Scholarships
رفتن به کانال در Telegram
Info about free scholarship's for Msc and PhD. @motisalale(@motisalalee)
نمایش بیشتر645
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز
آرشیو پست ها
645
#SelaleUniversity
በ2014 ዓም የትምህርት ዘመን በሰላሌ ዩኒቨርሲቲ ለተመደባችሁ አዲስ ገቢ ተማሪዎች ምዝገባ የሚከናወነው 👉 ግንቦት 8 እና 9 ቀን 2014 ዓ/ም መሆኑን እናሳውቃለን።
ለምዝገባ ስትመጡ
• የ8ኛ ብሔራዊ ፈተና ውጤት
• የ10ኛ እና 12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ውጤት • የ10ኛ እና 12ኛ ክፍል የተማራችሁበት ትራንስክሪፕት ኦርጅናልና ፎቶ ኮፒ
• ስምንት 3×4 የሆነ ጉርድ ፎቶ ግራፍ
• አንሶላ ፣ ብርድ ልብስ፣ የስፖርት ልብስ እና የትራስ ልብስ ይዛችሁ መምጣት ይጠበቅባችዋል፡፡
ማሳሰቢያ
• የምዝገባ ቦታ ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ ጀነራል ታደሰ ብሩ ካምፓስ
. ከተጠቀሰው የምዝገባ ቀናት ቀድሞም ሆነ ዘግይቶ የሚመጣ ተማሪ ዩኒቨርሲቲው የማያስተናግድ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
645
#ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ ስራ ፈጠራ ክህሎት ላይ ከተለያየ ትምህርት ክፍል ለተውጣጡ መምህራን ስልጠና ሰጠ፡፡
በጄኔራል ታደሰ ብሩ ዋና ግቢ የስድስት ቀን የስልጠና መርሃ ግብር ያዘጋጀው የሰላሌ ዩኒቨርሲቲ የኢንተርፕሪነርሽፕ አና ቢዝነስ ኢንኩቤሽን ሴንተር ዳይሬክቶሬት ሲሆን
በስልጠናው የተሳተፉት ደግሞ ከተለያዩ ኮሌጆችና ትምህርት ክፍሎች የተወጣጡ ከ60 በላይ የሚሆኑ የዩኒቨርሲቲው መምህራን ናቸው፡፡ ስልጠናውም የተሰጠው ከኢትዮጲያ ሥራ ፈጠራ አመራር ኢንስቲትዩት በመጡ አሰልጣኞች ነው፡፡
ስልጠናው በዋናነት ያተኮረው በስራ ፈጠራ መሰረታዊ የንግድ ንድፈ ሃሳብ ማፍለቅ፤ የስኬት መንገዶች፤በዓለም አቀፍ ደረጃ ያሉት በስራ ዘርፍ የስኬት መልካም ተሞክሮዎች፤ ከስልጠና በኋላ ከሰልጣኞች ምን ይጠበቃልና ወዘተ በመሳሰሉት ዋና ዋና ርዕሰ ጉዳዮች ነው፡፡ ሰልጣኞቹም በሁለት ምድብ ተከፍለው የሰለጠኑ ሲሆን ስልጠናውም ተግባር ተኮር ስራዎች ላይ ያተኮረና ተግባራዊ የአመለካከትና የባህሪ ለውጥ የሚያመጣ ስልጠና ነው፡፡
በስልጠናው መዝጊያ ፕሮግራም ላይ በመገኘት የመዝጊያ ንግግር ያደረጉት የሰላሌ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ገናነው ጎፌ እንደተናገሩት እንዲህ አይነቱ ስልጠና በሁሉም በተሰማራንበት የስራ ዘርፍ በቡድንም ሆነ በግል በምንኖረው ህይወት ውስጥ ስኬታማ ስራ እንድንሰራና የእያንዳንዳችንን የኑሮ ደረጃ ድሮ ከነበርንበት ወደ ፊት የሚያራምድና ከግልም አልፎ ለአገር እድገት እጅግ የጎላ አስተዋጽኦ ያለው ስለሆነ ከስልጠናው የተገኘውን እውቀትና ክህሎት እንዲሁም በአገርና በዓለም አቀፍ ያሉትን መልካም ተሞክሮዎች ወደ ተግባር በመቀየር ብሎም ለሌሎች ማህበረሰብ አርአያና ምሳሌ በመሆን የበኩላችንን ድርሻ ከተወጣን የምንፈልገውን ሁሉ በቅርብ ግዜ ማሳካት ይቻላል ብለዋል፡፡
በስተመጨረሻም አንዳንድ የስልጠናው ተሳታፊዎች እንደተናገሩት
645
ሰላም ጤና ይስትልን !!!
አዲስ ጋቢ (የ2014) ተማሪዎቻችን የመግብያ ቀናችሁን በሚቀጥሉት ሁለት ቀናት የምናሳዉቅ ስለሆና,
እስከዛዉም ከተሳሳተ መረጃ ተቆጥባችሁ በትግስት ጠብቁን።
645
#SalaleUniversity
ለ2014 ወደ ሰላሌ ዩንቨርሲቲ ለመግባት ያሰባቸው ተማሪዎች በሙሉ ስለ ግቢው አንዳንድ መረጃዎችን እንደሚከተለው ቀርቧል
#ሰላሌ_ዩንቨርሲቲ
1. የግቢ ብዛት ሁለት ካምፖሶች ሲኖሩት, የሚገኘው ሰሜን ሸዋ ዞን በፊቼ ከተማ ሲሆን። (ከአ.አ 112 ኪ.ሜ)
2, ዶርም በአሁኑ ሰዓት በአንድ ዶርም 6 ተማሪዎች ይመደባሉ።
3, የአየር ሁኔታ ወይናደጋማ ሲሆን እንዲሁም ማታ ላይ ቀዝቃዜ አዘል ንፋስ ያለው ሲሆን።
4, አንድ የተማሪዎች ላውንች በተመጣጣኝ ወጋና በግቢው ዙርያ ምግብ ቤትና ብና ቦታዎች ያሉት ሲሆን።
5, በሁለቱ ካንፓሶች መካከል የ10 ብር ባጃጅ ትራንስፖርት ማለትም ሁለት ባጃጅ የሚያስጠቅም ርቀት አላቸው።
📌 የትምህርት ፕሮግራም በአሁኑ ሰአት ሰላሌ ዩንቨርሲቲ የሚሠጣቸው 👇
፨college /department
👉college of health science ( @ #Abebach gobana campus )
1.Medicine
2.Public health
3.midwifery
4.medical lab
5.Nursing
👉colleges of:- Natural science , Social science, FB, Agricultural and School of law (@ #Genaral Tadesa biru campus the main one )
Computer science, Chemistry ,Physics, Biology ,Statics, Mathematics, Sport science, Geology
Agro-business and value, Agro-economic, plant science, animalscience, horticulture, Forestry, natural resources management, RDAE, veternery
Economics ,Marketing management, Accounting, Tourism and hotel management Management, Logistic,
Journalism, Afaan Oromo, Amharic, Civics, Sociology, Geographic, English, History and hertiege, Social anthropology,
Law
👉 በያዝነው አመት በተለያዩ ኮሌጆች ስር ብዙ የትምህርት ክፍሎችን ይጀመራሉ።
ወደ ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ ገብታችሁ መማር ያሰባቹህ ተማሪዎች ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ የሠላም አምባሳደር ስለ ሆነ ቤተሠቦቻቹህ በምንም ጉዳይ ስለ ሰላሙ ሳይሰጉ ተመርቃቹህ ትወጣላችሁ የሚል እምነት አለኝ።
የሰላሌ ዩንቨርሲቲ ተማሪዎች ሕብረት ዋና/ፕሬዚዳንት ተማሪ # ሞቲ ታምሩ 🙏🙏
645
ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ ለተፈጥሮ ሳይንስ ኮሌጅ መምህራን በ‘SPSS’ ላይ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ሰጠ። ስልጠናዉን ያዘጋጀው የስታትስቲክስ ትምህርት ክፍል ሲሆን ከተፈጥሮ ሳይንስ ኮሌጅ የተውጣጡ መምህራን ለተከታታይ አራት ቀናት በሰላሌ ዩኒቨርሲቲ ጄኔራል ታደሰ ብሩ ዋና ጊቢ ስልጠናውን ተከታትለዋል። የስልጠናዉን አላማ በማስመልከት አጭር ንግግር ያደረጉት የተፈጥሮ ሳይንስ ኮሌጅ ም/ዲን ዶ/ር ግርማ ሰላሌ መምህራኖችና ተመራማሪዎች ‘SPSS’ የመረጃ መተንተኛ ሶፍት ዌርን በመጠቀም ለሚያከናውኑት ምርምር ቀልጣፋና አስተማማኝ መረጃ ትንተና ዘዴን በቀላሉ መጠቀም እንዲችሉ የሚረዳ መሆኑን ገልጸዋል። የስታትስቲክስ ትምህርት ክፍል ሀላፊ መ/ር ደረጀ ገበየሁ በበኩላቸው ስልጠናው የተሰጠው በዩኒቨርሲቲያችን መምህራን በመሆኑ የራስን አቅም በራስ ማጎልበት እንደምሳሌ ሊጠቀስ የሚችል ተግባር መሆኑን ጠቅሰው በቀጣይነት ከሌሎች ኮሌጆች ጋር በመተባበር ለሁሉም የዩኒቨርሲቲው መምህራን ተመሳሳይ ስልጠና ለመሰጠት መታቀዱን ተናግረዋል።
በስልጠናው መዝጊ ስነስርአት ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዝደንት ዶ/ር ጸጋዬ ደዩ ሲሆኑ መምህራኖች ሙሉ ተመራማሪ ለመሆን ሁሉን አቀፍ የምርምር ክህሎት ማዳበር እንዳለባቸው ጠቅሰው ይሄንን አላማ ለማሳካት የስታትስቲክስ ትምህርት ክፍል የጀመረዉን ተግባር አድንቀዋል። ዶ/ር ጸጋዬ ሰልጣኝ መምህራኖች በነበራቸው የስልጠና ቆይታ ጥሩ የመማሪያና የመለማመጃ ጊዜ እንዳገኙና መደበኛ ስራቸውን ሳያስተጓጉሉ ስልጠናዉን በተሳካ ሁኔታ እንዳጠናቀቁ ሙሉ እምነት እንዳላቸውም ገልጸዋል። ስልጠና መውሰዱ በራሱ የመጨረሻ ግብ አለመሆኑን በመገንዘብ በስልጠናው ያገኙትን ክህሎት ወደ ተግባር በመቀየር የማህበረሰቡን ችግር የሚፈታ ምርምር ማካሄድ እንዳለባቸው ዶ/ር ጸጋዬ አሳስበዋል። ዶ/ር ጸጋዬ አክለውም ስልጠናዉን በራሳቸው ተነሳሽነት በማዘጋጀትና ባልተመቻቸ ሁኔታ ዉስጥ በተሳካ ሁኔታ ለማጠናቀቃቸው አመስግነው ወደፊት በሚሰጡ ስልጠናዎች የሴት መምህራኖችን ተሳትፎ ማሻሻል እንደሚገባ ጠቁመዋል።
በስልጠናው ተሳታፊ የነበሩትና አስተያየታቸውን የሰጡ አንዳንድ መምህራኖች ደግሞ በስልጠናው ላገኙት መሰረታዊ የSPSS አጠቃቀም ክህሎት አመስግነው በስልጠናው ያገኙትን ክህሎት ወደ ተግባር በመቀየር ለመጠቀም፣ እንዲሁም ለሌሎች ጓደኞቻቸውም ለማካፈል ዝግጁ መሆናቸዉንና ያገኙትን ክህሎት ለማደበር ቁርጠኝነታቸውን ገልጸዋል።
