cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

Mohammed Ahmed Official

ዩቲዩብ 👇 youtube.com/@gharuhira በግል ጥያቄ እና አስተያየት ካለዎ 👇 @afhasmen

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
4 525
مشترکین
-324 ساعت
-57 روز
-2530 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

እንባ ለሰው ልጆች የተቸረ ተፈጥሯዊ ፀጋ ነው። በሀዘን ፣ በደስታ፣ በስቃይ እና በህመም ስሜቶች ውስጥ ስናልፍ የእንባ ቋጠሯችን መፈታቱ የተፈጥሮ ምላሽ ነው። ግና ወደ እስልምና አፀድ የሚመለሱ የሌላ እምነት ተከታዮች በጉንጮቻቸው ላይ የሚንኳለለው እንባ ከእውነተኛ ምንጩ የሚቀዳ እንባ መሆኑን በቀላሉ መረዳት ይቻላል። ምክኒያቱም በዚያች ልዩ ቅፅበት «ሁሉም» ወደ እስልምና ተመላሾች በተመሳሳይ ሁኔታ ያለ አንዳች ምክኒያት የአዞ እንባ በጉንጮቻቸው ላይ እንዲያፈሱ የሚያስችላቸው አቅም ከየትም አያመጡም። ንፁህ እንባ በተፈጥሮ ግፊት የሚፈልቅ እንጂ በግል ፍላጎት የሚፈስ የውኃ መስመር ቧንቧ አይደለምና። ወገኖቼ ! ውስጥን ፈንቅሎ የሚፈነዳው ለቅሶ ከታደሉት ውጭ ሌሎች ሊረዱት የማይቻላቸው ረቂቅ ሥሜት ነው። ወደ ተፈጥሯዊ መጠለያቸው በተመለሱ አማኞች እስከዛሬ የፈሰሰው እንባ የገፈርሳን ግድብ ሳያስንቅ ይቀራል ብዬ አላስብም። የሚገርመኝ ነገር የነሱ የእንባ ቋጠሮ ሲፈታ የእኛንም የመፍታት ሥልጣን የሰጣቸው ኃይል ያለ በሚመስል ሁኔታ በለቅሷቸው ያላቅሱናል። ለዘመናት የተሸከሙት ክምር ደማሚት እንዳንኮታኮታው ተራራ በተውሒድ ቃል ከፊታቸው ሲፈረፈር ከማዬት በላይ ምን የሚያስለቅስ ነገር ይኖራል ? ለማንኛውም ፣ በምዕራቡ ዓለም እየነፈሰ ያለው አውሎ ነፋስ ከምንገምተው በላይ እየፈጠነ ነው። ቲክቶክን ለመዝጋት የሚደረገው ሩጫ ከጀርባው ብዙ ምክኒያቶች ቢደረደሩም ዋነኛው ግን ወደ እስልምና ጣቢያ በገፍ የሚፈልሱቱን ስደተኞች ለመገደብ ነው። http://t.me/abuafnanmoh
نمایش همه...
15👍 9
ከወራት በፊት ለኬሚስትሪ መምህሩ አብዱ ኢድሪስ ሐሰን በአገር ውስጥ ለሚያከናውነው የኩላሊት ንቅለ ተከላ 600,000 ብር የሚሆን የገንዘብ ድጋፍ እንደሚያስፈልገው ጥሪ ስናቀርብላችሁ በስድስት ቀናት ውስጥ 850,000 ብር ወደ አካውንቱ ገቢ በማድረግ የተለመደ ትብብራችሁን አሳይታችኋል። እንደናንተ አይነት መልካም ሰዎች ሲበዙ ጠያቂ አጥተው የነበሩ ግለሰቦች ጆሮ የሚሰጣቸው ወገን ያገኛሉ። አልጋ ላይ ወድቀው የሞታቸውን ቀን ይጠባበቁ የነበሩ ህሙማን ከተኙበት አልጋ ላይ በተስፋ ይነሳሉ። ህይወት ጀርባዋን አዙራባቸው ተስፋ የቆረጡ ሰዎች የመከራ ዳገቱን የሚሻገሩበት ምርኩዝ ያገኛሉ።   ወንድማችን መምህር አብዱ ኢድሪስ ያለበትን አሁናዊ ሁኔታ ከላይ በተያያዘው ቪዲዮ መመልከት ይችላሉ።                   ምሥጋና                  🍁🍁🍁 🚩 የገቢ ማሰባሰቢያውን ለማከናወን የመጀመሪያውን የምስልና ድምፅ ቀረጻ እንዲሁም የኤዲትንግ ሥራ በመስራት ከጎኔ ለነበሩት ወንድሞቼ ኢስማዒል ሰዒድ ፣ ሙሐጅሩ መሃመድ አቡ ከውሰር እና አሕመድ ኢብራሂም ሙሐመድ ምስጋናዬን ለማቅረብ እወዳለሁ። 🚩 ንቅለ ተከላውን በተሳካ ሁኔታ ላከናወኑት የ St. Paul's Hospital Millennium Medical College-SPHMMC ሐኪሞችና የጤና ባለሙያዎች ከፍ ያለ ምስጋናችንን እናቀርባለን።
نمایش همه...
21👍 6
23
15😢 3
ቁርኣን በወረደበት ወርሃ ረመዷን የአላህን (ﷻ) ቤት በመገንባት ሂደት ላይ የበኩላቸውን አሻራ ለማሳረፍ ቃል የገቡ ደጋግ ወገኖቻችን ቃላቸውን ለመፈፀም የተለያዩ ምክኒያቶች ወደ ኋላ ያስቀሯቸው ይሆናል እንጂ ቃላቸውን እንደሚሞሉ ቅንጣት አንጠራጠርም። ምናልባት የዘነጉ ካሉ ለማስታወስና በመስጂዱ የሒሳብ ቁጥሮች እየገቡ ያሉ ገንዘቦችን አጠቃላይ ድምር ለማሳወቅ አልፎ አልፎ ብቅ እያልን ሪፖርት እናደርጋለን። በዚህም መሠረት በረመዷን በቀጥታ ሥርጭት ከተከናወነው የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም በኋላ እስካሁን ድረስ በሁሉም የአዲሱ ሰፈር ኑር መስጂድ የባንክ ሒሳብ ቁጥሮች አጠቃላይ ሁለት ሚሊዬን አምሥት መቶ ሀምሳ ሰባት ሺህ አንድ መቶ ስድሳ አምሥት ብር ገቢ ሆኗል (2,557,165) በታላቁ ወር ለአላህ የገባችሁትን ቃል እየሞላችሁ ያላችሁ ወንድሞቻችን እና እህቶቻችን ሁሉ ፣ ቃሉን የማያጥፈው አላህ ጀነትን ለመውረስ ከወዲሁ የሽልማቱ ትኬት ከተቆረጠላቸው ደጋግ ባሮቹ ተርታ ያሰልፋችሁ። ሌሎቻችሁም ለመስጂዱ ድጋፍ ለማድረግ ቃል የገባችሁትን ገንዘብ እንደምታስገቡ በማመን በጉጉት እየጠበቅናችሁ ነው። http://t.me/abuafnanmoh
نمایش همه...
11👍 3
ሐቀል ሚልሕ ኦቶማን ቱርኮች ወደ ዓረቡ ዓለም ያስገቡት አንድ አስደናቂ ባህል አለ። «ሐቀል ሚልሕ» ይሰኛል። «ለጨዉ የሚገባ ሥጦታ» እንደማለት። ባል ከዒድ ሶላት ወደ ቤቱ ከመመለሱ በፊት ሚስት አቅሟ በፈቀደ ልክ ቤቷን ምድራዊ ገነት አድርጋ ትጠብቀዋለች። በማራኪ አልባሳት ተውባ ፏ ብትን ትላለች። ሰውነቷ ላይ አፍንጫን የሚያውዱ ሽቶዎች አርከፍክፋ ለምለማማ መስክ ላይ እንደምትሸቀረቀር ጣውስ አይኖቿን በሩ ላይ ትወረውራለች። ባል ወደ ቤቱ እንደገባ አንድ ስኒ ቡና ይቀርብለታል። ቡናውን ይጠጣል። ግና ከጠጣ በኋላ ስኒውን ባዶ አድርጎ ወደ እሷ አይመልስም። በረመዷን ሙሉ ላሳለፈችው ድካም እና ልፋት እውቅና ለመስጠት በባዶው ስኒ ውስጥ የወርቅ አሊያም የብር ቀለበት ያስቀምጥላታል። እሷም የቀረበላትን ሥጦታ በፈገግታ ትቀበላለች። በጥንዶቹ መሃል የተመሰረተው ፍቅር በመሰል ስጦታዎች ድርና ማግ ሆኖ የመቀጠል ዕድሜው ይረዝማል። «ሐቀል ሚልሕ» የተሰኘውም ሚስት በወርሃ ረመዷን እሳት ላይ ተጥዳ የምታዘጋጃቸው ጣት የሚያስቆረጥሙ ምግቦች የጨው መጠናቸው ውኃ ልኩን የጠበቀ ስለነበር ነው። ♥♥♥ ጉዳዩን ወደ ሀገርኛ ስንገለብጠው ነገር ዓለሙ ሁሉ ይገለባበጣል። የቀረበላቸውን ምግብ ጠራርገው የበሉበትን ትሪ ብቻ የሚያስተርፉ ዘጠኝ ወጠምሻ ጓደኞቹን ለፊጥራ የጋበዘ አባወራ ሚስቱ ቀኑን ሙሉ ማጀት ውስጥ በመዋል እሱን ጨምሮ የአስር ወንዶች ከርስ ሚዛን የሚያስተካክል ጣፋጭ ምግብ አቅርባ ስትጨርስ ወርቁ ቀርቶባት ግንባሯን ስሞ ምስጋና ይቸራት ይሆን ??? ነው ወይስ ገንዘብ ሳያወጣ «የስጋ ሳንቡሳ ስሪ ብየሽ እንግዶቼን እንዴት በምስር ሳንቡሳ ትሸኛለሽ ?» እያለ በቁጣ ብዛት ጸጉሩ የቦነነ አነር ነው የሚመስለው ??? 😃 👉 http://t.me/abuafnanmoh
نمایش همه...
17👍 10
ለዒድ ሶላቶች መስገጃ ተብሎ ከተዘጋጀው የባቲ ብርሃናማው ተራራ (ጀበለኑር) ላይ በዱንያ ውስጥ አንድ ክፍለዘመን ከአምስት ዓመት ከቆዩት የዕድሜ ባለፀጋው ጋሽ ሙሐመድ አደም ጋር ዓይን ለዓይን ተገጣጠምን። ዳገት ሲወጣ ጭሱን እንደሚያንፎለፉል ፊያት መኪና እያማጥኩ የወጣሁትን ፈታኝ ተራራ እኝህ የዕድሜ ባለፀጋ እንዴት እንደወጡት አላሁ አዕለም !! ዒድ ሙባረክ http://t.me/abuafnanmoh
نمایش همه...
13👍 5
23👍 2
በቅርቡ በባቲ ከተማ በአዲሱ ሰፈር የሚገኘውን ኑር መስጂድ ለመገንባት በቀጥታ ሥርጭት በተከናወነ የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም ላይ በተደረገ ድጋፍ በቃል፣ በዓይነት እና በጥሬ በጠቅላላ አራት ሚሊዬን አምስት መቶ ሺህ ብር (4,500,000) መሰብሰብ እንደተቻለ መግለፃችን ይታወሳል። በዚህም መሰረት የአላህን ቤት ለመገንባት ከአላህ ጋር ቃልኪዳን የገቡ ጀግና ወንድሞቻችን እና እህቶቻችን በአጭር ጊዜ ውስጥ ቃላቸውን እየሞሉ ይገኛሉ። የገቢ ማሰባሰቢያው ከተከናወነ በኋላ እስካሁን ድረስ በሁሉም የአዲሱ ሰፈር ኑር መስጂድ የባንክ ሒሳብ ቁጥሮች በድምሩ ሁለት ሚሊዬን ሁለት መቶ ሀምሳ ሺህ ሁለት መቶ አርባ ሥምንት ብር ገቢ ሆኗል (2,250,248) የገባችሁትን ቃል እየሞላችሁ ያላችሁ ወንድሞቻችን እና እህቶቻችን ሁሉ ፣ ቃሉን የማያጥፈው አላህ ጀነትን ለመውረስ ከወዲሁ የሽልማቱ ትኬት ከተቆረጠላቸው ደጋግ ባሮቹ ተርታ ያሰልፋችሁ። ሌሎቻችሁም ቃል የገባችሁትን ድጋፍ እንድትፈፅሙ በጉጉት እየጠበቅናችሁ ነው 😍😍😍 http://t.me/abuafnanmoh
نمایش همه...
18