cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

"ቃለ እግዚአብሔር "

"ጥበብን ማግኘት ምንኛ ከወርቅ ይሻላል! ማስተዋልንም ማግኘት ከብር ይልቅ የሚመረጥ ነው።" ምሳ 16 "ሥጋችን ምግብ ሲያጣ እንደሚደክም ሁሉ ነፍስም ምግቧን የእግዚአብሔርን ቃል ስታጣ ትደክማለች።" - ብጹዕ አቡነ ሽኖዳ በመንፈሳዊ ህይወት ዙሪያ ጥያቄ ካላችሁ ለመምህራችን በ @henokasrat3 መላክ ትችላላቹ።

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
8 193
مشترکین
-224 ساعت
-197 روز
-6430 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

Photo unavailableShow in Telegram
👍 3
❤በእንተ ስማ ለማርያም❤ሼር እናድርግ ! 👉ለኦርቶዶክሳውያን ምዕመናን በሙሉ “እነሆ፥ እግዚአብሔር ለመቅደስ የሚሆን። ቤትን ትሠራ ዘንድ መርጦሃልና ጠንክረህ ፈጽመው።” መፅሐፍ ዜና መዋዕል ቀዳማዊ 28፥10 የእግዚአብሔርን ቤት ለመሥራት የተመረጣችሁ ለበረከት ስራው የተጠራችሁ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሐይማኖት ከደም ከስጋችሁ የተዋሄዳችው “የቤትህ ቅናት ይበላኛል።”— ዮሐንስ ወንጌል 2፥17 የሚትሉ ኑ የነፍስ ዋጋ ለማግኘት ❤በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክ #በከምባታ #ጠምባሮና #አላባ ሀገረ ስብከት በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የጎፎሬ ደብረ መንክራት በኣታ ለማርያም ህንፃ ቤተክርስቲያን በጋራ እንሰራ። እነዚህ ጥቅት ምዕመናን ለሀገራቸውና ለነፍሳቸው የሚጸልዩበትን፣ መንፈሳዊ አገልግሎት የሚያገኙትን፣ ከእግዚአብሔር ጋር የሚገናኙበትን የእግዚአብሔር ቤተመቅደስ ለመሥራት ለበርካታ አመታት ያሰቡ ቢሆንም በእነርሱ አቅም የሚሆን አይደለምና ተስፋ ቆርጠው ይገኛሉ በጎን ደግሞ የሌሎች የእምነት ድርጀቶች በዚህ ደሳሳ ጎጆ የሚትጸልዩ አቅም የሌላችሁ ነችሁና ወደ እኛ ኑ በማለት ተላቅ የሆነ የስነልቦና ጫና እያደረሱባቸው ይገኛሉ እነርሱ ግን ይህንንና ሌሎችንም ጫናዎችን ችላው በሃይማኖታቸው ጻንተው ዛሬም አሉ ስለዚህ ወድ ኦርቶዶክሳውያን ምዕመናን ለበጎ ነገር የሚትተጉ የተዘጉና የተዘነጉ የገጣሪቷን ቤተክርስቲያን ለማገዝና በረከት ለማግኘት ሁሌ የሚትተጉ በሀገር ውስጥና በውጪ የሚትኖሩ በዚህ ሥራ እንድትሰተፋ በእመቤታችን በድንግል ማርያም ስም እንጠይቃለን ። በረከትን ልትወርሱ ለዚህ ተጠርታችኋልና።” — 1ኛ ጴጥሮስ 3፥9 የጠራን እኛ ሳንሆን መድከማችንን ያዬ አቅማችንን የተመለከተ ልዑል እግዚአብሔር ነው ይላሉ እነዚህ ጥቅት ምዕመናን። ለነፍሳችን ቤዛ የሚሆንልንን መንፈሳዊ ስራ በመስራት የአቅማችንን በማድረግ ዋጋችንን ብል በማይበላው ሌባ በማይሰርቀው በሰማያዊ መዝገብ እናስመዘግብ። ለዚህም የተቀደሰ አላማ እጃችሁን በመዘርጋት እንድትረዱና የበረከቱ ተካፋዮች ከዚህ በታች በተገለጸው የሂሳብ ቁጥር ገቢ በማድረግ የባንክ ደረሰኙንና የክርስትና ስማችሁን ለኩልን አባቶች በጻሎት እንድያስቦችሁ ። የህንፃ አሳሪ ኮሚቴ የባንክ አካውንት ቁጥር፦ 1,#የኢትዮጵያ_ንግድ_ባንክ፦ #1000624326281 የጎፎሬ ደብረ መንክራት በኣታ ለማርያም ህንፃ አሰሪ (Gofere D/M/B/Mariam B/k Hintsa Ase) 2, #ዓባይ_ባንክ፦ #3621111079916110 (አጭር ቁጥር 10799161) የጎፎሬ ደብረ መንክራት በኣታ ለማርያም ህንፃ አሰሪ ኮሚቴ (Gofere/B/K/Hin/Aseri Comite) ?? #ለበለጠ_መረጃ፦ የህንጻ አሰሪ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዲያቆን ደግነት፦ #0933055802፣ #0911414852። ❤በእንተ ስማ ለማርያም ❤
نمایش همه...
👍 1
1.6 ሚሊዮን ብር ለኛ ኦርቶዶክሳዊያን ማሰባሰብ ያቅተን ይኾንን !? 1000235717089 ባለቤታቸው ወ/ሮ ወርቅነሽ ደምሌ የኢትዮጲያ ንግድ ባንክ። #ዐይናችን_ካህኑ_ታሞአል ❝“ የቋቋም ፣ የቅዳሴ ፣ የድጓ ፣ ጾመ ድጓ ፣ የቅኔው ዘራፊ ፣ ዳባ ለባሽ ግስ ገሳሽ የመቅደሱ መቅረዝ ፣ የምእመናን ብርሃን ክህነት ከሊቅነት አስተባብረው የያዙት ቀሲስ #ልሳነ_ወርቅ #ከ7ኛፎቅ ወድቀው ይኾው #10ዓመት በዊልቼር ላይ ፤ እናም በደረሰባቸው ከፍተኛ አደጋ በአገረ #ጀርመን እንዲታከሙ የእኛን ዕርዳታ በእጅጉ ይጠይቃሉ ። ሰብዐዊነት የሚሰማችኹ በሙሉ እንረባረብ ! ❝ ተዘከሩ መኳንንቲክሙ ዘነገረክሙ ቃለ እግዚአብሔር ❞ ፤ የእግዘብሔርን ቃል የነገሯችሁን ፣ ሥርዐት ፣ ምግባር ፣ ሃይማኖት የነገሯችሁን ዋኖቻችሁን ዐስቡ ❨ ዕብ .13 ÷ 7*❩ ። ✝️ ⛪️◈⛪️ ✝️ @KaleEgziabeher
نمایش همه...

👍 4
💒💒💒       #የ2016 ፆመ_ሐዋርያት (#ሰኔ_ፆም) ✍✍✍✍✍✍✍✍✍✍✍✍ 👉ይህ ፆም ከቤተ ክርስቲያናችን የአዋጅ ፆሞች ውስጥ አንዱ ሲሆን ቅዱሳን ሐዋርያት ጌታቸንን ምሣሌ አድርገው የጾሙት ፆም ነው። 💒 የሰኔ ፆም :- ይህ ፆም የሀዋርያት ፆም በመባል ይታወቃል ስለ ምን የሐዋርያት ፆም ተባለ ቢሉ በበአለ ጴራቅሪጦስ ሀዋርያት መንፈስ ቅዱስን ከተቀበሉ በዉሀላ የፆሙት ፆም ስለሆነ ነው። 👉የሰኔ ዖም የሚፆምበት ጊዜያት የሰኔ ፆም ቢያንስ 15 ቢበዛ 45 ቀናት ያህል ይፆማል የሰኔ ፆምን እስከ 9 ሰአት እንድንፆም ቤተክርስቲያን አውጃለች ። 💒  የሚገባበት ቀን በየአመቱ የተለያየ ቢሆንም የፆሙ ማብቂያ ዕለት ግን ሐምሌ 5 ድረስ ነው ። ሐምሌ 5 ሁለቱ ሀዋርያት ጴጥሮስ እና ጳዉሎስ ሰማዕትነትን የተቀበሉበት እለት ነው ።   💒 ቅዱሳን ሐዋርያት የአምላካቸውን የመምህራቸውን አርአያ ተከትለው እርሱ ወደ ማዳን ሥራው ማለትም ህሙማነ ሥጋን በተዓምራት ሕሙማነ ነፍስን በትምህርት ከማዳን አስቀድሞ የስራውን መጀመሪያ በገዳመ ቆሮንቶስ ገብቶ 40 ቀን 40 ሌሊት እንደ ጾመና እንደጸለየ ሁሉ ቅዱሳን ሐዋርያትም አብነቱን ተከትለው ጾመዋል፡፡ ጸጋ መንፈስ ቅዱስን ከተቀበሉ በኋላ ዓለምን ዕጣ ተጣጥለው (ተከፈፍለው) ዞረው ከማስተማራቸው አስቀድመው የሥራቸው መጀመሪያን ጾምን አድርገዋል፡፡ 👉ሐዋርያትም ይህንን ጾም እንደሚጾሙ ጌታችን አስቀድሞ የዮሐንስ ደቀመዛሙርት ወደ እርሱ ቀርበው በጠየቁት ጊዜ ተናግሮ ነበር፡፡ ‹‹ እኛና ፈሪሳውያን ብዙ ጊዜ የምንጦመው ደቀመዛሙርትህ ግን የማይጦሙት ስለምንድን ነው? አሉት ኢየሱስም እንዲህ አላቸው ሚዜዎች ሙሽራው ከእነርሱ ጋር ሳለ ሊያዝኑ ይችላሉ? ነገር ግን ሙሽራው ከእነርሱ የሚወስድበት ወራት ይመጣል በዚያን ጊዜም ይጦማሉ›› ማቴ 9፥15-16 💒 እኛም ይህን ጾም የምንጾመው የሐዋርያትን በረከት ለመላበስ፣ እነርሱ ድል ያደረጉትን ዓለም እንድናሸንፈው አምላካችንን ለመማጸን በመሆኑ ይህንን ‹‹መሣሪያ›› አንጣለው ጾሙም ለመላው ክርስቲያን የተሰጠ ነው። አንድ አንዶች እንደሚሉት የቀሳውስት ብቻ አይደለም ለቄስና ለምዕመናን ተብሎ በክህነት ደረጃ የተለየ ጾምም የለም፡፡   💒 ፆሙን የበረከት ፆም ያድርግልን በሰላም ያድርሰን!!!
نمایش همه...
👍 12
ሰኔ 12 ቅዱስ ሚካኤል ቅድስት አፎምያ ያዳነበት ዕለት ሰኔ 12 ቀን ቅድስት አፎምያ የቅዱስ ሚካኤልን መታሰቢያ እያዘጋጀች ሳለች ሰይጣን ብርሃናዊ መልአክ መስሎ መጣ፡፡ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል እንደሆነ ገልጾ ሰይጣናዊ ምክሩን አሰማምሮ አቀረበላት፡፡ አሳቡንም የእግዚአብሔር ፈቃድና አሳብ እንደሆነ አድርጎ ለማሳመን ሞከረ፡፡ ሰይጣን አስቀድሞ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በገዳመ ቆሮንቶስ መጻሕፍትን እየጠቀሰ እንደተፈታተነው ሁሉ ቅድስት አፎምያንም ለማሳመንም አብርሃምን፣ ይስሐቅን፣ ያዕቆብን፣ ዳዊትን የመሳሳሰሉትን እየጠቀሰ ለማሳመን ቢሞክርም ቅድስት አፎምያ ቅዱስ ሚካኤል ከሆንክ በትረ መስቀልህ የታለ ብላ የቅዱስ ሚካኤል ስእል ቤቷ ነበረና ቅዱስሚካኤል ከሆንክ ይህ ያንተ ስእል ነውና ተሳለመው አለችው እሱም ተናዶ ዘሎ አነቃት ያንጊዜ ቅዱስ ሚካኤል ከሰማያት ወርዶ በበትረ መስቀሉ ቀጥቅጦ በጦሩ ወግቶ ሠይጣንን ድል ነስቶ አፎምያን ከእደ ሰይጣን አድኗታል እኛንም መላኩ ቅዱስ ሚካኤል ከሰይጣን አሽከላ ይጠብቀን፡፡ እስራኤላውያን በግብፃውያን ለ430 ዓመታት ከተገዙ በኋላ እግዚአብሔር ይቅር አላቸው።ሙሴን መሪ አድርጎ ነፃ እንዲወጡ አደረገ ታዲያ በጉዞ ላይ ሳሉ ፈርኦን በቁጣ ተከተላቸው ።እግዚአብሔር መልዓኩን ሚካኤልን ላከው።እርሱም ባሕር ከፍሎ መንገዱን እየመራ ወደ ከነዓን አገባቸው።በሐዲስ ኪዳንም በአማላጅነቱ የሀጥያትን ባሕር ከፍሎ ያሻግረን። ህዳር12 ባህርን ከፍሎ እስራኤልን ያሻገረበት ፈርኦንን ከነሰራዊቱ ያሰጠመበት ነው። ዛሬ እኛንም ከጠላት ዲያቢሎስ አድኖ ዘረኝነትንና ጥላቻን አጥፍቶ ሀገራችንን ሰላም ያድርግልን። #አሜን_አሜን_አሜን 🙏 🙏🙏
نمایش همه...
👍 18
Photo unavailableShow in Telegram
እንኩዋን ለብርሀነ ዕርገቱ በሰላም አደረሳችሁ ። "ዐርገ በስብሐት ውስተ ሰማያት ወነበረ በየማነ አቡሁ፣ በክብር በምስጋና ወደ ሰማይ ዐረገ በአባቱም ቀኝ ተቀመጠ"  ( ጸሎተ ሃይማኖት ) ። እንደ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አስተምህሮ መሰረት  በዐለ ዕርገት  ከጌታችን ከመድሃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ  ዘጠኙ በዐላት አንዱና ዋንኛው በዐል ነው። በዓለ ዕርገት ጌታችን አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መቃብር ክፈቱልኝ መግነዝ ፍቱልኝ ሳይል  ከሙታን ከተነሣ በኋላ ለዐርባ ቀናት በግልጽም በስውርም ለቅዱሳን ሐዋርያትና ለቅዱሳት አንስት መጽሐፈ ኪዳንን ፣ ትርጓሜ መጻሕፍትን ፣ ምሥጢራትን ፣ ሕግጋትንና ቀኖናተ ቤተ ክርስቲያንን ሲያስተምር ቆይቶ ወደ ቀደመ ዙፋኑ ወደ ሰማይ በክብር በምስጋና ማረጉን የሚነገርበት ታላቅ ዕለት ነው ። ጌታችን መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን ድል አድርጎ መቃብር ክፈቱልኝ መግነዝ ፍቱልኝ ሳይል ከተነሳ በኋላ ለ39 ቀናት ያህል ለቅዱሳን ሐዋርያት አባቶቻችን  በተለያየ ጊዜ እየተገለጠ ስለ እግዚአብሔር መንግስት ምስጢር እያስተማራቸው ከቆየ በኋላ በ40ኛው ቀን ወደ ሰማይ አረገ ። ያረገበትም ቦታ ቢታንያ አጠገብ ደብረ ዘይት ተራራ ላይ ነው ። 11ዱን  ቅዱሳን  ሐዋርያት ደብረ ዘይት ተራራ  ድረስ ከወሰዳቸው በኋላ ባርኳቸው እያዩት ዐርጓል ። ወደ ቀደመ ክብሩ፤ በመለኮታዊ ክብሩ ወደ ሰማይ አርጎ በአባቱ ቀኝ ተቀመጧል " አንትሙሰ ንበሩ ሐገረ ኢየሩሳሌም እስከ ትለብሱ ኀይለ እምአርያም ፣ እናንተ ግን ከላይ ኃይል እስክትለብሱ ድረስ በኢየሩሳሌም ከተማ ቆዩ። እስከ ቢታንያም አወጣቸው እጆቹንም አንሥቶ ባረካቸው። ሲባርካቸውም ከእነርሱ ተለየ ወደ ሰማይም ዐረገ" ( ሉቃ. 24፥48-51) " በዚህ ጊዜ  ደመና ከዓይናቸው ሰውራ ተቀበለችው። በእግዚአብሔርም ቀኝ ተቀመጠ።   "እያዩት ወደሰማይ ዐረገ”(ሉቃ .24÷50 ፣ሐዋ .1÷9) "ዐረገ እግዚአብሔር በይባቤ፤ ወእግዚእነ በቃለ ቀርን፤ ዘምሩ ለአምላክነ ዘምሩ፣ እግዚአብሔር አምላክ ብእልልታና በመለከት ድምጽ ወደ ሰማይ አረገ ዘምሩ ለአምላካችን ዘምሩ" ( መዝ . 46፥5-6) ጌታችን መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን ድል አድርጎ መቃብር ክፈቱልኝ መግነዝ ፍቱልኝ ሳይል በተነሣ በ40 ኛው ቀን ያረገውም በለበሰው ሥጋ በመሆኑ እና ለሁለተኛ ጊዜ ለፍርድ በሚመጣበት ጊዜ ይህን ክብር እኛም  እንድናገኝ ሊያስተምረን ነው። " በሚመጡ ዘመናትም በክርስቶስ ኢየሱስ ለእኛ ባለው ቸርነት ከሁሉ የሚበልጠውን የጸጋውን ባለ ጠግነት ያሳይ ዘንድ፥ ከእርሱ ጋር አስነሣን በክርስቶስ ኢየሱስም በሰማያዊ ስፍራ ከእርሱ ጋር አስቀመጠን። (ኤፌ .2፥6 ፣ ዮሐ .12፥32) " ወላጆች እንደ ሌላቸው ልጆች አልተዋችሁም፤ ወደ እናንተ እመጣለሁ " ።( ዮሐ . 14፥18) " እኔ ግን እውነት እነግራችኋለሁ፤ እኔ እንድሄድ ይሻላችኋል። እኔ ባልሄድ አጽናኙ ወደ እናንተ አይመጣምና፤ እኔብሄድ ግን እርሱን እልክላችኋለሁ።( ዮሐ . 16፥7) ነቢዩ ዳንኤል ስለ ጌታችን ዕርገት እና በአብ ቀኝ ስለመጡ  " በሌሊት ራእይ አየሁ፤ እነሆም፥ የሰው ልጅ የሚመስል ከሰማይ ደመናት ጋር መጣ በዘመናት ወደ ሸመገለውም ደረሰ፤ ወደ ፊቱም አቀረቡት ወገኖችና አሕዛብ በልዩ ልዩ ቋንቋም የሚናገሩ ሁሉ ይገዙለት ዘንድ ግዛትና ክብር መንግሥትም ተሰጠው ግዛቱም የማያልፍ የዘላለም ግዛት ነው መንግሥቱም የማይጠፋ ነው " ( ዳን .7፥13-14) ጌታ ኢየሱስም ከእነርሱ ጋር ከተናገረ በኋላ ወደሰማይ ዐረገ በእግዚአብሔርም ቀኝ ተቀመጠ። (ማር. 16፥9-19) ቅዱስ ሉቃስ ስለ ጌታችን መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዕርገት ሲጽፍ እንዲህ ብሎአል ፦ " ደግሞ አርባ ቀን እየታያቸው ስለ እግዚአብሔርም መንግሥት ነገር እየነገራቸው፥ በብዙ ማስረጃ ከሕማማቱ በኋላ ሕያው ሆኖ ለእነርሱ ራሱን አሳያቸው። ከእነርሱም ጋር አብሮ ሳለ ከኢየሩሳሌም እንዳይወጡ አዘዛቸው፥ ነገር ግን። ከእኔ የሰማችሁትን አብ የሰጠውን የተስፋ ቃል ጠብቁ፤ ዮሐንስ በውኃ አጥምቆ ነበርና፥ እናንተ ግን ከጥቂት ቀን በኃላ በመንፈስ ቅዱስ ትጠመቃላችሁ አለ። እነርሱም በተሰበሰቡ ጊዜ። ጌታ ሆይ፥ በዚህ ወራት ለእስራኤል መንግሥትን ትመልሳለህን? ብለውጠየቁት። እርሱም አብ በገዛ ሥልጣኑ ያደረገውን ወራትንና ዘመናትን ታውቁ ዘንድ ለእናንተ አልተሰጣችሁም፤ ነገር ግን መንፈስ ቅዱስ በእናንተ ላይ በወረደ ጊዜ ኃይልን ትቀበላላችሁ፥ በኢየሩሳሌምም በይሁዳም ሁሉ በሰማርያም እስከ ምድርዳርም ድረስ ምስክሮቼ ትሆናላችሁ አለ። ይህንም ከተናገረ በኋላ እነርሱ እያዩት ከፍ ከፍ አለ፤ ደመናም ከዓይናቸው ሰውራ ተቀበለችው እርሱም ሲሄድ ወደ ሰማይ ትኵር ብለው ሲመለከቱ ሳሉ  እነሆ ነጫጭ ልብስ የለበሱ ሁለት ሰዎችበአጠገባቸው ቆሙ ደግሞም የገሊላ ሰዎች ሆይ ወደስማይ እየተመለከታችሁ ስለ ምን ቆማችኋል? ይህ ከእናንተ ወደሰማይ የወጣው ኢየሱስ ወደ ሰማይ ሲሄድ እንዳያችሁት፥ እንዲሁ ይመጣል አሉአቸው። (ሐዋ.1፥3-11)  ቅዱስ ጳውሎስም ስለ ጌታችን እርገት እንዲህ ሲል ይመክረናል " እንግዲህ ከክርስቶስ ጋር ከተነሣችሁ ክርስቶስ በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀምጦ ባለበት በላይ ያለውን እሹ በላይ ያለውን አስቡ እንጂ በምድር ያለውን አይደለም ሞታችኋልና ሕይወታችሁም በእግዚአብሔር ከክርስቶስ ጋር ተሰውሮአልና  ሕይወታችሁ የሆነ ክርስቶስ በሚገለጥበት ጊዜ በዚያን ጊዜ እናንተ ደግሞ ከእርሱ ጋር በክብር ትገለጣላችሁ ( ቆላ. 3፥1-4 ) "ሥፍራ  አዘጋጅላችሁ ዘንድ እሄዳለሁ"  (ዮሐ.14፥2) በድጋሜ  እንኳን ለብርሃነ ዕርገቱ በሰላም አደረሳችሁ!!
نمایش همه...
👍 9
የዕርገት በዓል የሚከበርባቸውን 11 ገዳማትና አድባራት እንጠቁምዎ፡፡ ሰኔ 6፤ #በዓለ_ዕርገት፡፡ #በአዲስ_አበባ_የዕርገተ_እግዚእነ_ኢየሱስ_ክርስቶስ_ክብረ_በዓል_የሚከበርባቸው_ #7 #ገዳማትና_አድባራት፡፡ ፩. ማኅደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያምና ደብረ መድኀኒት መድኀኔዓለም ቤ/ን፤ አድራሻው፤ ልደታ ክፍለ ከተማ፥ ልደታ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መርካቶ) → ሜክሲኮ → ጦር ኃይሎች፤ ፪. ፈረንሳይ ገነተ ኢየሱስና ገነተ ማርያም ቤ/ክ (እናትና ልጇ)፤ አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ፈረንሳይ ሌጋሲዮን፥ 41 ኢየሱስ፤ ታክሲ፤ ከ4ኪሎ (6 ኪሊ) → 41 ኢየሱስ/ፈረንሳይ/ ፫. ገዳመ ኢየሱስ ቤ/ክ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፤ ታክሲ፤ ከመርካቶ → ኮልፌ፡፡ ወይም ከጦር ኃይሎች ዊንጌት/አስኮ/ → (በሚል ታክሲ) (በቀለበት መንገድ) ፬. አቃቂ መንበረ ሕይወት መድኀኔዓለም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ጋራው መድኀኔዓለም፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መርካቶ) (ለገሀር) (መገናኛ) (ቦሌ) → አቃቂ/ቃሊቲ ፭. መካኒሳ ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ፥ መካኒሳ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → መካኒሳ ፮. ጃቲ መካነ ሕይወት ኪዳነ ምሕረት ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ 08፥ ጃቲ፡፡ ታክሲ፤ ከፒያሳ(ከቦሌ) → ቃሊቲ → ጃቲ (አቃቂ በሚለው ታክሲ)፡፡ ፯. የካ ኮተቤ ደብረ ምሕረት ኪዳነ ምሕረትና መድኀኔዓለም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ወረዳ 9፡፡ ታክሲ፤ ከፒያሳ(መገናኛ) → ኮተቤ ወረዳ 9፡፡ ፰. ብርሃናተ ዓለም ቅዱስ ጴጥሮስ ወጳውሎስ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ጉለሌ ክፍለ ከተማ፥ ዊንጌት፤ ትራንስፖርት፤ ከፒያሳ አቡነ ጴጥሮስ → አስኮ/ዊንጌት/፤ ፱. ጀሞ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ነፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ፥ ጀሞ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (ሜክሲኮ) → ጀሞ፡፡ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ¤¤¤¤¤¤¤¤¤¤¤¤¤¤¤¤¤¤¤¤¤¤¤¤¤ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ከአዲስ አበባ ውጪ የሚከበርባቸው፤ ፩. መንዝ ዕመጓ ደብረ ቆጵሮስ ቅዱስ ኡር(ራ)ኤል ገዳም፤ አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ መንዝ ሞላሌ፥ ዕመጓ፡፡ ታክሲ፤ ከላምበረት መናኸርያ→ መንዝ ሞላሌ →ዕመጓ፡፡ ፪. አምቦ ኢየሱስ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ አምቦ ከተማ፡፡ ታክሲ፤ ከአስኮ መናኸርያ→ አምቦ፡፡ / #ክብረ_በዓላት #Feasts / / #ገዳማትና_አድባራት #Monasteries_and_Churches /
نمایش همه...
👍 6
ዕርገተ ክርስቶስ፤ እንኳን ለብርሃነ ዕርገቱ አደረሳችሁ (ሰኔ 06 2016)      ዕርገት ከታች ወደ ላይ፥ከምድር ወደ ሰማይ መውጣት ማለት ነው።ቅዱስ ዳዊት፡-የጌታ ርደቱን (ከሰማይ ወደ ምድር መውረዱን) በመዝሙረ ትንቢት እንደ ተናገረ ሁሉ ነገረ ዕርገቱንም ተናግሯል።ይኸንንም:-“እግዚአብሔር በእልልታ፥ ጌታችንም በመለከት ድምጽ ዐረገ፥ዘምሩ ለአምላካችን ዘምሩ፤” በማለት የራቀውን አቅርቦ፥ የረቀቀውን አጉልቶ በመንፈስ ዘምሯል።መዝ፡፵፮፥፭      ይህ ትንቢት የሚፈጸምበት ሰዓት በደረሰ ጊዜም ጌታ ከሙታን ተለይቶ በተነሣ በአርባኛው ቀን ደቀ መዛሙርቱን አስከትሎ ወደ ቢታንያ ሄዷል። በአንብሮተ እድም ባርኳቸዋል (ሹሟቸዋል)። እየባረካቸውም ራቃቸው፥ወደ ሰማይም ዐረገ። (ዕርገቱ በርህቀት እንጂ በርቀት አልነበረም)።ሉቃ፡፳፬፥፶።      ከዚያ በፊት ትንሣኤውን እርግጠኞች እንዲሆኑ በተለያየ ቦታ እየተገለጠ ተዳስሶላቸዋል፥አብሯቸው በልቷል፥ጠጥቷል፥ምሥጢረ መጻሕፍትን ገልጦላቸዋል።መጽሐፈ ኪዳንንም አስተምሯቸዋል ።“ኢየሱስ የመረጣቸውን ሐዋርያትን በመንፈስ ቅዱስ ካዘዛቸው በኋላ እስከ ዐረገበት ቀን ድረስ ያደርገውና ያስተምረው ዘንድ፥ ዐርባ ቀን እየታያቸው፥ስለ እግዚአብሔርም መንግስት ነገር እየነገራቸው፥በብዙ ማስረጃ ከሕማማቱ በኋላ ሕያው ሆኖ ለእነርሱ ራሱን አሳያቸው።”ይላል።የሐዋ ፩፥፫።       የጌታ ዕርገቱ በትንቢት የተነገረ፥በቅዱሳን መላእክትና በቅዱሳን ሐዋርያት የተመሰከረ ነው።እነርሱ በእውነት የዓይን ምስክሮች ናቸውና።የሐዋ፡፩፥፱-፲፩።ስለሆነም ዕርገቱ የታመነ ነው ።ሊቁ ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ዕርገቱ ፍጹም የታመነ መሆኑን ሲያስረዳ “ሕማም የሚስማማውን ግዙፍ ሥጋን ተዋሕዶ ሳለ ከስቅለቱ አስቀድሞ በባሕር ላይ ከሄደ፥ዛሬ ነፋስን ከፍሎ ሲያርግ ቢታይ ማንም ማን አይጠራጠር፤ሥጋው አልተለወጠምና።”ያለው ለዚህ ነው።ሃይ፡አበው፡ክፍል ፲፫፥፲፭።     የጌታ ጥንተ ዕርገቱ ሐሙስ ግንቦት ፰ ቀን ፴፬ ዓ.ም. በዘመነ ማርቆስ ነበር። @KaleEgziabeher
نمایش همه...

یک طرح متفاوت انتخاب کنید

طرح فعلی شما تنها برای 5 کانال تجزیه و تحلیل را مجاز می کند. برای بیشتر، لطفا یک طرح دیگر انتخاب کنید.