fa
Feedback
TheDeepThingsOfGod

TheDeepThingsOfGod

رفتن به کانال در Telegram

Glorious Church the bride of Christ. Rapture ready!

نمایش بیشتر
1 810
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز
آرشیو پست ها
ወሬው ሁሉ የሚያስፈራ፣ የሚሆነው በምድር ዙሪያ፣ እየከፋ ስሄድ ጊዜው፣ መሸሸጊያ ኢየሱስ ነው። ኢየሱስ በቶሎ ተመልሶ ይመጣል!

It's not just a song it's a prayer, pray it! Oh Lord, guard my heart from corruptions of this world!

ወንጌላችን ገና ድል ያደርጋል 🎸😁 ድንቅ መዝሙር

ቄስ በሊና ስለ በኢትዮጵያ ስለ ሚነሳው ሪቫይቫል ያዩትን ራዕይ እንዲህ አስተላልፈዋል "መሪዎች ሊያቆሙት የማይችሉት ታላቅ የመንፈስ ቅዱስ እንቅስቃሴ ይሆናል። መንፈስ ቅዱስም ታላላቅ ደኖችን እንደሚያቃጥል የሰደድ እሳት የቀድሞውን ያረጀ ስርአት ና ወግ ያቃጥላል። አብያተ ክርስቲያናት ይቀጣጠላሉ ታላላቅ ታምራቶች በየቦታው ይሆናሉ። ኢትዮጵያዊያን አገልጋዮች በሄዱበት ቦታ ሁሉ እንደ ጨው ይፈለጋሉ። እንደ መዳኋኒት የሚፈለጉ በእምነታቸው በአገልግሎታቸው በትጋታቸው የሚፈለጉ ሆነው ይገለጣሉ። ተሰርተው ይወጣሉ ወጥተውም መድኀኒት ይሆናሉ። ለወንጌል ሥርጭት በአገርና ከአገር ውጪ በስፋት የተሰማሩ አገልጋዮችን አየሁ። በታላላቅ ድንቅና ተዓምራት የሚያገለግሉ አገልጋዮች በኢትዮጵያ ውስጥ ሲያድጉ ተመለከትኩ። ብዙ ወጣቶችም ወደ ምስራቅ አገራት ለሚሲዮን ስራ ይሄዳሉ። በድንቅና በተዓምራት ታጅበው በኃይልና በስልጣን እየተናገሩ ሕዝብን ወደ እኔ ያፈልሳሉ። ኢትዮጵያ በመንፈሳዊ አገልግሎት ለዓለም እንደ መድኃኒት የምንፈልግበት ዘመን እንደሚሆን አየሁ። ለዓለምም መንፈሳዊ ተሃድሶን እንደምናመጣ ተረዳሁ።"          በዚህ ሪቫይቫል ተሳታፊ እንጂ audience መሆን አትፈልጉ! https://t.me/TheDeepThingsOfGod

እርሳቸው ላይ ያለውን ቅባት ለብዙዎች አካፍለው በመሄዳቸው ደስ ይለኛል ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁶ እኔ እንደ መጠጥ ቊርባን መሥዋዕት ለመፍሰስ ተቃርቤአለሁ፤ ተለይቼ የምሄድበት ጊዜ ደርሶአል። ⁷ መልካሙን ገድል ተጋድያለሁ፤ ሩጫውን ጨርሻለሁ፤ ሃይማኖትንም ጠብቄአለሁ። ⁸ ወደ ፊት የጽድቅ አክሊል ተዘጋጅቶልኛል፤ ይህንም ጻድቅ ፈራጅ የሆነው ጌታ በዚያ ቀን ለእኔ ይሰጠኛል፤ ደግሞም ለእኔ ብቻ ሳይሆን፣ የእርሱን መገለጥ ለናፈቁ ሁሉ ነው። 2ኛ ጢሞቴዎስ 4 (አዲሱ መ.ት)

photo content

"ትላልቅ ንስሮቹ መብረራቸውን ቀጥለዋል" ቄስ በሊና ሳርካ ከ60 አመት በላይ ወደ አገለገሉት አባታቸው ሄደዋል። በቄስ በሊና ሳርካ አማካኝነት እግዝብሔር የኢትዮጵያ ቤተ ክሪስቲያንን እንዴት እንደለወጠ ሁላችንም ምናውቀው ነገር ነው። እኚህ አባት ከኢትዮጵያ ከዳር እስከ ዳር ያገለገሉ ሲሆን በጎረቤት ኤርትራ 6 ከተሞች ተዘዋውረው አገልግለዋል ።እንዲሁም በአሜሪካ 42 ስቴት ፣በአውሮፓ ደግሞ ከእስፔን እና ከ ፖርቹጋል ውጪ ሁሉም ሀገር የመዳንን ወንጌል በመንፈስ ቅዱስ ሀይል ሰብከዋል። ሐዋሪያዊ ተልዕኮ የነበራቸው እኚህ ጄነራል በአፍሪካ እና በእስያም ያገለገሉ ሲሆን ከ 53 በላይ የተለያዩ ቤተክርስቲያንን በእርሳቸው ተተክለዋል። በአገልግሎታቸው ዘመን ስለ ተደረገው ሁሉ ጌታ ይባረክ።

ክርስትና የመገለጥ ሕይወት ነው ወዳጆች ሆይ ክርስትናን ከሰው በሰማነው፣ ከቤተሰቦቻችን በወረስነው በተለያየ አይነት መንገድ ባገኘነው መንገድ መኖር አንችልም ምክንያቱም #ክርስትና #የመገለጥ #ሕይወት ስለሆነ ነው!!! ክርስትናን ከልተገለጠልህ በሰተቀር ሃይሞኖት ከመሆን ያለፈ ትርጉም ላይሰጥህ ይችላል! ሲገለጥልህ አልያም ሲበራልህ ግን ከተፈጥሮ በላይ የሆነውን የክርስትናን ሕይወት መለማመድ ትጀምራለህ። 🌍🌎 አለምን የገለባበጡ ሰዎች ክርስትና (ክርስቶስ) የተገለጠላቸው ሰዎች ናቸው!! ##አለም እና በአለም ያለው የቀለላበቸው ሰዎች ክርስትና የተገለጠላቸው ሰዎች ናቸው 😎💡 ተጽዕኖ የፈጠሩ ሰዎች ክርስትና የተገለጠላቸው ሰዎች ናቸው!! 🔥🔥💪 በእሳት እና በሀይል ያገለገሉ ሰዎች ክርስትና ያበራላቸው ሰዎች ናቸው!! Even ጌታ ኢየሱስን የተገናኙ ወይም encounter ያደረጉም ሆነ የሚያደርጉ የተገለጠላቸው ሰዎች ናቸው!!! 😭😭 ጌታ ሆይ በዚህ ምድር ያሰብከውን ያን የአንተን ሕይወት ኖረን እንድናልፍ እንደ ሰው ልማድ ሰይሆን እንደ መለኮት ስርአት ኖረን እንድናልፍ አለም እና የአለም ነገር ቀሎብን እንድናልፍ አይኖቻችንን አብረውና እውነትን አሳየን ክርስትናን ግለጥልን። 😭😭 ጌታ ሆይ #ክርስትና #ይገለጥልንና የተቀየረ ሕይወት እንኑርልህ @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

ተልኮልኝ ነው በዚህም ተባረኩ እናም ከፊት ይልቅ በጸሎት በቃል በርቱ!!

ጌታ ሆይ ምን ቢገባቸው ነው?"    😭😭😭 "ምን ቢያገኛቸው ነው?"    😭😭😭 "ምን ሆነው ነው?"    😭😭😭 "ኧረ ምንድነው የተረዱት?"       😭😭😭 "ምን ቢነካቸው ነው?"     😭😭😭😭 "ምንድነው የበራላቸው ጌታ ሆይ?"     😭😭😭😭 "ለአመታት እንዲጸልዩና እንዲጾሙ ያደረጋቸው ምንድነው?"     😭😭😭😭😭 "ከአንተ ውጪ ሌላ ነገር እንዳይፈልጉ ያደረጋቸው ምንድነው?"    😭😭😭 "ከአንተ ውጪ ሌላ ነገርን እንዳይወዱ ያደረጋቸው ምንድነው?"      😭😭😭 "አለምንና የአለምን ነገር ያቀለለባቸው ምንድነው?" 😭😭😭😭😭 "ሁሉን ትተው አንተን መፈለግ ስራቸው እንዲሆን ያደረገው ምንድነው?"        😭😭😭 "ከአንተ ጋር ሕብረት ለማድረግና አንተን ከማወቅ በስተቀር፣ የአንተን ክብርና ኃይል ከመሸከም ውጪ ሌላውን ነገር ትርጉም አልባ ያደረገባቸው ምንድነው?"     😭😭😭😭 "ብዙ አማራጭ እያላቸው፤ አንተን ምርጫቸው እንዲያደርጉ ያደረጋቸው ምንድነው?" 😭😭😭😭 "በተገለጠው ነገር ረክተው እንዳይቀመጡ፤ ነገር ግን ለበለጠው፣ ለከበረውና ለጠለቀው ነገር ሁለንተናቸውን እንዲሰጡ ያደረጋቸው ምንድነው?" 😭😭😭😭 "ስጋዊነትን፣ ስንፍናን፣ ድካምን፣ ትዕቢትን፣ ንቀትንና ቅናትን፣ ራስ-ወዳድነትን፣ ተድላን መውደድን፣ የገንዘብ ፍቅርን፣ ዝናንና ክብርን፣ በቀላሉ ተስፋ መቁረጥንና መታከትን፣ መወላወልን ከእነርሱ የወሰደው ምንድነው?"    😭😭😭😭😭😭 "ያላቸውን ሁሉ ለክብርህና ለኃይልህ እንዲለውጡ ያደረጋቸው ምንድነው?"   😭😭😭😭😭 "ከምክንያት በላይ አንተን ያለማቋረጥ እንዲፈልጉ ያደረጋቸው፣ መንፈስህን ከህይወታቸው፣ ከምንም ደግሞም ከማንም በላይ እንዲወዱና እንዲጠሙ ያደረጋቸው ምንድነው?"   😭😭😭😭😭 "ነፍሳቸውን በስጦታው ሳይሆን በሰጪው ፍቅር እንዲያዝ ያደረጋቸው ምንድነው?"     😭😭😭😭😭😭😭 "የትውልድን መዳንና መለወጥን ረሃብ አጥንታቸው ውስጥ ዘልቆ እንዲገባ ያደረገው ምንድነው?"      😭😭😭😭 "አለምን በጀርባቸው ላይ እንደተሸከሙ ለመጸለይ መንበርከክን ያቀለላቸው፣ ምጥ እንደያዛት ሴት ተንበርክከው በእንባና በሲቃ እንዲያምጡ ያደረጋቸው ምንድነው?" 😭😭😭😭😭 "ኦ! ጌታ ሆይ የነካቸው ይንካን! የበራላቸው ይብራልን! የተገለጠላቸው ይገለጥልን! እነርሱን ያገኘው ያግኘን! ወደ ሕብረት፣ አንተን ወደ ማወቅ፣ ክብርህን ወደ መራብና መጠማት ደግሞም ወደ ማየት እናድግ ዘንድ የገባቸው ይግባን በኢየሱስ ስም!!" 😭

የመዝሙር ግብዣ የተወደደ ቆያት ያለ የሕብረት መዝሙር ❤❤ ሁላችሁም ስሙት!! Share @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

Special message from brother ABINET Why your prayer , intimation with word and your intimacy with God is decreasing? Hear this and share with your friends

የእግዚአብሔር በትር እግዚአብሔር እስራኤላውያን ነፃ ለመውጣት ሲመጣ በቅድምያ ያገኘው ሙሴን ነበር ባገኘውም ጊዜ እግዚአብሔር በእርሱ አማካኝነት ሕዝቡን ነፃ ሊያወጣ መሆኑን ሲነገር ሙሴ በአንዴ ለዚህ ቃል አልታዘዝም ነበር! እግዚአብሔርም በእጅህ ላይ ያለው ምንድነው ብሎ ሲጠይቀው? እርሱም በትር ነው አለ። እግዚአብሔር በዚያ በትር አማካኝነት ተአምራቱን በማሳየት ሀሳብን አስረድቶ እንድሄድ አደረገው። ሙሴም ወደ እስራኤላዊያን በሚመለስበት ጊዜ #የእግዚአብሔር #በትር ይዞ እንደ ተመለሰ በመጽሐፍ ይነገረናል። በጣም የሚገርመው ይህ በትር #የእግዚአብሔር ከመባሉ በፊት ሙሴ በጎችን ይጠበቅ የነበረበት ልክ ማንኛውም አይነት እረኛ ጋር እንደለው አይነት ከአንድ እንጨት የወጣ ዱላ ነው፤ አሁን ግን ሙሴ እጅ ላይ ያለው በትር ታሪኩ ተቀይሮአል በግ ከመጠበቅ እና መሳል ተግባራትን አልፎ የአምላክ ተአምራት፡ ድንቅ እና ምልክት የሚታይበት የእግዚአብሔር በትር ሆኖል! #ዛሬም ብዙም ዋጋ የማትሰጡት እናንተ ጋር ያለ ነገር ልሆን ይችላል ወይም ደግሞ እናንተ ጋር ያለው አይነት ነገር በተመሳሳይ ሁኔታ ሌላም ብዙ ሰዎች ጋር ልኖር ይችላል ከዚህም የተነሳ ብዙም ትርጉም የማይሰጣችሁ ነገር ልሆን ይችላል እግዚአብሔር ሲያገኘው ግን የነገር የእርሱ በትር ይበላል። እናንተ ጋር ያለው ማንኛውም ነገር በእርሱ ከተነካ በኋላ እንደ እግዚአብሔር በትር እንጂ ማንም ጋር እንዳለው ነገር አይሆንም። #ትምህርታችሁን፡ #ስራችሁ፡ #ንግዳችሁ እንድሁም #አገልግሎታችሁ... ያላችሁ ነገር ሁሉ እንደ እግዚአብሔር በትር ሆኖ ይለወጣል። በዚያ በተለወጠው ነገር በኩል የጌታ ጣት ሲገለጥ ይታያል!! ##ትንሽ ያላችሁት ነገር እግዚአብሔር ለውጦት እንደ ራሱ በትር ልጠቀመው ይችላል። ለሌሎች እንድደርስ share አድርጉ 👇👇👇👇ይቀላቀሉን👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

የእግዚአብሔር በትር ሙሴ ጋር የነበረው በትር እንዴ የእግዚአብሔር በትር ሆነ? ሁሉ ሰው ማስማት ያለበት ትምህርት!😭😭😭🔥 ለሌሎች እንድደርስ share 👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

Jesus delivered this man from evil powers all Glory be to the Lord! My first service in 🇺🇸 Started by delivering the oppres
+1
Jesus delivered this man from evil powers all Glory be to the Lord! My first service in 🇺🇸 Started by delivering the oppressed!🔥 @TheDeepThingsOfGod

Shared knowledge is the ground for spiritual fellowship, those who feed from the same table will have inner unity, so take heed who you listen too! የተጋሮ እውቀት የመንፈሳዊ አንድነት መሰረት ነው፣ እውቀትን የሚጋሩ ሰዎች ወይም ቡድኖች ውስጣዊ ሕብረት ይኖራቸዋል፥ ስለዚህ ማንን እንድትሰሙ በጥንቃቄ ምረጡ። @TheDeepThingsOfGod

First Sunday @ Church 🇺🇸 US ወዳጆቼ አሜሪካን ሃገር በጣም በሚገርም ሁኔታ በተቀራረበ መልኩ እጅግ ውበት ያላቸው የቤተክርስቲያን መሰብሰቢያ አዳራሾች ተገንብተዋል፣ በውስጣቸውም ሁሉንም አይነት ዘመናዊ መሳሪያዎች የታጠቁ ናቸው ነገር ግን እሁድ ቀን እንኳ ብዙ ሕዝብ አይገኝባቸውም፣ ጥቂት ሰዎች ይገኛሉ እነርሱም በእድሜ ጠና ያሉ ጎልማሶች አባቶች እና እናቶች ናቸው፣ እውነት ለመናገር ከሰዓታት በፊት በነበረው የእሁድ ፕሮግራም አንድም ወጣት ማየት አልቻልኩም! እጅግ የሚያሳዝን ነው፣ ለምን ይመስላችኋል? መፍትሔውስ ምን እንደሆነ ታስባላችሁ?? መልስ ያለው ሰው እንዲያጋራኝ በትህትና እጠይቃለሁ!

ትልቅ ምሳሌ ነው 😍

ወንድሜ አገልጋይ ሲሳይ አዙዛ በስጋ የወለዱትን ወላጆቹን በዚህ መልኩ የወንጌልን እውነት አስተምሮ የውሃ ጥምቀት መፈጸሙን ስመለከት እጅግ ደስ ብሎኛል! ለብዙ ወጣቶች ምሳሌ የሚሆን ወጣት የእግዚአብሔ
+1
ወንድሜ አገልጋይ ሲሳይ አዙዛ በስጋ የወለዱትን ወላጆቹን በዚህ መልኩ የወንጌልን እውነት አስተምሮ የውሃ ጥምቀት መፈጸሙን ስመለከት እጅግ ደስ ብሎኛል! ለብዙ ወጣቶች ምሳሌ የሚሆን ወጣት የእግዚአብሔር አገልጋይ ነው! እንኳን ደስ አለህ ወንድሜ! @TheDeepThingsOfGod