cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

ÅLL ĨŇ ŌŅË😷

በዚ ቻናል _ስዕል _ልቦለድ _ተከታታይ ድርሰት _ቴክ _መረጃ That's why we call cannel's name ALL IN ONE 👍👍👍👍👍👍👍 Plz don't touch leave button 😞😳😟😨

نمایش بیشتر
کشور مشخص نشده استزبان مشخص نشده استدسته بندی مشخص نشده است
پست‌های تبلیغاتی
150
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

Nikyam ( ኒኪያም ) በአለማችን ደማቅ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላት ሴት ናት። @aweall
نمایش همه...
ሄሪ ሚሼል ( Herry mishel ) አሜሪካዊ ሲሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ያመጣው ሰው ነው። @aweall
نمایش همه...
የአለማችን 2/3 ህዝብ በረዶ አይቶ አያቅም። @aweall
نمایش همه...
#የወርቅ_በርጩማውን_ፍለጋ ፡ ፡ #ክፍል_ሦስት(የመጨረሻ ክፍል) ፡ ፡ #በእንዳለጌታ_ከበደ ...እናቷ ቀጠሉ፡፡ « . . . እንዴት እየኖርኩ እንደሆነ ብታይልኝ! የሰፈር ሰው ያሾፍብኛል ብጤዎቻችን ሊያሳብዱኝ ደርሰዋል . . .» «አሁን ደግሞ ምን ሆናችሁ? ማለቂያ የለው የናንተ ጣጣ!» ገንዘብ አይደለም የጎደለብን ልጄ! ከአፍሽ ነጥቀሽ አይደል የምታጎርሽን? ዕድሜሽን ያርዝመው እንጂ ስራ ከጀመርሽ በኋላ ሰፈርተኛ የሚቀናብን ሆነናል ተንቀባርረን ከሰው ጋር እንቀላቀላለን በፊት የአፈር ገንፎ ይመስላሉ እያሉ ይሳለቁብን የነበሩ ሁሉ አሁን አፋቸውን ይዘዋል፡ ዕድሜ ላንቺ!» ጆሮዬን ቀስሬ ማዳመጤን ቀጥያለሁ:: የእናትና የልጅ የሹክሹክታ ድምፅ፡፡ ከየጣሪያው ስር ስንት አይነት አቤቱታ አለ? ስንት አይነት የተከፋ ልብ? ስንት አይነት አፅናኝ ያጣ ልቅሶ? ልብን የሚያጨልም መልሶ መላልሶ፡፡ «አጥሩን ኣሳጠርኩት:: ቤቱን አሳደስኩት:: አሁን ደግሞ ታናሽሽ ሊያገባ ነው አግዢው አላችሁኝ።ስንቱን ቀዳዳ ልሽፍን? እኔስ እማ? እኔስ! ... ለእኔስ?! » በእንባ ሳትታጠብ አልቀረችም፡፡ ድምፅዋ ነገረኝ፡፡ «ከወንድምሽ ጋር ተጣልተናል ... ተኮራርፈናል! ባንቺ ጉዳይም ተቀያይመናል» __«በእኔ ጉዳይ? ለምን?!» «እህትህን ለምን ታስቸግራታለህ? . . . ለኛ በመጨነቅ ዕድሜዋን ልትገፋ ነወይ! · . . ስለው "እኔ ትዳር ልመሰርት ስል ነው ወይ እንደዚህ አይነት እንድታመነታና እንዳትረዳኝ የሚያደርጋት ሃሳብ የምታመነጨው?' ብሎ ተቆጥቶ አኮረፈ . ዘሪቱ «እሺ አሁን እኔ ምን እንዳደርግ ነው የምትፈልጊው?» አለች። «የሰርግህን መሉ ወጪ እሸፍንልሃለሁ ብለሽ ደብዳቤ ጻፈለት፡፡ ቁጥርና ፊደል ታውቂበት የለ? » «እንዴ? የወንድሜን የሰርግ ወጪ ለመሸፈንኮ ቢያንስ ሁለት ሶስት ዓመት መስራት አለብኝ ያውም የደሞዝ ጭማሪ ካገኘሁ! .. .ከየት አመጣለሁ እማ? . በእርግጥ ታሳዝኚኛለሽ ግን ... » አሳዘነችኝ፡፡ ይህቺ ከተወለደች ሃያ አምስት ዓመት ያስቆጠረች የማትመስል ሴት ስንት መከራ ተሸክማለች? ቆይ ደሞዟን ... «ለሱ አታስቢ!» አሉ እናቷ «ለምኑ?» «ለወንድምሽ ሰርግ ወጪ» «ምን አዲስ ነገር ተገኝቶ ነው የማላስበው? እናንተ ሃሳባችሁን ሁሉ እኔ ጫንቃ ላይ ጥላችሁ አይደል በሰላም ዕንቅልፋችሁን የምትለጥጡት?! መስራት የሚገባችሁን ያህል ለመስራት ሰንፋችሁ በኔ ገንዘብ የከርሞ እቅድ ትነድፋላችሁ! ...›› « ይኸውልሽ ዘሪቱ፣ ጅማ ያሉት የቀርከሃ ሶፋ የሚሠሩ ወንድሞቼ ተደራጂበት፣ ነግጂበት ብለው የላኩልኝ ሁለት መቶ ብር አለ፡፡ ለወንድምሽ ' ለአንዳንድ ጉዳይ ማሟያ' ብለሽ ትልኪለታለሽ፡፡ ከማግባትህ በፊት ስራ መያዝ አለብህ' ብለሽ - ገንዘቡን 'ተሳፈርበት ወደኔ ናበት' ትይዋለሽ፡፡ ከኪስሽ እንዳወጣሽው እንጂ እኔ እንደሰጠሁሽ ወፍ እንዳይሰማ!» አንዳንዴ የምታመነጨው ሃሳብኮ «አይ እማዬ . . . «ምን ላድርግ? ብቻሽን ስትለፊ እያየሁ እጄን አጣጥፌ አልቀመጥ! ... የምሰጥሽን ብር ከላክሽለት ከተማ ገብቶ መስራት ብዙ ገንዘብ የማያስገኝ ይመስለዋል» የተስማሙ መሰለኝ። እኔም እፎይ ብዬ ዘሪቱ እንደማትሄድብኝ እርግጠኛ ሆኜ በባለቤቴ ሞት ምክንያት ያገኘሁትን ብር ምን መስራት እንዳለብኝ እያውጠነጠንኩ፣ የለውጥ ቀን ቅርብ እንደሆነ አስተውዬ . . . ወደ መኝታ ቤቴ ልሄድ ስል ስልኩ ጮኸ። ደነገጥኩ፡፡ በዚህ ሰዓት የሚደወልልኝ ከአስቴር ነው:: አስቴር ምን ሆና ይሆን? ስፈራ ስቸር ስልኩን አነሳሁት። ልክ ነኝ። ረጅም የሆነ ሰላምታ ከተለዋወጥን በኋላ፡ «እቴትዬ!» አለችኝ:: አቤት ድምዕዋ ውስጥ ያለው ፍቅር! በናፍቆት የተሞላ ዜማ! እንደዚህች ያለችዋን እህቴን በባዕድ አገር እንድትጎሳቆል መፍቀዱ ምን ሆኜ ነው? «ወዬ!» ‹ደወለልኝ!! » «ጓደኛሽ?›› «አዎ! ከደቡብ አፍሪካ! ... አሳዘነኝ:: ተላቀስን፡፡ እንዳያሳስበኝ ብለ አጽናናኝ:: የተባባልነወን እፅፍልሻለሁ ... እሺ እቴትዬ!» «አይዟችሁ ይነጋል . . .» «እንዴት ነው እቴት ቤተሰብ አቤቱታ ማሰማት አልጀመረም? . . ባለፈው የሰራሁበትን ብር ሁሉ ለጓደኛዬ ላክሁለት፡፡ ከወላጆቹ የወረሰውን ቤት አሳድሶ በኮንትራት ለሆቴል አከራይቶት እኮ ነው፤ በደቡብ አፍሪካ አድርጎ አሜሪካ ለመግባት ስንቁን የቋጠረው! . ስንደራጅ ቤቱን እኛ እንስራበታለን!» : «ይሁን እስኪ እንግዲህ . . .» «እቴትዬ! . . . ሁልጊዜ እጠይቅሻለሁ ብዬ እየረሳሁ!» «ምን?›› «ሰራተኛሽ ዘሪቱ አጫውታሽ ያዝናናሽኝ ያ የወርቅ በርጩማ ነገር የት ደረሰ? ለወንድሜ ተበረከተለት?» ተሳሳቅን:: «ለምን ጠየቅሽኝ?» «ወደሃገር ቤት ስገባ የራሴን የወርቅ በርጩማ ለመስራት ላቤን ማፍሰስ እንዳለብኝ ይሰማኛል፡፡ በከንቱ ምኞት የሚገኝ ሳይሆን ጠንክሮ የመስራት ውጤት ነው ያ የወርቅ በርጩማ!» ያለችበት ሃገር ስራን አለመናቅን አስተምሯታል፡፡ ሰው ትልቅ የሚባለው ጊዜውን በተግባር መተርጎም የቻለ እንደሆነ መሆኑን ዕውቀትና ልምድ ቀስማለች።ይሄ ነው ብላ ልታሳየኝ የማትችለው ዲግሪ እንደተበረከተላትም ተረዳሁ:: ከመሪር ሕይወት የተገኘ ዲግሪ! «አሪፍ ሃሳብ ነው!» አልኳት! ትንሽ ቆይታ «እቴትዬ! መርሮኛል! ትንሽ ሰራርቼ እመጣለሁ ላብድ ጥቂት ነው የቀረኝ ..በየጊዜው የጓደኞቼ ቁጥር ሲቀንስ፣በሙቅ ውሃ ሲነፍሩ፣ ከፎቅ ሲወረወሩ አሟሟታቸው ሲከፋ እያየሁ እንዴት እንዴት ሆኜ ነው እዚህ በሰው አገር የምኖረው » አለችኝ። « ለምን አትመጪም? ነይ እዚህ! ዛሬ ነገ አትበይ! እኛም በስጋት አለቅንኮ! የግድ ቤተሰቦችሽ እንዲያልፍላቸው ያንቺ ህይወት ማለፍ አለበት?» «አይ እቴትዬ! ...ዛሬ ነገ ሳትይ ነይ' አልሺኝ? ምን ይዤ? መጥቼስ ምን ሰርቼ ልበላ?!» «አንድ የመጣልኝን ሃሳብ ልንገርሽ?» አልኳት ለጥቂት ደቂቃ ሳሰላስል ቆይቼ። «ምንድነው?» «ላበድርሽ ነው! መለስተኛ ንግድ ሊያስጀምርሽ የሚችል ብር! .. ጓደኛሽ በውርስ ያገኘውን ቤት ወደ ንግድ ተቋም የመለወጥ ዕቅድ አላችሁ አይደል? እረዳችኋለሁ!» «ከየት አምጥተሽ?» እንደተገረመች ያስታውቃል:: «ለማንም እንዳትነግሪ! . . . ቤተሰብም ቢሆን እንዳያውቀው! ባለቤቴ ይሰራበት የነበረው ድርጅት ኢንሹራንስ ከፍሎኛል፡፡ ስለዚህ እሰጥሽና - ገንዘቡን ትሰሪበትና - ዕቁብ ገብተሽ ትከፍይኛለሽ .. .» «አይ እቴትዬ!» ከድምፅዋ ሃሳቤን እንደወደደችው ያስታውቃል፡፡ ስልኩን ከዘጋሁት በኋላ ነው፣ መፍትሄውን የኮረጅኩት ከዘሪቱና ከእናቷ እንደሆነ የታወሰኝ! በተገማሸረ መስክ ውስጥ እንደሚብሰከሰክ ውሃ . . እፎይ ብላ የተረጋጋች የምትመስለዋ ህይወታችን መንቀሳቀስ የምትጀምርበት ቀን ሩቅ እንደማይሆን ተሰማኝ፡፡ የዛሬዋን ማታ ወደድኳት፡፡ 💫አለቀ💫 @aweall @aweall
نمایش همه...
#የወርቅ_በርጩማውን_ፍስጋ ፡ ፡ #ክፍል_ሁለት ፡ ፡ #በእንዳለጌታ_ከበደ « . . . የአስቴርን ስቃይ ልቀንስ ብዬኮ ነው። አስቴር እስክትመጣ ድረስ ምን ያህል ጊዜ ይፈጅባታል?አይታወቅም፡፡ ለሁለት ዓመት ብዬ አስምዬ ሸኘኋት! ምላ ተገዝታ ሆነልኝም አልሆነልኝም ባልከኝ ጊዜ እመለሳለሁ አለችኝ።የት አለች ታዲያ?» አለኝ በመነጫነጭ፡፡ «እኛ አስቸግረናት እኮ ነው! ... ወላጆቼ ናቸው የመምጫ ጊዜዋን ያራዘሙት። እሷ ስትሄድ የችግር ቀዳዳዎቻቸው በእጥፍ በዙ» አልኩት። «አንቺ የማታውቂው ብዙ ነገር አለ፡፡ አስቴር ጫንቃዋ መሸከም ከሚችለው በላይ ጭነት እያረፈባት እንደሆነ እያወቅሁ ዝም ማለት እንዴት ያስችለኛል?!ፍቅር ማለት ምንድነው?!» አስቴር ከሄደች ጊዜ አንስቶ የትኛውም መ/ቤት አልተቀጠረም።ወደ የትኛውም ቦታ አስራ ሁለተኛ ክፍል መጨረሰን የሚጠቁም መረጃውን ይዞ ወዲያ ወዲህ አላለም:: ዕወቀቱም፣ ፍላጎቱም ድፍረቱም የለውም ... ታዲያ ለምን ዞር ዞር ብሎ እንጀራውን የሚጋግርበት ምጣድ ገዝቶ አይመለስም? የእሱ እጆች የተፈጠሩት ሌሎች ድል ሲያደርጉ፣ ሌሎች የአሸናፊዎች አሸናፊ ሲሆነ፣ ሌሎች የሜዳሊያ ባለቤት ሲሆኑ እንዲያጨበጭቡ ብቻ ነው እንዴ? ምን ይሰራል? «እና ልሰናበትሽ ነው› አለኝ ሩጫውን እንደጨረሰ ሰው መታከት እየታየበት። ይሂድ! እስኪ ይሂድና ‹‹የወርቅ በርጩማውን» ይፈልግ። ---==-- ዛሬ ምን እንደነካኝ አላውቅም። ቀንድና ጭራው የማይታይ መያዣ መጨበጫ የሌለው ሀሳብ ሲፈታተነኝ አምሽቷል፡፡ የዘሪቱ ነገር........ አገር ቤት ሄዳ በመጣች ቁጥር በቀርከሃ የተሰራ ጌጥ ታመጣልኛለች። ቢላዋ ማስቀመጫ ቄንጠኛ እቃ!የመመገቢያ እቃዎች! የሳጠራ ማስቀመጫዎች! የወለል ምንጣፎች! የማታመጣልኝ የዕደ ጥበብ ውጤት አልነበረም። «እናንተ አገር ይሸጣል?»ስላት «አባቴ ነው የሚሰሪው! ውሰጂላት ብሎኝ ነው»ትለኛለች። በወር ሰባ ብር ነው የምፍላት። ወር በሞላ ቁጥር «እትዬ ደሞዝ» አትለኝም፡፡ ዓመት ሲሞላ እኔ ዘንድ የተጠራቀመላትን ብር ትቀበለኝና አንዳንድ ነገር ገዛዝታ ለቤቶችዋ ትወስድላቸዋለች። «የተረፈሽን ገንዘብ ምን አደረግሽበት?! ... ብዬ እጠይቃታለሁ። «የወላጆቹን ቤት አሳደስኩበታ ...>> «አራት መቶ በማይሞላ ገንዘብ?! » አዎ! በትናንሽ ጎጆ ቤቶች እኮ ነው የምንኖረው!» ይገርመኝና ሌላ ጥያቄ አስከትላለሁ። «የመጀመሪያ ልጅ ነሽ?!» «ለእናቴ አዎ! ለአባቴ አይደለሁም። አባቴ ብዙ ሚስቶች አሉት:: አምና በወር ውስጥ ሁለቱ ሚስቶች ወልደውለት የሚያበላቸው አጥቶ ሲበሳጭ የወር ደሞዜን ላክሁለትና በጣም ተደሰተ፡፡ ባለብዙ ሚስት መሆን በኛ ጎሳ ነውር የለውም» «የት ነበር አልሺኝ ያንቺ አገር . . .» «ሩቅ ነው! ከአዲስ አበባ ወደ ሆሳዕና በሚወስደው መንገድ....>> ከዘሪቱ ጋር ባወራሁ ቁጥር ትዝ የምትለኝ አስቴር ናት። ባለፈው በፃፈችልኝ ደብዳቤ ላይ « . . . ሰሞኑን ወደ ግብፅ ሄደን ነበር፡፡ ወደ ቀጣሪዎቼ ሃገር! ለልጆቻቸው የትውልድ ሀገራቸውን ሲያስጎበኙ እኔም «ሞግዚት»ነኝና ከጎናቸው አልጠፋሁም ነበር፡፡ የአባይን ወንዝ ሲያሳዩአቸው በደስታ ተቅበጠበጥኩ፡፡ የምሆነውን አሳጣኝ፡፡ ምን ሆነሻል ሲሉኝ «አባይ እኮ የኛ ነው አልኳቸው ሳቁ፡፡ ከት ብለው ሳቁ፡፡ ምነው ስላቸው፣ምናሉኝ መሰለሽ? «አባይ ወይ ልትለውጪው ወይ ሊለውጥሽ ይገባል አንድ ነገር ካልሰራሽበት ያንቺ አይደለም።እኛ ከዚህ ውጪ መኖር አንችልም፤» ብለው ስቀው ተሳለቁብኝ .. ሌላ ጊዜ ደግሞ፣ «ዛሬም ልንሄድ ነው ተዘጋጂ»ሲሉኝ «አልሄድም» አልኳቸው:: አልሄድም ያልኳቸው አንደኛ፣ ባለፈው «አባይ የኛ ነው» በማለቴ «እሷ እኮ ናት እንዲህ ያለችው» ብለው በብዙ ሰው ስላሳቁብኝ ሲሆን ሁለተኛ፣ ላንቺ ደብዳቤ ለመፃፍ ግዜ እንዲኖረኝ ብዬ ነበር፡፡ «እንግዲያውስ ከኛ ጋር የማትሄጂ ከሆነ «ብላ የስራ መዓት ቆለለችብኝ፡፡ ከጉብኝትዋ ስትመለስ ይሰራ ካለችው የተወሰነውን ብቻ ነበርና የሰራሁት ጮኸችብኝ፡፡ ተንጨረጨረች፡፡» ድሮስ የናንተ ነገር! አባይን የሚያህል የአለማችን ታላቅ ወንዝ ከደጃችሁ ሲያልፍ ተአምር ልትሰሩበት ቀርቶ ረሃባችሁንም አላሸነፋችሁበት፡፡.ቤት ለማፅዳት፣ መጥረጊያ ለማንሳት» አለመስነፍሽም ይገርመኛል አለችኝ፡፡ እኔ ደግሞ ሃገር ውስጥ ያልነበረኝን ሃገር የመውደድ ስሜት ከየት እንዳመጣሁት እንጃ-ሃገሬ ስትሰደብ ያመኛል፣ እራስ ምታት፣ ጨጓራው ኧረ ምኑ ቅጡ?» ብላ ዕፋልኛለች፡፡ አስቴር የልጅ አዋቂ ናት፡፡ ያለሷ ድጋፍ ይኸን ጊዜ እንዴት ባለ የችግር ህይወት ኑሮአችንን እንገፋ እንደነበር ሲታወሰኝ ይዘገንነኛል፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን «እቴትዬ ጡር መፍራት ደግ ነው» የሚሉ ቃላት በየደብዳቤዎቿ መነሻና መቋጫ ብቅ ብቅ ማለት ጀምረዋል፡፡ «ትዝ ይልሻል? አንዲት ሰራተኛችን፤ ሰራተኛ ቀጥረው ሲሞላው አንድ አመት ሌባ ነው ይሉታል ደሞዝ ለማስቀረት! የሚል ግጥም ያለበት ዘፈን ዘፍና ምን ማለት ፈልገሽ ነው? ብዬ ከወር ደሞዟ አስር ብር ያስቆረጥኩባትኀቀን?! አቤት ያነባችወ እንባ! ያቺ አስር ብር ፕሮግራምዋን እንዴት አመሳቅሎባት ይሆን?! አንጋጠው የተፉት ምራቅ ሆኗል የኔ እጣ! ያን ግጥም ዛሬ እንዴት እንደምወደው እቴትዬ! ይህቺን ባለሁለት መስመር ስንኝ ስንት አይነት አንጀት የሚበላ የሀዘን እንጉርጉሮ አውጥቼላታለሁ መሰለሽ?! . . ባለፈው በማይረባ ሰበብ የስድስት ወር ደሞዜን እንደከለከሉኝ ነግሬሻለሁ አይደል?! .. .» ብላ ፅፋልኛለች! • • ወላጆቼ ሰራተኞቻቸውን ያስተዳድሩ ከነበረው እጅግ በተሻለ ሁኔታ ነው የምንከባከባቸው።በፈራረሰ ማእድቤት - ምድጃ ስር - የተበጣጠሰ ሰሌን አንጥፌ -አይደለም የማሳድራቸው፤ የምጣድ ማሰሻ የመሰለ ብርድ ልብስ - ያውም እግር ወይ አናት ብቻ የመሸፈን አቅም ያለውን ብርድ ልብስ ሰጥቼ አይደለም የማኖራቸው። ትርፍራፊ አይደለም የሚበሉት። ከ'ቡና ቤት ሴቶች' ይልቅ ለ'ቤት ሠራተኞች' የሚሰበር ልብ አለኝ፡፡ በተለይ መልከ ጥፉዎቹ ወንድን እንደተራቡት ወጣትነታቸው ሲያልፍ አቤት | ማሳዘናቸው :: ፍቅርን እንደተቸገሩት ያርጣሉ፣ እምዬ የሚል የእምቦቃቅላ ድምፅ ይናፍቃቸዋል፡፡ አንዳንዶቹ ደግሞ ከችግር እሸሽ ብለው ዘለው በገቡበት ቤት ይደፈራሉ፡፡ ሻሽ እየተወረወረላት-ቅባት እየተገዛላት- ርካሽ ሸበጥ እየተቸራት፣ ካረገዘች በኋላ እጣ ፈንታዋ በእመቤትዋ ወይም በጌታዋ መባረር ይሆናል:: 'ያለ ልጅሽ ነው የምንፈልግሽ' የሚል ፈታኝ ጥያቄ ይመጣል፡፡ ቀስ በቀስ ለልመና እጅዋን ትሰጣለች:: ልጅዋም በረንዳ አድሮ በጎዳና መተዳደር ይጀምራል። ካልሆነለት፣ የእለት ጉርሱን ሊሞላ ማጅራት መቺ ሊሆን! እኔ እንደዚህ እንዲሆነብኝ አልሻም። ግና ምን ዋጋ አለው?! ዘሪቱ ልትሄድብኝ ሳይሆን አይቀርም። ከጥዋት ጀምሮ ሲቀፈኝ የዋለው ያላንዳች ምክንያት አይደለም።እናቷ የመጡት ሊወስዷት ከሆነ፣ እኔ ከምከፍላት የተሻለ የሚከፍላት ሰው ቢገኝ ነው። አስር ብር ልጨምርላት ይሆን? (አንባቢዎቼ በ1996 ነው የተፃፈው የዚ ሰዓት አስር ብር ዋጋውን ለናንተው ልተወው) ዘሪቱ እናቷን ካገኘች ጊዜ ጀምሮ «እማ! ለምንድነው የመጣሽው?» ብላ መልሳ መላልሳ ስትጠይቃቸው እናትየው ግን ስለጤንነቷና ስለ ሥራዋ ነበር የሚያነሱባት፡፡ ዘሪቱ መወትወቷን ስትቀጥል «ማታ ስንተኛ እነግርሻለሁ» ሲሏት ሰምቻለሁ፡፡ ምንም በሹክሹክታ ቢሆን! ዘሪቱ ተስማምታኝ ነበር፡፡ ባለቤቴ ያረፈ ጊዜ እንዴት ትንከባከበኝ እንደነበር መርሳት አልችልም፡፡ አፅናንታኛ ለች፤
نمایش همه...
አኩርታኝ ነበር:: ምን ዋጋ አለው ልትሄድብኝ ነው መሰለኝ፡፡ እስኪመሽ ጨነቀኝ:: ልጆቼን አጣጥቤ - አጫውቼ አስጠንቼ አስተኛኋቸው። እነዘሪቱ ሳሎን ነበር መኝታቸውን ያነጠፉት። ሁላችንም የተኛን ሲመስላቸው እናቷ «ልጄ የቸገረ ነገር ገጥሞኛል።ዘንድሮም እንደ ድሮ ወንድምሽ ስራ-ጠል ሆኗል። አይሰራም:: አያርስም:: «የዌራ እንደትን» ብቻ ነው የሚያመልካት:: ትንሽ ዘርቶ ካጨደ ወስዶ ለሷ ነው:: ምንም ሀብት ንብረት ሳይኖረው «ባርኪልኝ!» ብሉ ይለምናታል:: ያ! የወርቅ በርጩማ! ልቡን ወስዶታል አባትሽም ችላ ይለኛል:: እኔ በወለድኩ እንዲህ መረሳት አለብኝ ወይ?!» «እማም! ድምዕሽን ቀንሺ ... እቴትዬን ከእንቅልፍ ትቀሰቅሻታለሽ!» 💫ይቀጥላል💫 ከአትሮኖስ እንዳገኘነው @aweall @aweall
نمایش همه...
እመለሳለሁ...አለችና ሄደች። አራት ዓመት ሆናት። አሁን ደግሞ እሱ - በርግጥ ፈገግ ብሎ ነበር የሚያናግረኝ፡፡ ያ ፈገግታ የእሱ እንዳልሆነ አውቃለሁ፡፡የእሱ አይደለም:: የእህቴ ነው። ከአስቴር የኮረጀው ፈገግታ ነው- ፊቱ ላይ እየተነበበኝ ያለው! አ! አ! የአስቴርም አይደለም. . .ፈገግታውን ፊቱ ላይ ለብዙ ደቂቃ አቆይቶት ነበር፡፡ የተሸነፈ ሰው- ማለት አሸንፋለሁ ብሎ በደጋፊዎቹ ፊት ሲፎክር የቆየ ሰው ከፍተኛ በሆነ የነጥብ ብልጫ ሲሸነፍ ፊቱ ላይ የሚታየው አይነት ፈገግታ ነው ያየሁበት። አስቴር ወደ ቤይሩት ልትሄድ ስትል ስለ ሀገሯ ስታወራኝ የነበራት አይነት ፈገግታ...ተስፋ የቆረጠ - ሀፍረት የበዛበት ፈገግታ! እንደ ልቡ ለመሆን አቅም ያነሰው! «እና ልትሄድ ነወ፡ ወሰንክ?!» አልኩት የሚያወራውን በፅሞና ስሰማ ቆይቼ! «አዎ! እስኪ ልሂድና ይዤ ልምጣ!» «ምን?» «ያንን የዘሪቱ ወንድም ከልብ የሚያመልከውንና የሚፀልይበትን የወርቅ በርጩማ!» ሀዘን የሞላው ፈገግታ ተለዋወጥን፡፡ ወደ አሜሪካ ሳይሆን ወደ ደቡብ አፍሪካ መሄዱን ከሚያውቁት ሰዎች መረጃ ያገኘሁት ዛሬ ነው! አስቴርንም እንደኔ ዋሽቷት ይሆን?! ማሰላሰል ቀጠልኩ። 💫ይቀጥላል💫 ሼር 🙏🙏🙏🙏 @aweall
نمایش همه...
#የወርቅ_በርጩማውን_ፍስጋ ፡ ፡ #ክፍል_አንድ ፡ ፡ #በእንዳለጌታ_ከበደ ፡ ፡ (በ1996 የተፃፈ ነው ውድ አንባብያን አንዳንዴ አሁን ላይ ቋጥኝ የሚሆኑብን ነገሮች ቀለል ተደርገው ሲገለፁ ግር እንዳይላችሁ መልካም ንባብ።) ----------=======----------======== የቋንቋ መምህርት ነኝ ... አንዳንድ ሰው፣ ጥዋት ከእንቅልፉ እንደነቃ 'ምላሱ ላይ የገባ'ን ዘፈን ቀኑን ሙሉ ሲያንጎራጉረው ይውላል፡፡ በእኔ አእምሮ ውስጥ ደግሞ ጥዋት የሰረገ ብሂል አብሮኝ ውሉ ያመሻል፡፡ ዳኛቸው ወርቁ ከፃፈው «አደፍርስ» ልቦለድ መፅሐፍ ላይ ያገኘሁት አንድ አገላለጽ በውስጤ ታትሞ ቀርቷል፡፡ «... ያቺ በሌላዋ አገር የምትጣደፈው፣ የምትፍለቀለቀው፣ የምትንቦለቦለው ሕይወት እዚህ እፎይ ብላለች። በእርጋታ ፣ በዝግታ ታምማለች በተገማሽረ መስክ ውስጥ እንደሚብሰከሰክ ውሃ ... » ሰሞኑን ከምንጊዜውም በላይ «ስለሀገር ጉዳይ» ያሳስበኝ ጀምሯል።የብሶቴ ምንጭ ግን ይሄ ብቻ አይደለም። ምን እንደሆነ እኔም አላውቀውም። ሰራተኛዬ ዘሪቱ ልትሄድብኝ ነው ብዬ ስለሰጋሁ ሳይሆን አይቀርም። ወይም ደግሞ የታናሽ እህቴ የአስቴር እጮኛ 'አሜሪካ ሄድኩ' ይበል እንጂ ደቡብ አፍሪካ ገብቶ ቀበቶ በመሸጥ እንደሚተዳደር ከሚቀርቡት ሰዎች በመስማቴም ይሆናል ወይም ደግሞ ባለቤቴ ነፍሱን ይማረውና ይሰራበት የነበረው ድርጅት 'ለሟቹ ቤተሰቦች' ብሎ የሠጠኝን ገንዘብ ምናባቴ አድርጌ የረባ ነገር እንደምፈይድበት ግራ ስለገባኝ ይሆናል። ብቻ የሆነ ነገር ሆኛለሁ፣ ወይም ልሆን ነው። ዘሪቱ ከሄደችብኝ ቤቴን ማን ቀጥ አድርጎ ይይዝልኛል? ሁለቱ ልጆቼ ትምህርታቸው ላይ እንዲያተኩሩ እፈልጋለሁ። የትምህርታቸው ውጤት ዝቅ ቢል የባለቤቴ መንፈስ እንደሚከፋብኝ ስለሚሰማኝ ብቻ አይደለም። አለጊዜያቸው ለምን ከሰውነት ተራ ይውጡ? እኔ እናታቸው እስካለሁ ድረስ! ... የስምንት ዓመት ወንድና የአምስት ዓመት ሴት ልጆች ያለ አባት ማሳደግ ይከብድ ይሆን? አላውቅም። . . ዘሪቱ እኔ ቤት በሰራተኛነት ተቀጥራ መስራት ከጀመረች አራት አመት ሆኗታል፡፡ ያኔ አስቴር ወደ ቤይሩት ለመሄድ ጓዝ ጉዝጓዟን መጠቅለል በጀመረችበት ሰሞን ነው ዘሪቱን ያገኘኋት- ያለተያዥም የቀጠርኩዋት። አመንኩዋት- ታመነችልኝም! «ባለቤቷን ስለማታምነው ነው ይህቺን መልከ ጥፉ፣ይቺን ከጨለማ በባሰ ሁኔታ የጠቆረች ሴት ለሰራተኝነት የቀጠረችው! . . .» ተብሎ ተወራ፡፡ ባለቤቴ ሾፌር ነበር፡፡ በአንድ የግል ድርጅት ውስጥ የሥራ አስኪያጁን መኪና ነበር የሚነዳው። ስለ አደጋወም ሆነ ሊሞት ሲል አይቼበት የነበረውን ስቃይ ላለማስታወስ ለራሴ ቃል ከገባህ: ሁለት ዓመት አልፎኛል። ጠመዝማዛወና ' እንኩዋንስ ሰወ ዝንጀሮ አይወጣውም' የተባለለት የአላማጣ መንገድ ለስንቶች ህይወት ማለፍ ተጠያቂ ሆኖ ይሆን?! ... አለማሰብ ነው የሚሻለው! * ከወራት በፊት አንዱን ቀን ፡ የባለቤቴን የኢንሹራንስ ጉዳይ ዳር ለማድረስ ስሯሯጥ ደካክሞኝ ነበር የዋልኩት። መላ ሰውነቴ ውሃ ውስጥ እንደከረመ ሳሙና ተልፈስፍሶ ነበር፡፡ « እቴትዬ አለችኝ ዘሪቱ። « አቤት!» « አይታዘቡኝና አንድ ነገር ባስቸግርዎትስ?!» « ምን ሆነሻል?› «ለእኔ የእርስዎን ያህል ክብር ሰጥቶ የሚያነጋግረኝ የለም! . . ከዚህ ቤት ወጥቼ ሌላ ስራ ባልጀምር ደስ ይለኛል። ግን የነር ጉዳይ ሆኖ . . ." «ደሞዝ አነሰኝ ለማለት ነው ይህ ሁሉ ዳርዳርታ?» ደንገጥ ብላ «ኧረ እቴትዬ ክፍያው አያንሰኝም! ...ግን ታናሽ ወንድሜ ገጠር ከሚሆን እዚህ ሆኖ ቢሰራ ይሻለዋል:: እኔስ እስከመቼ ድረስ የሰራሁትን ሁሉ ጥቂት ብር ብቻ አስቀርቼ ወደነሱ ልላክ?! . . .) «ምንድነው የወንድምሽ ስራ?» «ምንም!›› «እንዴት ምንም?!» «በአምልኮ ነው ጊዜውን የሚያሳልፈው!» «በአምልኮ?» «አዎ! በተወለድኩበት አካባቢ መድረሻውን የማላውቀው አንድ ወንዝ አለ ... 'የዌራ እንደት' ብለው የሚጠሩዋት አምላክ ትኖርበታለች:: ከክፉ ነገር እንድትጠብቃቸው ... ከብቶቻቸውንም በውሃ ሙላት ከመወሰድ እንድትጠብቅላቸው፣ ከክረምት በቀር ከዓመት እስከ ዓመት ይገብሩላታል፡፡ ለዌራ እንደት' ክብር ተብሎ በግ ይታረዳል፡፡ በአዝመራ ጊዜ ነጭ ገብስ በስሟ ይዘራል፡፡ ስብሉ በደረሰ ጊዜ ከሌላ ጥሬ ጋር ሳይደባለቅ በጥንቃቄ ይቀመጣል፡፡ የግብር ወቅት ሲደርስ 'ለዌራ እንደት' ይወሰድላታል፡፡ ኧረ ብዘ ነገር ነው የሚደረግላት» አለችኝ ዘሪቱ፡፡ «እና ወንድምሽ ምን ለማግኘት ነው ጣዖቷን የሚያመልካት?» አልኩዋት ራሷን ከእምነቱ ተከታዮች ለማራቅ የምታደርገውን ጥረት ከንግግሯ እየተረዳሁ። «የወርቅ በርጩማ ለማግኘት» «አልገባኝም» « ... ወንዙ ውስጥ ግዙፍ የሆነ የወርቅ በርጩማ አለ ይላሉ ወንዙ እምብርት ላይ ሁልጊዜ የሚሽከረከር ነገር አለ፡፡ እሱጋ ነው ያለው ይላሉ:: ውሃው ውስጥ ገብተው ለማውጣት የሞከሩ ሁሉ ህይወታቸው አልፏል፡፡ዋናተኞችም ቢሆኑ! ... ከልብ 'የዌራ እንደትን ያመለከ ሰው የወርቅ በርጩማውን ለግሉ ያደርገዋል ተብሎ ይታመናል፡፡» «አይ አለማወቅ! ይሄማ ከሁዋለኞች ሁሉ ሁዋላ የሚያስቀር አመለካከት አይደል?» «እንግዲህ፣ እንደዚያ ነው የሚያምኑት - ወንድሜ ደግሞ የሁላችንም ህይወት ሊለወጥ የሚችለው፣ 'በርጩማወ' በእጄ ሲገባ ነው ብሎ ያምናል፡፡የወገኖቹን የእጅ ሙያ ወርሶ ልክ እንደናቴ ወንድሞች መንቀሳቀስ ሲገባው! ... በዚያ ላይ በቅርቡ ማግባት ይፈልጋል» «እና አሁን ምን አስበሻል? .. .» «እዚህ ይምጣ፡፡ እንደኔ የማታ ትምህርት ጀምሮ ቁጥርና ፊደል ይለይ! የስራ ሰው ይሁን እስኪደራጅ ድረስ ብዙ ጊዜ ስለሚፈጅበት ልረዳው እፈልጋለሁ፡፡ ለሆዱ የቀን ስራ እየሰራ ለራሱ ይወቅበት! የአንድ ወር ደሞዝ ቅድሚያ እንዲሰጠኝ ነወ፡ የምለምንዎት....." ደስ አለችኝ! « ብርቱ ነሽ እኮ የኔ ልጅ! እኔ ደግሞ አንቺን አግዛለሁ» አልኳት። አቤት! ያን ሰሞን ይሄ «የወርቅ በርጩማ» ነገር እንዴት መዝናኛ ሆኖን ነበር? ለእህቴ ለአስቴር በስልክ ስነግራት «አትቀልጅ! መጥቼ እድሌን ልሞክር እንዴ? ስትል ቀለደች፡፡ እጮኛዋ ግን ምንም ስሜት አልሰጠውም። የእህቴን እጮኛ የእህቴን ያህል አውቀዋለሁ።ከወር በፊት፣ እኔ ወደማስተምርበት መለስተኛ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት መጥቶ፣ "ውጭ አገር ልሄድ ነው!» አለኝ «አሜሪካ . . .)ደነገጥኩ፡፡ «እናንተ ልጆች ምን እየሆናችሁ ነው?! አብዳችኋል? አስቴር ቤይሩት ሄደች:: የሄደችው የሁለታችሁን የተሻለ መኖር የሚያስችላችሁን አቅም ለማጎልበት ነው።ያለን ይበቃናል ፍቅራችን ያኖረናል ማለት ሲገባህ ያንተም ልብ እንደ ጠበል ዕቃ ውጭ ማደር ይጀምር?!...ብዬ ተቆጣሁት። ጥቁር ድንጋይ ላይ ውሃ የማፍሰስ ያህል ነበር! አስቴርና እጮኛዋ ከተማሪነት ዘመናቸው ጀምሮ አብረው ሲሆኑ መለያየት የሚባል ዕጣ፣ አለመስማማት የሚባል ጣጣ በሁለታቸው መሃከል መንገድ አልዘረጋም...አንድ ቀን አስቴር 'እቴት፣ ወደ ቤይሩት ልበር ነው።የምነግርሽ እንድታውቂው ነው:: መሄድ እንዳለብኝ ከወሰንኩ በኋላ ጓደኛዬን ለማሳመን ብዙ ሰዓት ፈጅቶብኛል፡፡ ብዙ ቀናት ልበልሽ እንጂ! እና ላንቺ እያማከርኩሽ ሳይሆን ውሳኔዬን እየነገርኩሽ ስለሆነ አለመሄድ እንደሚሻል በማሳመን እንዳታደክሚኝ አለቺኝ። 'ገንዘብ ከየት ይመጣል አስቴር?!' 'ለመሄጃ?!' 'አዎ!' 'ጓደኛዬ ከወላጆቹ የወረሰውን ቤት በኮንትራት አከራይቶታል፡፡ ከእሱ እወስዳለሁ።የምሄደው ለአንድ ለሁለት ዓመት ያህል ነው።ሰራርቼ
نمایش همه...
#የገንዘብ_ቦርሳው ፡ ፡ #ድርሰት_አንቶን_ቼኾቭ አንድ መልካም የማለዳ እለት ነው።ሶስት ተዘዋዋሪ ዘፋኞች በባቡር ሃዲድ ላይ ሲጓዙ የገንዘብ ቦርሳ ወድቆ አገኙ። ስሚርኖቭ፣ፖፖቭና ባላባይኪን ቦርሳውን ከፍተው ሲመለከቱ ከደስታቸው ብዛት የሚሆኑትን አጡ። ተፍነከነኩ፡ በጣምም ተገረሙ፡፡ ለካስ በቦርሳው ውስጥ 20 ኖቶች፣ ስድስት የሁለተኛ ዕጣ አሸናፊ የሎተሪ ትኬቶችና የሶስት ሺ ሩብል ገንዘብ ነበሩበት። በመጀመሪያ ከፈት አድርገው ሲመለከቱ “ወንዳታ” ብለው በጋራ ጮኹ።ከዚያም ሐዲዱ ጥግ ላይ ባለ ጉድባ ሆነው በደስታ መደመማቸውን ቀጠሉ፡፡ ለመሆኑ ለእያንዳንዳችን ስንት ይደርሰናል?” ሲል ስሚርኖቭ ገንዘቡን እየቆጠረ ጠየቀ፡፡ “ያንተ ያለህ! አምስት ሺ አራት መቶ አርባ አምስት ሩብል! ወገን! ከዚህ ሁሉ ገንዘብ በኋላ ብንሞትም አይቆጭ!" ባላባይኪንም ቀጠለ። “እኔ በበኩሌ ለራሴ አይደለም የተደሰትኩት” አለ“ለእናንተው ለምወዳችሁ ወንድሞቼ ነው በደስታ ያበድኩት።የገንዘብ ቦርሳው ከእንግዲህስ ወዲያ እየተራባችሁ በባዶ እግር መኳተን አከተመለት። ወደ ሞስኮ አቀናለሁ።ከእንግዲህስ ወዲያ እንደ አሚና እየዞርኩ አልዘፍንም ቄንጠኛ ሰው እሆናለሁ:: ባለ ሀሩን ክብ ባርኔጣና ልዩ የሆነውን የኦፔራ ባርኔጣም እገዛለሁ።እንደኔ ሽክ ማለት ለሚወድ ሰው አመዳዩ የሀር ባርኔጣም አስፈላጊ ነው። በነገራችን ላይ የዛሬዋን እለት ማከበር አለብን። እየበላንና እየጠጣን መደስት ያስፈልገናል፡፡ ደግሞም ለሶስት ተከታታይ ቀናት በቀዘቀዘ ምግብ ተቆራምደን ነው የቆየነው። ከእንግዲህ በኋላ ለየት ያለ ነገር ማድረግ ይኖርብናል አይመስላችሁም!?” ትክክል ነው ወገኖቼ!” ሲል ስሚርኖቭ በቀረበው ሀሳብ ተስማማ፡፡ “ብዙ ገንዘብ ኖሮን የምንበላው ግን ከሌለን ምን ይፈይዳል የእኔ ውዶች? ወንድም ፓፓቭ! መቼም አንተ ከመሃከላችን ወጣት ስለሆንክ ከቦርሳው ገንዘብ ውሰድና እባክህ ሮጥ በል፡ አደራህን የእኔ መልአክ እዚሁ ቅርባችን ነው መንደሩ፡፡ ተመልከት! መጠምዘዣው ላይ ነጭ የቤተክርስቲያን ጉልላት ይታይሃል? ትልቅ መንደር ነው፡፡ እዚያ ሁሉም ነገር ይገኛል። አንድ ጠርሙስ ቮድካ ግዛ፣ ትልቅ የእሪያ ስጋ፣ ሁለት ዳቦና ሰርዲንም ጨምርበት። እኛ እዚህ እንጠብቅሃለን የእኔ ጌታ! የእኔ ተወዳጅ...” ፖፖቭ እንደተባለው ገንዘቡን ተቀብሎ ለመሄድ ተዘጋጀ:: ስሚርኖቭ እንባ ባቀረረ አይኑ እቅፍ አድርጉ ሶስቴ አገላብጦ ሳመው፡፡ እያማተበም በምድር ላይ ያለ መልአክና ነፍስ የሆነ ሰው አድርጐ አሞጋግሰው፡፡ ባላባይኪንም ከስሚርኖቭ ባልተናነሰ አቅፎት ዝንተ ዓለማቸውን በጓደኝነት እንደሚቆዩ አድርጐ ፍቅሩን ገለፀለት፡፡ ሁለቱም እጅግ ስሜትን በሚነካ ሁኔታ አቅፈው እያሻሹት ወደ መንደሪቱ ሸኙት.. ፖፖቭም “አቤት! እንዴት ያለ ደስታ ነው!?” እያለ እግረመንገዱን በሀሳብ ኳተነ። “ከእንግዲህስ ወደ ትውልድ ሀገሬ እበራለሁ፡፡ ጓደኞቼን ስብስቤ አንድ የግሌን ትያትር ቤት እገነባለሁ:: እዚህ ላይ ግን መታወቅ ያለበት እም፣ ግን እኮ ተካፍዬ የማገኘው ገንዘብ ለምን ይሆናል? አንድ ደህና ክዳን ቤት እንኳ አይሰራልኝም፡፡ ቦርሳው ግን እንዳለ የእኔ ከሆነ ይህ ሌላ ጉዳይ ነው ምን የመሰለ ትያትር ቤት አቆምበታለሁ፡፡ ለእኔም ክብር ይሆነኛል፡ እንዲያው እውነቱን እንናገር ቢባል ስሚርኖቭና ባላባይኪን ተዋናይ የሚባሉ ናቸው? እነሱን ብሎ ተዋናይ! ተሰጥኦ የሚባል ነገር ያልፈጠረባቸው አሳሞችና ጡንቻ ራሶች ናቸው።ደደቦች! እነሱ እጅ ገንዘቡ ከገባ በዋዛፈዛዛ ያባክኑታል፡፡ እኔ ከሆንኩ ግን ለተወለድኩባት ኮስትሮም ከተማ ጥቅም አውላለሁ። ዘላለማዊ ቅርስ አኖራለሁ ..አንድ ሀሳብ መጣልኝ ቦርሳውን ለራሴ ማስቀረት አለብኝ፡፡ ቀጥሎ የማደርገውን እኔ አውቃለሁ። በምገዛው ቮድካ ውስጥ መርዝ እጨምራለሁ፡፡ እነሱ ወዲያው ይሞታሉ፡፡ ከዚህም በኋላ ሀገሬ ሩሲያ አይታ የማታውቀው ትያትር ቤት ይኖራታል፡፡ ማነው እሱ? ማከ-ማጐን ሳይሆን አይቀርም እንደተናገረው “ዓላማ ግብን ያመቻቻል”ብሎ ነበር። አዎን! ማከማጐን ታላቅ ሰው ነበር፡፡” እግረ መንገዱን ፖፖቭ ከራሱ ጋር በሚመካከርበት ጊዜ ጓደኞቹ ስሚርኖቭና ባሳባይኪንም ተቀምጠው ያወጋሉ። “ጓደኛችን ፖፖቭ ደህና ጉርባ እኮ ነው” አለ ስሚርኖቭ አይኑ እንዳቀረዘዘ፡፡ “እወደዋለሁ። ችሎታውንም በሚገባ አደንቅለታለሁ፡፡በእሱ ላይ ፍፁም ፍቅር ነው ያለኝ። ግን ምን ያደርጋል? ይህ ገንዘብ አጥፊው ነው፡፡ ይጠጣበታል ወይም ነጋዴዎች ያታልሉትና ገንዘቡን የትም በትኖ ይመለሳል። ወጣትም በመሆኑ የገንዘብ መያዢያ ጊዜው አይደለም፡፡ በሀሳቤ ትስማማለህ የእኔ ወንድም “አዎ!” ሲል ባላባይኪን በሀሳቡ መስማማቱን ለመግለጽ ስሚርኖቭን አቅፎ ሳመው።ቀጠለናም "ለምኑ ነው ለዚ ውርጋጥ ገንዘብ የሚያስፈልገው ? ካንተ ጋር ግን መካፈላችን የተለየ ጉዳይ ነው እኔና አንተ የቤተሰብ ኃላፊዎችና የሰከንን ሰዎች ነን ገንዘብ ብዙ ነገር ያደርግልናል።” ዝምታ በመሃከላቸው ሰፈነ “ስማኝ ወንድሜ?! ለረዥም ሰዓታት የዚህን ውርጋጥ ነገር እያወጋንና እየተፈላሰፍን መቆየት የለብንም። የገዛውን ዕቃ ተረክበን እንግደለው! ከዚህ በኋላ ለእኔና ላንተ ስምንት ሺ ሩብል ይደርሰናል ማለት ነው። እንግደለውና ሞስኮ ከተማ ውስጥ ፖፖቭን የባቡር ፉርጐ በልቶት ሞተ እያልን እናስወራለን። እርግጥ ነው እኔም ብሆን እወደዋለሁ፣ አከብረዋለሁ። ከሁሉም በላይ ግን የኪነ ጥበብ እሴት ትበልጥብኛለች፡፡ በግልጽ ካየነውም ተሰጥኦ የለሽና እንደዚህ እንደተነጠፈ የባቡር ሐዲድ የደነዘ ልጅ ነው::” “ምነው ጃል?! ምን ማለትህ ነው?” ሲል ስሚርኖቭ ደንግጦ በአባባሉ አለመስማማቱን ገለፀለት፡፡ “ይህን የተቀደሰና ሀቀኛ ወጣት እንዲህ ስታጣጥለው ትንሽ አታፍርም በእርግጥ በሌላ መልኩ ብንገድለው በወንድማዊነት የሚሆን ነገር ነው::”ስመለከተው፣ በግልፅም ለመናገር አንተ የማትረባ አሳማ ስትሆን እሱ ግን ክብሩን የጠበቀ እብድ፣ አዋሻኪና ሀሜተኛ ነው እንኳ እኛኑ ያስመሰግነናል እንጂ ሌላ ትርጉም አያሰጥብንም።ስለዚህ ወንድሜ፣ የእኔ ብስል፤ ምን የሚያስቀይም ነገር ይኖራል ብለህ ታስባለህ? ሞስኮ ከተማ ስንደርስ የሰውን ልብ የሚነካ የሀዘን መግለጫ ፅፈን በጋዜጣ እንዲታተም እናደርግለታለን። ይህም ቢሆን በወንድማዊነት የሚሆን ነገር ነው የተወራው መፈፀም አለበት ፖፖቭ ከተላከበት መንደር የገዛውን ሁሉ ይዞ እንደተመለሰ ይጠብቁት የነበሩት ጓደኞቹ አይናቸው እንባ እንዳቀረረ አንገቱ ላይ ፡፡ተጠመጠሙ:: አገላብጠው ሳሙት። ለተወሰኑ ሰዓታትም ስለ ታላቅ ተዋናይነቱ እያወሱ አደነቁት፡፡ በድንገት ግን ተጠቃቅሰው አፈርድሜ አስጋጡት:: ፖፖቭ ሞተ፡፡ወንጀሉ እንዳይደረስባቸው አስከሬኑን ጐትተው የባቡር ሐዲዱ ላይ ጣሉት ያስገዙትን ምግብና መጠጥ ተከፋፍለው በመልካም ቃላት እየተሞጋገሱ ተመገቡ። የፈፀሙትም ወንጀል ለቅጣት እንደማያደርስ እረግጠኞች ነበሩ:: ዳሩ ግን ምግባረ ሰናይ መከበሩ፣ ምግባረ እኩይ ደግሞ መቀጣቱ መቼም የታወቀ ነገር ነው:: መርዝ .... ፖፖቭ ገዝቶ ባመጣው ቮድካ ውስጥ የጨመረው መርዝና ከላዩ ላይ የተጐነጨለት ቮድካ ስራውን መስራት ቀጠለ። ጓደኛሞቹ ጨርሰው ለመጠጣት አልቻሉም:: ትንፋሻቸው ተቋረጠ፤ እነሱም ባቡር ሐዲዱ ላይ እንደተጋደሙ ቀሩ:: ከአንድ ሰዓት በኋላ አሞራ በላያቸው ላይ አንዣበበ። 💫አለቀ💫 @aweall @aweall መልካም ምሽት። 🙏 Join @frompages
نمایش همه...
በበአሉ ግርማ እምባ እምባ ይለኛል ይተናነቀኛል ግን እምባ ከየት አባቱ! ደርቋል ከረጢቱ ሳቅ ሳቅም ይለኛል ስቆ ላይስቅ ጥርሴ ስቃ እያለቀሰች መከረኛ ነፍሴ። ከገፅ 371 ቆነጠርን @frompages
نمایش همه...