fa
Feedback
Konso Zone Communication / ኮንሶ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

Konso Zone Communication / ኮንሶ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

رفتن به کانال در Telegram

Communication is the bridge between people and Government ! www.konsozone.org https://t.me/KonsoZone

نمایش بیشتر
1 130
مشترکین
-124 ساعت
-27 روز
-330 روز
آرشیو پست ها
‎የካራት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለ5ኛ ዙር በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን ሠልጣኞች አስመርቋል፣ ‎ ‎ካራት:ሐምሌ 16/2018 ዓ.ም (ኮንሶ ዞን ኮሙኒኬሽን) ‎ ‎ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጁ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን ከ70 በላይ ሠልጣኞችን አስመርቋል። ‎ ‎በምረቃ ስነ ስርዓቱ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉት የካራት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዋና ዲን አቶ አማኑኤል ሲዳሞ በፖሊ ቴክኒክ ኮሌጃችን እየተሰጠ ያለው ስልጠና በዘንድሮው ዓመት 5ኛ ዙር ሲሆን ከዚህ በበለጠ ክልሉ የሚፈቅደው አዳዲስ የሙያ ዘርፎችን ለመጨመር ያለው ዕውቀትና ሙያዊ ክህሎት ከነበረበት ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ ኮሌጁ የያዘውን ራዕይ እውን ለማድረግ ሁሉም ሊረባረብ ይገባል ብለዋል። ‎ ‎የካራት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ይህን ዕውቅና ካገኘ በኋላ ወዲያውኑ በክላስተር ደረጃ አጎራባች ኮሌጆችን እንዲያስተባብር በክልል ደረጃ ዕውቅና ማግኘቱን ገልጸዋል። ‎ ‎አቶ አማኑኤል ጨምረው በዘንድሮ ዓመት ኮሌጃችን በቴክኖሎጂ ፈጠራ ውድድር በክልል ደረጃ ከተወዳደሩ ኮሌጆች መካከል 3ኛ ደረጃ አግኝቶ በቀጣይ 1ኛ ደረጃ ለማግኘት ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛል፣ለዚህም ስኬት የሁሉም አካላት ርብርብ ይጠይቃል፡፡ ‎ ‎በዘንድሮ ዓመት የአይሲቲ፣ የአውቶሞቲቭ ቴክኖሎጂ የጋርመንትና የሰርቬይ ሙያ ዘርፎችን ሥልጠና አጠናቃችሁ ለዛሬ ምረቃ ቀን የበቃችሁ በድጋሜ እንኳን ደስ አላችሁ! እንኳን ደስ አለን! ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። ‎ ‎የዞኑ ስራና ክህሎት መምሪያ ኃላፊ አቶ ስምኦን ገልገሎ በበኩላቸው የአንድ አገር ዘላቂ የኢኮኖሚ ዕድገት የሚመሰረተው ብቁ፣ ሥራ ፈጣሪና ምርታማ የሆነ የሰው ሀብትን በመገንባት መሆኑን ገልጸዋል። ‎ ‎የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ተቋማት ይህንን ግብ በማሳካት ረገድ ወሳኝ ሚና የሚጫወቱ በመሆናቸው የዛሬው ተመራቂዎች በካራት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ቆይታችሁ የወቅቱን የሥራ ገበያ የሚመጥን ክህሎት፣ ተግባራዊ ዕዉቀትና የሙያ ሥነ-ምግባርን እንዳገኛችሁ እናምናለንና በድጋሚ እንኳን ለዚህ ክብር አበቃችሁ ሲሉ ምኞታቸውን ገልጸዋል አቶ ስምኦን። ‎ ‎የኮንሶ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ገለቦ ጎልቶሞ እንደገለጹት የዘንድሮው 5ኛ ዙር የሠልጣኞች ምረቃከባለፉት የምረቃ ስነ ስርዓት ልዩ የሚያደርገው ሀገራችን "ለሀገር በቀል ችግሮች ሀገር በቀል መፍትሄዎች" በሚል መሪህ የሀገራችን የቀጣይ ዕጣ ፈንታ ለመወሰን ሀገራዊ ምክክር እየተደረገ ባለበት መካሄዱ እናም ኮሌጁ ከቴክኒክና ሙያ ወደ ፖሊ ቴክኒክ ኮለጅ ያደገበት ወቅት ላይ መሆኑን ገልጸዋል። ‎ ‎የቴክኒክና ሙያ ትምህርት ስልጠና የሀገራችን ኢኮኖሚ ዕድገት እና ኢንዱስትሪ ትራንስፎርሜሽን መሠረት ነው ያሉት ክቡር አቶ ገለቦ፤ዛሬ ከዚህ ኮሌጅ የሚትመረቁ ምሩቃን በዕውቀት፣በክህሎት እና በስራ ወዳድነት ታንጻችሁ ስራ ፈላጊ ሳትሆኑ ስራ ፈጣሪ ሆናችሁ ለዞናችን፣ለክልላችን ብሎም ለሀገራችን በሠለጠናችሁት ሙያ ለሁለንተናዊ ብልጽግና የድርሻቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል። ‎ ‎የአርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ፕረዝዳንት ኢ/ር ከማል አብደላ (ዶ/ር) እንደተናገሩት ዛሬ በፍጥነት በሚቀየር ዓለም ውስጥ የአንድ ሀገር እድገት የሚለካው በተፈጥሮ ሀብቷ ብቻ ሳይሆን፣ በሰው ኃይሏ፣ በእውቀቷ እና በሙያ ብቃቷ ነው። ስለዚህ ቴክኒክና ሙያ ትምህርት የሥራ እድልን የሚፈጥር፣ የሥራ ፈጠራን የሚያበረታታ፣ የኢኮኖሚ እድገትን የሚያፋጥን ወሳኝ መሠረት ነው ብለዋል። ‎ ‎የካራት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅም ይህንን ታላቅ ተልዕኮ በመሸከም ብቁ ባለሙያዎችን በማፍራት፣ ወጣቶችን በክህሎት በማብቃት እና ለማኅበረሰቡ ተጨባጭ አስተዋጽኦ በማድረግ የሚያኮራ ተቋም ነው፣ ይህንን ስኬት ያመጣችሁት የአመራሩ ቁርጠኝነት፣ የመምህራን ትጋትዠ፣ የተማሪዎች ጥረት እና የማኅበረሰቡ ድጋፍ በመተባበር መሆኑን አስገንዝበዋል። ‎ ‎የቀድሞ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ቢሮ ምክትል ኃላፊ እና የቴክኖሎጂ ሽግግር እና ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ዘርፍ ኃላፊና የአሁኑ የባስከቶ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ኢንጂነር በዛብህ ገበየሁ በበኩላቸው የዛሬው ቀን ሠልጣኞች የትጋታቸውንና የልፋታቸውን ፍሬ ያገኙበት ልዩ ቀን ነው ብለው የካራት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የሰው ሀይል በማፍራትና በቴክኖሎጂ ሽግግር እያደረገ ያለው እንቅስቃሴ የሚነደቅ ነው ብለዋል። ‎ ‎ኮሌጁ ለ5ኛ ዙር ያስመረቃቸው ሠልጣኞች በአውቶሞቲቭ ቴክኖሎጂ 8፣በአይ ሲ ቲ 60፣በጋርመንት ቴክኖሎጂ 5 እና በሳርቬይንግ 4 አጠቃላይ ድምሩ 77 ሠልጣኞች መስመረቁን የኮሌጁ ምክትል ዲና የሰው ሀይል ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ገልሲሞ ገመይዳ ገልጸዋል። ‎ ‎በምረቃ ስነ ስርዓት ላይ የቀድሞው የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ቢሮ ምክትል ኃላፊ እና የቴክኖሎጂ ሽግግር እና ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ዘርፍ ኃላፊና የአሁኑ የባስከቶ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ኢንጂነር በዛብህ ገበየሁ፣የአርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ፕረዝዳንት፣የኮንሶ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ገለቦ ጎልቶሞ፣የዞኑ ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ጉራሾ ለሚታ፣የክልል ከፍተኛ ስራ ኃላፊዎች፣የዞኑ የፊት አስተባባሪዎች፣የካራት ከተማ አስተዳደር አመራሮች፣የወረዳዎች አስተዳዳሪዎች ተሳትፈዋል። ‎ ‎በኩሲቶ ካንቢሮ ‎ SeeMorePhotos, https://www.facebook.com/share/p/18CPfgo4qd/

"የትምህርት ለትውልድ ስራዎችን በቅንጅት በመስራት ለውጥ ማስመዝገብ ይገባል'' ፦ርዕሰ መስተዳደር ጥላሁን ከበደ ካራት ፣ ሐምሌ 06/2018 ዓ/ም ( ኮንሶ ዞን መ/ኮ/አገልግሎት ) በደቡብ ኢትዮጵያ
+3
"የትምህርት ለትውልድ ስራዎችን በቅንጅት በመስራት ለውጥ ማስመዝገብ ይገባል'' ፦ርዕሰ መስተዳደር ጥላሁን ከበደ ካራት ፣ ሐምሌ 06/2018 ዓ/ም ( ኮንሶ ዞን መ/ኮ/አገልግሎት ) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የ2018 የክረምት ወራት ትምህርት የተመለከተ የንቅናቄ መድረክ በሳውላ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል ። የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር ጥላሁን ከበደ ባስተላለፉት መልዕክት፣ሀገር የምትበለጽገው በትምህርት ዘርፍ የተሻለ ስራ ሲሰራ ነው ብለዋል። ለትምህርት ዘርፉ ውጤታማነት የባለድርሻ አካላት የተደራጀና የተቀናጀ ርብርብ ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው፤ በተለይ የትምህርት ልማት ስራዎችን የጋራ ኃላፊነት አድርጎ በመውሰድ በዘርፉ ያሉ ፀጋዎችን እና ፈተናዎችን ለይቶ ተግዳሮቶች ላይ ትኩረት አድርጎ መስራት አስፈላጊ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ዘርፉ በተቀናጀ መንገድ ከተመራ የሚፈለገው ውጤት ማስመዝገብ እንደሚቻል የገለፁት ርዕሰ መስተዳድሩ ትምህርት ቤቶችን የማዘመን ስራ በዘመቻ መልክ መተግበር እንዳለበት ጠቁመዋል ። ትምህርት ቤቶችን ለመማር ማስተማር ስራ ምቹ የማድረግና ግብዓት የማሟላት ተግባር በማጠናከር በትምህርት ጥራት ላይ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የገለፁት ርዕሰ መስተዳደሩ ይህንኑ የማጠናከር ስራ ትኩረት ሊሰጠው ይገባል ብለዋል። በዘንድሮው የክረምት ወቅት ከሚከናወኑ ተግባራት የትምህርት ዘርፍ ቀዳሚ አጀንዳ መሆን እንዳለበት የገለፁት የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር ለሚፈለገው ውጤት የትምህርት ቤቶች ግብዓት በተገቢ መንገድ ሟሟላት እንደሚያስፈልግ አጽንኦት ሰጥቷል። SEEMORE: https://www.facebook.com/share/1JPtnkgted/

በኢፌዴሪ የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ወ/ሮ በላይነሽ ግርማ የተመራው ልዑክ በካራት ዙሪያ ወረዳ የተከናወኑ የልማት ሥራዎችን ጎበኘ ካራት፣ ሐምሌ 03/2018 ዓ.ም. (ኮንሶ ዞን መ/ኮ አገልግ
+2
በኢፌዴሪ የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ወ/ሮ በላይነሽ ግርማ የተመራው ልዑክ በካራት ዙሪያ ወረዳ የተከናወኑ የልማት ሥራዎችን ጎበኘ ካራት፣ ሐምሌ 03/2018 ዓ.ም. (ኮንሶ ዞን መ/ኮ አገልግሎት) በኢፌዴሪ የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ወ/ሮ በላይነሽ ግርማ የተመራው ልዑክ በኮንሶ ዞን ካራት ዙሪያ ወረዳ በዓይዴ ገጠር ቀበሌ በIOM፣ በኮንሶ ልማት ማህበር (KDA) እና በኢትዮጵያ ወንጌል ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ማህበራዊና ልማት ኮሚሽን ከኮንሶ ዞን መንግስት ጋር በመተባበር እየተፈጸሙ ያሉ የውሃ፣ የአካባቢ ጥበቃና የኑሮ መሻሻል ፕሮጀክቶችን ጎብኝቷል። https://www.facebook.com/100069055695172/posts/1335683668743477/?mibextid=rS40aB7S9Ucbxw6v

#THE_ICON | የኮንሶ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት በሁሉም የማህበራዊ ሚዲያ መድረኮች ይከታተሉን! 📲 ወቅታዊ፣ ትክክለኛና ተዓማኒ መረጃዎችን፣ የልማት ሥራዎችን፣ መንግስታዊ አገልግሎቶች
#THE_ICON | የኮንሶ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት በሁሉም የማህበራዊ ሚዲያ መድረኮች ይከታተሉን! 📲 ወቅታዊ፣ ትክክለኛና ተዓማኒ መረጃዎችን፣ የልማት ሥራዎችን፣ መንግስታዊ አገልግሎቶችን፣ ማስታወቂያዎችን እና ሌሎች አዳድስ መረጃዎችን በሰዓቱ በቀጥታ ለማግኘት የኮንሶ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት በሁሉም የማህበራዊ ሚዲያ መድረኮች ይከታተሉ :: 🔵 Facebook :- https://www.facebook.com/konsozone.org 📸 Instagram :- https://www.instagram.com/konsozonecommunication?igsh=MW1ncTJrenFzaWVsNA== 🎵 TikTok :- https://www.tiktok.com/@konsozonegovernmentcomms?_r=1&_t=ZS-97rRPAWRaSK 📢 Telegram :- https://t.me/konsocommunication ▶️ YouTube :- https://youtube.com/@konsozonegovtcommunication?si=B6SNAh71M6ctoCxh 🌐 Website :- https://www.konsozone.org 🐦 X (Twitter) :- https://x.com/konso_zone 💬 WhatsApp Channel :- https://whatsapp.com/channel/0029VajH5rZHbFVAGLGuDG2C 🔗 All-In-One Links :- https://heylink.me/konsozonecomms 📷 Photo Request (ፎቶ ለመጠየቅ) :- https://www.konsozone.org/infoseekers/ 👉 ገጾቻችንን Like, Follow, Subscribe እና Share በማድረግ ትክክለኛውን መረጃ ለሌሎችም ያድርሱ። የኮንሶ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት "ኮሙኒኬሽን አንድ ለብዙ !" ሐምሌ 01/2018 ዓ/ም

በኮንሶ ዞን ከባህል አባቶችና ከኃይማኖት መሪዎች ጋር በሠላምና በመጪው 7ኛ ሀገራዊ ምርጫ ዙሪያ የምክክር መድረክ ተካሄደ። የዞኑ አስተዳዳሪ አቶ ገለቦ ጎልቶሞ ሠላምና ደህንነት ለማጠናከር ባህል፣ ኃ
በኮንሶ ዞን ከባህል አባቶችና ከኃይማኖት መሪዎች ጋር በሠላምና በመጪው 7ኛ ሀገራዊ ምርጫ ዙሪያ የምክክር መድረክ ተካሄደ። የዞኑ አስተዳዳሪ አቶ ገለቦ ጎልቶሞ ሠላምና ደህንነት ለማጠናከር ባህል፣ ኃይማኖትና መንግስት በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል ብለዋል። ተሳታፊዎችም ዘላቂ ሠላምና ልማት ለማረጋገጥ በጋራ መረባረብ እንዳለባቸው ገልፀዋል። READMORE ግንቦት 05/2018 ዓ.ም

#THE_ICON "ፓርቲያችን ብልጽግና የህዝባችንን የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ ለመመለስ አበክሮ እየሰራ ይገኛል። ሰው ተኮር የሆነውን የብልጽግና እሳቤ በመላበስ የተጀመሩ ተግባራትን
#THE_ICON "ፓርቲያችን ብልጽግና የህዝባችንን የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ ለመመለስ አበክሮ እየሰራ ይገኛል። ሰው ተኮር የሆነውን የብልጽግና እሳቤ በመላበስ የተጀመሩ ተግባራትን በጋራና በትብብር የምንሰራቸውን ስራዎች አጠናክረን በማስቀጠል የህዝባችንን ተጠቃሚነት እናረጋግጣለን" አቶ ገለቦ ጎልቶሞ የኮንሶ ዞን ዋና አስተዳዳሪ

#THE_ICON ምስክርነት በብልጽግና ተግባር ላይ “በአይኔ ባየሁትና በተጨባጭ በታዘብኩት ልክ፣ ብልጽግና በአዲስ አበባ ከተማ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሌሎች መንግሥታት ለ27 ዓመታት ማከናወን ያልቻሉትን
+3
#THE_ICON ምስክርነት በብልጽግና ተግባር ላይ “በአይኔ ባየሁትና በተጨባጭ በታዘብኩት ልክ፣ ብልጽግና በአዲስ አበባ ከተማ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሌሎች መንግሥታት ለ27 ዓመታት ማከናወን ያልቻሉትን ስራዎች አከናውኗል። ቢያንስ በቀጣይ 20 ዓመታት የማይሰሩ የልማት ስራዎች መሰራታቸውን እያየሁ፣ በአዲስ አበባ የተጀመረው ልማት ወደ ሌሎች ከተሞችም እንዲስፋፋ እያልኩ የእኔ ምርጫ ብልጽግና ነው። ብልጽግና በሰባት ዓመታት ውስጥ የሰራቸው ስራዎች በርካታ ናቸው፤ ወደፊት ደግሞ ምን እንደሚሰራ በጉጉት እጠብቃለሁ። በዞናችንም ቢሆን ለዘመናት የነበሩ የህዝብ ጥያቄዎች እየተመለሱ ይገኛሉ፤ ለአብነት የኮንሶ–ሰገን መንገድ ጥገና ስራ ማንሳት ይቻላል። “ትላንት ስንገዛ የነበርን ህዝብ፣ ዛሬ እኩልነትን ያገኘ ህዝብ ሆነናል፤ ይህንን ጉዞ ማስቀጠል አለብን” ሲሉ ነዋሪዎች ገልጸዋል። #ኮንሶ #ካራት

በኮንሶና ቦረና ዞኖች መካከል ያለው ታሪካዊ ትስስር በቀጣይነት በማጠናከር በሰላም፣ በልማትና በኢኮኖሚ ዘርፎች የተሻለ ውጤት ማምጣት እንደሚቻል ተገለጸ። የኮንሶና የቦረና ዞኖች አመራሮች በጋራ በልማ
በኮንሶና ቦረና ዞኖች መካከል ያለው ታሪካዊ ትስስር በቀጣይነት በማጠናከር በሰላም፣ በልማትና በኢኮኖሚ ዘርፎች የተሻለ ውጤት ማምጣት እንደሚቻል ተገለጸ። የኮንሶና የቦረና ዞኖች አመራሮች በጋራ በልማትና በሰላም ጉዳዮች ላይ ተስማምተው የህዝቦች አንድነት ማጠናከርና ሰላማዊ ሁኔታ መፍጠር አስፈላጊ መሆኑን ገለጹ። Read More: https://www.facebook.com/share/1B7x5HXajR/ https://www.facebook.com/share/1CmwyMcbqt/ በትክቶክ ይመልከቱ https://vt.tiktok.com/ZS9HBddpQ/

#THE_ICON በኮንሶ ዞን ለአሽከርካሪዎች የደህንነት ሥልጠና ተሰጠ። የትራንስፖርት መምሪያ “Safety First” በሚል መሪ ቃል ያዘጋጀው ሥልጠና አሽከርካሪዎች የታሪፍ ህግ መከበር፣ ፍጥነት መቆ
#THE_ICON በኮንሶ ዞን ለአሽከርካሪዎች የደህንነት ሥልጠና ተሰጠ። የትራንስፖርት መምሪያ “Safety First” በሚል መሪ ቃል ያዘጋጀው ሥልጠና አሽከርካሪዎች የታሪፍ ህግ መከበር፣ ፍጥነት መቆጣጠርና አደጋ መከላከል ላይ እንዲተኩሩ አሳስቧል። በዞኑ በ9 ወራት 20 አደጋዎች ተከስተው 8 ሰዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል፤ ሥልጠና ተሳታፊዎችም የተሻለ አገልግሎት ለመስጠት ቃል ገብተዋል። ለበለጠ :- https://www.facebook.com/100069055695172/posts/1276259868019191/?mibextid=rS40aB7S9Ucbxw6v

#THE_ICON በኮንሶ ዞን የትራንስፖርት ዘርፍ የታሪፍ ማሻሻያ ተግባራዊ ሆነ … https://www.facebook.com/share/18Y5vHBW2k/
#THE_ICON በኮንሶ ዞን የትራንስፖርት ዘርፍ የታሪፍ ማሻሻያ ተግባራዊ ሆነ … https://www.facebook.com/share/18Y5vHBW2k/

“አመራር ችግርን ወደ እድል መቀየር አለበት” – ኮሚሽነር ሐልገዮ ጂሎ በኮንሶ ዞን አመራሮች በዓለምና በሀገር የተፈጠሩ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ምክክር አካሄዱ። በውይይቱ የነዳጅ እጥረት፣ ያልተገባ የዋ
+2
“አመራር ችግርን ወደ እድል መቀየር አለበት” – ኮሚሽነር ሐልገዮ ጂሎ በኮንሶ ዞን አመራሮች በዓለምና በሀገር የተፈጠሩ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ምክክር አካሄዱ። በውይይቱ የነዳጅ እጥረት፣ ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ እና የአካባቢ ተፅዕኖዎች ተነሱ፤ እርምጃ መውሰድ እንዳስፈለገ ተጠቁመዋል። አመራሮች ፈተናን ወደ እድል በመቀየር እና በአንድነት በመስራት መፍትሔ ማምጣት እንዳስፈለገ አጠናክረዋል። ለበለጠ መረጃ :- https://www.facebook.com/share/1Eg12viCnU/