fa
Feedback
Kewashera

Kewashera

رفتن به کانال در Telegram

📈 تحلیل کانال تلگرام Kewashera

کانال Kewashera (@kewashera) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 16 635 مشترک است و جایگاه 13 228 را در دسته اخبار و رسانه‌ها و رتبه 2 009 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 16 635 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 14 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -656 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -18 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 11.14% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً N/A% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 1 853 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 0 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 17 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

توضیحی برای کانال ارائه نشده است.

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 15 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته اخبار و رسانه‌ها تبدیل کرده‌اند.

16 635
مشترکین
-1824 ساعت
-1287 روز
-65630 روز
آرشیو پست ها
Kewashera
16 619
ይኸ ገጽ ከብልጽግና ጋር የሚሠራ ሲሆን ሰላማዊ ሰዎችን ለማጥቃት የሚንቀሳቀስ ነው። በየከተሞች ደህና የሚባሉትን ግለሰቦች ቀድመው ወደ ሚዲያ በማምጣት በማኅበረሰቡ ዘንድ ኢላማ እንዲደረጉ ያደርጋል።
ይኸ ገጽ ከብልጽግና ጋር የሚሠራ ሲሆን ሰላማዊ ሰዎችን ለማጥቃት የሚንቀሳቀስ ነው። በየከተሞች ደህና የሚባሉትን ግለሰቦች ቀድመው ወደ ሚዲያ በማምጣት በማኅበረሰቡ ዘንድ ኢላማ እንዲደረጉ ያደርጋል። ወይም በእነሱ ቡድን እንዲገደሉ በማድረግ ከሞቱ በኋላ ሕዝቡ እንኳን ሞተ እንዲልና ፍትሕ እንዳይጠይቅ ያደርጋሉ። ባሕር ዳር ጎንደር አካባቢ ነው እንቅስቃሴ የሚያደርገው። የፋኖን ትግልም ተችቶ ጽፎ ያውቃል።

Kewashera
16 619
ወለጋ /ቢዛሞ አንሻ ሰይድ ዕዝ
+4
ወለጋ /ቢዛሞ አንሻ ሰይድ ዕዝ

Kewashera
16 619
አርሲ የሟቾች ቁጥር አሻቅቧል'የንጹሃን ጭፍጨፋው ቀጥሏል' እስካሁን ቦታው ላይ የደረሰ መከላከያ ሀይል አልተገኘም። ከ49 በላይ ንጹሃን ክርስቲያኖች ህይወታቸውን ተነጥቀዋል። 230 የሚሆኑት ደግሞ ታ
አርሲ የሟቾች ቁጥር አሻቅቧል'የንጹሃን ጭፍጨፋው ቀጥሏል' እስካሁን ቦታው ላይ የደረሰ መከላከያ ሀይል አልተገኘም። ከ49 በላይ ንጹሃን ክርስቲያኖች ህይወታቸውን ተነጥቀዋል። 230 የሚሆኑት ደግሞ ታፋነው ተወስደዋል ያሉበት አይታወቅም ብለዋል የአይን እማኞች። ነዋሪዎቹ የደራሽ ያለሽ እያሉ ቢሆንም አጋዥ ሀይል እንዳላገኙና አሁን በምስራቅ አርሲ ዞን በአሰኮ ወረዳ ታጣቂዎች ቀበሌዎችን ከበው መስመር በመዝጋት ህዝቡ እንዳይወጣ በማድረግ ጥቃት እየፈጸሚበት መሆኑም ተነግሯል። ግንቦት 25/2018

Kewashera
16 619

Kewashera
16 619
🔥#ገርጨጭ‼️ የልብ ኬዝ ያለባችሁና ነፍሰጡሮች ቪዲዮውን ባታዩት ይመከራል። ደቡብ ሜጫ መሃል ገነት (#ገርጨጭ) መሽጎ የነበረው የአብይ ሰራዊት በቴዎድሮስ ዕዝ 102ኛ ኮር 11ኛ ክፍለ ጦር ቃኝ እና መሀንዲስ ከዓለማየሁ ከቤ ሻለቃ ጋር በመቀናጀት በዚህ መልኩ የጠላትን #ጭንቅላት_ማፍረስ ተችሏል እድለኞች ተማርከዋል‼️ ደቡብ ሜጫ ወረዳ (ገርጨጭ ) የተገኙ ድሎች 🔸01ብሬን 🔸22 ክላሽ 🔸03 አይኮም መገናኛ 🔸1520 ተተኳሽ 🔸10 ምርኮኛ እና በርካታ ቁጥር ያለው ጠላት መደምሰስ ተችሏል።

Kewashera
16 619
√ የትግሉ ግብ ብልፅግናን ማስወገድ ሊሆን አይችልም! ብዙዎቻችን የአማራ ህዝብ እያካሄደ ያለው ትግል የሕልውና ትግል መሆኑን እንገልፃለን፡፡ ትክክል ነው፡፡ ከምንገኝበት የሕልውና አደጋ የደረስነው በረጅም ዘመናት የቁልቁለት ጉዞ መሆኑን ግን ማስመር ይገባናል፡፡ የአማራ ህዝብ ችግር መዋቅራዊና ስርአታዊ ነው፡፡ ረጅም ዘመን ያስቆጠረ የቁልቁለት ጉዞ ነው፡፡ በአብይ አህመድ ፈላጭ ቆራጭ አገዛዝ የተጀመረ አይደለም፡፡ በወያኔ አምባገነናዊ አገዛዝ የተጀመረ አይደለም፡፡ በደርግ አምባገነናዊ አገዛዝ የተጀመረ አይደለም፡፡ በአፄው ዘመን የተጀመረም አይደለም፡፡ አጀማመሩ ከዚያም ያልፋል፡፡ በደንብ ለመረመረው ከፋሽስት ጣልያን የወረራ ዘመንም ያለፈ ነው፡፡ በተከታታይ አገዛዞች በችግር ላይ ችግር እየተከመረ እዚህ ላይ ደርሰናል፡፡ በጆግራፊም በዲሞግራፊም የሀገሪቱ ግንባር ቀደም ህዝብ ሆነን ሳለ፣ የፖለቲካ አናሳ (political minority) ወደመሆን አሽቆልቁለናል፡፡ በኢኮኖሚው መስክ ኋላ ቀርተናል፡፡ በትምህርቱ መስክ የለንም ማለት ይቻላል፡፡ በሌሎች ማህበራዊ መሰረተ-ልማቶች ያለንበት ሁኔታ እጅግ እጅግ አሳፋሪ ነው፡፡ ይህ ሁሉ ድርብርብ ጭቆና እና ፈተና ሳያንስ ሕልውናችንም አደጋ ላይ ወድቋል፡፡ ወገኖቻችን ባልተቋረጠ ሁኔታ በየቦታው በማንነታቸው ተለይተው እየተሳደዱ ነው፡፡ እየተገደሉ ነው፡፡ ታፍነው በብዛት እየታሰሩ ነው፡፡ አደጋው እጅግ ሰፊና ጥልቅ ነው፡፡ ከመቼውም ጊዜ በላይ የዘር ማጥፋት አደጋው መጠኑን አስፍቶና ተጠናክሮ የመጣውም አሁን ነው፡፡ ስለዚህ፣ የትግላችን ግብ የኦህዴድ/ብልፅግናን አገዛዝ ማስወገድ ሊሆን አይችልም፡፡ የትግሉ ግብ ከዚያ የተሻገረ ነው፡፡ አዎ የኦህዴድ/ብልፅግና አገዛዝ የህዝባችን የወቅቱ ጠላት በመሆኑ መወገድ አለበት፡፡ ይሁን እንጅ እሱን ማስወገድ በራሱ የአማራን ሕዝብ የሕልውና አደጋና የነፃነት ጥያቄ አይመልሰውም፡፡ የአማራን ህዝብ የሕልውና አደጋ አስወግደን ህዝባችን የራሱን እድል በራሱ እንዲወስን እና በነፃነት እንዲኖር ከፈለግን አስተሳሰባችን ማስፋት አለብን፡፡ የትግሉን ግብ አስፍተን መተለም አለብን፡፡ ኢትዮጵያ እስካለች ድረስ በወርዳችንና በቁመታችን ልክ የፖለቲካ ውክልናና የኢኮሚ ተጠቃሚነታችን ተረጋግጦ በእኩልነትና ፍትሃዊነት የምንኖርበት ስርአት እንዲኖር መታገል አለብን፡፡ ከሁሉም በፊት ግን አደጋ ላይ የወደቀው ሕልውናችን መወገድ ይኖርበታል፡፡ የኢትዮጵያ እንደ ሀገር መቀጠል አደጋ ውስጥ የሚገባ ከሆነም ራሳችን ችለን መኖር እንደምንችል ከወዲሁ ማረጋገጥ አለብን፡፡ ከወዲሁ ጠንካራ ተቋማትን በየመስኩ መገንባት ይገባናል፡፡ ዝግጅቱ እስከዚህ መሆን ይገባዋል፡፡ በዚህ ደረጃ አስበን ካልተዘጋጀን የኢትዮጵያ ሕልውና አደጋ ላይ ሲወድቅ ዛሬ ካለንበትም የባሰ መቀመቅ እንገባለን፡፡ እንደምናውቀው ከዚህ ቀደም የህዝባችን ቀንደኛ ጠላት ወያኔ/ኢህአዴግ ነው የሚል መነሻ ተይዞ እሱን ማስወገድ የትግሉ ዋነኛ ግብ ሆኖ ቀረበ፡፡ ወያኔ/ኢህአዴግ ተወገደ፡፡ ይሁን እንጅ ከወያኔ በኋላ የህዝባችን እጣ-ፈንታ ምን ይሆናል? የሚለውን ጥያቄ የጠየቀና አስፈላጊውን ዝግጅት ያደረገ ሃይል ባለመኖሩ ህዝባችን መስዋዕትነት ከፍሎ ያመጣውን ለውጥ እንደ ዘበት ተነጥቋል፡፡ ህዝባችን የራሱን ጉዳይ በራሱ እንዲወስንና በነፃነት እንዲኖር የሚያስችሉ ጠንካራ ተቋማትን ያልገነባን በመሆኑ ምክንያት በመስዋዕትነት ያመጣነውን ለውጥ ተነጥቀናል፡፡ ለዚህ ነው አሁንም የትግሉን ግብና ትግሉን አላማዎች፣ በሌላ አባባል የትግሉን መዳረሻ ከወዲሁ በጠራ ሁኔታ ቀርጾ እና የስራ ክፍፍል አድርጎ ሁሉም በየሚናው ኃላፊነቱን መወጣት መጀመር ያለበት፡፡ አይመጣምን ትቶ ይመጣልን ማሰብና መዘጋጀት ከውርደትና ከሞት ያድናል፡፡ ከዚህ ቀደም ሊመጡ የሚችሉ አደጋዎችን እየተነተንን አስፈላጊውን ዝግጅት አድርገን ቢሆን ኖሮ በዚህ ደረጃ ባልተጠቃንም ነበር፡፡ ከታሪካችን አንፃር፣ ከህዝብ ቁጥራችን አንፃር፣ ካለን የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ሀብት አንፃር አሁን የምንገኝበት ሁኔታ ፈፅሞ መሆን ያልነበረበት፤ ፈፅሞ አሳፋሪ ሁኔታ መሆን መቀበል አለብን፡፡ የገባንበትን መቀመቅ በልኩ ስላልተገነዘብነው ነው ከዚህ መቀመቅ ለመውጣት በእርዳ ተራዳ መንፈስ በህብረት ከመንቀሳቀስ ይልቅ በትንሹም በትልቁም እየተባለን የጠላት መጫዎቻ የሆንነው፡፡ ደግነቱ ባህል የማይቀየርና ዘላለም የሚኖር አለመሆኑ ነው፡፡ ባህልና ልማዳዊ ድርጊት ይቀየራል፡፡ ይሻሻላል፡፡ እኛም ዛሬ እርስ በርሳችን የመናከስ ክፉ ልማድ አለን ማለት ከዚህ እስር ቤት መውጣት አንችልም ማለት አይደለም፡፡ በበቂ ሁኔታ ያለመተባበር ችግር አለብን ማለት ይህን ሁኔታ ቀይረን መተባበር አንችልም ማለት አይደለም፡፡ ለልዩነት ቦታ እየሰጠን፣ አንዳንድ ስህተቶችንም እንዳላየን እያለፍን፣ ከስም ማጠልሸትና ሰብእና ገደላ ተላቀን፣ ሁላችንም አሸናፊ ከሚያደርግ የይዋጣልን እልህ ወጥተን በጋራ መቆም ምርጫ ሳይሆን ግዴታ ነው፡፡ ይህን የአሸናፊነት መንገድ ጥቂቶች ብንጀምረው የነ አቶ ህላዌ ዮሴፍን መዝሙር ተውሰን “ነገ እልፍ እንሆናለን ታሪክ መስክር ነው” ብለን እንዝጋው፡፡ ከጠላትም ቢሆን በጎ ነገር ሲገኝ መውሰድ መልካም ነውና ነው! የአማራ ብሄርተኝነት ይለምልም! ንቃ አማራ ©ታጋይ የሕዝብ ልጅ

Kewashera
16 619
የተባበሩት ኢምሬቶች አዲሷ ኢምፔሪያሊስት ሆናለች። ከግማሽ ምዕተ ዓመት የማይበልጥ እድሜ ያላት፤ የአዲስ አበባን ሩብ ያህክል የህዝብ ቁጥር የሌላት ሀገር የሺህ ዘመናት የስልጣኔ ባለቤት እና በአፍሪካ የነፃነት አባት የሆነችዋን ኢትዮጵያ ቅኝ እየገዛች ትገኛለች። ትክክለኛ ሊደር ሺፕ እና የጋራ ርዕይ የሌለው ህዝብ እንዲህ ነው ሚሆነው። የኢትዮጵያ አየር ኃይል ከደመወዝ እስከ ቁሳቁስ በኢምሬቶች ይሸፈናል። ስራ ላይ ካሉት ድሮኖች መካከል ከአንቴና ውጭ ሳትኮም (ሳተላይት) እንዲጠቀሙ ተደርገው የተሻሻሉት TB2 ድሮኖች እና ከ 4 እስከ 24 ሮኬት ቦንቦች መሸከም የሚችሉ ዘመናዊወቹ አኪንቺ ድሮኖች ባለንብረቶች የሆኑት ኢምሬቶች ደብረ ዘይት፣ ባህርዳር እና አሶሳ ላይ የራሳቸውን ድሮኖች ኦፕሬት እያደረጉ ከትመዋል። AI ሲስተም የተገጠመላቸው እነዚህ እጅግ ዘመናዊ ድሮኖች ውድ ከመሆናቸው የተነሳ ኢትዮጵያ መታጠቅ ያልቻለቻቸው ናቸው። በግዜያዊነት ለስልጠና እና ክትትል የሚመጡትን ሳይጨምር ዛሬ ላይ ከ125 በላይ የአረብ ኤምሬት አየር ሃይል ስታፍ አባላት በደብረ ዘይት እና በሌሎች አየር ኃይል ግቢወች ይገኛሉ። በተለይ ከኢትዮጵያ ወደ ጎረቤት ሀገራት የሚደረገው ድንበር ዘለል የድሮን ኦፕሬሽን የሚከናወነው ሙሉ በሙሉ በUAE ዜጎች ሲሆን የሀገር ውስጥ ሰወች ምንም አይነት ተሳትፎ የላቸዉም። ምግብ ሳይቀር ከዱባይ የሚመጣላቸው እነኝህ የUAE ዜጎች አልፎ አልፎ የወርቅ ንግድ ቱጃሩ የሐምዳን ዳጋሎ ወንድም ከሚደግፋቸው በስተቀር የነዳጅ፣ የተተኳሽ እና የስታፍ ወጭ በሙሉ በሀገራቸው ይሸፈናል። የጀነራል ይልማ መርዳሳ ቢሮ መንደርደሪያወችን ከመፍቀድ የዘለለ ሚና የለውም። ከፖርት ሱዳን እስከ ዳሬ ሰላም ያሉ ፖርቶችን በመቆጣጠር የወደብ ተስፋፊ (Port- imperialist) ለመሆን የምትደክመው ሀገር በሊቢያ ጀነራል ቃፍታርን፣ በሱዳን ዳጋሎን፣ በሶማሊያ ጁባ ላንድ እና ፑንት ላንድ የመሳሰሉ ራስ ገዝ ክልላዊ ኃይሎችን፣ በቻድ የመሃማት ኢድሪስ ዴቢን ሽግግር መንግስት እና ሌሎችንም ስፖንሰር በማድረግ የአፍሪካን ወርቅ በመልቀም ላይ ትገኛለች። ኢትዮጵያ ውስጥም በሀገር ላይ ያመፀውን አብይን የምትደግፈው እና በተለይም የአማራን ህዝብ የምትወጋው ይህች ሀገር ፍላጎቷ ከእርሻ መሬት ፍለጋም አለፍ ያለ ፀረ-ኢትዮጵያዊ ፕሮጀክትንም ያካትታል። በነገራችን ላይ ፕሮፌሰር Alex de Waal ከመለስ ዜናዊ ጋር በተለያዬ ግዜ በነበረው ውይይት የያዘዉን ማስታወሻ እ.ኤ.አ 2018 ባካተተበት "The Future of Ethiopia: Developmental State or Political Market Place" በሚለው መጣጥፉ ስር መለስን በኢትዮጵያ ብሔራዊ ደህንነት ላይ ትልቁ ስጋትህ ምንድን ነው ሲል መጠየቁን አስፍሯል። መለስም ...ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ደህንነት አንፃር የሚያስቃዠኝ ጉዳይ ቢኖር የባህረ ሰላጤው ዘውዳዊ አገዛዞች (Gulf Monarchies) የአፍሪካ ቀንድን የፉክክር ሜዳቸው ሊያደርጉ የሚችሉበት እድል መኖሩ ነው... በተለይም ታዛዥነትን (loyalty) በስልጣን ሊያከራይ የሚደፍር አመራር ከመጣ ከባድ ችግር ይከተላል የሚል ይዘት ያለው ምላሽ ሰጥቷል። ይህ ፖለቲካዊ ምስቅልቅል ይከሰት ዘንድ በኢትዮጵያ ፖለቲካ የኃይል አሰላለፍ ስሌት ውስጥ ትልቅ ፖለቲካዊ ውስልትና በመስራት የፀረ-ኢትዮጵያዊ ኃይሎች አቅም ከልክ በላይ እንዲፈረጥም በሰራው ስትራቴጅካዊ ስህተት እርሱም ከደሙ ንፁህ ባይሆንም በበቂ ትንተና ላይ የተመሰረተው የሰውዬው የፖለቲካ ትንበያ አስገራሚ ነበር። ያ የተሰጋው የኢትዮጵያ ናሽናል ሴኩሪቲ አደጋ በመሐመድ ቢን ዛይድ እና በአብይ አህመድ ጥምረት እውን ሆኗል። ማንም ሀገሩን ማትረፍ የሚፈልግ ቢኖር ይህንን ስትራቴጅካዊ አሰላለፍ ተከትሎ ማስላት ይጠበቅበታል። ግብዝ ካልሆንን በስተቀር መወረር እና ቅኝ መገዛት ከዚህ በላይ መገለጫ ሊኖረው አይችልም። ደሃው የአማራ ገበሬ፣ ለነፍሱ ማይሰስተው ፋኖ እየተዋጋ ያለው የውስጥ አረመኔወችን ብቻ ሳይሆን የውጭ ቅኝ ገዥወችን ጭምር ነው። ©አርበኛ አስረስ ማረ ዳምጤ

Kewashera
16 619
ከምስራቅ ጎጃም ዞን ደብረ ማርቆስ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የተሰጠ መግለጫ ሚያዚያ 30/2018ዓ.ም --------------------------------------------------------------------- "በምርጫ ሰበብ ያለአግባብ የታፈኑ 7 የኮሌጃችን መምህራን እና 28 የተቋማችን ተማሪዎች በምስራቅ ጎጃም ዞን ፖሊስ መምሪያ የደህንነት ሰዎች በትናትናው ዕለት ከኮሌጁ ቅጽር ግቢ ተወስደዋል። የትምህርት ተቋማት ለማንኛውም የፖለቲካ እንቅስቃሴ ማስፈፀሚያነት እንደማይውሉ እየታወቀ በአለፉት 30 ቀና ውስጥ በኮሌጁ ግቢ ተማሪዎችን ፣መምህራን እንዲሁም የአስተዳደር ሰራተኞች በግዳጅ ከ5-7 የሚደርስ የምርጫ ካርድ በተለያዩ ስሞች እንዲያወጡ በመገደዳቸው ተቋማችን ይህ ተግባር እንዲቆምለት ለሚመለከተው አካል ማቅረባችን የሚታወስ ነው። በተደጋጋሚ በተጻፈልን ደብዳቤ መሰረት በኮሌጁ ውስጥ የምርጫ ካርድ የወሰዱ እና ያልወሰዱ መምህራን ፣ሰራተኞችና ተማሪዎችን ለይተን ሪፖርት እንድናቀርብ በመጠየቃችን ሒደቱ የአልተገባ እና ህገ-ወጥ በመሆኑ ተቋሙ በምርጫ ሒደቱ በቀጥታ እንዲሳተፍ እየተገደደ መሆኑን ለሚመለከተው አካል ብናሳውቅም አጥጋቢ ምላሽ በማጣታችን ምርጫ ካርድ የወሰዱ እና ያልወሰዱ መምህራን፣ ሰራተኞችና ተማሪዎችን ለይተን በስም ዝርዝር ማሳወቃችንም የሚታዎስ ነው። ይህ በእንዲህ እንዳለ በቀን 29/2018 ዓ.ም የብልጽግና ፓርቲ በደብረ ማርቆስ ከተማ በጠራው የምርጫ ቅስቀሳ አልተሳተፋችሁም፤ የምርጫ ካርድም አላወጣችሁም፤ የተባሉ 7 የኮሌጃችን መምህራን እና 28 ተማሪዎቻችን በደህንነት ሰዎች ታፍነዋል። በመሆኑም በተደጋጋሚ ኮሌጁን ለምርጫ ማስፈፀሚያነት ከመጠቀም ባለፈ መምህራን፣ የአስተዳደር ሰራተኞችና ተማሪዎች በመንግስት የፀጥታ ኃይሎች ሲንገላቱ ቆይተዋል። የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከተቋቋመለት ዓላማ ውጭ እንዲንቀሳቀስ መደረጉን አጥበቀን እየተቃወምን በቁጥጥር ስር የዋሉ መምህራን እና ተማሪዎቻችን እንዲለቀቁልን እንጠይቃለን። መላ ህዝባችንም ከተቋሙ ጎን እንዲቆም ጥሪ እናቀርባለን ። የደብረ ማርቆስ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ

Kewashera
16 619
photo content

Kewashera
16 619
አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 105ኛ ኮር 44ኛ ክፍለ ጦር ዛሬም ድል ተቀዳጅቷል ። ክፍለጦሩ ባደረገው ትንቅንቅ 44ኛ ክፍለ ጦር 68 ጥምር ጦር (ሚኒሻ፣ አድማ ብተና፣ መከላከያ ፣ፖሊስ ሲደ*መሰስ፡) 2
+2
አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 105ኛ ኮር 44ኛ ክፍለ ጦር ዛሬም ድል ተቀዳጅቷል ። ክፍለጦሩ ባደረገው ትንቅንቅ 44ኛ ክፍለ ጦር 68 ጥምር ጦር (ሚኒሻ፣ አድማ ብተና፣ መከላከያ ፣ፖሊስ ሲደ*መሰስ፡) 2 ብሬን 55 ክላሽ 3 መገናኛ ሬዲዮ 5000 በላይ ክላሽ 3000 የሚደርስ የብሬንና 2 አስቃጥላ የድሽቃ ተተኳሽ ሲማረክ 5 መከላከያና 2 አድማ ብተና ተማርኳል። በተመሳሳይ የ206ኛ ኮር አዳኝ ቡድን ከደብረ ማርቆስ ከተማ የካድሬዎች መገልገያ ፒካፕ መኪና ማርኳል ። ድል ለጀግናው አማራ ድል ለጀግናው ፋኖ !!

Kewashera
16 619
የአገዛዙ አንድ ሬጅመንት መደምሰሱና በርካታ የጦር መሳሪያዎች መማረካቸው ተሰማ! በአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ስር የሚንቀሳቀሱት የሰሜን አማራ በላይ ዕዝ እና የጎንደር ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ክፍለ ጦሮች በጋራ በመቀናጀት በፈጸሙት መጠነ ሰፊ ማጥቃት በአገዛዙ ሰራዊት ላይ ደማቅ ድል ማስመዝገባቸው ታውቋል። በሰማዕታቱ አርበኛ ፍቃዴ አለባቸው፣ አርበኛ አበበ አንለይ እና አርበኛ አንደበት ክንድዓለም ስም የተሰየመው ይህ ዘመቻ፣ ከጠዋቱ 02:00 እስከ ምሽቱ 11:45 ለተከታታይ ስምንት ሰዓታት በፈጀ ብርቱ ውጊያ የታጀበ ነበር። የአገዛዙ ሰራዊት ስንቅና ትጥቅ (ሬሽን) ለመቀባበል ከራስ ጋይንቱ ነፋስ መውጫ እና ከስማዳው ወገዳ ከተማ ተነስቶ "ወለላ ባሕር" በተባለች ከተማ ከተገናኘ በኋላ፣ ወደየመጣበት ለመመለስ ሲንቀሳቀስ በፋኖ ኃይሎች ድንገተኛና ፈጣን ጥቃት ደርሶበታል። በዚህ የተቀናጀ አውደ ውጊያ የሰሜን አማራ በላይ ዕዝ (ሜጀር ጀነራል ውባንተ አባተ 1ኛ ኮር) ስር የሚገኘው የጉና ክፍለ ጦር እስቴ ዴንሳ ብርጌድ ከአጎና እስከ ባዝራ መገንጠያ ያለውን የጠላት ኃይል ሲያሳድድ ውሎ፣ ተጨማሪ ኃይል ይዞ ወደ አጎና ሲመጣ የነበረውን የጠላት ስብስብ ደግሞ የሀገረ ቢዘን ብርጌድ ሸረፍ ጎዴና እና አስፋ ሜዳ ላይ አምበርክኮታል። በሌላ በኩል የጎንደር ጠቅላይ ግዛት ዕዝ (206ኛ ከፍያለው ደሴ ኮር) ስር የሚገኙት የአንበሳው ጋይንት እና የጀነራል ኃይሌ ዘ ውባንተ ክፍለ ጦሮች ከወለላ ባሕር እስከ ውሃ ምድር ባሉ አካባቢዎች እና በወገዳ ከተማ ዙሪያ ከፍተኛ ኪሳራ አድርሰዋል። በኦፕሬሽኑ የተገኘው ወታደራዊ ስኬት እጅግ ከፍተኛ ሲሆን፣ በአጠቃላይ 72 ክላሽንኮቭ፣ 3 ብሬን፣ 2 ስናይፐር እና አንድ ባለመነጽር ዲሽቃ ከነሸንሸሉ መማረኩ ተረጋግጧል። በተጨማሪም አንድ ሙሉ ተተኳሽ የጫነ FSR መኪና እና አንድ ፓትሮል ተሽከርካሪ ከነተተኳሹ በፋኖዎች እጅ መግባታቸው ታውቋል። በሰው ኃይል ረገድ 61 በላይ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ተማርከው እጅ የሰጡ ሲሆን፣ 30 የሚሆኑት ደግሞ ቆስለዋል። በውጊያው የአገዛዙ አንድ ሙሉ ሬጅመንት የተደመሰሰ ሲሆን፣ የሬጅመንት ዘመቻ መሪ፣ የዲሽቃ ተኳሽ እና የሻምበል መሪ መገደላቸውን የሜጀር ጀነራል ውባንተ አባተ 1ኛ ኮር የሕዝብ ግንኙነት ክፍል አረጋግጧል። ይህ ድል የአማራ ፋኖን አሸናፊነት ዳግም ያስመሰከረና የአገዛዙን ሰራዊት አካላዊና ሞራላዊ ኪሳራ ያከናነበ መሆኑ ተገልጿል።

Kewashera
16 619
ሰበር ዜና! ምኒልክ ዕዝ ለሁለት ሳምንታት ያክል ጥልቅ የስራ ግምገማና ተሃድሶ በማድረግ አመራሩን ሰየመ:: የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ ለሁለት ሳምንታት ያክል ጥልቅ የስራ ግምገማና ተሃድሶ በማድረግ በህልውና ትግሉ ያሉ ጠንካራና ደካማ ጎኖችን በመለየት ላሉ ድክመቶች የመፍትሄ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥና ያሉ ጠንካራ ጎኖችን የበለጠ አጎልብቶ የህልውና ትግሉን ለድል ማብቃት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ በከፍተኛ ደረጃ የመከረ ሲሆን በተጨማሪም የአማራ ህዝብ መሪ ድርጅት አፋብን ባወረደው መመሪያ መሰረት የዕዙን ሙሉ የአመራር መዋቅር በመስራትና ወደ ድርጅቱ የሚላኩ አመራሮችን በመመልመል ዛሬ ሚያዚያ 27/2018 ዓ.ም ስብሰባውን በስኬት አጠናቋል:: በመሆኑም ምኒልክ ዕዝ የአማራ ህዝብ መሪ ድርጅት አፋብን ያወረደውን መመሪያ ተግባራዊ በማድረግ መዋቅሩን መስራቱ ድርጅቱን መሰረት ከማስያዝና ከመትከል አንፃር ያለው ሚና ከፍተኛ መሆኑን በፅኑ በማመኑ የቤት ስራውን ለመስራት የበቃ ሲሆን ያለንበት ጊዜ የህልውና ትግሉ የሽግግር ወቅት በመሆኑ ፊታውራሪ ድርሳን ብርሃኔን የምኒልክ ዕዝ ሰብሳቢ በማድረግ ሾሟል:: ከዚህ ጋር ተያይዞም የምኒልክ ዕዝ የስራ አስፈፃሚ አመራር የሚከተሉት ናቸው፦ 1. ሰብሳቢ.... አርበኛ ድርሳን ብርሃኔ 2. ምክ/ሰብሳቢ... አርበኛ ረዳ ዉበቱ 3. ወታደራዊ አማካሪ... ኮ/ል ሞገስ ዘገዬ 4. ወታደራዊ አዛዥ አርበኛ ወንድሙ ማሩ 5. ምክ/ወታደራዊ አዛዥ አርበኛ ሃብታሙ ደምሴ 6. ወታደራዊ እቅድና ስትራቴጅ መምሪያ... ኮ/ል ተስፋዬ አየለ ምክ/ወታደራዊ እቅድና ስትራቴጅ መምሪያ... ኃላፊ ኮ/ል ፈንታው መኩየ 7. ዘመቻ መምሪያ... አርበኛ በለጠ ሸጋዉ ምክ/ዘመቻ መምሪያ... አርበኛ ሙላቱ ሰጠ 8. ወታደራዊ አስተዲደር መምሪያ... አርበኛ ትዝታ በዛብህ ምክ/ወታደራዊ አስተዳደር.. አርበኛ መስፍን አያሌው 9. ሎጂስቲክስ መምሪያ... ሻለቃ ኢሳይያስ መለሰ ምክ/ሎጅስቲክ መምሪያ... አርበኛ ሽመልስ አቦል ስንቅና ስርጭት... አርበኛ ሞላ ሰማው 10. ወታደራዊ ሥልጠና መምሪያ... አርበኛ አሌክስ ገርባው ምክትል የሥልጠና መምሪያ... ፶ ዓለቃ አበበ አጋዡ 11. ወታደራዊ መረጃና መገናኛ መምሪያ አርበኛ × × × × × × × ወታደራዊ መረጃ መምሪያ አርበኛ × × × × × × × ወታደራዊ መገናኛ መምሪያ አርበኛ × × × × × × × መኃንዲስ ክፍል አርበኛ × × × × × × × 12. ወታደራዊ ኢንዶክትሪኔሽን መምሪያ... አርበኛ አክሎግ ሲሳይ ምክ/ወታደራዊ ኢንዶክትሪኔሽን... አርበኛ አለሙ ገላው የኪነትና መዝናኛ ክፍል... አርበኛ ኪሮስ ደርቤ 13. ልዩ ዘመቻ መምሪያ... ሰብሳቢ አርበኛ ተሾመ ፈንታዬ 14. የመካናይዝድ ጦር መምሪያ... አርበኛ ሙሉቀን አያልነህ ምክ/የመካናይዝድ ጦር መምሪያ.... ሻለቃ ወንድሙ ተሾመ 15. ጤና መምሪያ... ዶ/ር ኡስማን ሰይድ ምክ/ጤና መምሪያ... አርበኛ ረብሶ ይላቅ 16. የፖለቲካ መምሪያ አርበኛ ሞገስ አባራው የፖለቲካ መምሪያ ምክ/ኃላፊ... አርበኛ ስንታየሁ ተስፉ 17. የፖሊሲና ስትራቴጅክ ጉዳዮች መምሪያ... አርበኛ ደርብ ተፈራ ምክ/የፖሊሲና ስትራቴጅክ ጉዳዮች መምሪያ... አርበኛ ገብረመስቀል ዘለቀ18. የአደረጃጀት መምሪያ... አርበኛ አሰፋ መሰለ ምክ/የአደረጃጀት መምሪያ... አርበኛ ሲሳይ ሳተናው 19. የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ... አርበኛ ብርሃን አረጋ ምክ/የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ... አርበኛ ሽመልስ ትዛዙ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን ኃላፊ... አርበኛ ደርብ መኮንን ምክ/ሚዲያና ኮሚኒኬሽን ኃላፊ... አርበኛ ደምሴ ጋሻው 20. የሴቶች ጉዳይ መምሪያ... አርበኚት ዚነት አደም ምክ/የሴቶች ጉዳይ መምሪያ... አርበኚት አበበች ሲሳይ 21. ትምህርትና ስልጠና መምሪያ... አርበኛ ፍቅሩ ፈንታው ምክ/ትምህርትና ስልጠና መምሪያ... አርበኛ ዘሪሁን ደምሴ 22. ማሕበራዊ ጉዳዮች መምሪያ... አርበኛ ኑረዲን አበበ ምክ/ማህበራዊ ጉዳዮች መምሪያ... አርበኛ ሚካኤል ጋሻው 23. የሕግና ስነ ምግባር መምሪያ... መቶ አለቃ ፈለቀ ጌትነት ምክ/የሕግና ስነ ምግባር መምሪያ... አርበኛ አብዱ አያሌው 24. የድርጅት ጽ/ቤት ኃላፊ... አርበኛ አለምነው መብራቱ ምክ/የድርጅት ጽ/ቤት ኃላፊ... አርበኛ ቃለአብ ወርቅየ 25. የፋይናንስና ግዥ አስተዳደር መምሪያ... አርበኛ ንጉስ አዳነ ምክ/የፋይናንስና ግዥ አስተዳደር መምሪያ ኃላፊ... አርበኛ አዘዘው ጌትነት አካውንታንት... አርበኛ ዮሃንስ ከልክሌ ገንዘብ ያዥ... አርበኛ አዲሴ ጌታሁን ግዥ ክፍል... አርበኛ አቢይ ቀፀላ የውስጥ ኦዲተር... አርበኛ ፀጋዬ ብርሃኑ 26. የሐብት አፈላላጊ መምሪያ... አርበኛ ምኒልክ ፋንታሁን ምክ/የሐብት አፈላላጊ መምሪያ... አርበኚት መሰረት ጫኔ 27. የሕዝብ አስተዳደር መምሪያ... አርበኛ አበበ ቀዬ ምክ/የሕዝብ አስተዳደር መምሪያ... አርበኛ ጋሻው ሙሉጌታ 28. የሰው ሃብት አስተዳደር መምሪያ... አርበኛ እስራኤል እሸቴ ምክ/የሰው ሃብት አስተዳደር መምሪያ... ሃምሳ አለቃ ሸዋነው አዲል 29. እቅድ ዝግጅትና ግምገማ መምሪያ... አርበኛ አራጋው ያለው ምክ/እቅድ ዝግጅትና ግምገማ መምሪያ ኃላፊ... አርበኛ ጌታቸው እሸቱ 30. የመረጃና ደህንነት መምሪያ አርበኛ × × × × × × × ምክ/የመረጃና ደህንነት መምሪያ አርበኛ × × × × × × × መረጃ መምሪያ አርበኛ × × × × × × × ፀረ መረጃ መምሪያ አርበኛ × × × × × × ×ስውር ድርጊያ መምሪያ አርበኛ × በመጨረሻም መላ ሰራዊታችንና ህዝባችን ለዚህ ትልቅ አላማ መሳካት ላበረከታችሁት ሁለንተናዊ አስተዋጽኦ የላቀ ምስጋናችንን እያቀረብን እንደ ህዝብ መስዋዕትነት የከፈልንበትና እየከፈልንበት ያለው አላማችን የአማራን ህዝብ ህልውና መረጋገጥ እና የሃገራችን ኢትዮጵያ ባለቤት የመሆን የመጨረሻ ተጋድሎ የተለመደው አበርክቷችሁ ተጠናክሮ ይቀጥል ዘንድ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን! መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል! ህልውናችን በተባባረ ክንዳችን! አፋብን ምኒልክ ዕዝ ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ ሚያዚያ 27/2018 ዓ.ም

Kewashera
16 619
photo content
+1

Kewashera
16 619
ለሁሉም ቀጠና ፋኖዎች ይድረስ!!! የወረዳ ምርጫ አስተባባሪዎች ከሚያዝያ 28 እስከ ግንቦት 1/2018 ዓ/ም በባህር ዳር ከተማ የምርጫ ስልጠና በድብቅ የሚወስዱ ናቸው። ከ26 ቀን ጀምሮ ጥብቅ ፍተሻ አርገን ተገቢ አቀባበል እንድናደርግላቸው በማለት መልዕክት እናስተላልፋለን፡፡ ከደጀን 1) አበባው ልንገረው 2) ይበልጣል ባዩልኝ 3) አሞኘሽ ደቤ ከቢቸና 1 ማርቆስ(0921328563) የምታውቋቸው ጓደኞቹ ከደብረ ማርቆስ 1 አንሙት ጌትነትና እናንተ ጋ የያዛችኋቸው ጓዶቹ ከድጓ ጽዮን 1) ጥላነህ ነበረ አዲስ 2) ልንገር እንዳሌ ደስታ 3) ቦሰና እውነቱ እንዳለ ከደብረ ወርቅ 1) ለወየሁ ተመስገን ሞሴ 2) አዲሱ ይሁኔ በላይ 3) የሽ ጫኔ ከቤ 4) አዝመራ ጠበቃው ዳኛው ከአምበር 1) ማስተዋል ታረቀኝ ይርሴ 2) ሁልጊዜ ታደለ 3) ስነወርቅ ታደለ ሁለቱ አግለዋል ማስተዋል ግን 2 አዲስ አስገብታ ለብልግና የምታሽቃብጥ አምበር ስራዋ ሉማሜ ማደሪያዋ(0949961004) ከየእድ ውኃ 1) ዮሴፍ ንጉሴ ማፈሪያ የሌለው ሆዳም ምን እንደምታረግ እናውቃለን 2) ሙሉጌታ መንግስት 3) እየሩስ እራሷን ያገለለች ከየጁቤ 1) ከዳርዳር አሳምረህ 2) አይመር ማናየ 3) ልጃለም ጤናው 4) ይደግ አንተነህ ከዱርቤቴ 1) ሀብታሙ አቸንፍ 2) እሱባለው አምሳሉ 3) ላቀ አይገኝ 4) መጣአለም ጌታነህ ከቡሬ 1) አንዷለም ታረቀኝ 2) መንግስት ጌታነህ 3) ንጹህ ሰለሞን 4) ማስተዋል በሪሁን 5) ኢዛና በላቸው አለባቸው 1) ዮናስ ሞገስ 2) ዘውዴ ብሻህ 3) ይልማ አበበ ከቁይ 1) ጽላት አበረ ፈጠነ 2) አለምነህ ፈጠነ መርሴ 3) መሰረት አለማየሁ 4) ነብዩ ላመነው እምሬ ከግንደወይን 1) መኮነን አወቀ 2) እሱባለው ጸጋ 3) መቅደስ አየሁ 4) ጥሩዓለንም መንግስት ከመርጦለማርያም 1) ሰለሞን ወርቅየ አስጨንቅ 2) እንደግ አግድ በዛብህ 3) አወቀ አባተ ይላቅ 4) ደመቀ ሙሉዓለም ተዋበ ከጎዛምን 1) ዳንኤል ማኔ 2) ማናየ አለኸኝ 3) ቴወድሮስ አያሌው ከሉማሜ 1) አዲሱ ዘሩ 2) እንቻለው አያሌው 3) ሳንበል ከዳንግላ 1) ቴወድሮስ መኮነን 2) ታደለ ዳኛው ከፍኖተ ሰላም 1 መለሰ ጌታነህና እናንተ የምታቋቸው ጓዶቹ ከአማኑኤል 1 ጽዮን ዳምጤና የምታውቋቸው ጓደኞቿ ከሞጣ 1) ተመስገን ፈለቀ 2) ታደገ ወንዴ 3) ላመስግን ከአዲስ ቅዳምን 1) ስሜነህ እንግዳ 2) መኳንንት በላይነህ ከረቡ ገብያ 1) ቢንያም እንቻለው ወንዳለ 2) ዝጋለ መንግስት አበበ 3) ውዴ እናውጋው በላይ ከባ/ዳር ሞላልኝ ደሳለው ከወረባቦ 1) መሀመድ ሙሳ ይመር 2) እንዳለው አበበ አላምረው 3) ሰይድ ኢብራሒም መሃመድ ከድል ይብዛ 1) አማረ ባየ 2) ዘመናይ መንግስቴ 3) ጀጃው ገ/ማርያም 4) ቢምረው በየነ ከደብረ ሲና 1 1) አበበ ዳምጠው 2) ሙሃመድ መንግስቱ 3) አሊ ምትኩ ከጃማ ደጎሎ 1) አቡሽ ፍስሃ 2) አብራክ ዘውዱ 3) ሳቦም ደመቀ ኃይሉ ከጎንደር ዙሪያ 1) ጌታቸው ሙጨየ አቡሃይ 2) መንበሩ ሙሉ 3) ሙሉቀን ከሳው ከድብረ ብርሃን 1 ስመኘው አታላይና እናንተ የያዛችኋቸው ጓደኞቹ ከመተማ 1 መሰረት ዋሲሁን መንግስቴና የምታውቋቸው ጓደኞቿ ከኩታበር 1 ይመር አህመድና የያዛችኋቸው ጓደኞቹ ከላይ አርማጭሆ 1 ሃጎስ ደነቀውና እናንተ የምታውቋቸው ጓደኞቹ ከደላንታ 1) አብርሃም ዓለሙ 2) ጌጥየ አበባው መልካም 3) ጌትነት አዳነ አዱኛ 4) ብርሃን ታርቀኝ ከጎንደር ዙርያ 1) ታድሎ ሹመት አየለና የምታውቋቸው ጓደኞቹ ከዓለም ከተማ 1) አግዘው ካሳና የያዛችኋቸው ጓደኞቹ ከደንቢያ 1) ናትናኤል ስመኘውና እናንተ የምታውቁቸው ጓደኞቹ ከወግራ 1 1) ፋሲል ዓለሙና የምታውቋቸው ጓዶቹ ከቃሉ 1 1) ቃልኪዳን ሰለሞን 2) ስመኘው አያሌው 3) አመለወርቅ የውድ 4) ሰለሞን በፍቃድ ከቃሉ 2 1) ሁሴን ሞሃመድ 2) ብርሃኑ አውራሪስ 3) ጀማል አብዱ 4) ሙስጦፋ ኢብራሒም ከጎንደር 04 1) መንበሩ ሙሉዓለም 2) ጌታቸው ሙጨየ ከመቅደላ 1) ዑስማን ሹምየ 2) አማኑኤል ዓለሙ 3) ዳንኤል ብርሃኑ 4) ሙራድ ፈጠነ ይቀጥላል...................!

Kewashera
16 619
የአማራ ሚዲያ ካውንስል (AMC) በሳተላይት ቴሌቪዥን ምስረታ ጉዳይ የተሰጠ መግለጫ! በአገር ውስጥና በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚገኙ ከ15 በላይ የሚሆኑ ታዋቂና ተፅዕኖ ፈጣሪ የሚዲያ ተቋማት፣ የሕዝባችንን የህልውና ትግል፣ ሰብዓዊ መብትና ሁለንተናዊ ፍላጎት ለማስከበር የአማራ ሚዲያ ካውንስልን (AMC) በማቋቋም ላለፉት ሁለት አመታት በጋራ ስንሰራ መቆየታችን ይታወቃል፡፡ አሁን ደግሞ ሳተላይት ቴሌቪዥን ጣቢያ ለመመሥረት ባለፉት ሁለት ወራት በጠንካራ ዝግጅት ላይ መሆናችንን ስንገጽ በታላቅ ኩራት ነው።  ይህ ካውንስል ከሁለት ዓመት በፊት ሲመሠረት በተበታተነ መልኩ የሚደረጉ የሚዲያ ሥራዎችን ወደ አንድ ወጥና ጠንካራ የጋራ አጀንዳ (Unified Narrative) ለማምጣት እንዲሁም የሚዲያ ባለሙያዎችንና ተቋማትን አቅም በማቀናጀት የሕዝብን ድምፅ ከፍ ለማድረግ ነው። በተለይም በአሁኑ ወቅት የሚታየውን የመረጃ አፈና ለመስበር፣ በጨለማው ውስጥ ላለው የአማራ ሕዝብ እና ድምፅ ለሌላቸው ኢትዮጲያዊያን ድምፅ ለመሆን፣ በዲጂታልና በሳተላይት አማራጮች አማካኝነት እውነቱን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማድረስ የተቋቋመ የሙያና የትግል መድረክ ይሆናል።  ካውንስሉ ካቀዳቸው ስትራቴጂካዊ እርምጃዎች መካከል ቀዳሚው፣ የኢንተርኔት መቆራረጥና ሳንሱር የማያግደው፣ ኢንተርኔት በማይደርሰበትና አገዛዙ ኢንተርኔት ለዘጋበት ሕዝብና አካባቢ ለመድረስ፣ በመላው ኢትዮጵያና በዓለም አቀፍ ደረጃ ተደራሽ የሚሆን "የሕዝብ ድምፅ" የሳተላይት ቴሌቪዥን ጣቢያ መመሥረት ነው። ይህ ጣቢያ የአባል ሚዲያዎችን ሰፊ የሕዝብ መሠረትና አቅም በማቀናጀት፣ የሕዝባችንን የታሪክ፣ የባህል፣ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ፍላጎቶች የሚወክል ቀዳሚ ተቋም ይሆናል።  ይህ ታላቅ ተቋም በምስረታ ላይ ባለበት በዚህ ወሳኝ ወቅት፣ የሚከተሉት ባለድርሻ አካላት አብረውን እንዲቆሙና እንዲሰሩ ጥሪያችንን እናቀርባለን፦ • ለሚዲያ ባለሙያዎችና ተቋማት፦ በካውንስሉ ውስጥ ያልታቀፋችሁ ሚዲያዎች የካውንስሉን አቅም በማጠናከርና የጋራ አጀንዳን በመገንባት ሂደት ውስጥ በሙያችሁ እንድትሳተፉ ጥሪ እናቀርባለን።  • ⁠በአማራ ሕዝብ የህልውና ትግል እየተሳተፋችሁ ላላችሁ የህልውና ታጋዮች አብረን እንድንሰራ ጥሪ እናቀርባለን። • ለሲቪል ማህበረሰብና ሙያ ማህበራት፦ በዚህ አመራር ሂደት ውስጥ በመሳተፍ የጣቢያውን ገለልተኝነትና ሕዝባዊነት እንድታረጋግጡ ጥሪ እናቀርባለን።  • ለባለሀብቶችና ለደጋፊዎች፦ ይህንን የመረጃ አፈና የሚሰብር የሳተላይት ፕሮጀክት ከሃሳብ ወደ ተግባር ለመቀየር በገንዘብና በቁሳቁስ ድጋፍ በማድረግ የታሪክ አሻራችሁን እንድታስቀምጡ ጥሪ እናቀርባለን።  • ለዲያስፖራው ማህበረሰብ፦ የትግሉ የጀርባ አጥንት በመሆን የካውንስሉን ዓለም አቀፍ ተደራሽነትና የፋይናንስ ዘላቂነት፣ የሀሳብ የበላይነት እንዲኖረው በምትችሉት ሁሉ የበኩላችሁን ሚና እንድትወጡ ጥሪ እናቀርባለን። የአማራ ሚዲያ ካውንስል (AMC) ለፍትሕና ለህልውና የሚደረገውን ትግል በጋዜጠኝነት ሥነ-ምግባር ታንጾ ለመዘገብና እውነተኛ መረጃ ለሕዝብ ለማድረስ ቆርጦ ተነስቷል። ይህ የመጀመሪያው እርምጃችን ሲሆን፣ በቀጣይ በዝርዝር የምናሳውቃቸው የሥራ እንቅስቃሴዎች ለሕዝባችን ታላቅ ተስፋ ይዘው እንደሚመጡ አንጠራጠርም።  "የጋራ ድምፅ ለፍትሕና ለእውነት!"  የአማራ ሚዲያ ካውንስል (AMC) ሚያዚያ 25 ቀን 2018 ዓ.ም

Kewashera
16 619
photo content

Kewashera
16 619
የአማራ አምላክ ተአምር መሥራተን ቀጥሏል። የመከላከያ ሰራዊት አባሉ የተደረገበትን ከበባ በመስበር አንድ ስናይፐርና አንድ ክላሽ በመያዝ ፋኖን ተቀላቀለ! የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ወሎ
+2
የአማራ አምላክ ተአምር መሥራተን ቀጥሏል። የመከላከያ ሰራዊት አባሉ የተደረገበትን ከበባ በመስበር አንድ ስናይፐርና አንድ ክላሽ በመያዝ ፋኖን ተቀላቀለ! የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ 303ኛ ግዙፉ አሳምነው ኮር አካል የሆነውን 14ኛ ክፍለ ጦርን የተቀላቀለው ስናይፐር ተኳሹ የመከላከያ ሰራዊት አባል በሦስት አቅጣጫ የተደረገበትን ከበባ በመበጣጠስ ካሰበው ቦታ ሊደርስ ችሏል። ሚያዚያ:-23/2018 ዓ/ም

Kewashera
16 619
+9

Kewashera
16 619
photo content
+8

Kewashera
16 619
+9