cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

ሕያው ቃል

''ነዋ ወንጌል መንግሠተ ሰማያት "፦ ወደ መንግሥተ ሰማያት የምታገባ ወንጌል እንሆ። "

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
5 923
مشترکین
-624 ساعت
-337 روز
-9930 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

ኤሌክትሮኒክስ ጥገና መማር ለምትፈልጉ ይህን ቻናል ተቀላቀሉ https://t.me/electronics_xegena
نمایش همه...
ኤሌክትሮኒክስ ጥገና

የምንሰጣቸው አገልግሎቶች . የቲቪ LED . Crt .ቲቪ ጥገና . ጂፓስ ሪሲቨር እና የመሳሰሉት

👍 4 1
ኤሌክትሮኒክስ ጥገና መማር ለምትፈልጉ ይህን ቻናል ተቀላቀሉ https://t.me/electronics_xegena
نمایش همه...
ኤሌክትሮኒክስ ጥገና

የምንሰጣቸው አገልግሎቶች . የቲቪ LED . Crt .ቲቪ ጥገና . ጂፓስ ሪሲቨር እና የመሳሰሉት

👍 8 1
Photo unavailableShow in Telegram
48
ይሄን ሊንክ በመንካት ቀጥታ ወደ ፌስቡክ አካውንታችን በመግባት ፎሎው ያድርጉን ። በአዲስ መልኩ የተከፈተ ነው አዳዲስ ነገር ያገኙበታል ። 👇👇 https://www.facebook.com/profile.php?id=100090438198637
نمایش همه...
Log in or sign up to view

See posts, photos and more on Facebook.

ከመታወቅ በላይ! እግዚአብሔር በእግዚአብሔር ታዉቆ ይኖራል እንጂ በፍጡር አዕምሮ የማይደረስበት ትልቅ አምላክ ነዉ። እግዚአብሔርን ያወቅነው እርሱ የሆነውን ያህል ሳይሆን እኛ ለማወቅ የቻልነውን መጠን ነው።  እርሱ ከቃላችን ከስብከታችን በላይ ነው።  ቃላት እርሱን ለመግለጥ ያነክሳሉ፣ አሳብም እርሱን ለማጠናቀቅ ይብረከረካል፣ እንዳይጠፋ ይሰጋል።  እግዚዓብሔር ከመታወቅ በላይ ቢሆንም እውነት ነውና እንድናውቀው ይፈልጋል። እርሱ ጨለማ የሌለበት ብርሃን ነው።  እንኳን እግዚዓብሔር የሰማይ ስፋት፣ የባህር ጥልቀት እንኳን አልተደረሰበትም። የፈጠረዉ ካልተደረሰበት ፈጣሪው ባይደረስበት ምን ይደንቃል! እግዚአብሔር ህልውናው ምክንያት የለውም፣ ለመኖሩም በማንም አይደገፍም፣ በራሱ ሕይወተ ባህርይ ይኖራል። ምሳሌ አልባ፣ ድካም የሌለበት አምላክ ነው። አባቶች እንደተናገሩለት ኃይሉ በመብረቅ፣ ፍጥነቱ በነፋስ፣ ልዕልናው በሰማይ፣ ስፋቱ በምድር፣ አስፈሪነቱ በእሳት፣ ጥልቀቱ በባህር አይመሰልም። ከፍጡራን አስረጅነት በላይ የሆነ በራሱ ታውቆ የሚኖር የእውቀት እውቀት ነው።  ጎዶሎው ሰው ፍፁሙን አምላክ በሙሉነት ማወቅ አይችልም። እግዚአብሔር ስለራሱ የገለጸልንን አለማወቅም ተገቢ አይደለም። እርሱ ግን በራሱ ታውቆ፣ ባሕርይው ባሕርዩን አክብሮት ይኖራል። በመታወቅም ባለመታወቅም ያስደስታል። ፅንፍ የለሽ ክብሩ ይወደስ!!!!!!!!!!!!
نمایش همه...
ኀጢአተኞች ኹሉ ምሕረት ያገኘንበት አዲሱ ኪዳናችን፣ ክርስቶስ ኢየሱስ ነው፤ የምሕረት ኪዳኑም ላይሻር በቅዱስ ደሙ ታትሞአል! አሜን።
نمایش همه...
Photo unavailableShow in Telegram
አቤቱ ጾም አስለምደኝ ጌታዬ ኢየሱስ ሆይ፦ ጾም ምግብን ከሥጋ ከመከልከል እንደሚጀመር አውቃለሁ። የሰባውን መተው እንደሆነም ተምሬአለሁ። ምግቤን በመቀየር መጾም አስቸግሮኝ አያውቅም። ነገር ግን እንዳንተ ወደ ምድረ በዳ መውረድን አልለመድኩም። ስሜቶቼን ከመብላቸው ልከለክላቸው አልቻልኩም። አርባ ቀን እስክትራብ ጾመሃል። ከዓለም ጫጫታ ተሰውረህ ብቻህን ከርመሃል። ሰይጣን መራብህን አይቶ የዘረጋውን የፈተና ወጥመድ ሰብረሃል። ልጅህ ግን ከምግብ ለውጥ ያለፈ የጾም ማዕረግ የለኝም። በተራብኩ ጊዜ ለብዙ ፈተና እጋለጣለሁ። ንዴት፣ ፍርድ፣ ስንፍና፣ ፌዝ የተባለ የሰባማዕድ ዛሬም ከፊቴ አልተነሳም። የምወደውን ለመጨበጥ ያለኝ ጉጉት ሰከን አላለም። ያየሁት ሲያምረኝ ሰውነቴ ሆይ ጾም ላይ ነህ! አልለውም። ከንፈሬ እስኪደርቅ ከውሃ እከለከላለሁ። ስንፍናን ለመናገር ግን መልሼ ከንፈሬን በምላሴ አረጥባለሁ። መልሼ ጾመኛ መሆኔን እናገራለሁ። አየህ ጌታዬ ያልተማርኩት ብዙ ጥበብ አለ። ያልደስረኩበት ብዙ መንፈሳዊ ማዕረግ አለ። ከነርሱ አንዱ መንፈሳዊ ጾም ነው። መጾምን እንድታስተምረኝ አለምናለሁ። ሁል ጊዜ በፊትህ የእውነት መኖርን እንድትሰጠኝ እለምናለሁ። የማያድግና በልማድ ዓለም የተዋጠ ህይወት እንዲኖረኝ አልሻም። እንደትንሽ ዘለላ በወደቀበት አድጎ የሚነሳ ታደርገኝ ዘንድ ከልቤ እጸልያለሁ። ተባረኩበት።
نمایش همه...
አሳርፎናል! ✔ለዘላለም ሕይወት ሰው ለእግዚአብሔር የሚሠራለት ምንም ነገር የለም፡፡ የኃጢአታችን ደመወዝ ሞት እንደ ሆነ ሁሉ፤ የዘላለም ሕይወት ደግሞ በክርስቶስ ኢየሱስ የእግዚአብሔር የጸጋ ስጦታ ነው (ሮሜ 6፥23)፡፡ ሰዎች ሁሉ የሚድኑበት የእግዚአብሔር ጸጋ፤ ኃጢአተኝነትንና ዓለማዊን ምኞት የሚያስክድ ጸጋ ከእግዚአብሔር ለእኛ ተገልጦአል፡፡    ✔  ክርስቲያን ስላመነ እንዳመነ ሰው በእምነት ይኖራል (ሮሜ 1፥17) እንጂ ለዘላለም ደኅንነት እግዚአብሔር ከተግባሩና ከእጅ ሥራው (ከሰው) የሚፈልገው ምንም ነገር የለም፡፡ ጌታችን "እኔ ላደርገው የሰጠኸኝን ሥራ ፈጽሜ በምድር አከበርሁህ . . " /ዮሐ. 17፥4/ እንዳለ፤ "ኢየሱስም ሆምጣጤውን ከተቀበለ በኋላ፡- ተፈፀመ አለ፤ ራሱንም አዘንብሎ ነፍሱን አሳልፎ ሰጠ" (ዮሐ. 19፥30)፡፡ 🙏 የፈፀመው ጌታ አሳርፎናል!
نمایش همه...
"የኢየሱስ ክርስቶስ ደም አገልግሎት" *** “ከኃጢአት ሁሉ የሚያነጻ”(1 ዮሐ .1÷9) “ በእግዚአብሔር ፊት ስለ እኛ አሁን የሚታይ” (ዕብ .9÷24) “በቅዱስ ደሙ ኃጢአታችንን የሻረ” ( ትምህርተ ኅቡዐት) “ መዓዛው የጣፈጠ ንጹህ መስዋዕት”(ቅዱስ ቄርሎስ) >ፊተኛው የደም አገልግሎት ኃጢአትን ከመቀነስ ይልቅ እየጨመረ ፣ከማንጻት ይልቅ እያዳፈነ የኃጢአት ፍህም በየማለዳው አዲስ እየሆነ ምድርን በእድፈትና በርኩሰት ስላካለለ ኢየሱስ ከዕድፈትና ከርኩሰት ፣ከፊት መጨማደድም ንጹህ የሆነች (ኤፌ .5÷27) ቤተ ክርስቲያንን ያዘጋጅና ይሞሽር ዘንድ ወደደ፡፡ስለዚህም በገዛ ደሙ የዋጃትንና ያነጻትን ቤተ ክርስቲያን እርሱ በገዛ ፈቃዱ መሠረተልን፡፡ ( ሐዋ.20÷28) ቤተ ክርስቲያን የደሙን አገልግሎት ፍጹም ታምናለች፡፡ የደመቀችበት ፣ያጌጠችበት ለሙሽራው ኢየሱስ የተሞሸረችበትና ሙሽሪት ሆና የቀረበችበት የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ደም ነው፡፡ የደሙን አገልግሎት የማታምን ቤተ ክርስቲያንና የማያምን አማኝ ፈጽሞ ክርስቶሳዊ ክርስቲያን መሆን አይችልም፡፡የኢየሱስ የደሙ አገልግሎት ዛሬም ያላቋረጠ፤የደሙን መስዋዕት አቅራቢው ሊቀ ካህን ክርስቶስ ኢየሱስም የማይለወጥና የዘላለም ክህነት ያለው ነው፡፡(ዕብ .7÷24) © አስተውሉ!!! የታረደው በግ ዛሬም በዙፋኑ ህያው ሆኖ አለ፤በእግዚአብሔር አሁን ውስጥ ሆኖም በዙፋኑ የሚታየው እንደታረደ ሆኖ ነው፡፡በዳግም ምጽአቱ የሚመጣው እንኳ የታረደበትን ችንካር እያሳየ ነው፡፡ (ራዕ .5÷9 ፤ማቴ.24÷30 ፤ራዕ.1÷7) ፡፡በጉ ሊታረድ ግድ የሆነው ምንም ኃጢአት የሌለበት ሆኖ ለኃጢአተኛው አዳም ሊሞት በሥላሴ ዘንድ ምክሩ ስለፀና ነው፡፡የሞተውንና የወደቀውን ሊያነሳ የማይሞተው ሞቶ ፤እንደታረደም ሆኖ ታየ፡፡ #የታረደው በግ ደም ዋና አገልግሎት፦ #1- ደሙ አዲሱን ኪዳንና ህያውን መንገድ መርቆ የከፈተ ነው፡፡ ፊተኛው ኪዳን እንኳ ያለደም አልተመረቀም፡፡ጌታ ደካማዋንና ሙት የነበረችዋን የኩነኔ አገልግሎት መንገዷን መርቆ የከፈተውና ሊቀ ካህኑ ወደቅድስቱ ሊገባ ድፍረት የሆነው በእግዚብሔር ፊት የሚያቀርበውና በእጁ የያዘው ደም ነው፡፡ ያለደም ወደቅድስት ፈጽሞ መግባት አይቻልም፡፡ በአንድ ሐገር የሚሰሩ ታላላቅ የመንገድ ሥራዎች የምረቃ ሥርዐታቸው የሚከናወነው በሐገሪቱ ዋና ባዕለሥልጣን (መሪ ) ነው፡፡ዋናው ባዕለሥልጣን የምረቃዋን ሪባን ገመድ ቆርጦ በመንገዱ ከተራመደበት በኋላ ሌሎች እርሱን ተከትለው ይጓዛሉ፡፡ ከዚያ ቀንም ጀምሮ መንገዱ ለሁሉም አካላት ክፍት ይሆናል፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በር ሆኖ በደሙ መርቆ የከፈተልን አዲስና ህያው መንገድ እርሱ የምህረቱ ዓመት አዲስ ኪዳን ነው፡፡“በመረቀልን በአዲስና በሕያው መንገድ ወደ ቅድስት በኢየሱስ ደም በመጋረጃው ማለት በሥጋው በኩል እንድንገባ ድፍረት … ”አለን፡፡ (ዕብ .10÷19) ፡፡ምንም እንኳ ኃጢአተኞችና በደለኞች ብንሆን በልጁ በኩል የምንገባው ወደዘላለም ክብሩ ፤የምንወርሰውም የዘላለም ህይወትን ነው፡፡(ቆላ .2÷13 ፤ ዮሐ.3÷15) ሕይወታችን የሆነ ክርስቶስ በሚገለጥበት በዚያን ጊዜ እኛም ደግሞ ከእርሱ ጋር በክብር እንገለጣለን፡፡ (ቆላ .3÷4 ፤ 1ተሰ .4÷17)  “ ይህም የእግዚአብሔር ስጦታ ነው እንጂ ከእኛ አይደለም … ”(ኤፌ .2÷8) ፡፡ያለእርሱ ጸጋና ያለእርሱ መንገድነት ወደአብ መድረስ አይቻልም፡፡ (ዮሐ .14÷6) ፡፡ቅዱሳን ሁሉ የሄዱበት መንገድ እርሱ መርቆ በከፈተው ቅዱስና ህያው መንገድ ነው፡፡ ወደአብ የሚያደርሰው ይህ መንገድ የማያሳስት መንገድ ነው፡፡ በደሙ ተመርቆ ከተከፈተውም መንገድ በቀር ሌላ ወደህይወትና ወደእረፍት የሚያደርስ መንገድ ፈጽሞ የለም፡፡ደሙ የከፈተልን መንገድ የህይወትና የልምላሜ መንገድ ነው፡፡ክርስትና የሚለው አዲስ መንገድ ላይ መጓዝ የጀመርነው ክርስቶስ መርቆ ከከፈተው በኋላ ነው፡፡አዲሱም ኪዳን ላያረጅ ፍጹም የታተመበት ህትመት ህያውና ለዘላለም ትኩስ በሆነው በኢየሱስ ክርስቶስ ደም ነው፡፡ #2- ደሙ ቤዛችን ነው፡፡ “ በውድ ልጁም፥ እንደ ጸጋው ባለ ጠግነት መጠን፥ በደሙ የተደረገ ቤዛነታችንን አገኘን እርሱም የበደላችን ስርየት።”(ኤፌ .1÷7) “ በኋለኛው ዘመን የምክርህን አበጋዝ መድኀኒት ቤዛ የሚሆን ልጅህን ሰደድህልን፡፡” ( የሐዋርያት ቅዳሴ ) " ስለፍጥረትህ ሁሉ ቤዛ ሆኖ በእግዚአብሔር ቸርነት በሥጋ ሞተ" ( ሃይማኖተ አበው ዘቄርሎስ ምዕ.70 ክ.1 ቁጥር 10) “ከአዳም ጀምሮ እስከዛሬ ከተፈጠረው ፍጥረት ሁሉ ማንም ማን ሊያድነን አልቻለም፤ ከእግዚአብሔር ቃል በቀር በሰው ቢሆን አለኝታችን ከንቱ እንዳይሆን የባህርይ አምላክ እርሱ ሰው ኾነ እንጂ፡፡ከሰው ወገን የሚሾም ሊቀ ካህናት ሁሉ በመጽሐፍ እንደተነገረ ስለሰው ይሾማል፤ስለዚህም ጌታ ከወዲያ ዓለም ወደዚህ ዓለም መጥቶ ከሰው ወገን ተወለደ እግዚአብሔር ቃል ሰው ሆነ፤ አምላክ በመሆኑ ያድነን ዘንድ ሰው በመሆኑም ለእኛ ቤዛ ሆኖ ይሞትልን ዘንድ፡፡( ሃይማኖተ አበው ዘኤጲፋንዮስ ምዕ.58 ቁ .49-50) “ ቤዛ” የሚለውን ቃል “ አዳኝ፣መድኃኒት ዋቢ፣ሃላፊ፣መድህን፡፡በካሳ መልክ ወይም እንደምትክ ፣እንደመለወጫ፣እንደመያዣ የሚቀርብ…” ብሎ ይፈታዋል፡፡ (ኣማርኛ መዝገበ ቃላት፡፡ (2001) ፤አዲስ አበባ፣አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ማተሚያ ቤት፡፡ገጽ .243) በሌላ ትርጉም ደግሞ “የተያዘን ወይም የተወሰደን ነገር ለማስመለስ የሚከፈል ዋጋ ፣ካሳ ፣ለውጥ … ” ነው ይለናል፡፡( በሞቱ ለሚያምንበት ሁሉ ቤዛ ሆኖ በእግረ አጋንንት ፤በሞት ይገዛ የነበረውን አዳምንና ዘሩን በሞቱ ካሳ ክሶ ፤ደሙን አፍስሶ በመከራና በሐዘኑ ሁሉ ምትክ ሆኖ ወደቀደመና ህያው ክብሩ የመለሰው ሥጋ የለበሰው ክርስቶስ ነው፡፡ጌታ ነፍሱን በቤዛነቱ ላመኑበት ለብዙዎች ራሱን የሰጠ ነው፡፡ (ማር .10÷45 ፤1 ጢሞ.2÷5) #ኢትዮጲያውያን ገበሬዎች በልዩ የሥነ መለኰት የእምነት እውቀታቸው “ ቤዛነት አምላክነት ያሻዋል” ይላሉ፡፡ክርስቶስን ቤዛችን ነው የምንለው የእኛ ምትክ ሆኖ ከታላቅ የፍቅሩ ባዕለጠግነቱ የተነሳ እኛን ተገብቶ፤ዕዳችንን ሁሉ ከፍሎ በመቤዥ በደሙ ነጻ ስላወጣን ነው፡፡ቤዛነት የክርስቶስ ብቻ ነው፤ከፍጡር ወገን ቤዛ መሆን የሚቻለው ማንም የለም፡፡ዋጋ የሚከፍል አካል እርሱ ቀድሞ ከዕዳ ነጻ መሆን መቻል አለበት፤ከክርስቶስም በቀር ከአዳም በደልና ዕድፈት ነጻ ሆኖ ዕዳችንን ከፍሎ መድኃኒትና ቤዛ የሆነን የለም፡፡እርሱ በንጹህ ደሙ ለበደለኛው የሰው ዘር ሁሉ ዋጋ የሆነና በዋጋውም ገዝቶን የዋጀን ነው፡፡“ ቤዛነት አምላክነት ያሻዋል” የሚባለው ከአምላክ በቀር ፍጹምና ንጹህ ቤዛ ፈጽሞ ስለሌለ ነው፡፡ምክንያቱም ሰው የማይበድል አይደለምና፤በተጨማሪም “ ጻድቅ አንድስ እንኳ የለም” (2 ዜና .6÷36 ፤ ሮሜ .3÷11) በማለት ቃሉ ስለደመደመ ንጹህና ፍጹም ቤዛ መሆን የሚቻለው ከብርሐን የተገኘው ብርሐን፣ከእውነተኛው አምላክ የተገኘው እውነተኛው አምላክ ከእመቤታችን ከድንግል ማርያም ፍጹም ሥጋን የነሳውና ዘመዳችን የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ ነው፡፡እርሱ አምላክ የሆነ ሰው፤ሰው የሆነ አምላክ ነውና፡፡ ክርስቶስ የመጣበት ዋና ዓላማው “ ነፍሱን ለብዙዎች ቤዛ ሊሰጥ” እንደሆነ ተገልጧል፡፡ (ማቴ .20÷28 ፤ማር.10÷45) አዎ! ከአምላክ በቀር ሰው ስለራሱ ነፍስ ቤዛ መሆን (
نمایش همه...
یک طرح متفاوت انتخاب کنید

طرح فعلی شما تنها برای 5 کانال تجزیه و تحلیل را مجاز می کند. برای بیشتر، لطفا یک طرح دیگر انتخاب کنید.