Kestedemena pre-primary, primary and middle school
رفتن به کانال در Telegram
نمایش بیشتر
888
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
+37 روز
+230 روز
آرشیو پست ها
Repost from Kolfe education official channel🇪🇹
የህጻናት ማቆያዎች የልደት ምዝገባ ያልተደረገላቸው ህጻናትን መቀበል እንደማይችሉ ተነገረ
በአዲስ አበባ ከተማ የ2017 ዓ.ም የትምህርት ቅበላ የልደት ምዝገባ ያላደረጉ ከ54 ሺ በላይ ህጻናት ምዝገባ እንዲያደርጉ መደረጉን የአዲስ አበባ ሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ አስታወቀ፡፡
የሲቪል ምዝገባ ስርዓት ለማማሻሻል ፣ የህፃናት መብት ጥብቃን ለማጠናከር፣ ዘመናዊ የትምህርት ስርዓት ለመዘርጋት እንዲቻል አስፈላጊ ነው።
ያልተመዘገበ ልደት ክምችትን ሙሉ ለሙሉ ለማቅለል የልደት ምዝገባ የምስክር ወረቀት በከተማዋ ላሉ ትምህርት ቤቶች የተማሪዎች ቅበላ የምዝገባ ቅድመ ሁኔታ አሰራር ስርዓት ሆኖ በአስገዳጅነት ተቀምጦ እየተሰራበት መሆኑን የአዲስ አበባ ሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ዮናስ ዓለማየሁ በተለይም ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ተናግረዋል፡፡
በዚሁ መሰረት ከዚህ ቀደሞ የልደት ምዝገባ ያላከናወኑ ህፃናት እና ተማሪዎች በወረዳ የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ጽ/ቤት ቀርበው እንዲመዘገቡ የተደረገ ሲሆን የልደት ምዝገባ ያላደረጉ ከ54 ሺ በላይ ተማሪዎች ምዝገባ ማድረግ መቻሉን ተጠቁሟል፡፡በተቋሙ የነበሩ የካርድ እጥረቶች ችግሮች በአሁኑ ወቅት ሙሉ ለሙሉ የተፈታ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን በ2017ዓ.ም የልደት ምዝገባ ያላደረጉ የከተማው የግል እና የመንግስት ተማሪዎች እንዳይኖሩ እየተሰራ እንደሚገኝ ተነግሯል፡፡
በተጨማሪ ማንኛውም በከተማው ውስጥ ያሉ የህፃናት ማቆያዎች የልደት ምዝገባ ያልተደረገላቸው ህፃናትን መቀበል እንደማይችሉ አስገዳጅ አሰራር ለመዘርጋት ከከተማው የሴቶች ህፃናት እና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ጋር እየተሰራ እንደሆነ አቶ ዮናስ ዓለማየሁ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ተናግረዋል፡፡
#ዳጉ_ጆርናል
+1
በክፉ እሳቤ ምክንያት የተቀበረው መስቀል የተገኘው ተስፋ ባለመቁረጥና በፅናት ነው!
መስቀል በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ ልዩ ቦታ የሚሰጠው የድህነት ምክንያት ነው።
በእምነቱ ተከታዮች ዘንድ ልዩ ቦታ የሚሰጠውን መስቀል በክፉ እሳቤ ልባቸው የተከተቡ ቢሰዉሩትም ተስፋ ያልቆረጡና በፅናት የፈለጉ ከተቀበረበት አገኙት
ዛሬ ላይ የገጠመን ችግር በአይነቱ የተለየ ነገር ግን የችግሮቹን ምክንያቶች በውል ለይተን በህብረትና በፅናት ከተጋን ደመናው ተገፎ ብርሀን መሆኑ አይቀሬ ነው
እንኳን ለብርሀነ መስቀሉ በሰላም አደረሰን!
መሠረት አስፈሪ
ርዕሠ መምህር
+2
መስከረም 16/2017ዓ.ም
"መርካቶ ሳሌም አጥቢያ ሐዋርያዊት ቤተ-ክርስቲያን" ትምህርት ለትውልድ በሚል መሪ ሐሳብ ለቀስተ ደመና ትምህርት ቤት 10 ጋሎን የተለያዩ ቀለማት ለገሡ።🙏🙏
የትምህርት ስብራትን ለመጠገን ምድረ-ግቢውን ውብ፣ ጽዱና ማራኪ ማድረግ ወሳኝ ምዕራፍ ነው። በዚህም መሠረት ቤተ-ክርስቲያኑ "ቀስተ-ደመናን እናስውባለን፤ ትውልዶች በተሻለ ይማራሉ።" በማለት 10 ጋሎን የተለያዩ ቀለማት ስለለገሱን በትውልድ ስም እናመሠግናለን።
እንዴት አደራችሁ
ነገ በቀን 16/1/2017 ዓ.ም የደመራ በአል በተመለከተ ትምህርት የሚኖረው ግማሽ ቀን ብቻ በመሆኑ ለወላጆች ከወዲሁ አሳውቁ ፡፡ ቀኑን ሙሉ ትምህርት የሚዘጋ ት/ቤት ኃላፊነቱን ይወስዳል፡፡
ዛሬ መስከረም 06/2017 ለሁሉም ተማሪዎች በተላለፈው ጥሪ መሰረት
-በርእሰ መምህራን፣መምህርራን እና ትምህርት ጽ/ቤት ሀላፊዎች በኩል በደመቀ ሁኔታ የተማሪዎች አቀባበልና የችቦ ማብራት ስነ ስርዓት ተከናወኗል ።
- በተማሪዎች ዲስፒልን ዙሪያ ከተማሪዎች ጋር ውይይት ተደርጓል በመመሪያው ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።
- በሂሳብና በእንግሊዘኛ ት/ቶች ስትራትጃክ እቅድ ዙሪያ ውይይት ተደርጓል፡ ፡ በቀጣይ በነገው የመማር ማስተማር ሂደቱ ይቀጥላል።
ቀስተ-ደመና ትምህርት ቤት 2017 ዓ.ም
"በትምህርት ዘርፍ የሚስተዋሉ ሁለንተናዊ ጉድለቶችን ማረም ወደ ትላንት ክብራችን እና ማንነታችን መመለሻ መታጠፊያ መንገድ ነው"
ትምህርት የአንድን ማህበረሰብ የአኗኗር ዘይቤ በመሰረታዊነት የመቀየር አቅም ያለው የዜጎች የዕድሜ ልክ አንጡራ ሀብት ነው።
በመሆኑም ትምህርት ላይ መስራት ወደ ቀደምት ክብራችን እና ማንነታችን የሚመልሰን መታጠፊያ መንገድ መሆኑን በመረዳት አሁን ከገባንበት የትምህርት ጥራት ችግር ለመውጣት ባለ ድርሻ አካላት በትኩረት ሊሰሩ ይገባል ።
የበለጸጉ ሀገራት የዕድገታቸው እና የቴክኖሎጂ ልህቀታቸው ምክንያት ጥራት ያለው ትምህርት ለዜጎቻቸው ተደራሽ በማድረጋቸው እንደሆነ ብዙወች ይስማማሉ።
ስለሆነም በዕውቀት፣ በክህሎት እና በአመለካከት የዳበረ ትውልድ ለመፍጠር ሁሉም የሚመለከተው በመሆኑ ወላጆች፣ መምህራን፣ ፖለቲከኞች፣ እራሳቸው ተማሪዎች እና አጠቃላይ ማህበረሰቡ ለትምህርት ጥራት ትኩረት ሰጥተው ሊሰሩ ይገባል ።
ትውልድ የሚገነባው እና ሀገር የሚለወጠው በትምህርት መሆኑን በፅኑ በማመን ከሁሉም በፊት ለትምህርት ስርዓት ጥራትና ተደራሽነት ትኩረት ሰጥተን በመስራት አሁን ከገባንበት ችግር ፈጥነን ልንወጣ ይገባል።
በዘርፉ ያጋጠመን ችግር ስርዓታዊና መዋቅራዊ ከመሆኑ ባሻገር ከችግሩ እንድንሻገር ከተፈለገ ሁሉም ወደ ውስጥ ሊመለከት እንደሚገባና ቅድሚያ የስነ ምግባር ስብራቱ እንዲጠገን ትኩረት ሰጥቶ መስራት የተልኳችን ሀሌታ ''ሀ''መሆን ይገባዋል እያልኩ።
ውድ ተማሪዎች መምህራን እና የትምህርት ባለድርሻዎች እንኳን ለዘመን መለወጫ ባዕል አደረሳችሁ።
መሠረት አስፈሪ
ርዕሠ-መምህር @ቀስቴ
01/01/2017ዓ.ም
