TheDeepThingsOfGod
رفتن به کانال در Telegram
1 810
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز
آرشیو پست ها
1 810
የ Smith wigglesworth የልጅ ልጅ ስለ አያቷ የተናገረችው እና እ.እ.አ በ 1939 ስለሚመጣው የመንፈስ ቅዱስ እንቅስቃሴ የተናገረውን....
#ስሙት! 3.8 MB ብቻ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
🦋🔥ፍጹም ለውጥ/transfiguration🔥🦋
ክርስቲያን ወንድሞቼ እና እህቶች በአእምሮአችን የምንታደስ ከሆነና በእርሱ(በክርስቶስ) የነበረውን ሃሳብ በእኛም እንድኖር የምናደርግ ከሆነ ፍጹም ለውጥን መለማመድ እንችላለን!
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
....የትውልድ ቦታ፤ ቤተሰብ፤ የቆዳ ቀለም፤ ቋንቋ ወዘተ...በአለም በተለያዩ ሰዎች መካከል ላሉ የአኗኗር ልዩነቶች የራሳቸው የሆነ አስተዋጽኦ አለቸው። በዋናነት ግን ልዩነቱን የፈጠረው እውቀት ነዉ። በልጽገዋል፤ አድገዋል ሆኖላቸዋል የምንላቸው ሰዎችም ሆኑ ሃገራት አልበለፀጉም፤ ድሆች ናቸው የሚባሉት ያላወቁትን የእውቀት ክልል ያገኙ ናቸዉ። ባደጉና ባላደጉት፤ በበለጸጉና ባልበለጸጉት፤ በተለወጡና በልተለወጡ መካከል ያለው ልዩነት የቆዳ ቀለም ወይም የትውልድ ሃረግ ሰይሆን የእውቀት ነዉ! የአስተሳሰብ ነዉ። እውቀትን አግኙ።
እኛ ግን ደግም የተወለድን ዓለም ያላወቀችውን የእግዚአብሔርን ሚስጥር እርሱም ክርስቶስን አውቀናል! ታድያ እንዴት እንብዛም? ታድያ እንዴት? እንዴትስ አንገዛም? ክብር ለእግዚአብሔር ይሁን እንበዛለን! እንገዛለን! የእግዚአብሔር ሚስጥር የሆነውን ኢየሱስ ክርስቶስን በጥልቀት ለማወቅ እንትጋ: ሕይወታችን ነዉና።
“በእውቀት ከከበረውና ካማረው ሀብት ሁሉ ጓዳዎች ይሞላሉ።”
— ምሳሌ 24፥4
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
ይህንን ከእኔ ጋር ተናገሩ!!!😍🔥
ከእግዚአብሔር ተወልጃለሁ! ከእግዚአብሔር ተወልጃለሁ! የእግዚአብሔር ልጅ ነኝ! የእግዚአብሔር ዘር በእኔ አለ! ዓለምንና በዓለም ያለውን ሁሉ አሸንፌያለሁ! በፍጹም የኃጢአት የሰይጣን እና የሞት ባሪያ አይደለሁም! ውስጥና ላዬ በክርስቶስ ተሸፍኗል!
ሕይወቴ የእግዚአብሔር ነዉ! ፍጹም የሆነ ሕይወት ሆኖልኛል: በመንፈስ ቅዱስ እየተመራሁ እና በፍቅር እየኖርኩ የመንፈስን ፍሬ አፈራለሁ! በእምነት እመላለሳለሁ በተስፋ እደሰታለሁ!
በእሳትና🔥በሃይል💪 እናገራለሁ የክርስቶስ መገለጫ የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ የእግዚአብሔር ሚስጢር መጋቢ ነኝ! በዙዎችን ለክርስቶስ አሸንፋለሁ! ዓለም የለሌት እኔ አለኝ: የልብ ሰላም ጽድቅ እና የመንፈስ ቅዱስ ሐሴት የእኔ ሆነዋል! የእግዚአብሔር በረከት በእኔ በጻድቁ ራስ ላይ ነዉ! አለመሳካት አልችልም!
ስለሁሉም እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ: አሜን አሜን! በመጨረሻም የእሳት ልሳን ይቀጥሉበት...😁
አስተውሉ ይህ ምላሳችን ላይ አይደለም ያለው: እኛ ይህ ነን!!!
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ልጆች ጸሎታችን ነገሮችን መለወጥ እንደምችል ታውቃላችሁ? “ትፈወሱም ዘንድ እያንዳንዱ ስለ ሌላው ይጸልይ፤ የጻድቅ ሰው ጸሎት በሥራዋ እጅግ ኃይል ታደርጋለች።”
— ያዕቆብ 5፥16
ይሄንን መልእክት የምታነቡ ሁሉ ስለ ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ + አብሮ-ሰራተኞቻቸው ለሆኑ የፖሎቲካ ሰዎች ወደ እግዚአብሔር ልመናችሁን አድርሱ። እንደ አማኝ ስለ ሀገር መሪዎች እና ስለ ሕዝባችን መጸለይ አንዱ ተግባራችን ነዉ። “እንግዲህ እግዚአብሔርን በመምሰልና በጭምትነት ሁሉ ጸጥና ዝግ ብለን እንድንኖር፥ ልመናና ጸሎት ምልጃም ምስጋናም ስለ ሰዎች ሁሉ ስለ ነገሥታትና ስለ መኳንንትም ሁሉ እንዲደረጉ ከሁሉ በፊት እመክራለሁ።”
— 1ኛ ጢሞቴዎስ 2፥1-2
👉የጸሎት ነጥቦች (prayer point)
1-ግድያዎችን በመቃወም ጸልዩ! ( PRAY against assassinations!)
2-የድካምን መንፈስ በመቃወም ጸልዩ!
3-አብሮ ሰራተኞች ጥበብ እንድበዛላቸው ጸልዩ!
4-ሃሰተኛ ውንጀላን በመቃወም ጸልዩ! (PRAY against false accusations)
5-ቁስሎች እንዲፈወሱ ጸልዩ።(pray for the healing of the wounds!)
....እኛ ስንጸልይ እግዚአብሔር ይሰራል....አሜን!
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
ወዳጆቼ ስለ እግዚአብሔር ቃል እና ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ምስክር መከራ ከተቀበላችሁ ታተርፋላችሁ: እግዚአብሔር መልሶ ይከፍላችኋል! ነገር ግን ከእነዚህ ምክንያቶች በተለየ ምክንያት መከራ እየተቀበላችሁ ከሆነ የእግዚአብሔር ፈቃድ አይደለም! እግዚአብሔርም እናንተም አታተርፉም!
👉በሽታ የእግዚአብሔር ፈቃድ አይደለም!
👉ውድቀት የእግዚአብሔር ፈቀዳ አይደለም!
👉ማጣት የእግዚአብሔር ፈቃድ አይደለም!
👉ኃጢአት የእግዚአብሔር ፈቃድ አይደለም!
👉ጭንቀት የእግዚአብሔር ፈቃድ አይደለም!
👉ፍርሃት የእግዚአብሔር ፈቃድ አይደለም!
👉ሞት የእግዚአብሔር ፈቃድ አይደለም!
....ስለዚህ ከላይ በሉት ነገሮች ምክንያት በመከራ ውስጥ እያለፍን ከሆነ የእግዚአብሔር ፈቃድ አለመሆኑን በማወቅ መቃወም እና ዘፀአት ማድረግ አለብን....
....የሰውን ከንቱን አመለካከት እየሰማን መሳት የለብንም ለእኛ ትርጉም የሚሰጠን የእግዚአብሔር ቃል ብቻ ነዉ! የምንሰማው የእግዚአብሔርን ቃል ብቻ ነዉ......
#እውነት_ነጻ_ያወጣል!
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
...ክርስቲያን መከራ ልደርስበት ይችላል? ጥያቄ የለውም ክርስቲያን መከራ ልደርስበት ይችላል! ነገር ግን ክርስቲያን መከራ ከተቀበለ መቀበል ያለበት ስለ እግዚአብሔር ቃልና ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ምስክርነት ብቻና ብቻ ነዉ! ክርስቲያን ከእነዚህ ምክንያቶች ውጪ መከራ የሚቀበል ከሆነ በአዲስ ኪዳን የተገለጠ የእግዚአብሔር ፈቃድ አይደለም! ነገር ግን ስለ እግዚአብሔር ቃል ወይም ደግሞ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ስለምንሰጠው ምስክርነታችን መከራ ቢደርስብን እሰየው የሚያሰኝ ነዉ! ምክንያቱም ዘላለማዊ ትርፍ አለው!
እውነቱን ልንገራችሁ ከእነዚህ ከሁለት ምክንያቶች ውጪ በመከራ ውስጥ ካላችሁ ወይም እየተሰቃያችሁ ከሆነ: እውነት እውነት እላችኋለሁ የእግዚአብሔር ፈቃድ አይደለም! ሰይጣንም ሆነ ሰው አዲስ ኪዳናዊ ያልሆ ወሬ እያወራ እንድያስታችሁ አትፍቀዱ: ተነሱና ተቃወሙት! ተቃወሙት! በኢየሱስ ስም ተቃወሙት! ከእናንተም ይሸሻል!
“የእግዚአብሔር ፈቃድ እርሱም በጎና ደስ የሚያሰኝ ፍጹምም የሆነው ነገር ምን እንደ ሆነ ፈትናችሁ ታውቁ ዘንድ በልባችሁ መታደስ ተለወጡ እንጂ ይህን ዓለም አትምሰሉ።”
— ሮሜ 12፥2
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
ጥያቄ ሦስት:-
ክርስቲያን መከራ መቀበል አለበት? መልሳችሁ አዎ! ከሆነ በምን ምክንያት? መጽሐፍ ቅዱሳዊ መልስ ስጡኝ።
Comment section ውስጥ መልሳችሁን አስቀምጡ።
1 810
🔥እንደገና ሙላኝ! እንደገና!🔥
መንፈስ ቅዱስ የእውነት መንፈስ!
(በዚህ መዝሙር መንፈስ ቅዱስን አውሩት)
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
የወደዳችሁን እወቁ! ከአሸናፊዎች ትበልጣላችሁ!
“በእኔ ሳላችሁ ሰላም እንዲሆንላችሁ ይህን ተናግሬአችኋለሁ። በዓለም ሳላችሁ መከራ አለባችሁ፤ ነገር ግን አይዞአችሁ፤ እኔ ዓለምን አሸንፌዋለሁ።”
— ዮሐንስ 16፥33
"አይዞአችሁ፤ እኔ ዓለምን አሸንፌዋለሁ።" ያለ ወዳጅ አለን! ዓለምን ያሸነፈ ወዳጅ አለን: ይህ ተስፋ የሚሰጥ ብቻ ሰይሆን እኛንም አሸናፊዎች የሚያደርገን ነዉ። ክብር ለወዳጃችን ይሁን! በሌላ ምክንያት ሰይሆን እግዚአብሔርን ለመምሰል በምናደርገው ጉዞ ውስጥ መሰደድ እና መከራ አለ: በዚህ ሁሉ ግን በወደደን በእርሱ ከአሸናፊዎች እንበልጣለን!
ለእውነተኛ ክርስቲያን ከጦርነት ነጻ ቀጠና የለም! እግዚአብሔር በፍጹም ጦርነት አይኖርባችሁም የሚል ተስፋ አልሰጠንም ነገር ግን “...እኔ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ።” በማለት ራሱን ሰጥቶናል! ከእኛ ጋር ነዉ! ድል ከፊታችን አለ! አሜን! አሜን!
.......ከአሸናፊዎች ትበልጣላችሁ.......
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
#የእግዚአብሔር_ልጆች_በሕይወታችሁ_ላይ_በስልጣን_እናገራለሁ!
ከዚህ ቀን ጀምሮ ሕይወታችሁ የሆነ ክርስቶስ ይገለጥላችኋል! የልብ አይኖቻችሁ ላይዘጉ ይከፈታሉ! በውስጣችሁ ያለውን የእግዚአብሔርን ሃይል ማወቅ ይሆንላችኋል! በዘመናችሁ ሁሉ ወደ ፊት እና ወደላይ ብቻ ትሄዳላችሁ! በሕይወታችሁ ያለውን የእግዚአብሔርን አጀንዳ ትፈጽማላችሁ! ሰማያዊ አቅርቦት በአናታችሁ ላይ ነዉ! የራዕይ ረዳቶቻችሁ ሁሉ ከሉበት በመንፈስ ስበት ተስበው አሁን ወደ ሕይወታችሁ ይቅረቡ!! በኢየሱስ ክርስቶስ ስም! አሜን!
1 810
📖የእግዚአብሔር ቃል📖
... ክፍል ስድስት...
❤የእግዚአብሔር ቃል ውጤቶች❤
1-የእግዚአብሔር ቃል የእምነት ምንጭ ነዉ።
“እንግዲያስ እምነት ከመስማት ነው መስማትም በእግዚአብሔር ቃል ነው።”
— ሮሜ 10፥17
እምነታችሁ ከፍ እንድል ትፈልጋላችሁ? ወደ እግዚአብሔርን ቃል ሂዱ: አንብቡት አሰላስሉት እመኑ ለራሳችሁ ተናገሩት።
2-የእግዚአብሔር ቃል አድስ ልደት ያስገኛል።
“ለፍጥረቱ የበኵራት ዓይነት እንድንሆን በእውነት ቃል አስቦ ወለደን።”
— ያዕቆብ 1፥18
አንድ ሰው የእግዚአብሔርን ቃል ስያገኘው አድስ ሕይወት ይጀምራል።
3-መንፈሳዊ መብል ነዉ።
“ጌታ ቸር መሆኑን ቀምሳችሁ እንደ ሆነ፥ ለመዳን በእርሱ እንድታድጉ አሁን እንደ ተወለዱ ሕፃናት ተንኰል የሌለበትን የቃልን ወተት ተመኙ።”
— 1ኛ ጴጥሮስ 2፥2-3
“ጠንካራ ምግብ ግን መልካሙንና ክፉውን ለመለየት በስራቸው የለመደ ልቡና ላላቸው ለፍጹማን ሰዎች ነው።”
— ዕብራውያን 5፥14
(....በመንፈሳዊ ህይወት ማደግ የሚፈልግ ሰው ምን ማድረግ አለበት? ከቃሉ ጋር መቆየት። የእግዚአብሔር በተለያየ የብስለት ደረጃ ላይ ላሉ ሁሉ ተስማሚ የሆነ አቅርቦት አለው: ከወተት እስከ ጠንካራ ምግብ።)
4-በኃጢአት ላይ ድል ያስገኛል።
መዝሙር 119
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁹ ጕልማሳ መንገዱን በምን ያነጻል? ቃልህን በመጠበቅ ነው።
¹¹ አንተን እንዳልበድል፥ ቃልህን በልቤ ሰወርሁ።
የእግዚአብሔርን ቃል ጠብቆ በልቡ የሚይዝ ጎልማሳ እግዚአብሔርን አይበድልም መንገድም ንጹሕ ይሆናል።
5-የእግዚአብሔር ቃል የማንጻት ውጤት አለው።
ኤፌሶን 5
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁵-²⁶... በውኃ መታጠብና ከቃሉ ጋር አንጽቶ እንዲቀድሳት ስለ እርስዋ ራሱን አሳልፎ ሰጠ፤
²⁷ እድፈት ወይም የፊት መጨማደድ ወይም እንዲህ ያለ ነገር ሳይሆንባት ቅድስትና ያለ ነውር ትሆን ዘንድ ክብርት የሆነችን ቤተ ክርስቲያን ለራሱ እንዲያቀርብ ፈለገ።
(የእግዚአብሔር ቃል በውሃ ተመስሏል ይህም የማንጻት ሃይል እንዳለው የሚያሳይ ነዉ።)
6-መንፈሳዊ መስታወት ነዉ።
ያዕቆብ 1
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²³ ቃሉን የሚሰማ የማያደርገውም ቢኖር የተፈጥሮ ፊቱን በመስተዋት የሚያይን ሰው ይመስላል፤
²⁴ ራሱን አይቶ ይሄዳልና፥ ወዲያውም እንደ ምን እንደ ሆነ ይረሳል።
(...ውጫዊውን ፊታችንን ለመመልከት ሁላችንም መስታወት እንጠቀማለን: የእግዚአብሔር ቃል ግን የልብን ሰው የሚያሳይ መስታወት ነዉ: ምን እንደምትመስሉ ማወቅ ከፈለጋችሁ ወደ እግዚአብሔር ቃል ጠጋ ማለት ነዉ...)
#የእግዚአብሔርን ቃል አንድ ኃጢአተኛ ስመለከተው የመጀመሪያ የወደቀ እና መነሳት፤ መንጻት፤ መዳንና ሕይወት መግኘት የሚያስፈልገው ኃጢአተኛ እንደሆነ በግልጽ ያሳየዋል በመቀጠልም እግዚአብሔር ያቀረበውን መድኃኒት ያሳየዋል: በዚህ ጊዜ ኃጢአተኛው እግዚአብሔር ያቀረበውን የመፍትሔ መንገድ በእምነት ከተቀበለ ወድያው በክርስቶስ ያገኘውን አድሱን ማንነቱን ያሳየዋል! ክብር ለእግዚአብሔር ይሁን።)
7-የእግዚአብሔር ቃል አእምሮን ያበራል።
“የቃልህ ፍቺ ያበራል፥ ሕፃናትንም አስተዋዮች ያደርጋል።”
— መዝሙር 119፥130
አስተዋይ መሆን የሚወድ ቃሉን ይስማ!
8-ሕይወት እና አካላዊ ፈውስ ያስገኛል።
“ቃሉን ላከ ፈወሳቸውም፥ ከጥፋታቸውም አዳናቸው።”
— መዝሙር 107፥20
“ለሚያገኙአት ሕይወት፥ ለሥጋቸውም ሁሉ ፈውስ ነውና።”
— ምሳሌ 4፥22
አካላዊ ፈውስ የሚፈልግ የትኛውም ሰው በዚህ ረገድ የእግዚአብሔርን ቃል ማግኘት ከዛም አምኖ መቀበል ነዉ: በፍጹም ጤንነት መመላለስ ይችላል።አሜን።
...የእግዚአብሔር ቃል ይሰራል...
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
ሽልማት ያለው ጥያቄ!😍
ኃጢአት ለማድረግ መፈተን ኃጢአት ነዉ? ወይስ ኃጢአት አይደለም? መልሳችሁ እንደቃሉ መሆን አለበት።
1 810
📖የእግዚአብሔር ቃል📖
ኢየሱስ ቅዱሳት መጽሐፍትን የተጠቀመው እንዴት ነዉ?
የዚህ የመጀመሪያው ማሳያ ምድረበዳ ላይ የነበረው ቆይታ ነው። ለጸሎትና ለጾም በምድር በዳ በነበረበት ወቅት ከዲያብሎስ ለአርባ ቀናት ተፈትኗል: ፈተናዎቹን ሁሉ ያለፋቸው ቅዱሳት መጽሐፍትን መጠቀም ስለቻለ ነዉ። ፈተናው በሦስት የሚጠቃለል ነዉ የመጀመሪያው ፈተና የስጋ ምኞት ነበር ሁለተኛው ደግሞ ስለ ገንዘብ መመካት፤ ሦስተኛው የአይን አምሮት ነዉ። ለእነዚህ ሁሉ ፈተናዎች መልስ የተገኘው ከዘዳግም መጽሐፍ ነበር።
ኢየሱስ እያንዳንዱን ፈተና የመከተው ከዘዳግም መጽሐፍ ጠቅሶ "ተብሎ ተጽፏል" በማለት ነበር። ከዚህ የምንረዳው የሰይጣንን ፈተና ማሸነፍ የምንችለው ብቸኛው መንገድ የተሞላነውን የእግዚአብሔር ቃል በአንደበት በመናገር ነዉ። የሰው ስልት እና ብልሃት የሰይጣንን ፈተናዎች ማለፍ አይችልም!
ሌላው ኢየሱስ ሦስቱንም መልሶቹን ከዘዳግም መጽሐፍ መውሰዱ: የዘዳግም መጽሐፍ የእግዚአብሔርን እስትንፋስን ስለመያዙ ጥያቄ ለሚያቀርቡ አንዳንድ ሰዎች መልስ የሚሆን ይመስለኛል!( በእኛ ዘመን አንዳንድ ሰዎች የዘዳግምን መጽሐፍ እንደሚጠራጠሩ ያወቀው ይመስላል😁) ስለዚህ የዘዳግምን መጽሐፍ ትክክለኝነት የሚጠራጠሩ በዚህ እውነት ተወቅሰው ብመለሱ መልካም ነዉ።
❤የእግዚአብሔር ልጆች በሕይወታችሁ ዘመን ሁሉ ለምትፈተኗቸው ፈተናዎች የእግዚአብሔር ቃል መልስ አለው❤
#የእግዚአብሔርን_ቃል_ተጠቀሙ!
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
በጣም በአጭር ጊዜ ከብዙ እስራት ተፈቶ የሚያስገርም ለውጥ በሕይወቱ እያሳየ ያለ ልጅ ነዉ! የእግዚአብሔር ቃል ፈጽሞ ይለውጣል!
መንፈስ ቅዱስ በስራ ለይ ነዉ!
በዚህ ቻናል ብዙዎች እውነተኛ እና ቀጣይ ለውጥ እየተለማመዱ ነዉ: ጌታችን ክብር ይሁንለት!.... He said that "my life, attitude, personality, focus is totally and dramatically changing by the holy Spirit!"
#𝙣𝙤_𝙬𝙤𝙧𝙙𝙨!
1 810
📖📖የእግዚአብሔር ቃል📖📖
... ክፍል አምስት...
ኢየሱስ ቃሉን አድራጊ ነበር።
(Jesus was a doer of the word.)
ቅዱሳት መጽሐፍትን መጥቀስ ሁሉም የሚችለው ተግባር ነዉ: አማኙም የማያምነውም ከቅዱሳት መጽሐፍት ጠቅሶ ንግግሩን ወይም ድርጊቱን ትክክለኛ (Justify) የማድረግ ዝንባሌ ሁላችንም የምናስተውለው ነዉ። ነገር ግን ስንት ሰው ነዉ የቃሉ አድራጊ የሆነው? ኢየሱስ ጥቅስ የሚጠቅስ ሰው ብቻ አልነበረም: የእግዚአብሔር ቃል አድራጊ ለመሆን በሕይወቱ ሁሉ ፍጹም ትጋት ነበረው ደግሞ ያለነቀፋ ቃሉን ፈጽሞታል:...“እኔ ሕግንና ነቢያትን ለመሻር የመጣሁ አይምሰላችሁ፤ #ልፈጽም_እንጂ_ለመሻር_አልመጣሁም።”
— ማቴዎስ 5፥17
ጌታችን ኢየሱስ የእግዚአብሔርን ፈቃድ በማድረግ ስራውንም በመፈጸም ይጠግብ ነበር።
“ኢየሱስም እንዲህ አላቸው፦ የእኔስ መብል የላከኝን ፈቃድ አደርግ ዘንድ ሥራውንም እፈጽም ዘንድ ነው።”
— ዮሐንስ 4፥34
ይህንንም በመጨረሻ እንደዚህ በማለት መፈጸሙን ተናግሯል: “እኔ ላደርገው የሰጠኸኝን ሥራ ፈጽሜ በምድር አከበርሁህ፤”
— ዮሐንስ 17፥4
(...በመጨረሻ እኛም ይህንን ማለት እንድንችል ፀጋው ይረዳናል! ብቻ በፀጋው እንትጋ......አሜን!-
ኢየሱስ የቃሉ አድራጊ ነበር። እኛም ልክ እንደ እርሱ የቃሉ አድራጊዎች እንድንሆን መንፈስ ቅዱስ ተናግሮናል....“ቃሉን የምታደርጉ ሁኑ እንጂ ራሳችሁን እያሳታችሁ የምትሰሙ ብቻ አትሁኑ።”
— ያዕቆብ 1፥22
........የቃሉ አድራጊዎች መሆን ይጠበቅብናል......
👇👇👇👇JOIN👇👇👇👇👇
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ልጆች የመከሩ ጌታ ወደ መከሩ እንዲልካችሁ እጸልያለሁ! እጅግ ብዙ ስራ አለ አይናችንን ከፍተን እንመልከት እግዚአብሔር ደስ የሚሰኝባቸው አብሮ-ሰራተኞች መሆን እንድንችል ፀጋ ይብዛልን!
አገልጋይ የበዛ ከመሰላችሁ ተሳስታችኋል የክርስቶስ ልብ ያላቸው አገልጋዮች በዓለማችን በኢየሱስ ስም ይብዙ! አሜን!
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
ማቴዎስ 9
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³⁷ በዚያን ጊዜ ደቀ መዛሙርቱን፦ መከሩስ ብዙ ነው፥ ሠራተኞች ግን ጥቂቶች ናቸው፤
³⁸ እንግዲህ የመከሩን ጌታ ወደ መከሩ ሠራተኞች እንዲልክ ለምኑት አላቸው።
1 810
በሕይወታችን የተነገረው የእግዚአብሔር ቃል ከሚሻር ሰማይና ምድር ብያልፉ ይቀላል! እግዚአብሔር የተናገራችሁን ሁሉ ይፈጽማልና በምስጋና ተሞሉ! ድል ከፍታችን አለ! ሃሌሉያ!
“ከአፌ የሚወጣ ቃሌ እንዲሁ ይሆናል፤ የምሻውን ያደርጋል የላክሁትንም ይፈጽማል እንጂ ወደ እኔ በከንቱ አይመለስም።”
— ኢሳይያስ 55፥11
አሜን! አሜን! ታማኝ ለሆነው!
