cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

My youth age for christ GOSPEL MINISTRY! ወጣትነቴን ለክርስቶስ!!🇪🇹🇪🇹

ወጣትነቴን ለክርስቶስ የታዳጊዎችና የወጣቶች የወንጌል አገልግሎት 👉ወጣቶችንና ታዳጊ ወጣቶችን ስለወንጌል እውነት ያስተምራል!! እንዲሁም ለታዳጊ ወጣቶች ሁለንተናዊ የሆነ ስልጠና ይሰጣል!! 👉ከተማሪዎች ጋር በመሆን በትምህርት ቤቶች ወንጌልን እንሰራለን።

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
288
مشترکین
+124 ساعت
+67 روز
+1030 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

ሰላማችሁን ለመጠበቅ ከመንፈስ ቅዱስ ጋራ ስሩ።
نمایش همه...
🙏 8
ሁሉም እኔን ይመስላሉ! ለምሳሌ ትላንት ጮኾ የጠራው ዓይነ ስውሩ ጠርቶት ሲጨነቅ በግርግሩ "ዝምበል" እያሉት ከእሱ የደረሰው እኔን ይመስላል ያ ለማኝ ሰው በእርግጥ... ዓይን ነበረኝ እንደ ምልክት ያገለገለኝ አምኜው ስጓዝ ገደል ሚጥለኝ ያላስመለጠኝ ስንቴ ስሰበር እንዲያይ ተፈጥሮ አያይም ነበር። ደግሞም የልብ ብርሃን ተስፋ ሚዝበት ለጨለማዬ ፋና ሞጋበት አልነበረኝም ብርሃን ለቤቴ ዘይት አልባ ነው ሸክላ ማኅቶቴ የለኝም ለእግሬ ጭላንጭል መብራት መርቶ ሚያደርሰኝ ለንጉስ እራት አልነበረኝም የመንገድ መብራት። በርግጥ... ዓይን ነበረኝ እንደ ምልክት ያገለገለኝ አምኜው ስጓዝ ገደል ሚጥለኝ አልጠቀሙኝም ማቃጭላቸው ሳንቲሞች እንኳን መቼ አስገቡኝ ከህይወት ድንኳን አልነበረኝም የተስፋ ፋኖስ እየሱስ ብሎ የዳነው ለማኝ እኔን ይመስላል በርጠለሚሆስ    ለካስ... ለእውር መነፅር ስውር ቃል አለች ሰው እየሱስ ሲል ዓለም ታንሳለች ፈጣሪያቸውን ፍጥረት ያውቁታል አፍ እየሱስ ሲል ዓለም መስህቧ ይረቋቆታል። ለካስ ሰው ያያል... ሰው ያያል ለካ እየሱስ ብሎ ማምለጥ ይቻላል እየሱስ ብሎ ፍቅሩ የነካው ሰው ይከተለዋል           መረቡን ጥሎ መረብ ኑሮዬ ፤ መረብ ትዳሬ ፤መረብ ህይወቴ የህይወት ተስፋዬ ፤ምድር ላይ መክበር፤ ነበር ስለቴ መረበኛ ነኝ ዘውትር የምውል በአጢአት ማህበል እድፌን ነክተ እንዳትቆሽሽ ፤ ከእኔ ራቅ በል ያለው ጴጥሮስ ልቡን ሲያየው ልቡ ተስቦት ቃል ደማ ካፉ ፤የነፍሱን ደምስር፤ ፍቅር አልቦት ስለቆሻሻው የሚነቅፈውን ሊሰማ ቢጥር እሱን ሊያደምጠው እርሱ ግን መልሱ "ተከተለኝ ነው ሰው ሊያስጠምደው" ነጥቆ ሊያወጣው፤ ከሞት ከተማ ፤ ከሙታን ግርግም ምርጫ ተወለት ፤ ልዝቡን ቀንበር ፤ ቀሊሉን ሸክም ማራኪው ፍቅሩ ፤ ጥልቁ ትህትናው፤ ልቡን ቢስበው    መረቡን ጥሎ ፤     ኑሮውን ጥሎ ትዳሩን ጥሎ ፤ ተከትሎታል ጴጥሮስ አበው ደግ አረገ... ይኖር የነበር ፤ በማረፊያ አልባ ፤ የኑሮ እንጥልጥል በሕያው መዝገብ ፤ አይሰፍርም ነበር ፤ መረቡን ባይጥል ትላንት በእሱ.. ከአጢሀት ውቂያኖስ ፤ ሰማይ የገባው፤ በህይወት መሰላል ፃድቁ አባቴ አበው ጴጥሮስ እኔን ይመስላል ። ይኸው እንካቸው ደካሞች ብሎ ፤ የነገረኝ ቅዱስ ቃሉ ቆም ብዬ ሳጤናቸው ፤ ሁሉም እኔን ይመስላሉ ። ደግሞ ያ የቄሳር አስገባሪው ...ጠፊ ጣዖት ገንዘብን ሰርሳሪው ጦጣ የመሰለው የዛፍ ላይ ሯጭ እኔን ይመስላል ዘኪዮስ ቀራጭ በአርባ ቀን ዕድል የተበደለው የሀጢአት ሰው ተብሎ የተገለለው መሲሕ ነው ሲሉት ከሩቅ ልይ ብሎ ጦጣ የመሰለው ዛፍ ላይ ተሰቅሎ ተስፋን ናፋቂው ቁመተ አጭሩ እኔን ይመስላል ሁሉ ነገሩ ጥቀርሻ ኑሮውን ነክቶ.......ካመድ ከትቢያ አንስቶ አዚሙን አባርሮለት.........የመገበው ዕለት ዕለት እያራቀው  ከአጢሃት ግፊት......ያከበረው በናቁት ፊት ስንት የሰው ፊት እንዳላየ......ሊያየው ወጥቶ በሱ የታየ ጦጣ መሳይ ዛፍ ላይ ሯጭ                     እኔ ነኝ ዘኪዮስ ቀራጭ ገብሬሃለው የአጢሀት ግብር......ሮጫለው ለራስ ክብር የልብ ጭንቄን ሚሰማ..........አብሮኝ በልቶ የማያማ እየሳመ የማይከዳ.......ናፍቅ ነበር ንፁህ እንግዳ አገኘሁ አገኘኸኝ አገኘሁ አንተን ጌታ..........ልቤ ጮቤ እየመታ             አነባሁኝ መንታ መንታ አስገረምከኝ ስሜን ጠርተኽ አወረድከኝ ከዛፌም ላይ          ....................    ልታስገባኝ ያንተ ሰማይ ልታደርገኝ የምድር ጨው......አልጫነቴን ልትፈጨው በጥዑም አጅህ አንኳክተኸው የልቤን በር ባትገባብኝ እኔ እኔን አልሆንም ነበር እንኳን መጣክ ! እንኳን መጣክ ቤተ ሳይዳ ከመፃጉዎች ስብሰባ ከዲዊያኖች መደዳ በገል መንደር ለቁሰለቴ ማከኪያዎቼን ሰንቄ ቁስሌ የውሻ አሎን ብሎኝ ስላልሻረ ተጨንቄ ወድቄ ነበር ደቅቄ.......ጭንቄን አዳማጭ ናፍቄ ባለሁበት ሰፈር መጥተህ.....ቁም ስትለኝ አበርትተህ ተገረመች ቤተ-ሳይዳ ተገረመች ቤተ-ሳይዳ ፤ እኔም አለሁ ተገርሜ ነፍሴን ፍሰሓ ያስናፈቃት ፤ የት ገባ ያመታት እርሜ ይገርማል... አመራረጡ የገረመው ፤ልቤ አውንም ይገረማል፤ እንዴት የኔ ደዌ ታየው ፤ ከዛ ሁሉ ደዌ መሀል ። ይገርማል ... ሰማይ ሰማያት ዙፋኑ፤ምድር ማትበቃው ለተረከዙ፤ በቁም ነገር ቆጥሮኝ መጣ ፤ እኔን ሊያደርግ ደመወዙ። ብቻ መዳኔ ግሩም ነው፤ አደራረጉም ይደንቃል፤ ማን እንደ እሱ ለእኔ ይወድቃል ማን እንደ እሱ ለእኔ ይደቅቃል ማን እንደ እሱ ለእኔ ይደርቃል ማን እንደ እሱ ለእኔ ይጎዳል ማን እንደ እሱ እኔን ይወዳል ያሉት ሁሉ.....እኔን ይመስላሉ ። ይኸው እንካቸው ደካሞች ብሎ ፤ የነገረኝ ቅዱስ ቃሉ ቆም ብዬ ሳጤናቸው ፤ ሁሉም እኔን ይመስላሉ።            ✍የሱ መልስ
نمایش همه...
7👏 1
አንተ ብቻ ና || ዘማሪት ህሊና ዳዊት sʜᴀʀᴇ◈sʜᴀʀᴇ◈sʜᴀʀᴇ በዚህ ቻናል የማይደመጥ መዝሙር የለም ብቻ ምን አለፋችሁ join ይበሉ  👇 https://t.me/+S2wsmZMSQp3vcGxp https://t.me/+S2wsmZMSQp3vcGxp
نمایش همه...
1
ሮሜ 4 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁹ የመቶ ዓመትም ሽማግሌ ስለ ሆነ እንደ ምውት የሆነውን የራሱን ሥጋና የሳራ ማኅፀን ምውት መሆኑን በእምነቱ ሳይደክም ተመለከተ፤ ²⁰-²¹ ለእግዚአብሔርም ክብር እየሰጠ፥ የሰጠውንም ተስፋ ደግሞ ሊፈጽም እንዲችል አጥብቆ እየተረዳ፥ በእምነት በረታ እንጂ በአለማመን ምክንያት በእግዚአብሔር ተስፋ ቃል አልተጠራጠረም። ²² ስለዚህ ደግሞ ጽድቅ ሆኖ ተቆጠረለት። ²³ ነገር ግን፦ ተቈጠረለት የሚለው ቃል ስለ እርሱ ብቻ የተጻፈ አይደለም፥ ስለ እኛም ነው እንጂ፤ ²⁴-²⁵ ስለ በደላችን አልፎ የተሰጠውን እኛን ስለ ማጽደቅም የተነሣውን ጌታችንን ኢየሱስን ከሙታን ባስነሣው ለምናምን ለእኛ ይቈጠርልን ዘንድ አለው።
نمایش همه...
4👍 3
ያዕቆብ 5 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁷ ኤልያስ እንደ እኛ የሆነ ሰው ነበረ፥ ዝናብም እንዳይዘንብ አጥብቆ ጸለየ፥ በምድርም ላይ ሦስት ዓመት ከስድስት ወር አልዘነበም፤ ሁለተኛም ጸለየ፥ ¹⁸ ሰማዩም ዝናብን ሰጠ ምድሪቱም ፍሬዋን አበቀለች። ✨ከዝህ በመቀጠል ያለው video ስለ ፀሎት ሰዎች የሚናገር ነው። ተባረኩበት🙏
نمایش همه...
3
“... ሕያውን ከሙታን መካከል ስለ ምን ትፈልጋላችሁ? ተነሥቶአል እንጂ በዚህ የለም።”   — ሉቃስ 24፥5 የክርስቶስ መስቀል:- የእግዚ/ር ዘላለማዊ    እና ጥልቅ ፍቅር ማሳያ - ወልድ ያለልክ ዝቅ ብሎ እኛን ያለልክ ከፍ ያደረገበት - ወልድ በሙታን መንደር ተገኝቶ እኛን ከሙታን መንደር ወደሕያዋን መንደር ያወጣበት - የታሪካችን ጅማሬ የክርስቶስ ትንሣኤ:- ልንከፍለው ያልቻልነው እና ያቃተን የኃጢአት ዕዳችን ተደምስሶ ነፃነታችንን ያወጅንበት እና ሰላምን ያገኘንበት - ከነገድ ሁሉ ከቋንቋ ሁሉ ከወገን ሁሉ ከሕዝብም ሁሉ ዋጅቶን ለአምላካችን መንግስት  ካህናት አደረገን!! ሰላም ሰላም✋🤚 እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤ መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳችሁ !! MYAFC
نمایش همه...
5
نمایش همه...
የእግዚአብሔር ኪዳን📜

የእግዚአብሔር ኪዳን የተሰኘው መፅሐፍ፦ ከእግዚአብሔር ለአንተ ያለህን ኪዳን ማወቅና መረዳትህ በሕይወት ላይ የምትነግስበት አንዲያ ቁልፍህ ነው!!

             "ቅርብ"  ሐምሌት በልጁን-||-New Song 🕐-5:12Min || 💾-4.8MB    
نمایش همه...
🥰 4