fa
Feedback
መርጌታ ይኸይስ የባሀል መድሃኒት ቀማሚ እና

መርጌታ ይኸይስ የባሀል መድሃኒት ቀማሚ እና

رفتن به کانال در Telegram
981
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز
آرشیو پست ها
Harris J - Eid Mubarak Ft_ Shujat Ali Khan _ Off qnxYiaHRPFY.m4a4.28 MB

#ይህችን #ምርጥ #ቂሳ #ጋበዝኳችሁ!! ✍አንድ ጥበበኛ ሽማግሌ የወንዝ ዳር ላይ ቁጭ ብሎ ሳለ፤ ድንገት አንድ #ድመት ወንዝ ውስጥ ሲወድቅ ይመለከታል። ድመቱም ራሱን ከመስመጥ ለማዳን መንፈራገጥ እና ወደ ላይ ለመዝለል መሞከሩን ተያያዘው። ጥበበኛውም ሰው ይህን ድመት ለማትረፍ ይወስንና ለድመቱ እጁን ዘረጋለት።ድመቱም የሰውየውን እጅ ባጨረው። ሰውየው እጁ ሲቧጨር ጮኅ እና እጁን ቶሎ መለሰ። በጣም አመመው። ጥቂት ደቂቃ ቆይቶም፤ ለ2ኛ ጊዜ እጁን ድመቱን ለማትረፍ ዘረጋለት። በድጋሚ ድመቱ የሰውየውን እጅ በሃይል ቧጨረው። እጁን እያመመው ጮሆ ወደ ኋላ መለሰው። ከመጀመርያው የበለጠ በጣም አመመው። አሁንም ጥቂት ሰከንድ ቆይቶ እጁን ለ,3ኛ ጊዜ ዘረጋለት። የሆነ ሌላ ወጣት ይህን ድርጊት ከቅርብ ይከታተል ነበር። ወጣቱም ለሰውየው ድምፁን ከፍ አድርጎ በመጮህ እንዲህ አለው "አንተ ጥበበኛ ሆይ! ለምን ከ1ኛው እና ከ2ኛው ድርጊትህ አትማርም። ድጋሚ ለ3ኛ ጊዜ እጅህን ትዘረጋለህ!? ስትሞክር እየቧጨረህ አይደል እንዴ!!?" አለው። ሰውየውም የወጣቱን ንግግር ችላ ብሎ በተደጋጋሚ መሞከሩን ቀጠለበት። በስተመጨረሻም #ድመቱን ማትረፍ ተሳካለትና ከወንዙ ውስጥ አወጣው። በመቀጠልም ጥበበኛው ወደ ወጣቱ ተጓዘና እንዲህ አለው "አንተ ልጄ! ድመት በባህሪው ይቧጨራል፤ እኔ ደግሞ በባህሪዬ ትሁትና አዛኝ ነኝ። ታዲያ የሱ ባህሪ የኔን እንዲያሸንፍ እንድፈቅድለት ለምን ትፈልጋለህ!? አንተ ልጄ! ሰዎችን በባህሪህ እንጂ በባህሪያቸው አትኗኗር፤ ምንም ቢሆኑ፤ አንተን የሚጎዳ ብልሹ ምግባራቸው ቢበዛ እንኳ። ለነዚያ ያንተን ጥሩ ባህርይ እንድትተው ለሚፈልጉ ብልሹ ምግባሮች ቦታ አትስጥ። አንተ ሰዎችን ለማስደሰት ስትኖር፤አላህ አንተን የሚያስደስትህን ይልክልሃል። { የበጎ ምግባር ምንዳ ከበጎ ውጭ ሌላ ነውን!? }። አንተ የውብ ምግባር ባለቤት ሁን። ሰዎችን ያስደሰትክባቸውን ሁኔታዎች እያስታወስክ ሰውየው ትህትና የማይገገባው ቢሆን እንኳ አትፀፀት። በሚያውቅህ ሰው ህይወት ውስጥ ቆንጆ ነገር ሁን። በመልካም መልካምን የሚመነዳው ጌታ አላህ በቂህ ነው!!" መልዕክቱ.... ✍ #ኢብኑል #ቀይም እንዲህ ይላሉ " ዲን ሁሉም ስነ-ምግባር ነው፤ በጥሩ ምግባር የበለጠህ በርግጥ በዲንም በልጦሃል" ይህን አስተማሪ ታሪክ ሼር (ፎርዋርድ) ሼር ሼር!! https://t.me/susui_slamic_channal

#ተውበት ማረግ ለምን አስፈለገ? በነብዩላህ ሙሳ (ዐ.ሰ) ዘመን ዝናብ ጠፋና ነብዩ ሙሳ (ዐ.ሰ) ህዝቡን ይዘው ወደ አንድ ሜዳ ወጥተው አላህን (ሱ.ወ)መለመን ጀመሩ ። ከዚያ አላህ (ሱ.ወ) ለነብዩ ሙሣ (ዐ.ሰ) መልክት አወረደ ። ሙሣ ሆይ ! ከእናንተ መካከል እኔን ለ 40 ዓመት ያህል ሲያምፀኝ የኖረ ሰው አለና እሱ ራሱን አጋልጦ ወደ እኔ እስካልተመለሰ ድረስ ዝናብ አልሰጣችሁም " አለ ። በዚህ ጊዜ ነብዩላህ ሙሳ (ዐ.ሰ) ከህዝቡ መካከል ተነሱና " አንተ አላህን (ሱ.ወ) ለ 40 ዓመታት ስታምጸው የኖርክ የ አላህ ባሪያ ሆይ! በአንተ ምክንያት ነው ዝናብ የተከለከልነውና እባክህ ወደ አላህ ተመለስና እራስህን አጋንጥ " በማለት ጥሪ አደረጉ ።ሰውዬውም ራሱን በማውቁ ምክንያት "ጌታዬ ሆይ! በእኔ ምክንያት ይህ ሁሉ ሰው ተበድሏል እና ማረኝ አታጋልጠኝ " በማለት ወደ አላህ ተመለሰ ። አላህም (ሱ.ወ) በሰውዬው መመለስ ወዲያውኑ ዝናብን አወረደላቸው ። ነብዩላህ ሙሳም (ዐ.ሰ) " ጌታዬ ይህን ሰውዬ አሳየኝ" ብለው ሲጠይቁት አላህ (ሱ.ወ) ሙሳ ሆይ ! 40 ዓመታትን ሙሉ እኔን ሲያምፅ የደበኩትን ባሪያዬን አሁን ወደ እኔ ሲመለስ የማጋልጠው ይመስልሃልን" በማለት መለሰላቸው ። አዎ ! አላህ (ሱ.ወ) አይብን ሠታሪ ፈጣሪ ነው ። ይህማ ባይሆን ኖሮ የሰው ልጅ በምድር ላይ ባልኖረ ነበር ። ከዚህ ታሪክ የምንማረው ቁም ነገር ቢኖር በ አንድ ሰው ወንጀል ምክንያት አለም ሊታመስ ድርቅ ሊከሰት ፣ ዝናብ ሊቋረጥ የተለያዬ ቅጣቾች ሊከሰቱ እንደሚችሉ ነው ። ስለዚህ ሁላችንም ወደ ራሳችን እንመልከት ምናልባት እኔ ፣ አንተ ወይም አንቺ በሰራነው ወንጀል ምክንያት ይሆናል ይህ ሁሉ መከራ እየደረሰ ያለው ። ያረብ ማረን !! ተውበት ማድረግ ግዴታ ነው ! አዎ ተውበት ማድረግ በሰው ልጅ ላይ ባጠቃላይ ግዴታ ነው ። ምክንያቱም ያለ ወንጀል የሚያነጋም ሆነ የሚያመሽ ሰው የለምና ።አላህ (ሱ.ወ) እንዲህ ይላል ፦ (یااَّیُّهَا الَّذِینَ اَمَنُوا تُوبُوااِلَی اللَّهِ تَوْبَۃَّ نَّصُوحَّا...) "እናንተ አማኞች ሆይ ! ንጽሕ የሆነችን ጸጸት በመጸጸት ወደ አላህ ተመለሱ ..." (አት - ተህሪም 8) {...وَمَن لَّمْ یَتُبْ فَاَّولَاِكَ هُمُ الظَّالِمُنَ} "... ያልተጸጸተም ሰው እነዚያ እነሱ በዳዬቹ ናቸው ።" አዎ በደለኛ ላለመሆን ወደ አላህ (ሱ.ወ) ንፁህ የሆነን መመለስ ልንመለስ ይገባናል ። አቡ ሁረይራ (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት "የሰው ልጆች ሆይ ! ወደ አላህ ተመለሱ (ንስሀ ግቡ ) እኔ በቀን ከ 70 ጊዜ በላይ ወደ አላህ እመለሳለሁ " በማለት ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ተናግረዋል ። ( ሙስሊም ዘግበውታል ) አስቡት እስቲ ! ምንም ወንጀል የማያውቁት ምርጡ ነብይ ( ሰ.ዐ.ወ) ወደ ጌታቸው በቀን ከ 70-100 ጊዜ ከተመለሱ እኛስ በየሰኮንዱ ወንጀልን የምንሰራ ሰዎች ምን ያህል ነው ወደ አላህ (ሱ.ወ) መመለስ የሚጠበቅብን ? ዑለሞች ባጠቃላይ ተውበት ማድረግ በሁሉም ሰው ላይ ግዴታ መሆኑን ተስማምተዋል ። (ኢማሙል ቁርጡቢ ጃሚዑል አህካሙል ቁርዓን ጥራዝ 5 ገፅ 90ን ይመልከቱ ።) ሁልጊዜም ቢሆን ወንጀልን ስንሰራ የወንጀሉን ትንሽነት ሳይሆን የምናምጸውን አምላካችንን የአላህን (ሱ.ወ) ታላቅነት መገንዘብ ነው የሚገባን ። 🔵 የተውበት መስፈርቶች ትክክለኛ ተውበትን ለማድረግ የሚፈልግ ሰው የሚከተሉትን መስፈርቶችን ማሟለት ይኖርበታል ። እነዚህ መስፈርቶች ካልተሟሉ ወይም አንዱ ከተጓደለ ተውበቱ ተቀባይነት አይኖረውም ። መስፈርቶቹም አንደሚከተለው ናቸው ፦ 1 በፈፀመው ወንጀል መጸጸት (ነደም )፦ ነብያችን (ሰ.ዐ.ወ)እንዲህ ይሉናል {الذدم توبۃ} "መፀፀት በራሱ መመለስ ነው "(ኢብኑ ማጃእ ዘግበውታል ) 2, ሙሉ ለሙሉ ከወንጀሉ መፅዳት ፦ ከወንጀሉ ሲመለስ ምንም ነገር ማስቀረት የለበትም አጠቃላይ ሊፀዳ ይገባዋል 3, ዳግም በወንጀሉ ላይ ላይመለስ ቁርጥ ውሳኔን መወሰን 4, ወንጀሉ የሰው ሀቅ ካለበት ደግሞ የሰውን ሃቅ መመለስ ወይንም ከሰውዬው ይቅርታ መጠየቅ ይኖርበታል ። እነዚህን መስፈርቶች የማያሟላ ሰው ተውበቱ ተቀባይነት አይኖረውም ። ማንኛውም ሰው ተውበት ማድረግ ይፈልጋል ነገር ግን የተለያዩ ምክንያቶች ተውበት እንዳያደረሸግ መሰናክል ይሆኑበታል ። እነዚህን መሰናክሎች አስወግዶ የሚከተሉትን መንገዶች ከተጠቀመ በአላህ (ሱ.ወ) ፍቃድ ንፁህ ተውበት ማድረግ ይችላል ። 🔵 ተውበት ለማድረግ የሚረዱን መንገዶች 1, ንፁህ የሆነ ንያ ማድረግ (ኢኽላስ)ሊኖረን ይገባል ። ነብያችን (ሰ.ዐ.ወ) "ማንኛውም ስራ አላህ ዘንድ ኢኽላስ ከሌለው ተቀባይነት አይኖረውም" ብለዋል ። (ነሳኢ ዘግበውታል ።) 2, መጥፎን ስራ በመልካም ስራ ማስከተል ፦ አላህ (ሱ.ወ) እንዲህ ይላል {...اِنَّ الْحَسَنَاتِ یُذْهدِبْنَ السَّیَّاتِ} "...መልካም ስራዎች ኀጢአቶችን ያስወግዳሉና..."(ሁድ 114) 3,የሚሰራው ወንጀል ጉዳቱ በዱኒያም በአኼራም የከፋ መሆኑን መሰብ 4,ወንጀል (ሃጢአት)ከሚሰራበት (ከሰራበት) አካባቢ ወይም ቦታ መራቅ 5,በመልካም ስራ ላይ የሚያግዘው ጥሩ ጓደኛ መያዝ 6, ወንጀለኞችን በተመለከተ የሚናገሩ የቁርዓን አንቀፆችን ማንበብ 7, የአላህን (ሱ.ወ)ቅጣት ሃያልነት ማሰብ 8, ሁል ጊዜ አላህ(ሱ.ወ)ማስታወስ ማብዛት 9, የአላህን (ሱ.ወ) ሰፊ እዝነት ማስታወስ 10, አላህ(ሱ.ወ) ተመላሽ ባሮቹን እንደሚወድ መገንዘብ እነዚህንና መሰል ሂደቶችን ተግባራዊ በማድረግ ኢንሻ አላህ ንፁህ ተውበት ለማድረግ ያስችለናል ። Shar 👉Join 👇👇👇👇👇 https://t.me/susui_slamic_channal

ቁርኣን → ሁልጊዜ የማይሰለች ብቸኛው መጽሐፍ‼ ============================== ይህ ሰው ቁርኣንን ለታዳሚዎች የገለጸበት መንገድ ስለተመቸኝ አካፈልኳችሁ! || ✍ አንደኛ ክፍል ላይ የተማራችሁበትን መጽሐፍ ዛሬ ላይ ብትመለከቱት ምንም አይመስላችሁም። ጠቃሚ የሆነ አዲስ ዕውቀት አታገኙበትም። በየክፍል ደረጃው የተማራችሁበትን መጽሐፍ በተደጋጋሚ አንብባችሁ ከጨረሳችሁት ከሆነ ጊዜ በኋላ ትሰለቻላችሁ። ወይ ትሸጡታላችሁ ወይንም ለሌላ ትሰጡታላችሁ ወይንም ትጥሉታላችሁ! ቁርኣን ግን በአንድ የረመዷን ወር ውስጥ ብቻ ከ10 ዙር በላይ ብታነቡት፤ የመልዕክቱን ጥልቀት ተረድታችሁ አትጨርሱትም። በተመስጦ ከቀራችሁት እያንዳንዱ ዙር አዲስ ነው የሚሆንባችሁ። ከ60 አመት በላይ ቁርኣንን በመማርና በማስተማር እድሚያቸውን የፈጁ ሰዎች፤ ለነርሱ አዲስ ነው የሚሆንባቸው! ቁርኣን ከሁሉም መጽሐፎች በላይ ነው‼ ዘመን የማይሽረው ሁልጊዜም ተወዳጅ የበርካታ ዕውቀቶች ምንጭ የሆነ መለኮታዊ መጽሐፍ ነው። አላህ ከቁርኣን ሰዎች ያድርገን! ♠ ከታች የተያያዘው የዐረብኛ ቪድዮ የአማርኛና የእንግሊዝኛ ህዳግ አለው! https://t.me/susui_slamic_channal

ባል ና ሚስት በመሀላቸው ግጭት ተፈጥሮ አይነጋገሩም፡፡ ሁለቱም በረጅም ትዝታ ተውጠዋል፡፡ መጀመሪያ ማውራት ሽንፈት መስሎ ስለታያቸው ሳይነጋገሩ መተኛ ሰአታቸው ደረሰ፡፡ ድንገት ግን ባል አንድ ነገር ትዝ አለው፡፡ ነገ በጠዋት የስራ ስብሰባ ለመታደም ወደ ሌላ ሀገር ለመሄድ በረራ አለው፡፡ ሁሌ ደሞ ወደ ስራ ሲሄድ እንቅልፋም በመሆኑ የምትቀሰቅሰው ሚስቱ ናት፡፡ የነገው ስብሰባ እንዳያመልጠው" 11 ሰአት ቀስቅሺኝ " ብሎ በአፉ መናገር ሞት መስሎ ታየው እና ወረቀት ላይ " ነገ የስራ ስብሰባ ስላለብኝ ወደ ሌላ ሀገር እበራለሁ፡፡ አደራ 11 ሰአት ላይ ቀስቂሺኝ" ብሎ በወረቀት ላይ ፅፎ እሷ የምታይበት ቦታ አስቀምጦላት ምንም ቃል ሳይተነፍስ ተኛ፡፡ ጠዋት ሰውየው ከእንቅልፉ ሲነቃ ከጠዋቱ 3 ሰአት ሆኖ በረራውም ስብሰባውም አምልጦታል፡፡ እንዴት እንደዛ አስጠንቅቄ ነግሪያት አትቀሰቅሰኝም?" ብሎ በጣም ተበሳጨ፡፡ ከአልጋ ለመነሳት ሲሞክር አንድ ወረቀት ኮመዲኖ ላይ ተቀምጦ አየ፡፡ " 11 ሰአት ሞልቷል ተነስ ስብሰባው እንዳያመልጥህ " የሚል ፅሁፍ ተፅፎበታል፡፡ ☞ ማነው ስተት የሰራው? ማነውስ ልክ? ወዳጄ ሴትን ልጅ በተንኮልም ሆነ በፍቅር ልትበልጣት አትችልም፡፡ ዝምታ ደሞ መቼም መፍትሄ ሆኖ አያውቅም፡፡ https://t.me/susui_slamic_channal

አንዱ አላህን ፈሪ ወንድማችን በጣም የሚወዳትን ልጅ እንዲህ ሲል ተሰናበታት አስተማሪ ነው ኢንሻ አላህ እንደምንጠቀምበት ተስፋ አደርጋለሁ። 📨 እንዲህ እየናፈቅሽኝም ቢሆን ላገኝሽ አልፈልግም ምክንያቱም እኔ ጌታየን ተገናኝ መሆኔን አውቃለሁ አውቃለሁም ላስተዳድርሽ አልችልም እንዲሁም ላገባሽ ሀቅም ስለሌለኝ ውበትሽ መፈተኛየ ነው ስለዚህ ወዳንቺ እየተሳብኩ አንችን ወደኔ አላቀርብሽም ሀራም በሆነ መልኩ ቀርቤሽ ባገኝሽ ተሸናፊው እኔ ነኝ ታዲያ ለምን እቀርብሻለሁ እናም ወደ ጌታየ ስደትን ስጀምር ስንቄ ተቅዋ(አላህን ፍራቻ) እንዲሆን ፈላጊ ነኝ። አየሽ አንዳንዱ በገንዘቡ ወዳጆቹን ያቀርባል ሌላው በቁንጅናው ቁንጅናዎችን ይጠራል እኔ ግን ላንቺ ያለኝን ፍቅር ሰውቼ የጌታየን ፍቅር ማግኜት እፈልጋለሁ   ብቀርብሽ እንደምትጠጊኝ እርግጠኛ ሁኜ ሳለ እርቅሻለሁ ምክንያቱም እኔ ጌታየን የበለጠ በጥሩ ስራ መቅረብ እፈልጋለሁ አዎ የእርሱ ፍቅር የእርሱ እርዳታ አንችን እንደሚያስረሳኝ አምኜም ደህና ሁኚ እልሻለሁ ደህና ሁኚ እኔ ወደ ጌታየ ሂያጅ ነኝ መንገዴንም ይመራኛል የአላህ ፍቃድ ከሆነ ዘለዓለማዊ በሆነው ሀገር (ጀነት) እንገናኛለን። ❗️❗️❗️❗️❗️❗️❗️❗️ አላሁ አክበር❗️ አየህ አንተ የአኼራ ጓደኛየ ስማሽ እህቴ ዱንያ አላታለለችውም ሴት ልጅም አልፈተነችውም ስማሽ ሰማህ ይሄ ወንድማችን ስሜቱን እንዴት ለአላህ ብሎ መቆጣጠር እንደቻለ እንማርበት ካለፈው ያልተማረ ሌላ በምን ሊማር ይችላል። እንደዚህ ወንድማችን ወደ ትዳር መግባት ካልቻልን ከሀራም ፍቅር መራቅ አለብን ለሚያልፍ ስሜት አላህን አናምፀው። ወላሂ የስሜት ጥፍጥናው ሳያልቅ ምሬቱ ያደፈርሰዋል ማለትም ስሜታችንን ተቆጣጥረን ፈተናውን መወጣት ካልቻልን ባጭር ጊዜ አላህ ብቻ የሚያውቀው ጭንቀትና ቁጭት ነው ሚለቅብን እና ስሜታችንን እናሸንፈው። አንተ ወንድሜ አንቺም እህቴ ዱንያ ናት አውቃለው ወጣትነት ፈተናው ከባድ ነው ግን ከአላህ ያለውን ውድ ሀገር ጀነት ለሚፈልግ ፈተናዎቹ ቀላል ናቸው ምክንያቱም ክፍያው ውድ እንደሆነ ያውቃል ክፍያዋም ጀነት ናት። ይህቺ እድሜ ደግሞ ተመልሳ አትመጣም። ደስታ በሃራም ፍቅር ውስጥ ትንሽና ጊዜያዊ ነው እኛ ግን ትልቅ ደስታ እንዳለ ነው ምናስበው ግን በጣም ትንሽ ነው ከግዜ በኋላ አላህ ብቻ የሚያውቀው ጭንቀትና ቁጭት ነው ሚለቅብን ለምን ይሄን አደረኩ ለምን ለምን እያልን እራሳችንን መውቀስ እንጀምራለን ምክንያቱም የሸይጧን መንገድ ነው። ወላሂ ምንም ኸይር ነገር የለውም ልብ ማድረቅ ግዜን መግደል ገንዘብ ማጥፊያ አላህን ማመፅ ብቻ ነው ትርፉ። ግን ይሄን ፈተና አላህ ካዘነላቸው በቀር ፈተናውን ይወድቃሉ ሸይጧንም ይስቅባቸዋል። እና ስሜታችንን ያዝ አድርገን ጀነትን በማሰብ ወጣትነታችንን እንጠቀምበት አላህን የበለጠ ለማወቅና ለመገዛት ጀነትንም ለመውረስ እንቻኮል።   ፍቅር ወዳቂ ነው የአላህ ፍቅር ግን ሁሌም ህያው ነው በሁለቱም ሀገር አይወድቅም። ወላሂ በሃራም ተነካክተህ ተነካክተሽ ትዳር ውስጥ ብትገቢም አላህ ለትዳርሽ ጥፍጥና አይሰጥሽም እና እንዴት ነው ልጆችሽን በንፁህ መንፈስ ማሳደግ ምትችይው ልጆችሽ ያንችን በሀራም ያሳለፍሽውን አይነት ጊዜ እንዲያሳልፉ ትፈልጊያለሽ❓ አትፈልጊማ እና እራስሽን ሳታስተካክይ እንዴት ነው ልጆችሽን ማስተካክል የምትችይው አንተስ ወንድሜ እንዴት ነው ቁጥብ የሆኑ የዚህ ዲን የበላይነት የሚያስመልሱ ልጆችን ማፍራግ ምትችለው በዚህ በሀራም መንገድ ተገናኝተህ።   እስኪ ጠንካራ እንደሆንሽ ለውስጥሽ አሳምኝውና ከዚህ የሃራም ፍቅር ውጪ ወይም ባስቸኳይ ወደ ትዳር ቀይሪው። ወላሂ አላህ ያግዝሻል እስካሁን የሰራሽውንም ወንጀል አላህ ይምርሻል ወደ አላህ ከተመለሽ። አስታውሽ እህቴ አስታውስ ወንድሜ ከወንጀል የተመለሰ ልክ ወንጀል እንደሌለበት ነው ኧረ እንደውም አላህ ይደሰትበታል። አላህ ተመላሾችንና ተጥራሪዎችን ይወዳል። 👉 ጓደኛሽ ወይም በሃራም ፍቅር አብሮሽ ያለው ሰው ጠንካራ ሁኖ እራሱን አሸንፎ ከዚህ የሃራም ፍቅር ሊያስወጣሽ ካልቻለ አንቺ ጠንካራ ሁነሽ ለመራቅ ሞክሪ ይሄን ስታደርጊ ጓደኛሽ ከተቃወመሽ ከጠላሽ ከመጀመሪያውም አይወድሽም ማለት ነው ግን ይሄን ስታደርጊ ደስተኛ ሁኖ ወደ ሀላል(ትዳር) ለመቀየር ከቻለ የእውነት ይወድሻል ማለት ነው። ወይም ሊያገባሽ ሳይችል ቀርቶ ግኑኝነቱን ካቆመ ይወድሻል ማለት ነው ምክንያቱም ወደ አላህ እያቃረበሽ ነው። እና በዚህ ማረጋገጥ ትችያለሽ ግን ብዙዎች ለሀራም ነገር እስከሚያመቻቹሽ ድረስ ነው አብረውሽ ያሉት። ☞ የቀረውን እናስተካክል ያለፈውን ይምረናል ካልሆነ ግን ባለፈውም በቀረውም እንያዛለን።   እንቻኮል ወደ አላህ ባረከላሁ ፊኩም። 👇👇👇join https://t.me/susui_slamic_channal

#ዘፈን - የሰይጣን መዝሙር ዘፈን (ሙዚቃ)ለሌሎች ወንጀሎች መንገድ ከፉች የሆነ ፣ አላህን(ሱ.ወ) እንዳንፈራው ፣ ከኢስላም መንገድ እንድንወጣና ፣ የአላህን( ሱ.ወ) ውዴታ እንዳናገኝ የሚያደርገን የሰይጣን መዝሙር ነው ።እነሆ ዘፈን አለማችንን አናግቷል ፣ፍትህን አሳጥቷል ታማኝነትን አጥፍቷል ባሪያውን ከ ጌታው ጋር አራርቋል ፣የቀልብ ድርቀትን አስከስቷል ፣ ከማህበረሰቡ ላይ ሃያዕ(ዕፍረትን )አንስቷል ። ዛሬ አለማችን ላይ በሰዎች ቀልብ ውስጥ ከቁርአን በላይ ተፅዕኖን ፈጥሯል ፣የሰዎች ማንነት ሙሉ በሙሉ አሳጥቷል ። የቱ ተወርቶ የቱ ይተዋል ? ዘፈን በማህበረሰቡ ላይ የፈጠረውን ተፅዕኖ ሁሉም በየእራሱ ይቁጠረው ። ዘፈን በእኔ ህይወት ላይ ምን ተፅዕኖ ፈጥሯል? ብለን እስቲ ራሳችንን እንጠይቅ ። ወላሂ ከዚህ ቀደም ታናሽ ታላቁን ፣ጃሂል አሊሙን ፣ ሚስት ለባሏ ባል ለሚስቱ ፣ ልጅ ለወላጅ ፣ ወላጅ ለልጁ ወዘተ...ይተዛዘንና ይከባበር ነበር ። አሁንስ ? አሁንማ ሰዎች በፊልም ፣ዘፈን ፣በተለያዩ ሃራም በሆኑ ተግባራት ላይ ሲዘፈቁ አላህ (ሱ.ወ) ሃያዕን (እፍረትን ) ከላያቸው ላይ አነሣባቸውና ይህ ሁሉ መተዛዘን ፣ መከባበር ፣መረዳዳት ቀረ ። ነብያችን (ሰ.ዐ.ወ) "ለታናሾቹ ያላዘነ ታላቆቹን ያላከበሰ ከእኛ አይደለም " ብለዋል አንዳንዱ የሱዳንዘፈንና የአረበኛ ዘፈን ሲያዳምጥ ቁርአን እየቀሩ እንጂ እየዘፈኑ የማይመስለው አለ ። ልናውቅ የሚገባው ዘፈን ዘፈን ነው አረበኛ ፣ ሱዳነኛ ፣ ስልጠኛ ፣ ትግረኛ ፣ ኦሮምኛ ዘፈን ከሆነ ያው ዘፈን ነው ። (واسْتَفْزِزْ مَنِ اسْتَطَعْتَ مِنْهُم بِصَوْتِكَ وَاَّجْلِبْ عَلَیْهِم بِخَیْلِكَ وَرَجِلِكَ وَشاَرِ كْهُم اْلاَّمْوَالِ والْاَّوْلاَدِ وَعِدْهُم وَماَ یَعِدُهُمُالشَّیْطَنُ اِلاَّ غُرُورََ) (۱۷:٦٤) "ከእነሱ የቻልከውን ሰው በድምጽህ አታል ። በእነሱም ላይ በፈረሰኞችህ ፣ በአሸግረኞችህም ኾነህ ለልብ ። በገንዘቦቻቸውም ፣ በልጆቻቸውም ተጋራቸው ፣ ተስፋ ቃልም ግባላቸው ። ሰይጣንም ማታለልን እንጂ ተስፋ ቃልን አይገባላቸውም ።" ( አል - ኢስራዕ 64) ቡኻሪ በዘገቡት ሃዲስ ነብያችን (ሰ.ዐ.ወ)"አንድ ሰው በሞተበት ሁኔታ ላይ ሆኖ ነው የሚቀሰቀሰው " ብለዋል ። በሌላ ሐዲስም "አንድ ሰው የሚቀሰቀሰው ከወደደው ጋር ነው"ብለዋል ። ይህ ማለት ዘፋኝንና ዘፈንን የወደደ ከዘፋኙ ጋር ይቀሰቀሳል ፤ነብዩን (ሰ.ዐ.ወ) የወደደ ፣ ፈለጋቸውን የተከተለ ከእርሳቸው ጋር ነው የሚቀሰቀሰው ። እና ውድ ወንድምና እህቶቼ! እንደው በ አላህ ይሁንባችሁ ከአንድ ተራ ዘፈኝ ጋር ነው ወይስ ከውዱ ነብያችን (ረ.ዐ.ወ) ጋር ነው መቀስቀስ የምንፈልገው? የሁላችንም መልስ " ከነብያችን (ሰ.ዐ.ወ) ጋር ነው " የሚል መሆኑ አይጠረጠርም ። ይህ ከሆነ መልሳችን መፍትሔው ነብያችንን(ሰ.ዐ.ወ) ወደን ብቻ ሳይሆን መስለንም መገኘት ስንችል ብቻ ነው ከእርሳቸው ጋር መቀስቀስ የምንችለው ልብ በሉ ፦ ⏺ ዘፈን ከአላህ (ሱ.ወ)ጋር ያጣላል ⏺ ዘፈን ከነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) መንገድ ያስወጣል ⏺ ዘፈን ቁርአንን ያስረሳል ( ከውስጥ ያወጣል) ⏺ ዘፈን ቀልብ ያደርቃል (ይገላል) ⏺ ኢማንን ያተናል ⏺ ዘፈን ሃያዕ (እፍረትን)ከላያችን ላይ ያነሳል ⏺ ዘፈን ሌላ ወንጀሎችን ይጠራል ⏺ ዘፈን ክብረ ቢስ ያረጋል ወዘተ... ምኑ ተወርቶ ምኑስ ይተዋል! ኢብኑ ቀይም "በዘፈን ምክንያት ስንትና ስንት ጨዋ ሴትና ጨዋ ወንዶች ናቸው ዝሙተኛ ሆነው የቀሩት " ብለዋል ። ይህን ተግባር ደግሞ ቤት ይቁጠረው ለዘፈን የምንጠቀምበትን ድምፃችንን ለ ቁርአን ብንጠቀምበት ነገ የውመል ቂያማ ከታላላቅ መላኢካዎች ተርታ እንደምንሆን እናውቃለን ? #ሰለፍቻችን ስለ ዘፈን ምን ይላሉ? ➡️ አቡበክር ሲዲቅ(ረ.ዐ) የሸይጧን መዝሙር ብለው ይጠሩት ነበር ➡️ ኢማሙ ማሊክ (ረ.ሂ) "ስለ ዘፈን ምን ትላለህ ?" ተብለው ሲጠየቁ "ፋሲቅ (ከመንገድ የወጣ ሰው )ካልሆነ በስተቀር አይተገብረውም በማለት መልሰዋል ። ➡️ ኢማሙ ሻፊኢይ (ረ.ሂ) "ደዩስ +ቅናት የለሽ )ያደርጋል" ብለዋል ደዩስ ሰው ደግሞ ጀነት አይገባም። ➡️ ኢማሙ አቢ ሃኒፋ (ረ.ሂ)ስለ ዘፈን ሲጠየቁ "እሱ ሃራም ነው ጅማሬው ከሰይጣን የመነጨ ሲሆን ፍፃሜው የአላህን (ሱ.ወ) ቁጣ ማትረፍ ነው"ብለው መልሰዋል ። ➡️ የዚድ ቢን ወሊድ (ረ.ሂ)"ዘፈንን አደራችሁን እሱ እፍረትን ያስወግዳል ፤ ወደ ስሜት ይገፋፋል ፤ የሰውዬውን ክብር (ስብዕና) ይንዳል በማለት ያስጠነቅቁ ነበር። ➡️ የተወሰኑ ሰለፎች(ቀደምት ትውልዶች )ሲናገሩ ዘፈን ቀልብ ላይ ኒፋቅን (ጥመትን) ያበቅላል ፤ በህዝቦች ላይ እፍረትን ያጠፋል እንዲሁም ውሸትን ያስፋፋል የሰዎችን ክብርም ያነሳል ( ክብረ ቢስ ያደርጋል ) ብለዋል ። ➡️ ኢብኑ ተይሚያ ፦ "አራቱም መሪዎች(ከላይ የጠቀስናቸውን ማለት ነው ) ዘፈን ሃራም በመሆኑ ተስማምተውበታል "ብለዋል ። ኢብኑ አባስ (ረ.ዐ) ፣ኢብኑ መስዑድ (ረ.ዐ) ፣ጃቢር ቢን አብደላህ(ረ.ዐ) ፣ሸይኹል ኢስላም ቢን ተይሚያህ(ረ.ሂ) ወዘተ...እንዲሁም የዘመናችን ዑለምች እንደ ኡሰይሚን ፣ ፈውዛን ፣ ኢብን ባዝ አሊ ባጠቃላይ ዘፈንን አጥብቀው ከልክለዋል ። #ዘፈንን ለመተው የሚያግዙን ሁኔታዎች አንድ ሰው ከዘፈን ወጥመድ ለመውጣት የሚከተሉትን ሁኔታዎች በሚገባ ማስተዋልና መተግበር ይኖርበታል ። ይህን ተግባራዊ ካደረገ በአላህ (ሱ.ወ) ፍቃድ ይሳካለታል 1 የአላህ (ሱ.ወ) ውዴታ ውስጣችን እንዲገባ ማድረግ 2 አኼራን (መጪውን አለም )ማስታወስ 3 በዱንያ ላይ መስገብገብን ማስወገድ 4 የነብያችንን (ሰ.ዐ.ወ) ፈለግ መከተል 5 መጥፎ ጓደኛን መራቅ 6 አላህን(ሱ.ወ) በብዛት ማውሳት(ዚክር ማብዛት ) 7 ወደ ዕውቀት ገበታዎች መጓዝ 8 ሰደቃን ማብዛት 9 ከዑለሞች (አላህን (ሱ.ወ) ፈሪ ከሆኑ ሰዎች ) ጋር መቀማመጥን ማብዛት ምንጭ፦ ፍቅርህ አሸነፈኝ ከሚል መፀሃፍ የተወሰደ እናንተም ባነበባችሁት እኔም በፃፍኩት ተጠቃሚ ያርገን አሚን shar/Join 👇👇👇 https://t.me/susui_slamic_channal

💜 አንዲት እናት ወደ አንድ ሸይኽ ፈትዋ ለመጠየቅ ትመጣና ለሸይኹ " ሸይኽ ሆይ የልጆቼ እንቅልፍ በጣም ከባድ ነው ፣ ለፈጅር ሰላት እነሱን መቀስቀስ ደከመኝና ምንድነው መፍትሄው? " በማለት ጠየቀች ። ๏ ሸይኹም " ሙቀት መቆጣጠሪያው ተቃጥሎ እሳት ቢተፋ ኖሮ ምን ታደርጊ ነበር? " አላት ๏ እናት " እቀሰቅሳቹኋለሁ " አለች ๏ ሸይኹ " ግንኮ እንቅልፋቸው ከባድ ነው " አላት ๏ እናት " በአላህ ይሁንብኝ አንገታቸውን እየጎተትኩ ቢሆንም እቀሰቅሳቸዋለሁ " አለች ๏ ሸይኹ " ይህን የምታደርጊው ከዱንያ እሳት ልታድኚያቸው ነው ፣ ልክ እንደዛውም ከአኺራ እሳት ለማዳን ቀስቅሺያቸው " አላት ። (يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا قُوا أَنْفُسَكُمْ وَأَهْلِيكُمْ نَارًا وَقُودُهَا النَّاسُ وَالْحِجَارَةُ عَلَيْهَا مَلَائِكَةٌ غِلَاظٌ شِدَادٌ لَا يَعْصُونَ اللَّهَ مَا أَمَرَهُمْ وَيَفْعَلُونَ مَا يُؤْمَرُونَ) " እናንተ ያመናችሁ ሆይ! ነፍሶቻችሁንና ቤተሰቦቻችሁን መቀጣጠያዋ ሰዎችና ደንጋዮች ከሆነች እሳት ጠብቁ ፡፡ በእርሷ ላይ ጨካኞች ፣ ኀይለኞች የሆኑ መላእክት አልሉ ፡፡ አላህን ያዘዛቸውን ነገር (በመጣስ) አያምጹም ፡፡ የሚታዘዙትንም ሁሉ ይሠራሉ ፡፡" [ተህሪም 6] 👇👇👇join https://t.me/susui_slamic_channal

የነፍስ አድን ጥሪ ሃያት ቲክቶክ ከገባችበት የህይወት አደጋ እንታደጋት፡፡ ሳታዳምጡ ምንም አይነት አስተያየት እንዳትሰጡ በአላህ ስም እጠይቀችኋለሁ፡፡ https://t.me/susui_slamic_channal

ሙስሊሟ እህቴ ሆይ! በዚህ ዘመን የኢስላም ጠላቶች ሂጃብሽን አስወልቀው ከተራ ዱርየዎች ተርታ ሊያሰልፉሽ ተዘጋጅተዋል፡፡ ለዚህ ተንኮላቸው ደግሞ ከፍተኛ ሚና የሚጫወቱት ቴሌቪዥኖች፣ ሞባይሎች ፣ ጋዜጦች እና የተለያዩ ሚዲያዎች ናቸው፡፡ በመሆኑም አንዲት ሙስሊም ሴት አላህ ባዘዛት መሰረት ቀጥ ካለችና ሒጃቧን ባግባቡ ከለበሰች በኢማኗ ጥንካሬ የሚከሰቱ ውዝንብሮችን እና የሰይጣን ተንኮሎችን በአላህ ፈቃድ ትከላከላለች፡፡ ከዚሀ ቦታ የኡሙ ሰለማን ረዲየሏሁ ዐንሃ ጠንካራ ባህሪ ማስተዋል ይቻላል፡፡ ረሡል ﷺ ልብሱን በኩራት እየጎተተ ስለሚሄድ ወንድ ስለሚያጋጥመው ቅጣት በተናገሩ ጊዜ ኡሙ ሰለማ ረዲየሏሁ ዐንሃ ሴቶች ምን ማድረግ እንዳለባቸው ስትጠይቅ “አንድ ስንዝር ታስረዝም” አሏት “እንደዛ ከሆነማ እግሮቻችን ይገለጣሉ” አለቻቸው፡፡ “በቃ አንድ ክንድ ታስረዝም ከዚህ በላይ እንዳትጨምር” በማለት ምላሽ ሰጡ፡፡ አህመድ፡ ቲርሚዚይ፡ 1731 ነሳኢይ 5336 ኢማኗ የደከመባት ሴት በተቃራኒው አንድ ስንዝር ወይም አንድ ክንድ ወይም ከዚያ በላይ እንደ ኢማኗ ድክመት አካሏን ትገልጣለች፡፡ ለቅኑ ጎዳና እንዲመራሽ ፤ ግልጽም ከሆነ ስውር ፈተና እንዲጠብቅሽ ፤ እርሱን በመታዘዝ ላይ እንዲያግዝሽ ፤ በሐቁ ላይ እንዲያጸናሽ አላህን እማጸናለሁ፡፡ እነሆ አላህ ዱዓን ሰሚና ተቀባይ ነውና ፡፡ ከሼይኽ አብድረዛቅ በድር ሀፊዘሁሏህ ኪታብ የተወሰደች..!! https://t.me/susui_slamic_channal

ኢና አዕጠይና ከልከውሰር... የዚህች ሱራ ታሪክ . ሁላችንም እንደምናውቀው ለረሱል ሰዐወ ሶስት ወንድ ልጆች ነበሯቸው።በጣም እሚዐጅበው ሁሌም ወንድ ልጅ ሲወልዱ ወድያው ይሞትባቸው ነበር ሰዐወ... የሆነ ቀን ረሱል ሰዐወ በመካ ከተማ ሲዘዋወሩ አንድ ሙሽሪክ ይመለከታቸውና፦" አንተ አብተር (ዘሩ ማይበረክትለት)" ብሎ አፌዘባቸው። ማለትም ዘርህን ካልተካህ ልክ ስትሞት ትረሳለህ። ምክንያቱም ባንተ የሚጠራ ልጅ ስለሌለህ እሚያስታውስህም የለም። እሳቸው ደግሞ ስማቸውን ሚያስጠራ ልጅ አልበረክት ብሏቸው አንዱ ሲሞት ሌላው እየተከተለ ልጅ አልባ ሁነዋል። ረሱል ሰዐወ ይህን ሲሰሙ ሀዘን ወረራቸው። ይህን ግዜ አላህም፦"ኢና አዕጠይና ከልከውሰር...." የምትለዋን ሱራ አወረደላቸው። ሙሀመድ ሆይ!!! እኛ ከውሰር የተባለን ጅረት ሰጥተንሃል። ከውሰር ማለት ጀነት ውስጥ የሚገኝ ጅረት ሲሆን፤ ካንተ ሌላ ማንም አይቀምሰውም። በሚያፌዙብህ ነገር እንዳታዝን... ሰላትህንም ስገድ እርዶችንም እያረድክ ለድሆችም አከፋፍል። ሙሀመድ ሆይ!!! ያ አንተን (ዘረ ማይበረክትለት) ብሎ የዘለፈህን ሰውዬማ እሱን ራሱ ዘር አልባ አደርገዋለሁ። የቂያማ እለት ስለሱ ሚያወሳም እሱን ሚጠይቅም ስለሱ ዱንያ ላይም እንዳይወሳ አድርጌ እተውልሃለሁ። ይህን ግዜ ረሱል ልባቸው በሀሴት ተሞላ። እንዴት አይደሰቱ...!!!? አላህ ምንም እንኳን ወንድ ልጅ ቢከለክላቸውም በጀነት ከውሰርን አዘጋጅቶላቸዋል። በስማቸው ሚጠራ ወንድ ልጅ ባይኖራቸውም ለ1439 ያህል አመታት እስካሁን ድረስ ቀን ማታ፦"ነቢ...ነቢ..." እያለ በብዙ ቢልየን ሰለዋት ሚያወርድ ኡመት ሰጥቷቸዋል። https://t.me/susui_slamic_channal

👉 የጀናዛ ብልት ውስጥ እጇ አልወጣ ያለች ሴት! .........መዲና ውስጥ አንዲት ሴትዮ ትሞትና ጀናዛዋ መታጠብ ይጀምራል በድንገት የአጣቢዋ ሴት እጅ ከጀናዛው ብልት ጋር ተጣብቆ አልላቀቅም አለ መዲና ውስጥ ያሉ ኡለማዎች የአጣቢዋ እጅ ይቆረጥ ወይስ የጀናዛው ብልት በሚል ከፍተኛ ውዝግብ ውስጥ ገ ቡ በዚህ ጊዜ ነበር ለእንግድነት ለመጡት ኢማሙ ማሊክ ይህ ጥያቄ የቀረበው እሳቸውም ወደ አጣቢዋ በመዞር .......see more ወላሂ ውሸት አደለም ገብተው ያንብቡት ከስር ነክተው ሙሉውን ለማንበብ 🄾🄿🄴🄽 ሚለውን ተጫኑ።

⚡️ብዙዎቻችሁ ይሄ Bot fake ነዉ እያላችሁ ነዉ ግን አመኑኝ 100%ይሰራል 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://telegram.me/ask_anything_ethiopia_bot?start=i487784393 ⚠️ መርሳት የሌለባችሁ ነገር Start ካላችሁ በዋላ Join Channel ማለቱ የግድ ነው

ያልተፈቀደልህን ሴት የምታበላሸው ወንድሜ ሆይ! ነገ ራቁትህን ሁነህ ጌታህ ፊት በሰራሃት የዝሙት ወንጀል እንደምትተሳሰብ አስታውስ.!? አላህን ፍራ! ከቻልክ አግባ ካልቻልክ ፁም!!! ግልባጭ ትዳር ሲሏት በመጥፎ ስራዋ ማፈርና መሣቀቅ ተውበት ማድረግ ሲገባት=>ጓደኛ<= አለኝ!❗️እያለች ትዳር ፈላጊ ጥብቅ እህቶቻን ሣይቀር በመጥፎ እንድጠረጠሩ ምክንያት ለምትሆነው Share share share -------------------- http://t.me/susui_slamic_channal ----------------------------- 🍀🍀🍀 በቴሌግራም ይ🀄️ላ🀄️ሉን! ➢👇👇👇 http://t.me/susui_slamic_channal

👉 የጀናዛ ብልት ውስጥ እጇ አልወጣ ያለች ሴት! .........መዲና ውስጥ አንዲት ሴትዮ ትሞትና ጀናዛዋ መታጠብ ይጀምራል በድንገት የአጣቢዋ ሴት እጅ ከጀናዛው ብልት ጋር ተጣብቆ አልላቀቅም አለ መዲና ውስጥ ያሉ ኡለማዎች የአጣቢዋ እጅ ይቆረጥ ወይስ የጀናዛው ብልት በሚል ከፍተኛ ውዝግብ ውስጥ ገ ቡ በዚህ ጊዜ ነበር ለእንግድነት ለመጡት ኢማሙ ማሊክ ይህ ጥያቄ የቀረበው እሳቸውም ወደ አጣቢዋ በመዞር .......see more ወላሂ ውሸት አደለም ገብተው ያንብቡት ከስር ነክተው ሙሉውን ለማንበብ 🄾🄿🄴🄽 ሚለውን ተጫኑ።

ያልተፈቀደልህን ሴት የምታበላሸው ወንድሜ ሆይ! ነገ ራቁትህን ሁነህ ጌታህ ፊት በሰራሃት የዝሙት ወንጀል እንደምትተሳሰብ አስታውስ.!? አላህን ፍራ! ከቻልክ አግባ ካልቻልክ ፁም!!! ግልባጭ ትዳር ሲሏት በመጥፎ ስራዋ ማፈርና መሣቀቅ ተውበት ማድረግ ሲገባት=>ጓደኛ<= አለኝ!❗️እያለች ትዳር ፈላጊ ጥብቅ እህቶቻን ሣይቀር በመጥፎ እንድጠረጠሩ ምክንያት ለምትሆነው Share share shar ----------------------------- 🍀🍀🍀 በቴሌግራም ይ🀄️ላ🀄️ሉን! ➢👇👇👇 http://t.me/susui_slamic_channal

#የቲሙ_አህመድ አንድ አከባቢ ይገዛና ያስተዳድር የነበረ ንጉስ ነበር። የዚህ ንጉስ አገልጋዮች ከዕለታት አንድ ቀን በመንገዳቸው ላይ አንድ ህጻን ልጅ ያገኙና ይዘውት ወደ ንጉሱ ይሄዳሉ። ንጉሱም ከቤተሰቦቹ ጋር ተቀላቅሎ አብሮ እንዲያድግ አዘዘ። ስሙንም የቲሙ አህመድ ሲል ሰየመው ። . ይህ ህጻን እያደገ በመጣ ጊዜ ብልህነትና ቅልጥፍና ይታይበት ጀመር። ይህን የተመለከተው ንጉሱም ተገቢውን ትምህርትና ስልጠና እንዲወስድ በማድረግ ከባለሟሎችና ቤት ውስጥ ካሉት አገልጋዮች በሙሉ እሱን በማስቀደም የቅርብ ባለሟሉ አደረገው። ከዕለታት አንድ ቀን ይሄ ንጉስ ከቤተ መንግስት ባንዱ ክፍል እቃ እንዲያመጣለት ያዘዋል። ወደታዘዘበት ቦታ በሚሄድበት ጊዜ አንዲት የንጉሱ አገልጋይ የሆነች ልጃገረድ ከአንድ የቤተ መንግስቱ ሰራተኛ ጋር ያልተገባ የሆነ ድርጊትን(ዝሙት) ስትፈጽም ተመለከተ። የቲሙ አህመድ እንደተመለከታት የተረዳችው ይህች ልጃገረድ ወደእሱ እሩጣ በመምጣት የተመለከተውን ነገር ለንጉሱ ባለመንገር እንዲተባበራት ተማነጸነችው። ይህንንም የሚያደርግላት ከሆነ እራሷን አሳልፋ ለሱ እንደምትሰጥ ደጋግማ ቃሏን ሰጠችው። አህመድም ንግግሯን ካደመጠ በኃላ "እኔ ንጉሱን ከማታለል በአላህ እጠበቃለሁ በእርግጥ እርሱ ለኔ መልካም የዋለልኝ ሆኖ ሳለ!" በማለት ትቷት ሄደ። . ልጃገረዷ በውስጧ ፍርሀት አደረባት፤ ሚስጥሯንም የሚያሰራጭባት መስሎ ታያትና እያለቀሰችና እሮሮ እያሰማች ወደ ንጉሱ ሄደች። ንጉሱም ምን እንደሆነች ሲጠይቃት የቲሙ አህመድ አስገድዶ ሊደፍራት እንደሞከረ ነገረችው። በዚህ ጊዜ ንጉሱ በጣም ተቆጣ አህመድንም ለመግደል ወሰነ። ለዋና አገልጋዩም እንዲህ ሲል ትዕዛዝ ሰጠው፦ "የሆነን ሰው የሆነ ነገር እንዲያመጣ ወደአንተ በላኩት ጊዜ በቀጥታ ግደለውና ጭንቅላቱን ወደእኔ ላካልኝ" አለው። . ከቆይታ በኃላም አህመድን አስጠራና "ወደዋናው አገልጋይ ሂድና የሚሰጥህን እቃ ይዘህ ና " ሲል አዘዘው። አህመድም ትዕዛዙን ተቀብሎ እየሄደ ባለበት ጊዜ የቤተ መንግስት አገልጋይ የሆኑ የተወሰኑ ሰዎች ያገኙትና እርስ በራሳቸው በተጨቃጨቁበት ጉዳይ ላይ ፍርድ እንዲሰጣቸው ጠየቁት አህመድም ተልኮ የሚሄድበትን ጉዳይ በመግለጽ ሊዳኛቸው እንደማይችል ይነግራቸዋል። አገልጋዮቹም "ከእኛ እከሌ የተላክበትን ለመፈጸም እንዲሄድ እናደርጋለን አንተ እዚሁ ሁነህ በመካከላችን ፍርድ ስጠን" ሲሉ ሀሳብ አቀረቡለት። . አህመድም በሐሳባቸው ተስማማ። ከመካከላቸው የአህመድን ተልዕኮ የተሰጠው አገልጋይም አህመድ ወደተላከበት ቦታ ሄደ። አገልጋዩ ከቦታው ደርሶ የተላከውን ነገር በሚጠይቅበት ጊዜ ዋና አገልጋዩ ንጉሱ ባዘዘው መሠረት ገድሎ ጭንቅላቱን ወደ ንጉሱ ይዞለት ሄደ። ንጉሱም የተሸፈነበትን ፎጣ ገልጦ የተቆረጠውን ጭንቅላት በሚመለከትበት ጊዜ ጭንቅላቱ የአህመድ ሳይሆን የሌላ አገልጋይ ሆኖ አገኘው። . በዚህን ጊዜ ንጉሱ አህመድን አስጠርቶ ምን እንደተፈጠረ ጠየቀው። አህመድም የሆነው ሁሉ ለንጉሱ ነገረው። ንጉሱም "ለመሆኑ በዚህ አገልጋይ ላይ የምታውቀው የፈጸመው ወንጀል አለን? " ሲል ጠየቀው። አህመድም "አዎን ንጉስ ሆይ ይሄ አገልጋይ እገሊት የምትባል የርስዎ ልጃገረድ አገልጋይ ጋር ዝሙት ሲሰሩ አግንቻቸዋለሁ። ቢሆንም ግን በአላህ ስም አይቧን እንድሰትርላት (እንድደብቅላት)ስለጠየቀችኝ እስካሁን ለማንም አልተናገርኩም።" ሲል መለሰ። . ንጉሱም የአህመድን ንግግር በሰማ ጊዜ በአህመድ ላይ አድሮበት የነበረው ቁጣ በረደለት ለሱም የነበረው እምነት ተመለሰለት ልጃገረዲቷም እንድትገደል አዘዘ። . #ስራ_ለሰሪው እሾህ ላጣሪው። 🍀 http://t.me/susui_slamic_channal

√ ለዱንያ ሂወት ማሰብ ግድ ይለናል √ ለአኼራ ሂወታችን ደግሞ ዚክር ያስፈልጋል √ ነገር ግን አብዛኞቻችንን ዱናያዊ "ሀሳብ" ከአኼራው ቤታችን ስንቅ ከ "ዚክር" አዘናግቶናል… √ አሏህን ሳታወድስ የምታልፍብህን ጊዜ በፍጥነት በተስቢህ ወይም በእስትግፋር ቀልብህን ከተኛችበት አንቃት… √መዘንጋትና መርሳት በሽታዎች ሲሆኑ ለነዚህ በሽታዎች ደግሞ ዚክርና እስትግፋር ፍቱን መድሀኒቶች ናቸው… √ "ሱብሀነሏህ ወቢሀምዲህ ሱብሀነሏህ አልአዚም" 🍀 http://t.me/susui_slamic_channal

=]የዙል_ሂጃ አስር ቀናቶች ትሩፋት[=
``````````
★ከዱንያ ቀናቶች ሁሉ በላጭ ናቸው።★ =]>የአላህ መልዕክተኛ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም በሀዲሳቸው እንዲህ ይላሉ፡– =]>"أَفْضَلُ أَيَّامِ الْدُّنْيَا أَيَّامُ الْعَشْرِ، يَعْنِي عَشْرُ ذِي الحْجَّةِ". "ከዱንያ ቀናቶች ሁሉ በላጭ ቀናቶች አስሩ የዙል ሒጃ ቀናቶች ናቸው።" =]>በሌላም ሀዲስ እንዲህ በማለት በእነዚህ ቀናቶች የሚሰራ ስራ ያለውን ደረጃ ያስቀምጣሉ። « *ما من أيام العمل الصالح فيهن أحب إلى الله من هذه الأيام العشر، قالوا ولا الجهاد في سبيل الله؟ قال ولا الجهاد في سبيل الله، إلاّ رجلا خرج بنفسه وماله فلم يرجع من ذلك بشيء» =]>ከእነዚህ ከአስር ቀናቶች የበለጠ መልካም ስራ ወደ አላሁ ሱብሀነሁ ወተዐላ የሚወደድበት ቀን የለም። አሉ‼ ሰሀቦችም በአላህ መንገድ ላይ መታገል (መጋደል) ቢሆንም? ብለው ሲጠይቋቸው…… አው በአላህ መንገድ መታገል ቢሆንም ግን አንድ ሰው ሲቀር አሉ…… እሱም በአላህ መንገድ ለመታገል ነፍሱንም ንብረቱንም ይዞ ወጥቶ እስከ ንብረቱ እዛው የቀረ ሲቀር አሉ =]> እናንተ ሙስሊሞች ሆይ ……‼ ለራሱ የሚጨነቅና ንቃተ ህሊና ያለው ሰው እንዲህ አይነት ብርቅዬ አጋጣሚዎችን በከንቱ አያሳልፍም። =]>እኛንም አላህ ከሚጠቀሙ ያድርገንና በእነዚህ ቀናቶች ከዚህ በፊት ስናደርገው ከነበረው ለየት ባለ መልኩ ለመስራትና ለመጠቀም ራሳችንን ማነሳሳት አለብን‼ እላለው =]>አላህን አብዝተን በማውሳት……… ተህሊል፣ተክቢር ፣ተስቢህ እና ተህሚድ በማድረግ ወደ አሏህ መቃረብ አለብን። =]>አላህን አብዝተን በመለመን =]>ሰደቃን በማብዛት =]>ቁርዐንን አብዝተን በማንበብ =]>የጀምዐ ሰላትን በመጠባበቅ =]>ተጨማሪ(ሱና) የሆኑ ሰላቶችን በመስገድ =]>የቻልነው በመፆም እና አጠቃላይ ኸይር ከተባለ ነገር ሰብስበን ተጠቃሚ ለመሆን ልንተጋ ይገባናል። ታላቁ አሊም ኢብኑ ዑሰይሚን እንዳሉት ብዙሀን ሰዎች የሚገርሙ ናቸው። ከረመዷን አሽረል አዋኺር ላይ የቻሉትን ያህል እየታገሉና እየሰሩ ይታያሉ ዙል ሂጃ ላይ ግን ምንም የተለየ ነገር ሲያከናውኑ አይታዩም በማለት ሀዘናቸውን ይገልፃሉ። =]>ከፊል ኡለሞች ከረመዷን አሽረል አዋኺር የዙል ሂጃ አስር ቀናቶች እንደ ሚያስበልጡስ ስንቶቻችን እናውቃለን?? =]> ምንም እንኳን መስዐላው ዒብኑል ቀይም እንዳስቀመጡት ……ቢሆንም =]>ከለሊቶቻቸው አንፃር የረመዷን አሽረል አዋኺር ሲበልጡ……‼ =]>ከቀኖቻቸው አንፃር የዙልሂጃ አስር ቀናቶች ይበልጣሉ። ★]>ማለት የፈለኩት ግን……… ምን አልባት በቀጣዩ አመት ላንደርስበት እንችላለን ብዙሀን ለአምናው ደርሰው ለዘንድሮው መድረስ እንደ ተሳናቸው እኛም እድሉን ሳንጠቀምበት ሊያልፈን አይገባምና በተቻለን እንበራታ የሚል ጥቆማ ለመስጠት ያክል ነው። በተለይ ደግሞ………‼ አለማችን በፊትና ባህር እየዋኘች ባለችበት በዚህ ወቅት··· =]>አላህ አስፈሪ የሆነ የፀሀይ ግርዶሽን ያክል ክስተት እና ለብዙሀን ህይወት ጤንነት ማጣት ምክንያት የሆነ ኮሮና የሚባል ወረርሽኝ በሽታ እያሳየ በሚያስፈራራበት ጊዜ እንዲህ አይነት አጋጣሚዎችን ማግኘት ማለት ከእድለኝነትም በላይ እድለኝነት ነው እናም ነቃ ብለን እንጠቀምበት። =]>በመጨረሻም ለዒደል አድሀ ኡዱህያ ማድረግ የሚፈልግ ሰው የዙል ሂጃ ወር ከገባ ጀምሮ ፀጉሩንም ይሁን ጥፍሩን ከመንካት መቆጠብ አለበት። ልክ መልዕክተኛው ሰለሏሁ አለይሒ ወሰለም እንዳሉት፡– فأراد أحدكم أن يضحي فلا يأخذن من شعره ولا من بشرته ولا من ظفره شيئا =]>ከእናንተ አንዳቹ ኡዱህያ ለማድረግ ከፈለገ ከፀጉሩም ይሁን ከጥፍሩ ምንም ነገር እንዳይነካ አሏህ ከተጠቃሚወች ያድርገን አሚን……‼ http://t.me/susui_slamic_channal