fa
Feedback
Addis Chamber

Addis Chamber

رفتن به کانال در Telegram

ይህ የአዲስ ቻምበር የዲጂታል ሚዲያ ዋነኛ ዓላማ በንግድና ኢንቨስትመንት ዙሪያ ለንግዱ ህብረተሰብ መረጃ ማቅረብ ነው።Addis Chamber Telegram channel is a media platform to provide news and analysis that affect businesses. Tel: +251 115 573544 Email: media@addischamber.com Web: addischambernews.com

نمایش بیشتر
830
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
+97 روز
+2230 روز

در حال بارگیری داده...

ابر برچسب‌ها
هیچ داده‌ای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
اشارات ورودی و خروجی
---
---
---
---
---
---
جذب مشترکین
ژوئیه '26
ژوئیه '26
+27
در 0 کانال‌ها
ژوئن '26
+31
در 1 کانال‌ها
Get PRO
مه '26
+42
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '26
+24
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '26
+63
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '26
+22
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '26
+25
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '25
+34
در 0 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '25
+33
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '25
+39
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '25
+20
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '25
+21
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '25
+28
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '25
+33
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '25
+20
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '25
+27
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '25
+39
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '25
+23
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '25
+58
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '24
+37
در 0 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '24
+27
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '24
+36
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '24
+354
در 0 کانال‌ها
تاریخ
رشد مشترکین
اشارات
کانال‌ها
20 ژوئیه+3
19 ژوئیه0
18 ژوئیه+2
17 ژوئیه+2
16 ژوئیه+1
15 ژوئیه+3
14 ژوئیه0
13 ژوئیه+2
12 ژوئیه0
11 ژوئیه0
10 ژوئیه0
09 ژوئیه+1
08 ژوئیه+3
07 ژوئیه+2
06 ژوئیه+2
05 ژوئیه0
04 ژوئیه0
03 ژوئیه+2
02 ژوئیه+2
01 ژوئیه+2
پست‌های کانال
Repost from Capitalethiopia
የኢትዮጵያ እና የተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ የንግድ ትስስርን የሚያጠናክር የቢዝነስ ፎረም በዱባይ ሊካሄድ ነው የአዲስ አበባ ንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት (አዲስ ቻምበር)፣ ከዱባይ ንግድ ምክር
+1
የኢትዮጵያ እና የተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ የንግድ ትስስርን የሚያጠናክር የቢዝነስ ፎረም በዱባይ ሊካሄድ ነው የአዲስ አበባ ንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት (አዲስ ቻምበር)፣ ከዱባይ ንግድ ምክር ቤት እና ከተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ጋር በመተባበር የቢዝነስ ፎረም በዱባይ ሊያካሂድ መሆኑ ተነገረ። እኤአ መስከረም 2 ቀን 2026 የሚካሄደው ይህ የንግድ ለንግድ ውይይት፣ ከ40 በላይ የሚሆኑ የአዲስ ቻምበር አባል ኩባንያዎችና ባለሀብቶች የሚሳተፉበት ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል። የፎረሙ ዋና ዓላማ የሁለቱን ሀገራት የንግድ፣ የኢንቨስትመንት እና የገበያ ትስስር በማጠናከር፣ የኢትዮጵያ አምራቾች፣ ላኪዎችና አገልግሎት ሰጪዎች ከአቻ የዱባይ ኩባንያዎች ጋር ፊት ለፊት የሚገናኙበትን መድረክ መፍጠር እንደሆነ ተጠቁሟል። አዲስ ቻምበር ለካፒታል በላከዉ መግለጫ እንዳስታወቀው፣ ይህ መድረክ አባል ኩባንያዎች አለም አቀፍ ተወዳዳሪነታቸውን እንዲያሳድጉ እና የውጭ ኩባንያዎችን ወደ ኢትዮጵያ ገበያ ለመሳብ ትልቅ ሚና ይኖረዋል። ኢትዮጵያ እና የተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ የንግድ ልውውጥ በቅርብ ጊዜ ከ6 ቢሊዮን ዶላር በላይ መድረሱ የተገለፀ ሲሆን ይህም የሁለቱ ሀገራት የኢኮኖሚ ግንኙነት እያደገ መሆኑን የሚያመለክት ነዉ ተብሏል።

2
The Ethio-Dubai Business Forum is just around the corner, with about 40 local exhibitors invited to sign up.   Addis Chamber, July 20, 2026: Investors and company leaders from Ethiopia and Dubai are expected to discuss business opportunities, explore new markets, and contemplate partnerships and networking, scheduled for September. The forum will feature a business conference with participation from over 40 local companies across various sectors, such as manufacturing, agriculture, export, and import. This event follows the previous Ethio-Dubai Business Conference held in May 2026 at Sheraton Addis, which brought together more than 300 members of the Addis Chamber and over 20 investors from Dubai. The forum is an extension of a Memorandum of Understanding (MoU) signed between the two chambers, which aim to promote business and investment.   Addis Business Serving Businesses Since 1947!    https://forms.gle/gCGAenqEzCx4nqxEA
107
3
+6
بدون متن...
122
4
ከ40 በላይ የንግድ ኩባንያዎች የሚሳተፉበት የኢትዮ-ዱባይ የንግድ ፎረም በዱባይ ሊካሄድ ነው። የአዲስ አበባ ንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት (አዲስ ቻምበር) ከዱባይ ንግድ ምክር ቤትና ከኢትዮጵያ ኤምባሲ በተባበሩት አረብ ኤሚሬት ጋር በመተባበር በተለያዩ የቢዝነስ ዘርፎች የተሰማሩ ከ40 በላይ የአዲስ ቻምበር አባል ኩባንያዎችና ባለሐብቶች የሚሳተፉበት ታላቅ የቢዝነስ ውይይትና ኮንፈረንስ በቀጣዩ መስከረም ወር መግቢያ በዱባይ ይካሄዳል ። አንጋፋው አዲስ ቻምበር እ.ኤ.አ. መስከረም 2 ቀን 2026 በዱባይ በሚካሄደው የቢዝነስ ለቢዝነስ ውይይትና ፎረም ላይ፣ የሐገራችን አምራቾች፣ አገልግሎት ሠጪዎች ላኪዎችና አስመጪዎች እንዲሳተፉ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በጋራ እየሠራ ነው። የዱባይ ባለሀብቶች እና ኩባንያዎች ከኢትዮጵያዊያን ነጋዴዎች ጋር ፊት ለፊት በመገናኘት የንግድ፣የኢንቨስትመንትና የገበያ ትስስር ይፈጥራሉ ተብሎ እየተጠበቀ ነው። አዲስ ቻምበርም በአምራች ኢንዱስትሪ ፣ በግብርና ፣ በላኪነት እና አስመጪነት ዘርፍ የተሠማሩ ኩባንያዎች በፍጥነት በአዲስ ቻምበር እንዲመዘገቡና ይህን የቢዝነስ ትስስር መድረክ እንዲጠቀሙበት ጥሪውን አቅርቧል ። አዲስ ቻምበርና የዱባይ ቻምበር ንግድና ኢንቨስትመንት በማስፋፋት ረገድ በቅርቡ የጋራ መግባቢያ ሠነድ መፈራረማቸው ይታወሳል። የዚሁ አንድ አካል የሆነውና በባለፈው ግንቦት ወር በአዲስ አበባ ሸራተን ሆቴል የተካሄደው የኢትዮ ዱባይ የቢዝነስ ኮንፈረንስ አንዱ ማሳያ ሲሆን ከ20 በላይ የዱባይ ባለሐብቶች በተገኙበት ከ300 በላይ የአዲስ ቻምበር አባል ኩባንያዎች የንግድ ለንግድ ውይይት መደረጉ ይታወቃል ። አዲስ አበባ ንግድ ምክር ቤት (አዲስ ቻምበር) ባለው አለም አቀፋዊ ስምና ከሌሎች ሐገራት ከተሞች ንግድ ምክርቤቶች ጋር ባለው የጋራ መግባቢያ ስምምነት መሠረት ለንግዱ ህብረተሰብ የገበያና የንግድ ትስስር በመፍጠር ኩባንያዎች ተወዳዳሪነታቸው እንዲጎለብት በመስራት ላይ ይገኛል። የውጪ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ እና በአዲስ አበባ በቢዝነስና በኢንቨስትመንት ዘርፍ በይበልጥ እንዲሳቡና እንዲሠማሩ ጥረት እያደረገ ነዉ። በቅርቡ ከሚካሄደው የኢትዮ ዱባይ የቢዝነስ ፎረም በተጨማሪ በሌሎች ሐገራት ከተሞች የሚከናወኑ በርካታ የንግድ እና የገበያ ትስስር መድረኮችን ለንግዱ ማህበረሰብ እየተመቻቸ መሆኑም ለማወቅ ተችሏል ። ኢትዮጵያ እና የተባበሩት አረብ ኢምሬትስ የቅርብ ጊዜ (የ2025) የንግድ ልውውጥ መጠናቸው ከ 6 ቢሊዮን ዶላር በላይ መሆኑን መረጃዎች ይጠቁማሉ ። ባለፉት 79 ዓመታት የንግዱን ማህበረሰብ እያገለገለ የሚገኘው አንጋፋው አዲስ ቻምበር የሁለቱ ሀገራት የንግድና ኢንቨስትመንት ትስስር እንዲያድግ ካደረጉ ተቋማት መካከል አንዱ መሆኑ ተመላክቷል። https://forms.gle/gCGAenqEzCx4nqxEA #አዲስ ቻምበር፣ የንግዱ ማህበረሰብ ድምፅ እና አገልጋይ
155
5
+6
بدون متن...
146
6
የንግዱ ህብረተሰብ ችግኝ በመትከል የአረንጓዴ አሻራውን አሳረፈ። (አዲስ ቻምበር፤ ሀምሌ 11 ቀን 2018 አ.ም) በኢትዮጵያ የንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት አስተባባሪነት የንግዱ ማህበረሰብ ተወካዮች  የተሳተፉበት የ2018 በጀት ዓመት “ተስፋን እንትከል” በሚል መሪ ቃል የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በአዲስ አበባ ቦሌ ክ/ከተማ ሳሊተ ምህረት አከባቢ ተከናውኗል።   በዚህ መርኀ ግብር የአዲስ ቻምበር አመራሮች፤ የቦርድ አባላት፤ የኢትዮጵያ ንግድና ቀጠናዊ ትስስር ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሰራተኞች እንዲሁም የንግድ ምክር ቤቶች ተካፋይ ሆነዋል። የችግኝ ተከላ ፕሮግራሙን ያስጀመሩት የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ  (ዶ/ር) የንግዱ ማህበረሰብ አረንጓዴ አሻራን በማሳረፍ ለትዉልድ የምትምች ሀገር እንዲፈጥር ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ኢትዮጵያ በየዓመቱ በምታካሂደው የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር እስካሁን ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል ትልቅ አገራዊ ሥራ መሰራቱን ገልጸው ይህ ስኬት ኢትዮጵያ የCOP32 አዘጋጅ ዝግጅት ሆና እንድትመረጥ እንዲሁም በተፈጥሮ እንክብካቤ ረገድ በዓለም ቀዳሚ ከሚባሉት ተርታ እንድትሰለፍ ማስቻሉን አብራርተዋል።   አዲስ ቻምበር ማህበራዊ ኃላፊነትን መወጣትን ጨምሮ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐግብር ከተጀመረ አንስቶ የተስተካከለ እና ዘላቂነት ያለው ሥነ ምኅዳር ለመፍጠር ፣ የደን ሽፋንን ለማሳደግ፣ የግብርና ምርታማነትን ለመጨመር፣ የአየር ንብረት ለውጥ ጫናን ለመቋቋም በሚደረገው ጥረት ላይ ንቁ ተሳትፎ በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡   አዲስ ቻምበር የግሉ ዘርፍ አገልጋይ!
148
7
+1
بدون متن...
163
8
+9
بدون متن...
175
9
የአዲስ ቻምበር 9ኛው ዙር የስራ አስፈጻሚዎች መድረክ በሀገራችን በተለያዩ ዘርፎች ከፍተኛ ልምድ ያካበቱትን ወ/ሮ መአዛ አሸናፊን እንግዳ አድርጎ አቀረበ፡፡  (ሐምሌ 10 ቀን፣ 2018 አ.ም) በአዲስ ቻምበርና በኤስኤኬ ( S.A.K) የስልጠና እና አማካሪ ድርጅት በትብብር የሚሰናዳው የስራ አስፈጻሚዎች መድረክ በአዲስ አበባ ኢሊሊ ሆቴል ተካሄደ ። በሁለቱ ተቋማት የጋራ ትብብር የሚዘጋጀው የስራ አስፈጻሚዎች መድረክ በዚህኛው ዙር  በኢትዮጵያ የህግ፣ የሴቶች መብት፤ የፋይናንስ ዘርፍ ውስጥ ከፍተኛ ልምድና ተሞክሮ ያካበቱትና የቀድሞው የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንትና የቀድሞው የእናት ባንክ መስራችና የቦርድ ሠብሳቢ፤ የኢትዮጵያ የህግ ባለሙያ ሴቶች ማህበር መስራቾች ከነበሩት አንዷ የሆኑነት ወ/ሮ መአዛ አሸናፊን በእንግድነት አቅርቧል፡፡   ወ/ሮ መአዛ የኢትዮጵያ ሴት የህግ ባለሙያ ማህበርን በመስራችነትና በዋና ስራ አስፈፃሚነት በማገልገል የሴቶች እኩልነት እንዲረጋገጥ ፤ አካታችነት እንዲኖር ህጎች እንዲሻሻሉ፤ የሴቶች የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ በርከታ ስራዎችን ሰርተዋል።  Leadership and Service Excellence በሚል መሪ ቃል የተካሄደው የስራ አስፈጻሚዎች መድረክ ላይ የካበተ ልምዳቸውን ያካፈሉት ወ/ሮ መአዛ አሸናፊ አንድ መሪ ስኬታማ ሊሆን የሚችለው ሰው ተኮር ሲሆን እና ውጤታማ ተግባቦት ስትራቴጂ ሲቀርፅና ሲተገብር እንደሆነ ገልፀዋል ።   ከዚህም ባለፈ አንድ መሪ ተቋምን ዘላቂ ለማድረግ ከተፈለገ ከባለ ድርሻ አካላት በተለይም ከደንበኛ  ጋር ያለውን ግንኙነት ማጠናከር ሲቻል ነው በሚል ማብራሪያ ሰጥተዋል። ትልቁ የአመራር ስኬት ቁልፍ መሳሪያ እምነትን ማዳበር በተለይም በፍትህ ስርአት አመራር ውስጥ በአገልግሎት ሰጪውና በአገልግሎት ተቀባይ መካከል መተማመን መኖር እንዳለበት ካካበቱት ልምድ በመነሳት ተናግረዋል፡፡   እኚህ እንግዳ ካካፈሉዋቸው ነጥቦች መካከል አመራር ሰጪነት ውጤታማ ሊሆን የሚችለው በቅንጅትና በቡድን ስሜት ሲሰራ መሆኑን ፤ የአመራር ጥበብ ቀደም ካሉት በመሪነት ያካበተ ልምድ ካላቸው ዜጎች ትምህርትንና እውቀትን መቅሰም እንደሚያስፈልግ፤ ውሳኔ ሰጪነት ከግላዊነት ይልቅ በምክክርና በአካታችነት ላይ የተመሰረተ መሆን እንዳለበት አክለው ተናግረዋል፡፡   በተለይም ተቋማትን በዘላቂነት ለመገንባት ከተፈለገ በተቋማት መካከል አብሮ የመስራት ባህል መዳበር እንዳለበት፤ የተቋማት አቅም ግንባታ ስልጠናዎች በዘላቂነት መሰራት እንዳለበት፤ በአጠቃላይ ዜጎች ተሻጋሪ ሀገር መፍጠር እንዲችሉ ራሳቸውን ማብቃት እንዳለባቸው ከራሳቸው ልምድና ተሞክሮ በመነሳት ተነጋረዋል፡፡   አንድ ማህበረሰብ ማደግ ካለበት ሴቶችን በሁሉም መስክ እኩል እድል መስጠትና ማካተት ጠቃሚ መሆኑን የአለም ተሞክሮ ያሳያል ያሉት በኢትዮጵያ የሴቶችን የኢኮኖሚ፤ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ተሳትፎ ለማሳደግ በርከታ ጥረቶች መደረጋቸውን ለውጦች መታየታቸውን ነገር ግን አሁንም ቢሆን ብዙ ያላለቁ የቤት ስራዎች መኖራቸውን የዚህ መድረክ እንግዳ ተናግረዋል፡፡     በኤስኤኬ ኩባንያ ማኔጂንግ ዳይሬክተር በዶ/ር አደራ አብደላ አወያይነት የተካሄደው 9ኛው ዙር የስራ አስፈጻሚዎች መድረክ በርካታ የኩባንያ አመራሮች የተሳተፉበት ሲሆን እንዲህ አይነት መድረኮች ሀገር በቀል የአመራር እውቀቶችን ተተኪ መሪዎች ልምድና እውቀትን የሚቀስሙበት እንዲሁም ዘላቂ የሆኑ ተቋማትን ለመገንባት የሚያስችል ጠቃሚ መድረክ ነው ብለዋል፡፡   የአዲስ ቻምበር የስራ አስፈጻሚዎች መድረክ የኩባንያ አመራሮች፤ ምሁራኖች፤ የተቃማት ተወካዮችና ኃላፊዎችና የአዲስ ቻምበር የቦርድ አባላትና ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል። የአዲስ ቻምበር የስራ አስፈጻሚዎች መድረክ ከዚህ ቀደም ስመጥር የቢዝነስና የኩባንያ አመራሮችን በእንግድነት ያቀረበ ሲሆን ከነዚህም መካከል አቶ ክቡር ገና፤ አምባሳደር ሙሉ ሰለሞን፤ ዶ/ር አረጋ ይርዳው፤ ዶ/ር ያሬድ ሞላ፤ አቶ ብስራት ንጋቱ፤ አቶ ጁነዲን ባሻ ፤ አቶ በቃሉ ዘለቀ፤ ዶ/ር አንዱአለም አድማሴን እንዲሁም በዚህኛው ዙር ደግሞ ከሶስት አስርት አመታት በላይ ከባለሙያነት እስከ አመራርነት ድረስ በማገልገል ለዜጎች እና ለተቋማት እድገት የበኩላቸውን አስተዋጾ ያበረከቱትን ወ/ሮ መአዛ አሸናፊን እንግዳ አድርጎ አቅርቧል፡፡    #አዲስ ቻምበር፡ ትክክለኛ የግሉ ዘርፍ አገልጋይ
133
10
+1
بدون متن...
130
11
አዲስ ቻምበር የቦሌ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት በወረዳ 11 የንግድ ምክክር መድረክ አካሄደ ​አዲስ ቻምበር ሐምሌ 10 ቀን 2018 ዓ.ም፦ የአዲስ አበባ ንግድና የዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት (አዲስ ቻምበር) የቦሌ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት፣ በየወረዳው ከሚገኙ ነጋዴዎች ጋር የጀመረውን ተከታታይ የውይይት መድረክ በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 11 አካሂዷል። የውይይት ትኩረቱን በወረዳው በሚገኙ የንግድ ዘርፎች የአገልግሎት አሰጣጥ ላይ በማድረግ ምቹ የንግድ ከባቢ መፍጠር በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ ሰፊ ምክክር አድርጓል። በዚህ መድረክ ላይ የአዲስ ቻምበር የቦሌ ክፍለ ከተማና የወረዳ 11 የቻምበሩ አመራሮች፣ የነጋዴዎች ተወካዮች እንዲሁም ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከታቸው የወረዳው የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች በጋራ ተገኝተዋል።   ​በዕለቱ በተካሄደው ግልጽ ውይይት ላይ በዋናነት በየዓመቱ በሚከናወኑ የግብር አከፋፈልና የግምት ሁኔታዎች እና ተያያዥ አገልግሎቶች ላይ የሚስተዋሉ ቢሮክራሲያዊ መዘግየቶችን በዘላቂነት ለማስወገድ እንዲሁም በሥርዓት ግብር ከፍለው የሚሠሩ ነጋዴዎችን ተወዳዳሪነት የሚጎዳውን ሕገ-ወጥ የጎዳና ላይና ያልተመዘገቡ የንግድ እንቅስቃሴዎችን በቅንጅት መቆጣጠር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ሰፊ ትኩረት ተሰጥቷል። ከዚህም በተጨማሪ በወረዳው ውስጥ ለሚንቀሳቀሱ ነጋዴዎች የሥራ ቦታ እጥረትን ማቃለልና ተያያዥ የመሠረተ-ልማት እክሎችን በጋራ መፍታት ስለሚቻልበት አቅጣጫ በጥልቀት ተመክሮበታል።   ​የወረዳ 11 የገቢዎች ጽሕፈት ቤት ተወካይ በበኩላቸው ጽሕፈት ቤታቸው የአገልግሎት አሰጣጥ ሂደቱን ይበልጥ በማዘመን ለነጋዴው ቀልጣፋና ከእንግልት የጸዳ አገልግሎት ለመስጠት ቁርጠኛ መሆኑን ገልጸው፣ ከንግዱ ማኅበረሰብ ጋር የሚደረጉ እንዲህ ያሉ ቀጥተኛ የግብረ-መልስ መድረኮች አሠራርን ለማስተካከልና መልካም አስተዳደርን ለማስፈን ትልቅ ሚና እንዳላቸው አረጋግጠዋል። የቻምበሩ አመራሮችም ነጋዴዎች በምክር ቤቱ ጥላ ሥር በንቃት በመሳተፍ አቅማቸውን እንዲገነቡና መብቶቻቸውን በተደራጀ መንገድ እንዲያስከብሩ ጥሪ ያቀረቡ ሲሆን፣ ውይይቱ በነጋዴው፣ በምክር ቤቱና በወረዳው አስተዳደር መካከል ጠንካራ የሥራ አጋርነት በመፍጠር እንዲሁም ለቀጣይ የጋራ ሥራዎች አቅጣጫ በማስቀመጥ ፍጻሜውን አግኝቷል።   ​አዲስ ቻምበር የግሉ ዘርፍ አገልጋይ!
140
12
+5
بدون متن...
151
13
The 9th round of Forum for Executive Leadership (FEEL) one of the initiatives of Addis Chamber is happening at Elilly International Hotel, hosting Meaza Ashenafi, Ethiopia's former first female chief justice, co founder of the Ethiopian women lawyers association and Enat Bank, the first women's bank in Ethiopia. Previously the FEEL hosted giant business and industry leaders including Dr. Arega Yirdaw, the former CEO of MIDROC Ethiopia, Mr. Kibour Ghena, the former president of Addis Chamber, Mr. Bekalu Zeleke, President of Abissinia Bank and Ambassador Mulu Solomon, the former president of Ethiopia Chamber of Commerce and Addis Chamber. The FEEL leadership experience forum is jointly run by Addis Chamber and S. A. K, the renowned business consulting firm in Ethiopia. Business leaders from different business sectors are attending the forum. Addis Chamber, serving businesses since 1947
150
14
+6
بدون متن...
173
15
የአዲስ ቻምበር የመጀመርያው ዙር የስልጠና መርሃ ግብር በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከተማ ተጠናቀቀ   አዲስ ቻምበር ሀምሌ 9 2018 አ.ም፡- ከሰኔ 4 2018 አ.ም ጀምሮ በ5 ዙር ለጀማሪና መካከለኛ የቢዝነስ አንቀሳቃሾች ሲሰጥ የነበረው ስልጠና በአጠቃላይ 550 አነስተኛና መካከለኛ የቢዝነስ አንቀሳቃሾችን ተጠቃሚ አድርጓል፡፡ ስልጠናው በቢዝነስ አመራር፤ በቢዝነስ ስነምግባርና አስተዳደር እንዲሁም በስራ ፈጠራ ላይ ትኩረቱን ያደረገ ሲሆን በዘርፉ የረጅም አመት ልምድ ያካበቱ አሰልጣኞች ተሳትፈውበታል፡፡   አዲስ ቻምበር ከልማት አጋር አካላት ጋር በመተባበር የንግዱን ማህበረሰብ የንግድ አመራር አቅምና ተወዳዳሪነትን ለማሳደግ የሚያስችል ስልጠናዎችን ከባለፉት ጥቂት ሳምንታት ጀምሮ በአዲስ አበባ በሁሉም ክፍለ ከተሞች ሲሰጥ ቆይቷል፡፡ ስልጠናው ከዚህ ቀደም በሁሉም ክፍለ ከተሞች የሚገኙ የአዲስ ቻምበር አባል ነጋዴዎችን ተጠቃሚ ያደረገ ሲሆን ለተከታታይ ሳምንታት ተሰጥቷል፡፡ በዛሬው እለት ደግሞ 5ተኛው ዙር የማጠቃለያ ስልጠና በአቃቂ/ቃሊቲ እና በን/ላፍቶ ለሚገኙ የነጋዴ አመራሮች ተሰጥቷል፡፡      ምክር ቤቱ ወቅቱ የሚጠይቀውን የንግድ ሥራ ክህሎት እና እውቀት እንዲያገኙ በማደርግ  ተወዳዳሪ የንግድ ሕ/ሰብ እንዲፈጠር በመስራት ላይ ይገኛል ብለዋል የአዲስ ቻምበር ዋና ጸሐፊ አቶ ዘካርያስ አሰፋ የእለቱን ስልጠና ሲያስጀምሩ፡፡        በተለይ የአነስተኛና መካከለኛ  ኤንተርፕራይዞች ባለቤቶች ዘመኑ የሚጠይቀውን የንግድ ጥበብ በመያዝ  ተወዳዳሪነታቸውን  ለማሳደግ  ጥረት መድረግ እንዳለባቸው አክለው ተናግረዋል፡፡     ስልጠናው የተዘጋጀው በአዲስ ችምበርና በአለማቀፉ የግል ኤንተርፕራይዝ ትብብር ሲሆን ምክር ቤቱ ከአጋር አካላት ጋር በመሆን የሚያደርገው የአቅም ግንባታ ስልጠና ቀጣይነት እንዳለው ለማወቅ ተችሏል፡፡   አዲስ ቻምበር የንግዱ ማህበረሰብ አገልጋይ!
161
16
بدون متن...
166
17
የንግድ እድል ለአዲስ ቻምበር አባላትና ለንግዱ ህብረተሰብ አዲስ ቻምበር ከዱባይ ቻምበርና በተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ጋር በመተባበር ታላቅ የንግድ ለንግድ ውይይትና የኢትዮ ዱባይ የቢዝነስ ፎረም እኤአ መስከረም 2:2026 በዱባይ ከተማ አዘጋጅቷል። በመሆኑም በማኑፋክቸሪንግ ፣በግብርና ፣በላኪነት እና አስመጪነት የተሠማራችሁ የንግድ ተቋማት ከታች በተቀመጠው ሊንክ እንድትመዘገቡና እንድትሳተፉ አዲስ ቻምበር ይጋብዛል። ለተጨማሪ ማብራሪያ 0911212179 ይደውሉ። https://forms.gle/Q3ZRuHM74fTZcWsv7
164
18
بدون متن...
158
19
+3
بدون متن...
173
20
በቦሌ ክፍለ ከተማ የንግድ ማህበረሰቡን ችግሮች ለመፍታትና ትስስርን ለማጠናከር ያለመ የምክክር መድረክ ተካሄደ አዲስ ቻምበር ሀምሌ 8 ቀን 2018 አ.ም :- ​አዲስ ቻምበር — የአዲስ አበባ ንግድና የዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት (አዲስ ቻምበር) የቦሌ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት በየደረጃው ከሚገኙ የንግድ ማህበረሰብ አባላት ጋር የሚያደርገውን ተከታታይ የምክክርና የንቅናቄ መድረክ በይፋ መጀመሩን አስታወቀ።   የንግድ ዘርፉን ይበልጥ ለማነቃቃት፣ የነጋዴውን ድምፅ በቅርበት ለመስማትና ለአሠራር ማነቆዎች እልባት ለመስጠት የታለመው ይህ መድረክ የመጀመሪያ ምዕራፉን በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 በይፋ አከናውኗል።   ​በውይይት መድረኩ ላይ የአዲስ ቻምበር ባለሙያዎች፣ የቦሌ ክፍለ ከተማና የወረዳው የቻምበር አመራሮች፣ የንግዱ ማህበረሰብ አባላት እንዲሁም ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከታቸው የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች በጋራ ተሳትፈዋል። ​የዝግጅቱ አስተባባሪዎች እንደገለጹት፣ መድረኩ በዋናነት በግብር አከፋፈል ሂደት ዙሪያ የሚስተዋሉ የአሠራር እክሎችን በጋራ ለመፍታትና ግልጽነትን ለመፍጠር ያለመ ነው።   ከዚህም ባሻገር አዳዲስ አባላትን ወደ ምክር ቤቱ በማስገባት የተደራጀ የጋራ አቅም መገንባትና ከወረዳ እስከ ክፍለ ከተማ የሚዘልቅ ዘላቂና ጠንካራ የንግድ ትስስር መፍጠር ዋነኛ የውይይቱ ትኩረት ነው። በመድረኩ ላይ ከተሳታፊዎች በግብር አወሳሰን፣ በአሠራር መዘግየቶችና በተለያዩ የንግድ ተግዳሮቶች ዙሪያ በርካታ ጥያቄዎችና ገንቢ አስተያየቶች የተነሱ ሲሆን፣ በቦታው በተገኙት የቻምበር ባለሙያዎች፣ የክፍለ ከተማና የወረዳው አመራሮች እንዲሁም በሚመለከታቸው የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች አማካኝነት ዝርዝርና ሙያዊ ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል።   የወረዳ 5 ንግድ ጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ ሥርዓቱ ደሣለኝ በውይይቱ መክፈቻ ላይ  የንግዱ ሕ/ሰብ በንግድ ምክር ቤቶች ጥላ ስር ተደራጅቶ መብትና ጥቅሙን  እንዲያረጋገጥ መንግሥት አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልጸው ጽ/ቤታቸው በወረዳው የሚገኙ ነጋዴዎች ተወዳዳሪ እንዲሆኑ  ከሁሉም ባለድርሻዎች ጋር  ተባብሮ ለመሥራት ዘግጁ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ ​ይህ የምክክር መድረክ በነጋዴው፣ በምክር ቤቱና በወረዳው አመራሮች መካከል የጋራ መግባባትን ከመፍጠሩም በላይ ለቀጣይ የተቀናጁ የጋራ ሥራዎች ትልቅ መነሳሳትንና አዲስ የአጋርነት ምዕራፍን የከፈተ ሆኖ መጠናቀቁ ተገልጿል። አዲስ ቻምበር የግሉ ዘርፍ አገልጋይ!
155