39 ስለዚህ ማመን አቃታቸው፥ ምክንያቱም ኢሳይያስ ድጋሚ እንዲህ አለ፦ διὰ τοῦτο οὐκ ἠδύναντο πιστεύειν, ὅτι πάλιν εἶπεν Ἡσαΐας
ዮሐንስ 12፥40 "በዓይኖቻቸው እንዳያዩ፣ በልባቸውም እንዳያስተውሉ፣ እንዳይመለሱም፣ እኔም እንዳልፈውሳቸው፣ ዓይኖቻቸውን አሳወረ ልባቸውንም አደነደነ"። Τετύφλωκεν αὐτῶν τοὺς ὀφθαλμοὺς καὶ ἐπώρωσεν αὐτῶν τὴν καρδίαν, ἵνα μὴ ἴδωσιν τοῖς ὀφθαλμοῖς καὶ νοήσωσιν τῇ καρδίᾳ καὶ στραφῶσιν, καὶ ἰάσομαι αὐτούς.
ኢሳይያስ "ጌታ ሆይ" የሚለውን ያህዌህን ሲሆን "የጌታ ክንድ" ያለው እንደ ዮሐንስ ጸሐፊ ኢየሱስን ነው፥ "ክንድ" አገናዛቢ የሆነለት "ጌታ" ያህዌህ ሲሆን በግሪኩ ሰፕቱጀንት ጌታም፦ "ማንን እልካለሁ? ማንስ ለዚህ ሕዝብ ይሄድለታል?" ሲል ኢሳይያስም፦ "እነሆኝ እኔን ላከኝ" አለ፦
ኢሳይያስ 6፥8 የጌታንም ድምፅ፦ ማንን እልካለሁ? ማንስ ለዚህ ሕዝብ ይሄድለታል? ሲል ሰማሁ። እኔም፦ "እነሆኝ እኔን ላከኝ" አልሁ። καὶ ἤκουσα τῆς φωνῆς Κυρίου λέγοντος· τίνα ἀποστείλω, καὶ τίς πορεύσεται πρὸς τὸν λαὸν τοῦτον; καὶ εἶπα· ἰδοὺ ἐγώ εἰμι· ἀπόστειλόν με.
"የጌታ ድምፅ" የሚለው ይሰመርበት! ላኪው ያህዌህ ተላኪው ኢሳይያስ ነው፥ ያህዌህም ለኢሳይያስ ሂድ ይህንን ሕዝብ፦ "በዓይኖቻቸው እንዳያዩ፣ በልባቸውም እንዳያስተውሉ፣ እንዳይመለሱም፣ እኔም እንዳልፈውሳቸው፣ ዓይኖቻቸውን አሳወረ ልባቸውንም አደነደነ" አለው፦
ኢሳይያስ 6፥10 "በዓይኖቻቸው እንዳያዩ፣ በልባቸውም እንዳያስተውሉ፣ እንዳይመለሱም፣ እኔም እንዳልፈውሳቸው፣ ዓይኖቻቸውን አሳወረ ልባቸውንም አደነደነ"። ἐπαχύνθη γὰρ ἡ καρδία τοῦ λαοῦ τούτου, καὶ τοῖς ὠσὶν αὐτῶν βαρέως ἤκουσαν καὶ τοὺς ὀφθαλμοὺς αὐτῶν ἐκάμμυσαν μήποτε ἴδωσι τοῖς ὀφθαλμοῖς καὶ τοῖς ὠσὶν ἀκούσωσι καὶ τῇ καρδίᾳ συνῶσι, καὶ ἐπιστρέψωσι, καὶ ἰάσομαι αὐτούς.
2 449
እመኑ!
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
57፥7 በአላህ እና በመልክተኛው እመኑ፡፡ آمِنُوا بِاللَّهِ وَرَسُولِهِ
አምላካችን አሏህ በእርሱ አምላክነት እና በመልእክተኛው መልእክተኝነት "እመኑ" በማለት ይናገራል፦
57፥7 በአላህ እና በመልክተኛው እመኑ፡፡ آمِنُوا بِاللَّهِ وَرَسُولِهِ
እዚህ አንቀጽ ላይ አሏህን እና ነቢያችንን"ﷺ" "ወ" وَ በሚል አርፉል አጥፍ እና "አሚኑ" آمِنُوا በሚል በአንድ ግሥ ተጫፍሮ እና ተዛርፎ ስለመጣ ሚሽነሪዎች ነቢያችን"ﷺ" እንደሚመለኩ ለማስመሰል ሲቃጣቸው እና ሲዳዳቸው እያየን ነው፥ ጭራሽ "እመኑ" ማለት "አምልኩ" ማለት አርገው መረዳታቸው ስናይ ደግሞ ምን ያህል ለቅዱሳን መጻሕፍት ባዕድ እና ባይተዋር እንደሆኑ እንረዳለን። አምላካችን አሏህ፦ "በአሏህ እና በመልእክተኞቹ እመኑ" እያለ ብዙ ቦታ ይናገራል፦
3፥179 በአላህ እና በመልክተኞቹም እመኑ፡፡ فَآمِنُوا بِاللَّهِ وَرُسُلِهِ
4፥171 በአላህ እና በመልክተኞቹም እመኑ፡፡ فَآمِنُوا بِاللَّهِ وَرُسُلِهِ
አሏህ ጥንት በላካቸው ነቢያት "እመኑ" ሲል "አምልኩ" ማለቱ ነው ብሎ መረዳት ምን ያህል ቂልነት እንደሆነ በቀላሉ መረዳት ይቻላል፥ አሏህ "በመልክተኛው እመኑ" ሲል "በመልክተኞቹም እመኑ" በተባለበት ስሌት እና ቀመር ነው። እዚህ ድረስ ከተግባባን ከባይብል ይህንን ስሑት ሙግት በስሙር ሙግት እንሞግት፦
ዘጸአት 14፥31 በያህዌህ እና በባሪያው በሙሴ አመኑ። וַיַּֽאֲמִ֙ינוּ֙ בַּֽיהוָ֔ה וּבְמֹשֶׁ֖ה עַבְדֹּֽו׃ פ
እዚህ አንቀጽ ላይ ያህዌህ እና ሙሴ "እና" በሚል መስተጻምር እና "አመኑ" በሚል በአንድ ግሥ ተጫፍሮ እና ተዛርፎ ስለመጣ በእናንተ ስሑት ሙግት ሙሴ ይመለካልን? "በሙሴ አመኑ" ማለትስ "ሙሴን አመለኩ" ማለት ነውን? እንቀጥል፦
2 ዜና መዋዕል 20፥20 "በአምላካችሁ በያህዌህ እመኑ! ትጸኑማላችሁ፥ በነቢያቱም እመኑ ነገሩም ይሰላላችኋል"። הַאֲמִ֜ינוּ בַּיהוָ֤ה אֱלֹהֵיכֶם֙ וְתֵ֣אָמֵ֔נוּ הַאֲמִ֥ינוּ בִנְבִיאָ֖יו וְהַצְלִֽיחוּ׃
ማመን ማምለክ ከሆነ ነቢያቱን አምልኩ እያለን ነውን? "እረ በጭራሽ" ካላችሁ እንግዲያውስ ከላይ ያለውን የቁርኣን አንቀጽ በዚህ መልክ እና ልክ ተረዱት! እዚህ አንቀጽ ላይ "እመኑ" የሚለው ለአምላክ እና ለነቢያቱ ሁለት ጊዜ እንደተጠቀሙበት ኢየሱስም በተመሳሳይ የሰዋስው አወቃቀር "በአምላክ እመኑ" "በእኔም እመኑ" በማለት እርሱ እና አምላኩ ሁለት የተለያዩ ምንነት እና ማንነት እንደሆኑ አበክሮ እና አዘክሮ ተናግሯል፦
ዮሐንስ 14፥1 በአምላክ እመኑ፥ በእኔም ደግሞ እመኑ። πιστεύετε εἰς τὸν Θεόν, καὶ εἰς ἐμὲ πιστεύετε.
"በእኔ" በሚለው ቃል ላይ “ም” የሚለው ጥገኛ ምዕላድ በዐማርኛ ተጨማሪ ነገርን ለማሳየት የገባው በግሪኩ "ካይ" καὶ ማለትም "እና" የሚለውን መስተጻምር ለማሳየት የገባ ነው፥ ይህም አምላክ እና መልእክተኛው ሁለት የተለያዩ ሃልዎት እና ኑባሬ እንደሆኑ ቁልጭ አርጎ ያሳያል። ኢየሱስ መልእክተኛ እንደሆነ ማመን እና አንዱ አምላክ ላኪ እንደሆነ ማመን የእምነት መሠረት ነው፥ በእርግጥም በመልእክተኛው ማመን በላከው ማመን የሚሆንበት ምክንያት መልእክቱ የላኪው እንጂ የተላኪው ስላልሆነ ነው፦
ዮሐንስ 12፥44 ኢየሱስም ጮኸ፥ እንዲህም አለ፦ በእኔ የሚያምን በላከኝ ማመኑ ነው እንጂ በእኔ አይደለም።
ዮሐንስ 14፥24 የምትሰሙትም ቃል የላከኝ የአብ ነው እንጂ የእኔ አይደለም።
እንደተግባባን ተስፋ አደርጋለው። አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።
✍ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://t.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
2 449
እውነተኛ ብርሃን ማን ነው?
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡
ነጥብ አንድ
"እውነተኛው ብርሃን በቁርአን"
አሏህ ከፍጡራን ጋር በምንም አይመሳሰልም፤ ማንምና ምንም እርሱን የሚመስል የለም፦
42፥11 "የሚመስለው ምንም ነገር የለም"፡፡ እርሱም ሰሚው ተመልካቹ ነው፡፡
112፥4 ለእርሱም "አንድም ብጤ የለውም"፡፡
16፥74 ለአላህም "አምሳያዎችን አታድርጉ"፡፡ አላህ መሳይ እንደሌለው ያውቃል፡፡ እናንተ ግን አታውቁም፡፡
19፥65 እርሱ የሰማያትና የምድር በሁለቱም መካከል ላለው ሁሉ ጌታ ነውና ተገዛው፡፡ እርሱን በመገዛትም ላይ ታገስ፡፡ "ለእርሱ ሞክሼን" ታውቃለህን?
አላህ በዛቱ ማለትም በህላዌው"essence" ከማንም ከምንም ነገር ጋር የማይመሳሰል መሆኑን ካየን ዘንዳ የህላዌው መገለጫ ማን መሆኑን የምናውቀው በሲፋቱ ማለትም በባህርያቱ"attribute" ነው፤ አላህ ከፍጡራን ጋር የማይመሳሰል የራሱ ታላቅ ባህርይ አለው፦
16:60 ለአላህም "ታላቅ ባሕርይ" مَثَلُ አለው፤ እርሱም አሸናፊው ጥበበኛው ነው።
"መሰል" مَثَل ማለት "መገለጫ ባህርይ" "description" ሲሆን በሰማይና በምድር ከፍተኛ ማለትም ታላቅ ባህርይ አለው፦
30:27 ለርሱም በሰማያትም በምድርም "ከፍተኛ ባሕርይ" الْمَثَلُ አልለው፤ እርሱም አሸናፊ ጥበበኛ ነው።
አላህ የህላዌው መገለጫ በሰማይና በምድር ታላቅ ባህርይ እንዳለው ከተመለከትን "ኑር" نُور ማለት ብርሃን ማለት ሲሆን አላህ የሰማይና የምድር እውነተኛ ብርሃን ነው፦
24:35 አላህ የሰማያትና የምድር "ብርሃንنُورُ ነው፤ "የብርሃኑ" نُورِهِ "ምሳሌ" مَثَلُ ፥ በውስጧ መብራት እንዳለባት ዝግ መስኮት፥ መብራቱ በብርጭቆ ውስጥ የሆነ፣ ብርጭቆይቱ ፍጹም ሉላዊ ኮከብ የምትመስል፣ ምሥራቃዊም ምእራባዊም ካልሆነች፣ ከተባረከች የወይራ ዛፍ፣ ዘይቷ እሳት ባይነካውም እንኳ ሊያበራ የሚቀርብ ከሆነች ዘይት የሚቃጠል እንደኾነ መብራት ነው፤ ይህ በብርሃን ላይ የሆነ ብርሃን ነው፤ አላህ ወደ ብርሃኑ የሚሻውን ሰው ይመራል፤ አላህም ለሰዎች ምሳሌዎችን ያቀርባል። አላህም በነገሩ ሁሉ ዐዋቂ ነው።
አላህ ብርሃን ነው የተባለበት ፍጡራን በተባሉበት ሂሳብ አይደለም፤ አላህ እውነተኛ ብርሃን ነው።
ነጥብ ሁለት
"እውነተኛው ብርሃን በባይብል"
1ኛ ዮሐንስ 1:5 ከእርሱም የሰማናት ለእናንተም የምናወራላችሁ መልእክት፦ "እግዚአብሔር ብርሃን ነው ጨለማም በእርሱ ዘንድ ከቶ የለም" የምትል ይህች ናት።
ፀሃፊፍ ከኢየሱስ የሰማው መልእክት "እግዚአብሔር ብርሃን ነው ጨለማም በእርሱ ዘንድ ከቶ የለም" የሚል ነው፤ ነገር ግን ኢየሱስ በአራቱ ወንጌላት "እግዚአብሔር ብርሃን ነው ጨለማም በእርሱ ዘንድ ከቶ የለም" ብሎ ያስተማረበት አንድም ቦታ የለም፤ ይህ የሚያሳየው ኢየሱስ ተናግሮ ነገር ግን በአራቱ ወንጌላት ላይ ያልተካተቱ የኢየሱስ መልእክት እንደነበሩ ነው፤ ከቁርአኑ ጋር በተመሳሳይ ፈጣሪ እውነተኛ ብርሃን መሆኑን ካየን ዘንዳ ሚሽነሪዎች ኢየሱስ ብርሃን ተብሏል ስለዚህ በቁርአንና በኢየሱስ ንግግር ፈጣሪ የተባለው ኢየሱስ ነው ብለው አረፉት፦
ዮሐንስ 8፥12 ደግሞም ኢየሱስ፦ "እኔ የዓለም ብርሃን" ነኝ፤
እኛም ምግታችንን ሰፋ አድርገን ታዲያ ኢየሱስ የዓለም ብርሃን መባሉ አምላክ ያሰኘዋልን? ብለን ጥያቄ እናቀርባለን፤ መልሱ አዎ ከሆነ እንግዲያውስ ብዙ አምላኮች ሊኖሩ ነው፤ ምክንያቱም የዓለም ብርሃን የተባለው ኢየሱስ ብቻ ሳይሆን ሃዋርያትም ጭምር ናቸው፦
ማቴዎስ 5፥14 "እናንተ የዓለም ብርሃን" ናችሁ።
አይ ሃዋርያትን ብርሃን ያደረጋቸው እግዚአብሔር ስለሆነ የእነርሱ ብርሃንነት በመደረግ የተመሰረተ የፀጋ እንጂ የባህርይ አይደለም ከተባለ ኢየሱስንስ ብርሃን ያደረገው እግዚአብሔር አይደለምን? ስለዚህ የኢየሱስ ብርሃን መሆን እንደ ሃዋርያት በፀጋ እንጂ የባህርይ አይደለም፦
ኢሳይያስ 49፥6 እርሱም፦ የያዕቆብን ነገዶች እንድታስነሣ ከእስራኤልም የዳኑትን እንድትመስል ባሪያዬ ትሆን ዘንድ እጅግ ቀላል ነገር ነውና እስከ ምድር ዳር ድረስ መድኃኒት ትሆን ዘንድ ለአሕዛብ ""ብርሃን አድርጌ"" ሰጥቼሃለሁ ይላል።
ኢሳይያስ 42፥7 እኔ እግዚአብሔር በጽድቅ ጠርቼሃለሁ፥ እጅህንም እይዛለሁ እጠብቅህማለሁ፥ የዕውሩንም ዓይን ትከፍት ዘንድ የተጋዘውንም ከግዞት ቤት በጨለማም የተቀመጡትን ከወህኒ ቤት ታወጣ ዘንድ ለሕዝብ ቃል ኪዳን ለአሕዛብም ""ብርሃን አድርጌ"" እሰጥሃለሁ።
✍ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://t.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
2 449
የመስቀል አምልኮ
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
11፥2 እንዲህ በላቸው፡- «አላህን እንጂ ሌላን አታምልኩ! እኔ ለእናንተ ከእርሱ የተላክሁ አስጠንቃቂ እና አብሳሪ ነኝ» أَلَّا تَعْبُدُوا إِلَّا اللَّهَ ۚ إِنَّنِي لَكُم مِّنْهُ نَذِيرٌ وَبَشِيرٌ
ዘርዓ ያዕቆብ ከደረሳቸው መጻሕፍት አንዱ መስተብቁዕ ዘመስቀል ነው፥ መስተብቁዕ ዘመስቀል ላይ መስቀል እና ማርያም ከፈጣሪ ጋር ተካክለው ምስጋና እንደሚቀርብላቸው ይናገራል፦
መስተብቁዕ ዘመስቀል ቁጥር 8
"ለእሉ ክልኤቱ ፍጡራን ስብሐተ ፈጣሪ ይደልዎሙ እስመ ተዐረዩ በክብሮሙ"
"ለእነዚህ ሁለት ፍጥረታት የፈጣሪ ምስጋና ይገባቸዋል፥ በክብር ተካክለዋልና"
"ሁለቱ" የተባሉት "መስቀል እና ማርያም" ሲሆኑ እነዚህ ሁለት ፍጡራን ከፈጣሪ ጋር "በክብር ተካክለዋል" ይለናል፥ ኢየሱስን፦ "ዘዕሩይ ምስለ አብ በመለኮቱ(በባሕይርው ከአብ ጋር የሚተካከል)" ሲሉት ሲገርመን ማርያም እና መስቀልን "እስመ ተዐረዩ በክብሮሙ(በክብር ተካክለዋል)" ሲሏቸው አስደመመን። ስለተስተካከሉ ለፈጣሪ የሚገባው የፈጣሪ ምስጋና "ይገባቸዋል" ብለው አረፉት፥ ይህ እልም ያለ ሺርክ ነው። ስብሐት ለሦስቱ ማለትም ለእግዚአብሔር፣ ለድንግል እና ለመስቀል እንደሚገባ የዘወትር ጸሎት ላይ ተገልጿል፦
የዘወትር ጸሎት ቁጥር 9
"ስብሐት ለእግዚአብሔር ወወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር"
ትርጉም፦ "ለእግዚአብሔር፣ ለወለደችው ለድንግል እና ለክቡር መስቀሉ ምስጋና ይገባል"
መስቀል ከመመስገንም አልፎ ይሰገድለታል፦
የዘወትር ጸሎት ቁጥር 8
“እሰግድ “ለ”መስቀለ እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘተቀደሰ በደሙ ክቡር”
ትርጉም፦ “በደሙ ክቡር “ለ”ተሰቀለበት ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል እሰግዳለው”
እንደ ትምህርታቸው ኢየሱስ የተሰቀለበት እና ደሙን ያፈሰሰበት እንጨት እኮ አንድ ነው፥ ዛሬ በእጃቸው የሚያሳልሙበት እና በጉልላት ላይ የሚሰቅሏቸው መስቀሎች የተሰቀለባቸው፣ ደም የፈሰሰባቸው እና ወዝ የተንጠፈጠፈባቸው ስላልሆኑ በምንም ሒሣብ ክቡር አይደሉም።
የሚገርመው መስከረም 17 ቀን "ዮም መስቀል ተሰብሐ" ማለትም "ዛሬ መስቀል ተመሰገነ" በማለት ካመሰገኑት በኃላ መልሰው በደመራ ያቃጥሉታል። "የማናቸውንም ምሳሌ፥ የተቀረጸውንም ምስል ለአንተ አታድርግ፣ አትስገድላቸው፣ አታምልካቸውምም" እየተባለ ለማይሰማ እና ለማይለማ፥ ለማይናገር እና ለማይጋገር ለግዑዝ እንጨት የጸጋ ስግደት መስገድ አግባብ አይደለም፥ ይህ ድርጊት አሳፋሪ እንደሆነም ተገልጿል፦
ዘጸአት 20፥4 የማናቸውንም ምሳሌ፥ የተቀረጸውንም ምስል ለአንተ አታድርግ! አትስገድላቸው፥ አታምልካቸውምም።
መዝሙር 97፥7 ለተቀረጸ ምስል የሚሰግዱ ሁሉ፥ በጣዖቶቻቸውም የሚመኩ ይፈሩ።
"ለተቀረጸ ምስል የሚሰግዱ ሁሉ ይፈሩ" የሚለው ይሰመርበት! እኛም ሙሥሊሞች የምንለው ደግሞ "የፈጠራችሁን አሏህን ብቻ አምልኩ" ነው፦
11፥2 እንዲህ በላቸው፡- «አላህን እንጂ ሌላን አታምልኩ! እኔ ለእናንተ ከእርሱ የተላክሁ አስጠንቃቂ እና አብሳሪ ነኝ» أَلَّا تَعْبُدُوا إِلَّا اللَّهَ ۚ إِنَّنِي لَكُم مِّنْهُ نَذِيرٌ وَبَشِيرٌ
የፈጠረንን አንዱን አምላክ ብቻ ማምለክ ምንኛ መታደል ነው? አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።
✍ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://t.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
2 449
አንተ ለኔ አድርጎህ ልቤ ካልደረጀ
እንዳሰብኩት ሆኖ ኑሮዬ ካልበጀ
የጸለይኩት ጸሎት አንተን ካላመጣህ
እስኪ ልሳል ደሞ ከልቤ እንዲያሶጣህ
@fkren_be_4_mesmr
2 449
በገና ለገና ይሆን ይሁን እያልኩ
አንተን እንዳላጣ አይኖቼን ከጨፈንኩ
እንቅልፌን አጥቼ ሳልተኛ አድራለው
ካራራቀን ብዬ ህልሜን እፈራለው
@fkren_be_4_mesmr
2 449
ካንተ ጋር እያለው የምትሞቀኝ ጸሀይ
ላይኔ ጥሩ ሆኖ የሚታየኝ ሰማይ
አንተ ሳትኖር ጎኔ ላንተ እየወገኑ
ሁሉም ባዶ ይሆናል ከኔ ጋ ላይሆኑ
@fkren_be_4_mesmr
2 449
ትላንት አጥቼ ዛሬ አጊንቻለው
ብዙ ሰው እረስቶኝ እኔም ረስቻለው
እኔን የቸገረኝ የሆነኝ አበሳ
ያጣሁት መዳኒት አንቺን የሚያሥረሳ
@fkren_be_4_mesmr
2 449
ለልቤ መድሀኒት ያንተን ልብ ስሻ
ላኖርህ ሳልሽርህ እስከ መጨረሻ
ዳንኩ ስል ተነሳው አገገምኩኝ ካምና
ያንተም ጦር ሰበቀኝ ቆሰልኩ እንደገና
@fkren_be_4_mesmr
2 449
ሳልፈራ እንደ ልቤ በረርኩኝ በረርኩኝ
አንዱን እየለቀኩ አንዱን እየያዝኩኝ
አወይ የኔ ነገር የኔ መጨረሻ
ከኔው ቢጤ እንዳይሆን ልቡ ከማይረጋ
@fkren_be_4_mesmr
2 449
ደና ነኝ እላለው መድከም የት አባቱ
ገደልኝ አልልም ሰበረኝ ናፍቆቱ
ልክ እንደ ጀግነ ሲዋሽልኝ አፌ
ደና ነኝ እላለው ፎቶህን ታቅፌ
@fkren_be_4_mesmr
2 449
ለሰው ማይወራ ሚስጥር እንዳልለው
እሷ እንዳታቅብኝ ከሷ እንዳልደብቀው
እንደተረታሁኝ ልቤ እንደ ደከመ
አይኔ ይናገራል ካፌ እየቀደመ
@fkren_be_4_mesmr
2 449
ናፍቆት ህመም ሆኖ አመመኝ በብርቱ
መከፋት ማዘኑ የቱ ይወራ ስንቱ
ህመም ማስያገሻ መዳኒት የሌለው
አወይ ናፍቆት ሞኙ ገድሎኝ እንዳያርፈው
@fkren_be_4_mesmr
2 449
የኔ ያልኩትን ሰው በፍቅር ያየሽው
እንደምን ብለሽ ሞትን ተመኘሽው
ማርያምን ብያለው ደግሜ አልምልም
እሱንማ ደፍረው ካዩብኝ አልምርም
@fkren_be_4_mesmr
