fa
Feedback
TheDeepThingsOfGod

TheDeepThingsOfGod

رفتن به کانال در Telegram

Glorious Church the bride of Christ. Rapture ready!

نمایش بیشتر
1 810
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز
آرشیو پست ها
👆 SHARE አድርጉ! ሰዎችን አንቁ፥ ጌታችሁን ኢየሱስ ክርስቶስን አገልግሉ።

1948, May 14 እንዳ አውሮፓውያን አቆጣጠር ከላይ በጠቀስኩት ቀን በመጨራሻው መጨረሻ እንደሚሆኑ በትንቢት ከተነገሩት ክስተቶች ትልቁ እና በጣም ጠቃሚ የሆነው የእስራኤል እንደሃገር ከእንደገና የመመስረት ትንቢት ዓለምን ሁሉ ባስደነቀ መልኩ ተፈጸመ። ከ 30 ዓ.ም ትንሽ ቀደም ብሎ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ኢየሩሳሌም እንደዚህ የሚል ትንቢት ተናገረ ማቴዎስ 24 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ ኢየሱስም ከመቅደስ ወጥቶ ሄደ፥ ደቀ መዛሙርቱም የመቅደሱን ግንቦች ሊያሳዩት ቀረቡ። ² እርሱ ግን መልሶ፦ ይህን ሁሉ ታያላችሁን? እውነት እላችኋለሁ፥ ድንጋይ በድንጋይ ላይ ሳይፈርስ በዚህ አይቀርም አላቸው። ይህም በ 70 ዓመት ምህረት Titus, እና  Tiberius Julius Alexander በተባሉ የሮም ንጉሰ ነገስታት የተመራው የሮም ወታደር የእስራኤል ማእከል የሆነችውን ኢየሩሳሌምን እና የእስራኤላውያን ሁሉ ልብ የሆነውን የእግዚአብሔር ቤተመቅደስ ሙሉበሙሉ አወደሙት፥ በዚህም መልኩ በጌታ የተነገረው ትንቢት ከተነገረ ከአርባ አመት በኋላ ተፈጸመ። ጌታችን የተናገረው እስራኤል መፍረስ እና የእስራኤላዊያንን ከምድራቸው መነቀል ብቻ ሰይሆን፥ ተመልሶ መሰብሰብን እና እንደ ሃገር በድጋሚ መቆምን ጭምር ነዉ፥ ይህ ክስተት ግን ትልቅ ትርጉም ያለው ነዉ። ጌታችን የእስራኤልን እንደገና እንደ ሃገር መቆምን በቀጥታ ከመጨረሻው መጨራሻ ክስተቶች አንዱ አድርጎ ነው ትንቢቱን የተናገረው። ሉቃስ 21 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ²⁹ ምሳሌንም ነገራቸው እንዲህ ሲል፦ በለስንና ዛፎችን ሁሉ እዩ፤ ³⁰ ሲያቈጠቍጡ ተመልክታችሁ በጋ አሁን እንደ ቀረበ ራሳችሁ ታውቃላችሁ። ³¹ እንዲሁ ደግሞ እናንተ ይህ ሁሉ መሆኑን ስታዩ የእግዚአብሔር መንግሥት እንደ ቀረበች እወቁ። በዚህ ስፍራ በለስ በማለት የተገለጸችው ምድረ እስራኤል ናት። ጌታችን ቀድሞ የእስራኤልን መፍረስ እና እንደገና ማቆጥቆጥ አውቆ ተናግሯል፥ እንግዲህ ጌታችን በተናገረው መሰረት እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር 1948 ግንቦት 14 ቀን እስራኤል የመፍረሷ ዘመን ተፈጽሞ እንደገና እንደ ሃገር ተመሰረተች፥ በዓለም ሁሉ ተበታትነው የነበሩ የተባረኩ ልጆቿም ተሰበሰቡ፥ ትንቢቱ ተፈጸመ። የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ልጆች በለስ አቆጥቁጣለች፥ እንግዲያውስ የእግዚአብሔር መንግስት እንደቀረበ እወቁ። “እናንተም እነዚህ ነገሮች መፈጸም ሲጀምሩ፣ መዳናችሁ ስለ ተቃረበ፣ ቀጥ ብላችሁ ቁሙ፤ ራሳችሁንም ወደ ላይ ቀና አድርጉ።”” — ሉቃስ 21፥28 (አዲሱ መ.ት) 〽️ 🔺ይ🀄️ላ🀄️ሉን🔺 〽️ @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

“እናንተም እነዚህ ነገሮች መፈጸም ሲጀምሩ፣ መዳናችሁ ስለ ተቃረበ፣ ቀጥ ብላችሁ ቁሙ፤ ራሳችሁንም ወደ ላይ ቀና አድርጉ።”” — ሉቃስ 21፥28 (አዲሱ መ.ት)

#CryForRevival! Let Us Cry for the later Rain before the rapture of the Church!😭 ከቤተክርስቲያን ንጥቀት በፊት ለኋለኛው ዝናብ ወደ እግዚአብሔር እናልቅስ! “በኋለኛው ዝናብ ጊዜ ከእግዚአብሔር ዘንድ ዝናቡን ለምኑ፤ እግዚአብሔር መብረቅ ያደርጋል፤ እርሱም የበልግ ዝናብን ለእያንዳንዱም በሜዳ ውስጥ ሣርን ይሰጣል።” — ዘካርያስ 10፥1 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

Rapture soon, but before rapture revival very soon!!!! #CryForRevival!😭

“ከእግዚአብሔር እንደ ሆንን ዓለምም በሞላው በክፉው እንደ ተያዘ እናውቃለን።” — 1ኛ ዮሐንስ 5፥19 “We know that we are of God, and the whole world is under the power of the evil one.” — 1Jn 5፥19 (AMP)

👆YOU CAN JOIN THE VOICE CHAT AS A SPEAKER AGAIN.

👆Join የሚለውን በመጫን የድምጽ ውይይታችንን መቀላቀል ይቻላል

-ሀያላን አደራችሁን ይህ ማንቂያ ደውል ስለሆነ 🔔 ላላችሁበት የክርስቲያን group እና ለምታውቋቸው ሰዎች ላኩላቸው የአንድ ሰው መንቃት ምክንያት ትሆናላችሁ እናንተም ደጋግማችሁ ስሙት። 👆 Comment ላይ ተጽፎ ያገኘሁት ነዉ።

ክርስቲያን ስለጌታ ተመልሶ መምጣት ስሰማ መደሰት ነው ያለበት፥ አሜን ይሁን ነው ማለት የሚገባው። ስለቤተክርስቲያን ንጥቀት ወይም ስለጌታ ዳግም መምጣት ስሰበክ የሚፈራ ክርስቲያን ሕይወቱን በትክክል እየኖረ አይደለም ማለት ነው፥ እንደዚህ አይነቱ ክርስቲያን ንስሃ ማድረግና በእውነት መኖር መጀመር ነው ያለበት። @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

በጣም ጠቃሚ ማሳሰቢያ ስሙት! መንፈስ የሚለውን ጆሮ ያለው ይስማ። @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

JESUS CHRIST IS COMING SOONER THAN WE THINK!😁🥰 Are you RAPTURE READY? ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከምናስበው በላይ በቅርብ ይመጣል! ለመነጠቅ ተዘጋጅተሃል? ለመነጠቅ ተዘጋጅተሻል?

የእውነተኛ መንፈሳዊነት ማረጋገጫ እውነተኛ መንፈሳዊነት ማረጋገጫው ምንድነው? ፕሮቴስታንት ወይም ኦርቶዶክስ ወይም ካቶሊክ የሚባል ተቋም ተከታይ መሆን ነዉ? በፍጹም አይደለም! እሽ መጸለይ ወይም መጾም በየሰንበቱ ቤተክርስቲያን መሄድ ነዉ? ይህም አይደለም። መጸለይ እና መጾም ወይም የአጥቢያ ቤተክርስቲያን አባል መሆን መንፈሳዊ ሰዎች የሚያደርጉት ልምምድ ቢሆንም፤ የሚጸልዩ እና የሚጾሙ ወይንም የአጥቢያ ቤተክርስቲያን አባል የሆኑ ሰዎች ሁሉ የእውነት መንፈሳዊ ናቸው ማለት አይደለም። ምክንያቱም የህንዱ ወይም የቡድሃ እምነት ተከታዮችም ይጾማሉ ይጸልያሉ፥ እነርሱም የራሳቸው ተቋማዊ ቅርጽ እና መንፈሳዊ ትምህርቶች አሏቸው። ስለዚህ መጸለይ ወይም መጾም የመንፈሳዊነት ምልክት ልሆኑ የሚችሉት ትክክለኛ መሰረት ላይ ስንቆም ብቻ ነው፥ የቆምንበት መሰረት ትክክለኛው( ክርስቶስ) ከልሆነ ጸሎትና ጾም ሌሎችም መንፈሳዊ ልምምዶች የጨለማው ዓለም በሮች ናቸው። እውነተኛ መንፈሳዊነት መጀመሪያ እና ግብ አለው። መንፈሳዊነት በእውነት መለማመድ የሚወድ ሰው በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ስም በማመን ደግም ተወልዶ ነው መጀመር የሚችለው፥ ጅማሬው ዳግም ልደት ቢሆንም ግቡ ግን በጊዜ ሒደት ከመንፈስ ቅዱስ እና ከቃሉ ጋር በሚደረግ የማያቋርጥ ሕብረት የፍጥረት ፈጣሪ የሆነውን ኢየሱስ ክርስቶስን መምሰል ነዉ። የእውነተኛ መንፈሳዊነት ምልክት ይሄ ነዉ፥ ኢየሱስ ክርስቶስ ከቀን ወደቀን ራሳችን ላይ እየደመቀ ስናየው ነው። የክርስቶስ ልብ በእኛ ስኖር እና በእርሱም በለ ሐሳብ ሕይወታችንን ስንኖር ነዉ። እውነተኛ መንፈሳዊነት ኃጢአትን ስንጸየፍ እና ስናሸንፍ ነዉ። እውነተኛ መንፈሳዊነት የእግዚአብሔርን መንፈስ እና ምክር አብዝተን ስንፈልግ ነዉ። እውነተኛ መንፈሳዊነት ኢየሱስ ክርስቶስን ስንመስለው ነዉ። በመጋረጃ በማይሸፈን ፊት ክብሩ በእኛ ስንጸባረቅ ነው። የእግዚአብሔር ልጆች "እግዚአብሔርን ለመምሰል ራሳችሁን እንድታስለምዱ" ማሳሰቤን አልተውም፥ የተወለዳችሁት እና የምትኖሩት ለዚህ ነዉ። 〽️ 🔺ይ🀄️ላ🀄️ሉን🔺 〽️ @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

እግዚአብሔር አባቴ ነው። እግዚአብሔር አባትሽ ነዉ። እግዚአብሔር አባትህ ነዉ። 😁😁😁🥰🥰😁😁😁

“አምላኩን እግዚአብሔርን መፍራት ይማር ዘንድ፥ የዚህን ሕግ ቃል ሁሉ ይህችንም ሥርዓት ጠብቆ ያደርግ ዘንድ፥ ልቡ በወንድሞቹ ላይ እንዳይኰራ ከትእዛዙም ቀኝና ግራ እንዳይል፥ እርሱም ልጆቹም በእስራኤል ልጆች መካከል ረጅም ዘመን ይነግሡ ዘንድ መጽሐፉ ከእርሱ ጋር ይኑር፥ ዕድሜውንም ሁሉ ያንብበው።” — ዘዳግም 17፥19-21

መጽሐፍ ቅዱስ በምናነብበት ጊዜ የእግዚአብሔርን ቃል ለማግኘት መከተል ያለብን ስድስት መርሆች: ከዚህ በፊት በጻፍኩት ጽሑፌ የመጀመሪያዎቹን ሦስት መርሆች አስቀምጫለሁ፥ ዛሬ ደግሞ የሚቀጥሉትን ሦስት መርሆች እጽፋለሁ። 4. ማሰላሰል (Meditation) :- መጽሐፍ በመዝሙር አንድ ላይ ብሩክ ስለሆነው ሰው ስናገር የእግዚአብሔር ቃል በቀንም በለሊትም የሚያሰላስል ሰው መሆኑን ይነግረናል፥ በጸሎት፣ በዝግታ እና በተደጋጋሚ የምናነበውን የእግዚአብሔርን ቃል በልባችን ያለማቋረጥ ማሰላሰል ይገባል፥ የእግዚአብሔርን ቃል ያለማቋረጥ በቀንም በሌሊትም የሚያሰላስል ሰው በውሃ ፈሳሾች ዳር የተተከለችን ዛፍ ይመስላል፥ በውሃ ዳር የተተከለች ዛፍ ቅጠሏ አይረግፍም በየጊዜውም ፍሬዋን መስጠት አታቋርጥም፤ ይህም ሰው እንደዚህ ነው ውስጡም ውጪውም ለምለም ነው። 5. በአንደበት መናገር(Confession):- የእግዚአብሔርን ቃል ያለማቋረጥ ስናሰላስል ልባችን በእግዚአብሔር ሐሳብ ይሞላል በዚህ ጊዜ ቀጣዩን ደረጃ መለማመድ እንጀምራለን ይህም የእግዚአብሔርን ቃል በአንደበታችን መናገር ነው። ጌታችን በ — ሉቃስ 6፥45 “በልብ ሞልቶ ከተረፈው አፉ ይናገራልና...” በማለት ልባችን የተሞላው ነገር ንግግራችን እንደሚሆን ይገልጻል። ከላይ የቀረቡትን ሁለቱን መርሆች በአንድ ለይ የያዘ ቃል ከመጽሐፍ ኢያሱ እንመልከት፥ እግዚአብሔር ኢያሱን ያዘዘው ቃል ይህ ነው በዚህም መንገድ እግዚአብሔር ከሙሴ ጋር እንደነበረ እንደዚያው ከኢያሱ ጋር እንደሚሆን ተናግሮታል። “የዚህ ሕግ መጽሐፍ ከአፍህ አይለይ፥ ነገር ግን የተጻፈበትን ሁሉ ትጠብቅና ታደርግ ዘንድ በቀንም በሌሊትም አስበው፤ የዚያን ጊዜም መንገድህ ይቀናልሃል ይከናወንልሃልም።” — ኢያሱ 1፥8 እግዚአብሔር ሕጉን(ቃሉን) በተመለከተ ኢያሱ ማድረግ ስላለበት ነገር ስነግረው ሁለት ነገሮች ነው ያዘዘው የመጀመሪያው በቀንም በሌሊትም ቃሉን ማሰላሰል ነው፥ ቀጣዩ ደግሞ ቃሉን ሁልጊዜ መናገር/ማወጅ ነዉ። ይህንንም "የዚህ የሕግ መጽሐፍ ከአፍህ አይለይ" በማለት ይገልጸዋል። የእግዚአብሔርን ቃል በቀንም በሌሊትም አሰላስል ከአፍህም አትለየው፣ ያለማቋረጥ ተናገረው። 6. በቀጣይነት (Consistently) ማንበብ:- ከላይ ያሉትን አምስት መርሆች በቀጣይነት መከተል ስድስተኛው መርህ ነዉ። በጸሎት፣ በዝግታ፣ በተደጋጋሚ የምናነበውን እና ያለማቋረጥ በልባችን እያሰላሰልን በአፋችን የምናውጀውን የእግዚአብሔር በቀጣይነት በዚህ መልኩ ማንበብ የመጨረሻው መርህ ነው፥ እንዚህን መርሆች በመከተል ቅዱሳት መጽሐፍትን የምታነቡ ከሆነ ሕይወታችሁን ይለውጠዋል። 〽️ 🔺ይ🀄️ላ🀄️ሉን🔺 〽️ @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

መርህ የምንለው ውጤት የምንፈልግ ከሆነ የግዴታ መከተል ያለብን ነገሮችን በትክክለኛው አግባብ የምናደርግበት መንገድ ነው። ለምሳሌ የስንዴ ምርት ማጨድ የሚፈልግ ሰው የግዴታ የስንዴ ዘር መዝራት አለበት፥ የእግዚአብሔር ቃል በገላትያ 6፥7 “ሰው የሚዘራውን ሁሉ ያንኑ ደግሞ ያጭዳልና፤” ይላል። ይህ መርህ ነው፤ በዚሁ መንገድ የእግዚአብሔር ቃል ስናጠና መንፈስና ሕይወት ለማጨድ መከተል ያለብን መንፈሳዊ መርሆች አሉ። @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

መጽሐፍ ቅዱሳችሁን ስታነቡ የእግዚአብሔርን ቃል ለማግኘት መከተል ያለባችሁ ስድስት መርሆች: 1.በጸሎት(prayerfully) ማንበብ:- ቅዱሳት መጽሐፍት ሁሉ በእግዚአብሔር መንፈስ በተነዱ መንፈሳዊ ሰዎች የተጻፉ መንፈሳዊ ጽሑፎች ናቸው፥ ስለዚህ መጽሐፍ ቅዱስን ለመረዳት በሚደረግ ጥናት ጊዜ በአእምሮ ልህቀት ላይ ከመደገፍ እና ከብልጣብልጥነት ነጻ ወጥቶ በጸሎት የመንፈስን አስተማሪነት እና መሪነት መፈለግ የመጀመሪያው ጥበብ ነዉ። 2.በዝግታ(Slowly) ማንበብ:- ቅዱሳት መጽሐፍትን በጥድፊያ ማንበብ ብዙዎች የሚሰሩት ስህተት ነዉ፥ ቅዱሳት መጽሐፍት የያዙትን መንፈስ እና እውነት ለማግኘት በንባብ/በጥናት ጊዜ ትኩረታችንን በመሰብሰብ በዝግታ ማንበብ ሁለተኛው መርህ ነዉ። 3. በተደጋጋሚ(frequently) ማንበብ:- ቅዱሳት መጽሐፍትን በምናነብበት ወቅት በአንድ ጊዜ እጅግ ብዙ ምዕራፎችን ማንበብ የመጀመሪያ ግባችን መሆን የለበትም፥ አንድ ምዕራፍ አንብበን ያገኘነው ጥልቅ እውነት እና መንፈስ ከሌለ ያንኑ ምዕራፍ በተደጋጋሚ ማንበብ፥ አስፈላጊ በሚሆንበት ጊዜ ደግሞ ከእርሱ ምዕራፍ ቀድሞ ያለውን ምዕራፍ እና ቀጥሎ ያለውን ምዕራፍ ማንበብ ይኖርባችኋል፥ ይህ ሂደት ሰባት ጊዜ እንኳ ቢደገም አትሰላቹ፥ ምክንያቱም ሕይወትን ልታገኙ ነዉ፥ ተዓምራትን ልታዩ ነዉ። የቀሩትን ሦስት መርሆች በሚቀጥለው ጽሑፌ አቀርባለሁ፥ በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ለእግዚአብሔር እውነት አእምሮችሁ እንዲከፈት እጸልያለሁ፥ የቅዱሳት መጽሐፍትን ሚስጥር እንዲታዩ እና አድራጊዎች መሆን እንድትችሉ የእግዚአብሔር ፀጋ በሕይወታችሁ እንዲበዛ እጸልያለሁ፡ አሜን። 〽️ 🔺ይ🀄️ላ🀄️ሉን🔺 〽️ @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit