Shekib Abdullahi Secondary School
رفتن به کانال در Telegram
772
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
-1230 روز
آرشیو پست ها
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
" ተማሪዎች ምደባቸውን በድረ-ገፅ፦ https://student.ethernet.edu.et እና
በቴሌግራም ቦት፦ @moestudentbot መመልከት ይችላሉ " - ትምህርት ሚኒስቴር
የ2018 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ምደባ ተለቋል፡፡
በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ ብሔራዊ ፈተና ወስደው ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የ Remedial ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችል ማለፊያ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች የተቋም ምደባቸው ዛሬ ይፋ ተደርጓል።
ከታች በተዘረዘሩት አማራጮች ተማሪዎች ምደባቸውን ማየት የሚችሉ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል፡፡
በድረ-ገፅ፦ https://student.ethernet.edu.et
በቴሌግራም ቦት፦ @moestudentbot
Via @tikvahuniversity
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#Update
የ2018 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ይዘቶች ይፋ ሆኑ፡፡
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ፤ ተማሪዎች፣ የተማሪ ቤተሰቦች፣ መምህራንና የትምህርት አመራር ለፈተና ዝግጅት በሚያደርጉበት ወቅት ፈተና የሚሸፍናቸው የይዘት አካባቢዎች ይፋ አድርጓል።
የ2018 ትምህርት ዘመን 12ኛ ከፍል ፈተና ዝግጅትና አስተዳደር የሚከተሉትን ያካትታል፡፡
1. የትምህርት ዓይነቶችን በተመለከተ
ለተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች ፦
- እንግሊዘኛ፣
- ሒሳብ፣
- እስኮላስቲክ አፕቲትዩድ፣
- ኬሚስትሪ፣
- ፊዝክስና ባዮሎጂ
ለማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች ፦
- እንግሊዘኛ፣
- ሒሳብ፣
- እስኮላስቲክ አፕቲትዩድ፣
- ታሪክ፣
- ጂኦግራፊና ኢኮኖሚክስ ናቸው።
2. ፈተናው ከ9ኛ እስከ 12ኛ ከፍል ደረጃዎችን እና በተማሪው መጽሐፍ ላይ ያሉትን ሁሉንም ምዕራፎች ይሸፍናል፡፡
3. ከ10ኛ – 12ኛ ክፍል ሁሉም የትምህርት ዓይነት ፈተና በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት መሠረት እየተዘጋጀ ያለ ሲሆን የ9ኛ ክፍል ደግሞ የሁሉም የትምህርት ዓይነቶች ፈተናዎች ከቀድሞውና ከአዲሱ ሥርዓተ ትምህርቶች የጋራ ይዘቶችን ብቻ አካቶ እየተዘጋጀ ይገኛል፡፡
4. ፈተናው ማንኛውም ተፈታኝ ተማሪ ከተማረው ሥርዓተ ትምህርትና ከተማሪው መጽሐፍ ላይ ብቻ ተመስርቶ እየተዘጋጀ ይገኛል፡፡
5. የፈተናው አስተዳደር በበይነ መረብና በወረቀት ጎን ለጎን የሚሰጥ ሲሆን አብዛኛው ተፈታኝ በበይነ መረብ እንዲፈተን እየተሠራ ያለ በመሆኑ ተፈታኞች እራሳቸውን በበይነ መረብ ለመፈተን ሊያዘጋጁ ይገባል፡፡
#EAES
@tikvahethiopia
የሽኪብ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት በዛሬው እለት በቀን 5/2/2018 ለ12 ክፍል ተማሪዎች የማጠናከሪያ ትምህርት በዚህ መልኩ መስጠት መጀመሩ መልካም ጅምር መሆኑንና የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል የትምህርት አመራሩም : መምህራን :ወላጆች እጅ ለእጅ በመያያዝ የታቀደውን ግብ ለማስካት ወደ ስራ መግባታቸው የሚበረታታ በመሆኑ በትምህርት ቤቱ ስም በርቱ ተበራቱ እንላሉን።
በዛሬው እለት በቀን 3/2/2018 በሸኪብ 2 ደረጃ ት/ቤት የስንደቃላማ ቀን በዝህ መልኩ በደማቅ ተከብሯል።
የሸኪብ 2ኛ ደረጃ ት/ ቤት በዛሬው እለት በቀን 29/1/2017 አዲሱ አመራር ከተማሪ ወላጆች ጋር ትውውቅ በማድረግና ከወላጅ ጋር የውል ስምምነት መፈጠሩና የተማሪዎችን መብትና ግዴታን በማሳወቅ እንዲሁም ከወላጅ ምን ይጠበቃል በሚል ርእስ በግልጽ በመወያየት እንዲሁም በቀጣይ ለተማሪዎች የማጠናከሪያ ትምህርት ለመስጠት የወላጆች ድርሻ የጓላ መሆኑን ስፊ ውይይት በማድረግ የተጠናቀቀ ሲሆን ወላጆችም ለትምህርት ቤቱ በጉልበትም ሆነ በገንዘብ ለመረዳት ቃል በመግባት ውይይቱ አጠናቀዋል።
የሽኪብ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት በዛሬው እለት በቀን 26/1/2017 ከተማሪዎች ጋር በመማር ማስተማር እንዲሁም በተማሪዎች መብትና ግዴታ ዙሪያ ስፊ ውይይት በማድርግ የቀጣይ የስራ አቅጣጫ በትምህርት ቤቱ ርእስ መምህር በመስጠት ውይይቱን በዚህ መልኩ አጠናቀዋል።
+1
ነፃ የትምህርት ዕድል!
በሐረር ከተማ የሚገኘው የሰዎች ለሰዎች ድርጅት አግሮ ቴክኒክና ቴክኖሎጁ ኮሌጅ ከፍተኛ ትምህርት ተቋም መግቢያ ውጤት ያመጡ ተማሪዎችን አወዳድሮ በነፃ ማስተማር ይፈልጋል።
በመሆኑም ይህን እድል ለት/ቤታችሁ ተማሪዎች በማሳወቅ የዕድሉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ እንድታደርጉ እንጠይቃለን።
መልካም ዕድል
የሽኪብ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት በዛሬው እለት በቀን 16/1/2018 ከመምህራን ጋር ስፊ ውይይት መደረጉንና በ2018 በየትምህርት አይነቱ የተጣለውን ግብ እንዱሳካ ሁሉም የድርሻቸውን እንደ ሚወጡ ቃል መግባታቸውን እንዲሁም በግዜ የለንም እቅዳቸውን መተግበር እንዳለባቸውና ለተማሪዎች ውጤት መሻሻል የተማሪዎች (time on task) ከወዴሁ በጥብቅ ዲስፕሊን እንዲመራ መግባባት መፈጠሩን የተመዘገበው ውጤት የሚያኩራራ ሳይሆን በቀጣይ የበለጠ እንድንስራ አነሳስቶናል በማለት ውይይታቸውን አጠናቀዋል።
