fa
Feedback
ዲያቆን ሞገስ አብርሃም|moges abreham

ዲያቆን ሞገስ አብርሃም|moges abreham

رفتن به کانال در Telegram

እግዚአብሔር ቢፈቅድ ይህ ቻናል በተለያዩ ርእሰ ጉዳዮች ላይ እና በተለያዩ ጊዝያቶች ያዘጋጀዋቸውን ኦርቶዶክሳዊ መጣጦፎች ጽሑፎች እና የመጻሕፍት ዳሰሳዎች መማርያ ይሆኑ ዘንድ የማጋራበት ይሆናል። https://t.me/Mogesabreham https://t.me/joinchat/AAAAAEczV7heeRJD86ok2g

نمایش بیشتر
495
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
-630 روز

در حال بارگیری داده...

کانال‌های مشابه
هیچ داده‌ای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
ابر برچسب‌ها
هیچ داده‌ای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
اشارات ورودی و خروجی
---
---
---
---
---
---
جذب مشترکین
اوت '25
اوت '25
+1
در 0 کانال‌ها
ژوئیه '25
+7
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '25
+2
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '25
+4
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '25
+1
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '25
+7
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '25
+10
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '25
+2
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '24
+7
در 0 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '24
+10
در 1 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '24
+5
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '24
+21
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '24
+11
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '24
+10
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '24
+6
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '24
+6
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '24
+11
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '24
+34
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '24
+25
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '24
+8
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '23
+27
در 0 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '23
+10
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '23
+38
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '23
+36
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '23
+3
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '23
+19
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '23
+4
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '23
+7
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '23
+6
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '23
+6
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '23
+7
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '23
+37
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '22
+8
در 0 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '22
+15
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '22
+8
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '22
+7
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '22
+11
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '22
+9
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '22
+15
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '22
+16
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '22
+29
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '22
+17
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '22
+7
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '22
+9
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '21
+5
در 0 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '21
+10
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '21
+13
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '21
+10
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '21
+16
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '21
+24
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '21
+21
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '21
+14
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '21
+18
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '21
+14
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '21
+19
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '21
+16
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '20
+433
در 0 کانال‌ها
تاریخ
رشد مشترکین
اشارات
کانال‌ها
06 اوت0
05 اوت0
04 اوت+1
03 اوت0
02 اوت0
پست‌های کانال
❤ከልብ መዝገብ የተቀዱ ሐሳቦች ፩ ¤<><¤>¤<><¤>¤<><¤>¤<><¤> ✔️🌴ውኃ ስናበዛቸው የተሰበሩ አበቦች አሉ። ውኃን መቋቋም የማይችሉ የሚያምሩ አበቦች አሉ ድንገት ውኃ ስናበዛባቸው የሞቱ ወርቃማ አበቦች አሉ። ውብ ሆነን ደካማ ቅርንጫፎች አሉን የማንችላቸው እንክብካቤዎች መሰበርያችን ይሆናሉ ላያችንን ሳይሆን ውስጣዊ ድካማችንን ተረድቶ በልካችን የሚጎበኝን ቅዱስ እግዚአብሔር ብቻ ነው። ¤<><¤>¤<><¤>🔴¤<><¤>¤<><¤> ✔️🌴እንደ መብረቅ ብልጭታ ልባችን ላይ ድንገት በተኛንበት ሚያስባንነን ነውር አለብን። ከጨዋታ መካከል የሚያስተክዘን ሕመም አለብን ቃሉን በሰማን ቁጥር ለሕሊና ወቀሳነት የሚያስቀምጠን አንድ ከባድ ኃጢአት አለብን። ለመተው ያቃተን ልማድ የውድቀታችን ማንሻ ሆኗል። ግን ደግሞ ለመነሳት አቅም አጥተናል አይደል.....ጥጦስ ሆይ ቀና ማለትን አስተምረኝ... ¤<><¤>¤<><¤>🔴¤<><¤>¤<><¤> ዲ/ን ሞገስ አብርሃም https://t.me/deaconmoges17

2
ሰው የሆነ አምላክ የተሰኝውን መጸሐፍ ከዚህ በታች ባሉት የሰንበት ትምህርት ቤቶች መሸጫ ሱቅ ያገኙታል ✔️አ/ኅ/ደ/ም ቅዱስ ሚካኤል ሰንበት ት/ቤት ✔️ብሥራተ ገብርኤል ✔️ጎፋ ኪዳነ ምሕረት ✔️ቅዱ
ሰው የሆነ አምላክ የተሰኝውን መጸሐፍ ከዚህ በታች ባሉት የሰንበት ትምህርት ቤቶች መሸጫ ሱቅ ያገኙታል ✔️አ/ኅ/ደ/ም ቅዱስ ሚካኤል ሰንበት ት/ቤት ✔️ብሥራተ ገብርኤል ✔️ጎፋ ኪዳነ ምሕረት ✔️ቅዱስ ቂርቆስ
109
3
ድጓ ከምን ያድናል?? አንድ ሰው ታላቁን የድጓውን መምህር የናቀ መስሎት "የኔታ ድጓ ከምን ያድናል "ሲል ጠየቃቸው እሳቸውም ቀበል አድርገው "እንዲህ ከማለት ያድናል" አሉት ይባላል የድጓ ጓዳ እልፍኙ ብዙ ነው ሁሉም እልፍኝ ውስጥ ወንጌል በመደብ በመደብ ሳይዛነፉ ተቀምጧል ብሉያትና ሐዲስት ከነ ምሥጢራቸው ተሰይመዋል።
185
4
ለክሙን ነው፡፡ መሸነፍ ከዚህ ይጀምራል፡፡ አንተ ግን ይህን አታድርግ! እባብና ጊንጥ በበዛበት በረሀ ቢጥሉህም ለተራበ አንበሳ ቢሰጡህም፤ በነደደ እሳት ቢከቱህም፤ ሰይፍ እየሳሉ ብታያቸውም፤ አገልግሎትህን እተዋለሁ አትበል፡፡ ከአርባ ሐራ ሰማይ አንዱ አክሊል ለመቀበል አንድ ቀን ሲቀረው አገልግሎቱን ቢያቋርጥ ከወንድሞቹ ተለይቶ ከክብር ጎድሎ ሞተ፡፡ አንተ በአገልግሎትህ አክሊል የምትቀዳጅባት ሰዓት ያች አገልግሎትህን ተስፋ ቆርጠህ የተውክባት ሰዓት ብትሆንስ? ወደ እግዚአብሔር የምትጠራባት ዕለት ያች ብትሆንስ ምን ታውቃለህ? አገልግሎት የሚቋረጥ ቢሆን ኖሮ ዮሐንስ መጥምቅ ከሞተ በኋላ እንዲያርፍ እንጅ የተቆረጠች አንገቱ ክንፍ ተሰጥቷት እየዞረች ለሰባት ዓመታት ስትሰብክ ባልሰማናትም ነበር፡፡ አየህ በሕይወት ሳለ ስድስት ወር ብቻ የሰበካትን ወንጌል ከሞተ በኋላ ግን ሰባት ዓመት ሰበካት፡፡ ዓላማ ካለህ አገልግሎትህን እንኳን ሰዎች ሞት አያቋርጥህም፡፡ ( በሊቀ ሊቃውንት ስምዐ ኮነ መልአክ )
355
5
++ " አገልግሎት ላቆም ነው " ++ ---------------- (በ ሊቀ ሊቃውንት ስምዐ ኮነ መልአክ ) በትምህርት ቤት የማውቀው አንድ ወንድሜ ሁልጊዜ ከምንለዋወጠው የተለየ ደብዳቤ ላከልኝ፡፡ እንደተለመደው መስሎኝ ደብዳቤውን ከፍቼ እስከማየው ቸኮልሁ፡፡ ገና የመጀመሪያውን መስመር ሳነበው ደም የሚያደርቅ ንባብ ተጽፎበት አገኘሁት ደግሜ አነበብሁት፤ አገልግሎት ላቆም ነው ይላል፡፡ መጨረስ ቢያቅተኝም መጨረስ ስለነበረብኝ እየመረረኝ ጨረስሁት፡፡ የመጨረሻው መስመር ላይ እየቀለድሁ ነው የሚለኝ መስሎኝ እጠብቅ ነበር፡፡ ግን አልሆነም፡፡ መረረኝ፤ ሰዎች አላሠራኝ አሉ፡፡ ቤተ ክርስቲያኒቱማ ሕጓ የቀና፣ ሥርዓቷ የተስተካከለ ዜማዋ የሚናፍቅ፣ ማኅሌቷ የሚደነቅ፣ ቅዳሴዋ የሚመስጥ ነበር ነገር ግን በሰዎች ግፊት ከዛሬ ጀምሮ ሁሉንም ትቼ ወጥቻለሁ አለኝ፡፡ አገልግሎት ይቋረጣል? ሰው ያለ አገልግሎት ይኖራል? አገልግሎቴን ላቆም ነው ማለትስ ምን ማለት ነው? በቅንነት በሚያገለግሉ አገልጋዮችስ ላይ ተስፋ የሚያስቆርጡ ሰዎች የሚበዙት ለምንድነው? የሠራኸው አይመቻቸውም፤ እንዳይሠሩት ዐቅሙም ፍላጎቱም የላቸውም፡፡ እያልሁ በጥያቄ ራሴን አስጨነቅሁት፡፡ አይሁድ በሞሏት በኢየሩሳሌም አገልግሎትን መጀመር እንዴት ከባድ ነው? ድውይ ብትፈውሱ ሰንበት ነው ይሏችኋል፡፡ ውኃ ከዐለት ላይ ብታፈልቁ “ደጋ ስለሆነ ውርጩን እያረጋ ውኃ አፈለቅሁ ይላል እንጅ ቆላ ቢሆን አይችልም ነበር” ብለው ያሟችኋል፡፡ ትምህርታችሁን ይወዳሉ፤ ነገር ግን አባቱን የምናውቀው የዕገሌ ልጅ አይደለምን? ብለው ያናንቋችኋል፡፡ እንደዚህ ካሉ ሰዎች ጋር ማገልገል እንዴት ይቻላል? ከእነዚህ ሰዎች መካከል መኖር በጣም ከባድ ነው፡፡ ግን የእግዚአብሔር ፈቃድ እንዲሁ ነውና ሆነ፡፡ ቤተ ክርስቲያን አገልግሎት የጀመረችው በክፉዎች አይሁድ መካከል ነው፡፡ እጅ መንሻ የያዙ ሰዎች ክርስቶስ ወደ ተወለደበት ቦታ መጡ እንጅ ክርስቶስ እጅ መንሻ ወደ ሚያቀርቡለት ነገሥታት ከተማ ሂዶ አልተወለደም፡፡ በተወለደበት ቦታ ያሉ ሰዎች አላወቁትም አብረውት ያደጉ የናዝሬት ሕጻናትም አላከበሩትም፡፡ ሁሉም ክፉዎች ስለነበሩ አብረውት ካደጉት መካከል ለደቀ መዝሙርነት መዐርግ የበቃ ማንም የለም፡፡ በክፉዎች መካከል ተመላለሰ፡፡ የቤተ ክርስቲያንን አገልግሎት ከዕለተ ምጽአት በፊት ንስሐ መግባት በማይችሉት ክፉ ሕዝቦች መካከል መሠረታት፡፡ በጣም የሚገርመው እንደ እስራኤላውያን ትንቢት ተገልጾላቸው ሱባኤ ገብተው ባያውቁትም የክርስቶስን መምጣት በፍልስፍናቸው በጥበባቸው ተመራምረው አግኝተው ቀኑን እየጠበቁ የነበሩ አሕዛብ ነበሩ፡፡ ፍርዱ ለኛ ቢሰጠን “ከሀገራችን ውጣልን” ማቴ 8÷34 ብለው ከሚለምኑ ሰዎች መካከል ከሚኖር የሐዋርያትን መምጣት እየተጠባበቁ በነበሩ በግሪክ ፈላስፎች ጉባኤ መካከል ቢኖር ደስ ይለን ነበር፡፡ አንድ አስደናቂ ለፍርድ የሚያስቸግር የሥነ ፍጥረት ታሪክ ላጋራችሁ፡፡ ውኃ ልህሉህ ነው፤ ነገር ግን በደደረው የዐለት ደረት ላይ እንዲፈስ መደረጉ ለምንድነው? መሬት ጽኑ ነው ነገር ግን በልህሉህ ውኃ ላይ እንዲንሳፈፍ ሆኖ መፈጠሩ ለምንድነው? እኔ ሲገባኝ ውኃ ንጽሕናውን ጠብቆ እንዲኖር በጠነከረ ዐለት ላይ መፍሰስ አለበት፡፡ የውኃ መንገዱ እንዳይቋረጥ ከተፈቀደለት ውቅያኖስ ድረስ ለመፍሰስ ከድንጋይ ጋር እተጋጨ መቀጠል ግድ ሆኖበታል፡፡ ድንጋዩ ከቆመበት ፈቀቅ ባለማለቱ፤ በውኃው መንገድ ላይ ቆሞ አንዳንዴ ውኃው መንገዱን ለቅቆ እንዲሄድ ቢያደርግም ውኃውን በመሬት ውስጥ ሰርጎ የመሬት ሲሳይ ሆኖ ከመቅረት የታደገው ዐለቱ ድንጋይ ነው፡፡ ውኃና ድንጋይ ቢካሰሱ መንገዴን ይልቀቅልኝ፤ አፈሩን ጠርጌ ባወጣሁት መንገድ መካከል እየገባ አስቸገረኝ ቢላችሁ ለማን ትፈርዳላችሁ? ከላይ ስናየው ውኃ ያቀረበው ክስ እውነት ነው፡፡ ነገር ግን ድንጋዩ ቢነሳ ዐለቱ ተሰብስቦ ቢወገድ የውኃን መንገድ ማን ያጸናለታል፡፡ ውኃ መንገዱን ጠብቆ እንዲሄድ በሜዳ ፈስሶ እንዳይቀር ዳርና ዳሩን ማን ይጠብቅለታል? በዳር ያለው አፈር ተደርምሶ የውኃን መንገድ እንዳይዘጋ ጠባቂ ሆኖ የተቀመጠውን ድንጋይ ከውኃ ጋር መጋጨቱን አንዳንድ ጊዜም የውኃን መንገድ ማስቀየሱን የተመለከተ ሰው ድንጋዩን ለማስወገድ ጥረት ያደርግ ይሆናል፡፡ አለበለዚያም ለውኃ ሌላ ድንጋይ የሌለበት መንገድ መፈለግ ያምረው ይሆናል፡፡ እስኪ አስቡት ባክኖ፣ በሜዳ ፈስሶ ከመቅረት ያዳነውን፤ ከመሬት ጋር ተቀላቅሎ ውበት ንጽሕናውን አጥቶ እንዳይኖር የጠበቀውን ዐለት ውኃን የሚያማታው፣ እንዲጮኽም የሚያደርገው እሱ ነውና ይውጣ አለበለዚያም መንገድ እንቀይርለት እንዴት ይባላል? በኛም የአገልግሎት ስፍራ እንዲሁ ነው፡፡ ክፉ ሰዎች የሌሉበት አገልግሎት ያለው በሰማዩ ቤተ መቅደስ ብቻ ነው፡፡ እዚያ ገብተን ማገልገል እስክንጀምር ድረስ በሃይማኖት የሚመስሉን ከሆነ ከሁሉም ሰው ጋር እንሰለፋለን፡፡ እነዚህ ሰዎች ላወቀባቸው ሰው የጸጋ ምንጭ ናቸው፡፡ እንደዛማ ባይሆን ኖሮ ጌታ በቅዱስ ወንጌል “ሲነቅፏችሁና ሲያሳድዷችሁ በእኔም ምክንያት ክፉውን ሁሉ በሐሰት ሲናገሩባችሁ ብፁዓን ናችሁ ዋጋችሁ በሰማይ ታላቅ ነውና ደስ ይበላችሁ” ማቴ 5÷11 ባላለንም ነበር፡፡ የዚህ ቃል ኪዳን ተጠቃሚ የምንሆነው እንዲህ ካሉ ሰዎች ጋር ታግለን ስናሸንፍ እንጅ መንገድ ስንቀይር አለበለዚያም አገልግሎት ስናቋርጥ አይደለም፡፡ የቆሎ ተማሪዎች ሆነን ልመና ስንወጣ የአንበሳ ደቦል የሚያኽል ውሻ ያጋጥመናል፡፡ አለመለመን ለረሀብ አሳልፎ ይሰጣል፤ መለመንም ከውሻ ጋር ያታግላል፤ እልፍ ካለም ያስነክሳል፡፡ ሆኖም ግን የተማሪው ምርጫ ከውሻው ጋር ታግሎ እንጀራ ማግኘት ነው፡፡ አንድ አገልጋይም በአገልግሎት ጎዳናው ላይ የሚያደናቅፉት ሰዎች ቢኖሩ እነዚያን ከአንበሳ ዝቅ የሚሉ ውሾች ታግሎ እንጀራ እንዳገኘ ታግሎ ጸጋ እግዚአብሔርን መውረስ ነው፡፡ ባሳለፍነው ጊዜ ረሀቡን የታገሥነው፤ ፊታችን ላይ ጓደኞቻችን ትምህርት ፍለጋ መጥተው በቆላ ወባ (ወረርሽኝ) ተነድፈው ሲሞቱ እያየን ቀብረን ተመልሰን ትምህርታችንን የቀጠልነው ቤተ ክርስቲያኒቱን አስበን እንጅ እነዚህን ሰዎች አስበን አይደለም፡፡ በደመና ጊዜ ፀሐይ ቢያምረን ደመናው እስኪያልፍ መታገሥ ግድ ነው፡፡ ደመናውን ማን ይገፋዋል? ደመና ወደ ሌለበት ስፍራ በፍጥነት መዘዋወርስ ለማን ይቻለዋል? ደግነቱ ደመናው አላፊ ነው፤ ፀሐይ ግን ለዘወትር የሚኖር ነው፡፡ ክረምት የሚረገረገው ደመና የበጋውን ፀሐይ ካስረሳን ችግሩ እኛ ላይ ነው፡፡ ሁል ጊዜ ከደመናው ጀርባ ፀሐይ መኖሯን አስተውሉ፡፡ ፀሐይ ስትወጣ ደግሞ ይሄ ሁሉ ቆፈን አድራሻው እንደማይገኝ ልብ በሉ፡፡ አገልግሎታችንን አንተውም፤ ትግላችንንም ከሰዎቹ ጋር አናደርግም፡፡ ብዙ ጊዜ ሰዎችን በየደረጃው ካለው አገልግሎት የሚያርቃቸው ትግላቸውን ከሰዎች ጋር ስለሚያደርጉት ነው፡፡ ሰዎችን ለመለወጥ አትሞክር ሥራህን አስተካክለህ ቀጥል፡፡ ጌታ ጸሐፍት ፈሪሳውያንን ለመለወጥ ጊዜውን አላባከነም፡፡ ለቤተ ክርስቲያን ሊያሳያት የሚገባውን አገልግሎት ግን በሚገባ አከናወነ፡፡ ፈሪሳውያን በጥያቄ ሲፈትኑት፣ ከነገሥታት ነገር ሲሠሩበት፣ በቤተ መቅደስ ሲዶልቱበት ስለእነሱ “ዘለፋ ካህናትን” ማቴ 23÷1 ካስተማረበት ጉባኤ በቀር የትምህርቱ ርዕስ አድርጓቸው አያውቅም፡፡ እኛ ግን የወሬ ርዕስ የምናደርገው የሚያግዙንን የሚረዱንን ሰዎች ሳይሆን አላሠራን ያሉትን ሰዎች ነው፡፡ ደጋግመን የምንሰብከው አንቀፀ ብፁዓንን ሳይሆን ዓሌ
300
6
ድል ንሱ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መሔድ ያለብን በምን አይነት መንገድ እንደሆነ ፥ ማንን መከተል እንዳለብን ፥ ይህንን ዓለም እንዴት እና በምን ድል መንሳት እንደምንችል ፥ እርሱን መከተል የት ድረስ እንደሆነ እና እርሱን መምሰልን በቃል በተግባርም አሳይቶናል። እኛም ኦርቶዶክሳዊያን በመንፈስ ከማይጠፋው ዘር ዳግም የተወለድን(በጥምቀት) ባሪያዎቹ የእርሱን ፈለግ ተከትለን በእርሱ መንገድ እንሄዳለን። "ኃይል የእግዚአብሔር ነው" እንዲል መጽሐፍ ጌታን ኃይላችን አድርገን ድል የማንነሳው አንዳች ነገር የለም። ድክመታችንን ሁሉ የሚያውቅ አምላክ ምን ያህል እንደሚረዳን ሥጋ ለብሶ ፤ የሰውን ባሕሪይ የገዛ ገንዘቡ አድርጎ ከዓለም መከራ ተካፈለ። አርአያ ሲሆነንም ድል ነስቶ ድል ንሱ አለን። "ለሚያምን ሁሉ ይቻላል" ብሎም በእርሱ ካመንን የሚያስቆመን ኃይል እንደሌለ በማይታበል ቃሉ ነገረን። "ሰማያት ተከፈቱ" ተብሎ መኖርያችን ተስፋ እንደተሰጠን እና ምሥጢር እንደተገለጠልን ሁሉ ይህን ዓለም የምናሸንፍበትን እያንዳንዱን መሳሪያ(ጦም ፥ ጸሎት ፥ ቃለ እግዚአብሔር...) ገልጦልን "አቸናፊው ጌታ አቸንፉ አለን።" "ከእኔም ተማሩ" ፤ "ፍለጋውን እንድትከተሉ ምሳሌ ትቶላችሁ" - ማቴ 11፥28 ፤ ፩ ጴጥ 2፥21 እንዲህና የመሳሰሉ ኃይለ ቃላትን ተንተርሰን አንድ የወንጌል ክፍል ጠቅሰን ነገራችንን እንቋጭ። "በእኔ ሳላችሁ ሰላም እንዲሆንላችሁ ይህን ተናግሬአችኋለሁ። በዓለም ሳላችሁ መከራ አለባችሁ ፤ ነገር ግን አይዞአችሁ እኔ ዓለምን አቸንፌዋለሁ።" - ዮሐ 16፥33 ያለን ጌታ ፦ ድል ንሱ እያለ ዕለት ዕለት ያበረታናል። #አይዞአችሁ_የሚል_ጌታ ታሪኩ ትዕግስቱ ወልደሀና ሐምሌ 01 2017
158
7
"ተስፋዬም እግዚአብሔር ነው" መዝ 69 ....በጥንት ዘመን አንድ ንጉሥ በሁለት ሰዎች ላይ ሞት ፈርዶ ሲያበቃ ለመጨረሻ ጊዜ የምትናገሩት ሐሳብ ካለ ይዛችሁት ከምትሞቱ ሐሳባችሁን ግለጹ አላቸው። አንደኛው የሞት ፍርዱ ላይነሳልኝ ምን አደከመኝ ብሎ ያስብና ምንም የምናገረው ነገር የለኝም የለኝም ይላል። ሌላኛው ግን ዝም ብዬ ከምሞት ብሎ ያስብና አንድ መላ ያመጣል። ንጉሱ አንድ በጣም የሚወዳት ምርጥ ፈረስ እንዳላቸው ስለሚያውቅ "ንጉስ ሆይ ሺ ዓመት ይንገሡ! እኔ የሚወዱትን ፈረስዎ ለአንድ ዓመት መብረር ላለማምውደ እችላለሁ" ይህ የሚሆነው ግን የአንድ ዓመት ዕድሜ ከተሰጠኝ ብቻ ነው ይላል። ንጉሡም አባባሉ ቢያስገርመውም "የሚበር ፈረስ ያለው በዓለም ላይ ብቸኛ ንጉሥ" መባሉን ውስጡ ስለወደደው በነገሩ ተስማምቶ የአንድ ዓመት ዕድሜ እንዲሰጠው ፈቀደ ። ከችሎቱ መልስ ያ ዝም ያለው ባልንጀራው በዚህኛው ላይ ስላቅ ተናገረበት "ወፈፍ ያረግሃል ልበል? አሁን በየት ሀገር ነው ፈረስ የሚበረው? አንድ ዓመት ረዥም መስሎህ ነው ይህን የማይሆን ነገር የምትናገረው? ምናለ ጣርህን ባታበዛው" አለው። ብልሁ ሰው ግን ተኩራርቶ እኔ እንዳንተ ዝም ብዬ አልሞትም ይህን ሃሳብ ሳቀርብ ነጻ ለመውጣት አራት አማራጮች አሉኝ እነርሱም፡- ፩ኛ. በዚህ አንድ ዓመት ንጉስ ሊሞቱ ይችላሉ ፪ኛ. እኔ እራሴ ልሞት እችላለሁ ፫ኛ. ፈረሱ ሊሞት ይችላል ፬ኛ. ማን ያውቃል ምን አልባት ፈረሱን መብረር አስተምረው ይሆናል። አለው ይባላል።።።።። "ተስፋ የተሰበረ ልብ ማከሚያ ለተያዘ እግር ብርታት ነው ጊዜን ዘመናትን ከሚያፈራርቅ ከእግዚአብሔር ውጪ ነገን ማን ያውቃል...... መቆዘምያ......
195
8
++ሐራሩኤል ጭርዋቅ++ ጥበብን የለበሳት ጠቢብ ሰሎሞን ለራሱ ሐራሩኤል ጭርዋቅ የሚል ስመ አምላክ የሰፈረበት ቀለበት ነበረው። ትእምርተ መንግሥቱ ግርማ ሞገሱ እሱ ነው ከሴት ሲደርስ አንበሳ መደብ ሲወጣ ቀለበቱን አውልቆ ከዙፋኑ ላይ ያኖረው ነበር። በአንድ ወቅት አንበሳ መደብ ደርሱ ሲመጣ ሰይጣን ለምቀኝነት አያርፍምና ቀለበቱን ከዙፋኑ ማንሳት ባይቻለው ከነዙፋኑ ጠቅሎ ባሕር ላይ ጣለው ሰሎሞን ሲመለስ ዙፋን ቤቱ ከለከለው የንግሥናውን ምልክት ግርማ ሞገሱን አጥቷልና ጎስቋላ ሆነ። ከዚህ በኋላ በገዛ ከተማው ሁለት ሳምንት ለምኗል ሰይጣን የሰው ልቡና አጽንቶበት የሚሰጠው አጥቶ ከመሠግራነ ዓሳ ሄዶ ስመ እግዚአብሔር ጠራባቸው ከመሀከላቸው አንዱም ይህ ዘብዛባ ብሎ የሞተ አሳ ጣለለት ሆድ እቃውን አውጥቶ ለመመገብ ቢቀደው ቀለበቱን አገኘ ቀለበቱን እንዳገኘ ግርማ ሞገሱ ከነክብሩ ተመለሰለት። በሰይጣን የተነጠቀው መንግሥቱ ተመለሰ ብዙዎቹም ሰሎሞን መሆነን ሲያውቁ ንጉሥን ከዚህ ምን አመጣው ብለው ከበቡት ቡሀላም መርበበተ ሰሎሞን የሚባል ስመ አምላክ አትሞ ቀብሮታል።ሰሎሞንን እዚህ ያደረሰው ምንድነው ቢሉ ከዕለታት በአንዳቸው የተራበ ሰው ስመ እግዚአብሔር እየጠራ ሲለምነው ይህ ሰው ምን ሆኗል አለ ተርቦ ነው ቢሉት ረኀብ ምንድነው ብሎ ነበርና የረኀብን ጽናት ሊያሳየው ይህ ተፈጸመበት።>>{ቅዳሴ ማርያም ትርጓሜ} 👇👇👇👇👇 የሰሎሞን መንግሥት እና ንግሥና በቀለበት ምክንያት እንደተመለስ በአዳም የሄድ አንድም ያጣነው ልጅነት እንደ ቃልህ ይደረግልኝ በሚለው የእምነት ቃሏ በእርሷ ተመልሱልናልና መርበብት ሰሎሞን ተብሎ የታተመበት ሐሩራኤል ጭርዋቅ የሚል ስመ አምላክ የተጻፈባት የሰሎሞን ቀለበት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት እንላለን። የሰው ልጅ በጥንት መርገም ተይዞ በነበረበት ዘመን በንጽህናና በቅድስና አጊጣ በምክረ ከይሲ በአዳም ስህተት ያጣነውን ልጅነት ያገኘንባት ለእርሷ ለሰው እንዲረዳ መሰልንላት አንጂ ከሰሎሞን ቀለበት በብዙ ትልቃለች። በረከቷ ምልጃዋና ጸሎቷ አይለየን ዲ/ን ሞገስ አብረሃም ሰኔ 23 የንጉሥ ዳዊት ልጅ ጠቢቡ ሰለሞን ያረፈበት ቀን ነው ።
190
9
#አዛኝ_ቅቤ_አንጓች አንድ ከወሬ በስተቀር የማያውቅ የሥራ ሰው ያልሆነ ሰው ይታመምና አልጋ ላይ ይውላል። ቦታው ለህክምና ባዳ በመሆኑ የቀየው ነዋሪ እንደልማዱ በሽተኛውን ከሐኪም ለማገናኘት ከነአልጋው ወሳንሳ ተሸክሞ የ3 ሰዓቱን የእግር ጉዞ ተያይዞታል። ያ ምላስ ሀብቱ የሆነ ሕመምተኛ ሰዎቹ ትከሻ ላይ እንዳለ ከአልጋው ቀና ሲል አንድ የተጣለውን የሰፈር ሰው ከፊት ሲሔድ ያየዋል። ይኼኔ ፊቱን ጨፍገግ ያደርግና "ስማ ማነህ? አንተ! ባዶህን ከፊት ቀድመህ ከምትሄድ ምናለበት የተሸከሙኝን ሰዎች ብታግዛቸው?" ይለዋል። እንዲህ የተባለውም ሰው በሰውየው ድርጊት ብስጭት ይልና "ካዘንክላቸው ውርደህ በእግር አትሄድም" አለው ይባላል" 🔴🔴🔴🔴 ከኃጢአት ልማድ ይከፋል። የወሬ ልማድ ደግሞ ጓዙ ብዙ ነው። አንድ አንዶች የሚሸከሙህ አመልህ ስላማረ ሳይሆን ስላዘኑልህ ይሆናል አልያም እራሳቸውን ከጸጸት ለማዳን አስበውም ይሆናል። አመልህንም ህመምህንም ታግሰው የተሸከሙህን ሰዎች ወረድ ብለህ አግዛቸው በሰዎች ጫንቃ ላይ ተደላድሎ መሔድ እና ከፍ ብሎ መቀመጥ ያስደስታል ነገር ግን የሰው ሸክም ሆነህ ሌላ ተሸካሚ አትሻ። ከአካል ደዌ በወሬ የሚመጣ ደዌ የከፋ ነው። ይህ ደዌ በቃሬዛ ላይ እያቃስትክ እንኳን እገሌ ከመቃብሬ እንዳይቆም የሚያስብል የምላስ ወለምታ ያስጋሳሀል። እናማ ወንድም አለም ከተጣላህ አንድ ሰው ይልቅ ወደውህ ሳይሆን አዝነውልህ የተሸከሙህን ሰዎች እዘንላቸው ። አካልህንም ምላስህንም ይሸከሙ ዘንድ አታስጨንቃቸው። ሌላው ቁምነገር ወዲህ ነው ከወሬኛ አዛኝ የንጉሥ ጅራፍ ይሻላል። የልቤ ምክር ለልቤ ዲ/ን ሞገስ አብርሃም
201
10
#እዚህ_ሰፈር_አይደለውም በአንድ ሀገር ሁለት እብዶች በጠራራ ፀሐይ ይከራከራሉ ሁለቱም እህል ውሃ የሚያሰኝ ዱላ ይዘዋል። የክርክራቸው ርእሰ ጉዳይ ፀሐይዋ ናት። አንደኛው እብድ "አሁን ከሌሊቱ ፮(6) ሰዓት ነው ካላመንክ ይኧው ጨረቃዋ ይለዋል" ሌላኛው እብድ " አይደለም ከቀኑ ፮(6) ነው!ይህች ጨረቃ ሳትሆን ፀሐይ ናት" ይላል በዚህ ሁኔታ ሲሟገቱ አንድ መንገደኛ አጠገባቸው ይደርስና እንዲያውም እሱ ይጠየቅ ብለው ሁለቱም እብዶች እየሮጡ ወደ መንገደኛው ተጠጉ "ይህች ፀሐይ አይደለችም?" አለ አንዱ እብድ ....ሁለተኛውም ቀጠለና "ይህቺ ጨረቃ አይደለች?" አለ .....አይደለችም አሁን ከቀኑ 6 ሰዓት ነው አለ የመጀመርያው እብድ "ኧረ አይደለም ከለሊቱ 6 ሰዓት ነው"አለ እሽ እሱ ይመስክር ተባባሉና ዝም አሉ። መንገደኛው ጨረቃ ናት ቢል ፀሐይ ነች ያለው በያዘው ዱላ አይለቀውም። ፀሐይ ነች ቢል ደግሞ ጨረቃ ናት ባዩ ማይለቀው ሆነ። ስለዚህ አውጥቶ አውርዶ "ወዳጆቼ እኔ እዚህ ሰፈር አይደለሁም ሌላ ሰው ጠይቁ" ብሎ ተገላገለ ይባላል ዱላ ፍራች የሚሠወሩ እውነታዎች አሉ። በእብዶች መካከል ሙሉ ጤነኛ መሆን ያስፈራል። የዓለማችን ጥቂት እውነታዎች ባሸበረቀ ልብስ ውስጥ በተደበቁ እብዶች ተገለዋል። የነቁ ከማስተዋል የደረሱ ዝም የሚሉባት ዱላ አይነቷ ብዙ ነው። እንዲህ ያሉ እውነቶች በእብዶች ፍልስፍናና ዱላ ተሸሸገዋል። እናማ የአንድ አንድ አዋቂዎች መልስ እዚህ ሰፈር አይደለውም ወደማለት ይጠጋል። ዲ/ን ሞገስ አብርሃም
189
11
+ሥርዓተ ቅዳሴ+ ጥቆማ ይህ ሥርዓተ ቅዳሴ የተሰኝው መጽሐፍ ከዚህ ቀድሞ በሠመሩ ሰነዶች ድርጅት ያለ አኮቴተ ቁርባን በሚል መጸሐፋቸው የተዋወቅናቸው ቀሲስ መብራቱ ኪሮስ ዳግመኛ ያዘጋጁት ሥርዓት ተኮር መጸሐፋቸው ነው። አዘጋጁ የሥርዓተ አምልኮ መናገሻ የጸሎት ሁሉ ጉልላት የሆነው የሥርዓተ ቅዳሴ ክብር እና ልዕልና በእያንድ አንዱ ክርስቲያን ልቡና ታትሞ እንዲቀር ያላቸው ፍላጎት ጽኑ መሆኑን በሁለቱ ድርሰቶቻቸው እንታዘባለን። ሥርዓተ ቅዳሴ የተሰኝው መጸሐፍ የቅዳሴ ልኡካን ዲያቆናትና ካህናት በሥርዓተ ቅዳሴ የሚሳተፉ ምዕመናን ሁሉ ቢያነቡት ለቅዳሴ የሚገባውን ክብር ሥርዓትና ምሥጢር ጠንቅቀው ይረዱታል። ከ100 በላይ ዋና ዋና ርእሶች ያጠቃለለው መጸሐፍ 387 ገጾች ያሉት ሲሆን ለማስተዋወቅ ይረዳ ዘንድ የመጸሐፉ የትኩረት መአከል የሆኑ ጉዳዮችን በመደብ በመደብ አድርገን ማየት እንችላለን። 🔴በሥርዓተ ቅዳሴ ስለሚሳተፉ ልዑካን በቅዳሴ ወቅት የሚሳተፉ የሚቀድሱ የሚያቆርቡ የቅዳሴ ልኡካን ሊያደርጉት ስለሚገባ ቅድመ ዝግጅት ስለ ሚጸልዮት ጸሎት በጥቅሉ ሊጠብቋቸው ሊጠነቅቋቸው የሚገቡ በዛ ያሉ ሥርዓቶችን ያትታል። 🔴መገልገያ ዕቃዎችን በተመለከተ በቅዳሴ ጊዜ ልዑካኑ ከሚለብሱት ልብሰ ተክህኖ ጀምሮ ነዋያተ ቅድሳት ላይ የሚጸለዮ ጸልቶችና ምሥጢራቸውን በተመለከት በጉልህና በተረዳ ያስረዳል። 🔴ጸሎትና ምሥጢራት ከላይ ለመግለጥ እንደተሞከረው ካህናቱ የሚጸልዮቸውን ጸሎቶች እንዲሁም በሥርዓት ቅዳሴ ላይ ያሉ ጸሎቶች ቡራኬዎች ምንነትና ዝርዝር ያብራራል። እንዲሁም በሥርዓት ቅዳሴ የሚደረጉ ክንዋኔዎች ምሥጢራዊ ፍቺያቸው ምሳሌነታቸውና ትርጉሞች ያትታል። 🔴ሥርዓተ ቁርባን ጸሎተ ቅዳሴ ለቁርባን የተዘጋጀ ምስጋና ሥርዓት እንደመሆኑ የቅዳሴ ዋና መአከላችን ቅዱስ ቁርባን ነው በዚህ መጸሐፍም ለቁርባን የሚደረገውን ጸሎት ጭምሮ ሊደረጉ የሚገቡ ጥንቃቄዎችን ያብራራል። 🔴 በሥርዓተ ቅዳሴ የሚሳተፉ ምዕመናን በተመለከተ ሥርዓተ ቅዳሴ ምእመናን እና ካህናት በጋር የሚሳተፉበት ታላቅ ምሥጢር ነው። ስለዚህም የካህናትን ተግባር ዘርዝሮ የምእመናን ድርሻና ሥርዓት ሳይጠቅሱ ማለፍ አይቻልም። በዚህ አግባብ በመጸሐፉ ምእመናን በቅዳሴ በቆሙ ጊዜ አበክረው ሊከታተሏቸው የሚገቡ ትእዛዞችና ትምህርቶች ጨምሮ የምእመናንን ሱታፌ ይተነትናል። 🔴 ሥነ ምግባር ይህ መጸሐፍ በቅዳሴ ጊዜ የምእመናን ካህናት ምግባር መሆን እንዳለበት ይናገራል። በቅዳሴ መካከል መሳቅ መሳለቅ ወዛ ፌዝ ማብዛትን ጭምሮ ቀኖና የሚያሰጡ እኩይ ምግባራትን ያነሳል። ለጥቆማ እንዲመች በመደብ አድርገን ገለጽነው እንጂ በጥቅሉ የቅዳሴን ሥርዓትና ምሥጢር ሥነ ምግባር በተረዳ የሚዘረዝር መጸሐፍ ነው። በሥርዓተ ቅዳሴና በሌሎች የሥርዓት መጸሐፍቶች የተቀመጡ ሐሳቦችን ዘርዘር አድርጉ ለትውልድ ማሻገር ትልቅ አበርክቶ ሲሆን ከምእመናንና ከካህናት ቤት ሊኖር የሚገባ መጸሐፍ ነው። ዲ/ን ሞገስ አብርሃም ግንቦት 2017
57
12
بدون متن...
186
13
بدون متن...
278
14
#በከንቱ_አምተናታል ዮሴፍ በጽኑ መረበሽ የተያዘበት ወቅት ነበር። የእመቤታችን መፀነስ ከሚያወቀው ተፈጥሯዊ አካሔድ ውጪ ስለሆነበት ልቡ ክፉኛ ተሸብሮ ነበር። በእርግጥ ዮሴፍ በእመቤታችን መፀነስ መደናገጡ ብዙም ላያስደንቅ ይችላል። መካን ሆነው ሳለ በልመናቸው ብርታት የወለዱ አሉ÷ እንደነ ሣራ በስተርጅናቸው የፀነሱም አሉ። የእርሷ ግን የተለየ ነው በድንግልና የወለደ ከእርሷ በፊትም ይሁን ከእርሷም በኋላ አልተገኘም። መጻሕፍት እንደሚነግሩን ዮሴፍ ግን ከመደነቅ ይልቅ ከንግድ ሲመለስ ያገኘው ፈላስፋው ዮሐንስ "ይህቺ ሴት ካንተ ነው የፀነሰችው" ብሎ የተናገረው ቃል ከድንጋጤ አድርሶታል። በዚህም ምክንያት ነበር "መኑ ቀረጸ አክናፈ ድንግልናኪ" ብሎ የመፀነሷን ነገር የጠየቃት። ንጽሕት የሆነች እርሷ ግን "መልአኩ አክብሮ ከነገረኝ ውጪ ሌላ ምንም የማውቀው የለም አለችው" የእመቤታችን ትሕትና መግለጽ የሚቻለው አንደበት የለም ቃሏና ምላሿ ሁሉ በትሕትና የታሹ ናቸው። ዮሴፍ አሁንም ቢሆን ከጥርጣሬው መዳን አልቻልም አንድ አንድ ጊዜ ፍርሐት እና የሰዎችን ወቀሳ ማስታወስ ወደ ጥርጣሬ አሮንቃ ውስጥ ይከተናል አረጋዊው ዮሴፍም የሆነው እንዲሁ ነው። ይህንን ጥርጣሬውን ልታስወግድለት የወደደች እመቤታችን ግን አአዕዋፍ እንዲራቡ የሚያደርግ አአዕዋም እንዲያፈሩ የሚያደርግ ማን ምስሎሃል? ብላ ከግሰጸችው በኋላ ከደጃቸው የቆመ ደረቅ ግንድ ነበር እርሱን አለምልማ አሳየችው። መልአኩ ትፀንሺያለሽ ብሎ ባበሠራት ወቅት ይህ እንዴት ይሆንልኛል ብትለው "ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለም" ብሎ የመለሰላትና እርሷ በተግባር አሳየችው። በተረቱበት መርታት ልማድ ነው። እመቤታን ያለውንድ ዘር በድንግልና የመጸነሷ ነገር ምትሐት ሳይሆን የእግዚአብሔር ሥራ መሆኑን ብትገልጥለትም። ለቆጠራ ወቅት ግን ይዟት ይወጣ ዘንድ ፈራ። ከእግዚአብሔር ሥራ ይልቅ ፍርሐታችንን እናምነዋለን በዚህም በተሳሳተ እምነታችን የእግዚአብሔር ዓላማ አደናቃፊዎች ሆነን እንገኛለን። ዮሴፍም ያለ ወንድ ዘር እንድትጸንስ ያደረገውን የእግዚአብሔርን ሐይል ሳያስተውል ይዟት ሲወጣ ግን አይሁዶች ሊፈጥሩት የሚችሉት ትንኮሳ አስፈራው። ይዟት ቢወጣ ሕጋቸውን ቢያስቀራት ደግሞ ያደረገውን ዓውቆ ጥሏት ወጣ እንዳይሉ ወሪያቸውን ፈርቶ ሳለ መልአኩ ከያዘው ፍርሐት አርቆ ይዟት ይወጣ ዘንድ አዘዘው። ዮሴፍ በመልአኩ ትዕዛዝ ይዟት ቢወጣም የዲያቢሎስ የግብር ልጆች የሚሆኑ በትጠጣው ለሞት የሚያደርሳትን ማየ ዘለፋን ትጠጣልን አሉ። የአምላክ እናት እርሷ ግን ማየ ዘለፋን ከጠጣችው በኋላ እነርሱ እንዳሰቡት ሳይሆን ከወትሮው አበራች ጽድልት ሆና ታየች ከፀሐይ ይልቅ አብርታ ተገኘች በጊዜ የተቀሩት አይሁድም ይህን ቢመለከቱ "ይህችን ብላቴና በከንቱ አምተናታል" አሉ። የእመቤታችንን ክብር ከመናገር እርቀው በከንቱ የሚያሙ ሰዎች የበቀሉት ገና በማኅጸን ሳለች ነው። መወለዷን የጠሉ ዳግመኛ የመውለዷን ነገር አለወደድዱምና በጊዜው ነውር እንደተገኘባቸው ሴቶች እርሷን በከንቱ አሟት። እውነት ደቆ ሐስት ረቆ ባየለበት በእኛ ዘመንም ዓይነ ልቦናቸው የታወረባቸው በከንቱ ያማሉ። የእግዚአብሔርን ሳይሆን የግብር አባታቸውን የዲያቢሎስን ድምፅ እየሰሙ በቅዱሳኑ ላይ በከንቱ ይናገራሉ። ከሁሉ ልቆ የታየው ግን የአይሁድ ከንቱ የሆነው ሐሜታቸው ሳይሆን ስለ ክፉ ፈንታ ክፉ ያለመለሰች የእመቤታችን ትሕትና ነበር። ዲ/ን ሞገስ አብርሃም
275
15
#መኑ_መሀረከ(ማን አስተማረኽ) °°ከምኩራብ ሰዎች ይልቅ በክርስቶስ አንደበት ምስክርነትን ያገኙ ሰዎች የነቢያትን መጻሕፍት ያላመሠጠሩ በሥጋ አነዋወር ያሉ ምን አልባት ወደ ገቢረ ኃጢአት ያደሉ ናቸው። መቶ አለቃው ከቤቴ ጣርያ በታች ልትገባ አይገባም ቃልን ብቻ ተናገር ልጄ ይነሳል በማለት ስለ እምነቱ ከክርስቶስ ምስጋናን አግኝቷል። ዘማዊት የነበረችው ሴት በእንባዎቿ እግሮቹን ብታርሰው ስለ ኃጢአቷ እግሩ ላይ ተደፍታ ብታነባ ወንጌል በተነሳበት ሁሉ ስሟ የሚጠራ አደረጋት። °° የቤተ ምኩራብ ሰዎች የነቢያት መጻሕፍትን ጠንቅቀናል የሙሴን ሕግ ይዘናል ቢሉም ቅሉ በኩረ ኃጢአት የሆነው ትዕቢት ይዟቸው ለሙሴ ሕግን የሰጠላቸው አስቀድሞ ለአባቶቻቸው በበረሐ ድንቅን ያደረገላቸውን አምላክ ለመከራ አሳልፈው ሰጡት። ከቤተ ምኩራብ ተቀምጠው ኦሪትን ከወጋቸው ጋር ቀለቅለው ሰዎችን አብዝተው ከሚያስጨንቁ አዋቆች ይልቅ ውጪ ያሉ ምን ያክል እንደተሻሉ ከሚያሳዮን ታሪኮች ደግሞ በቀኝ የተሰቀለው ወንበዴ ጥጦስ ነበር። °°ጥጦስ ሽፍታ ቀማኝ ብዙ ሰዎችን በተግባሩ ያሳዘነ ወንበዴ ነው ከቤተ ምኩራብ ቢፈልጉት አይገኝም የነቢያት መጻሕፍት ባሉበት ዙርያ የለም እርሱ የዕለት ሥራው ውንብድና ነው። ከጥጦስ ምንም ዓይነት የነገረ እግዚአብሔር እውቀት ይገኛል ማለት ዘበት ይመስል ነበር ነገር ግን በመስቀል ላገኝው አምላክ ምሥክርነት ሰጠ። አንደኛውና ዋነኛው ዛሬ ቤተክርስቲያን ቃሉን ቃል አድርጋ በቅዳሴ ሰዓት የምታዜመው ንባብ ይገኝበታል እርሱም "በመንግስትህ በመጣህ ጊዜ አስበኝ" የሚል ነበር። ፈሪሳውያን አይደለም ዳግመኛ በመንግስቱ መጥቶ መፍረዱን ሊያምኑ ይቅርና ከቀደሞውንም ሊያድናቸው መምጣቱም ተሰውሮባቸው ነበር ጥጦስ ግን ከምኩራብ አዋቆች የተሰወረውን ስለምትመጣው መንግስቱ ተናገረ ። °°ኢትዮጵያዊው ሊቅ ቅዱስ ያሬድ በጾመ ድጓ ድርሰቱ ይህንን ወንበዴ «የቀኙ ወንበዴ ሆይ ይህንን ታውቅ ዘንድ ማን አስተማረህ? ማንስ ነገረህ?›› ‹"ፈያታዊ ዘየማን መኑ መሀረከ ወመኑ ነገረከ ፤ ታእምር ዘንተ" ብሎ ያወድሰዋል እውነትም ይህ በረሐ ለበረሐ በሽፍታነት ይኖር የነበረው ቀማኝ ይህን እውቀት ከየትኛው መምህር እግር ስር ቁጭ ብሎ ተማር ያሰኛል። መጻሕፍትም እንደሚነግሩን ጥጦስ ከተመረጡ ሰዎች ቀድሞ ገነት ገባ እርሱ በመንግስቱ ሲመጣ እንዳይዘነጋው ጠየቀ ጌታ ደግሞ ይሰቀል ብለው ከጮሁ ካህናት የላቀ እምነትና ሥራ ቢያገኝበት ዛሬ በገነት ከእኔ ጋር ትሆናለህ አለው። °°የጽሑፌ አጭር ቁም ነገር ይሄ ነው ቅዱስ ያሬድስ ጥጦስን ማን አስተማረህ ከወዴት አመጣህው ያለው ቢደንቀው ነው በክርስቶስ የተወደደለትን ድንቅ እውቀታዊ ምሥክርነት ቢሰማ ነው ሊቁ ቃሉ የአድናቆት ነበር። ይህንን የሊቁን ቃል በዕለተ ዓርብ በቀራንዮ አደባባይ ላይ በተመሠረተችው ዓመናዊቷ ቤተክርስቲያን ውስጥ ኖረው በነፍስ ደዌ(ክኅደት) ለሚሰቃዩ ሰዎች በየመድረኩ ሁሉ በትዕቢት መንፈስ ለሚያስተምሩ አገልጋዮች እና አባቶች ብንጠቀመው ሳይበጅ አልቀረም። ይህንን ቃል ማን አስተማራችሁ? ማንስ ነገራችሁ? የነገረ መለኮትና የዜማ ሊቅ የሆነው ቅዱስ ያሬድ ነውን ወይስ ኢትዮጵያዊ ቄርሎስ ዓመደ ሃይማኖት ቅዱስ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ነውን? ወይ አርዮስን ድል የነሳው ቅዱስ አትናቴዎስ ነውን የእመቤታችን ፍቅር አላደርስ ያላቸው የሶርያው ቅዱስ ኤፍሬም እና የብህንሳው ህርያቆስ ነውን? ከማን ተማራችሁት? ማን ነገራችሁ?...... ዲ/ን ሞገስ አብርሃም 16/7/2017
239
16
https://youtu.be/UonnYNPViWQ?si=0MlvM918MKFOVPl0
230
17
https://youtu.be/f-5MOHOdGJk?si=y852RSk9hOw4_HSo
224
18
ወዮ ለእኔ ጌታ ሆይ በፊትህ የቆምኩኝ ጊዜ ወዮታ አለብኝ.... ወዮ እንባና ጸጸት ለሌለብኝ ለእኔ ለቅሶና ዋይታ ይገባል... በደም የተለወሰ ፊትህ የተቸነከረ እጅህን አይቼ ላላዘንኩ ለእኔ መከራ አለብኝ...መከራህን አስታውሼ ኃጢአቴን ላልተውኩኝ ስቅላትህን አስቤ አንተን ላለመሰልኩኝ ለእኔ ሐዘን ይገባል... በደም የተለወሰ ልብስህን በኃጢአት ድሪቶ ለቀየርኩኝ ለእኔ ዋይታ አለብኝ.. ጌታዬ ክርስትናዬ የልምድና የይምሰል ስግደቴና ጸሎቴ ለደንቡ ብቻ ለሆነብኝ ቁስልህ ያልጠዘጠዘኝ መውደቅ መነሳትህ ላላመመኝ እእኔ ከፊትህ ስቆም ምን ትለኝ ይሆን? ከዝሙት መንደር ከውሸትና ከስርቆት መንደር ከክፉ ሐሳብን ከኃጢአት መንደር ሳልጠፋና አንተን ሳለብስ መንፈሳዊ ሰው ለምመስል ለእኔ ፍርድህ ምን ይሆን? ህመምህን የሚያስብ ልቦና ስጠኝ ሞትህን አስቤ ሰውነቴን የምገዛበትን ጥንካሬ ስጠኝ ከፍቅርህ የተነሳ የምታመም አድርገኝ ቁስልህ ይጠዝጥዘኝ መዋረድህ ያስለቅሰኝ መወጋትህ ይሰማኝ መከራህን ተሸክሜ መገለጫህ ልሁን.... የነፍሴ ተምኔት....
242
19
https://youtu.be/RKMe6mBhxw4?si=oEfp_FDHglWqCgMB
238
20
NZP9yXZ0
1