cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

ጠብታ-እውቀት

ራስን መፈለግ ወከባ ፤ ልፊያና ግፊያ በበዛባት የዛሬ ዘመን የሰው ልጅ ከግርግሩ ገለል ብሎ እራሱን መፅሐፍ ውስጥ መፈለግ ይኖርበታል። የምናገኛትን ጠብታ-እውቀት እንፅፋለን ማንም ግን እንዲያነብ ብለን አንፅፍም። አሁን አለም ያላትን ጣዕም ማጣጣም የምንችለው ጥቂት ሀሳባዊያን በሰጡን ጠብታ እውቀት በመጠቀም ነው። “ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ ” ትርጉም: "መሞትን ሁሉም ይሞታል"

نمایش بیشتر
کشور مشخص نشده استزبان مشخص نشده استدسته بندی مشخص نشده است
پست‌های تبلیغاتی
252
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

#kindness @tebtaewket
نمایش همه...
Never Celebrate Too Eearly Even A Moment Can Change Your Life. በጭራሽ ቀደም ብለክ አታክብር አጋጣሚዎች ሂወትክን ሊቀይሩት ይችላሉ። እና በጭራሽ ተስፋ አትቁረጥ @tebtaewket
نمایش همه...
"የኔነት ስሜት በአንድ ወገን፣ የእኛነት ስሜት በሌላ በኩል እንደምሶሶ ተራርቆ የተተከለበት መሬት አሁንም ስቃይዋን ለመቀነስና ዕድሜዋን ለማርዘም፣ ቀሪ ውበቷን እንደያዘች እንድትቆይ ለማድረግ አልተቻለም። "ሁለት የሚንቆራቆሱ ሐሳቦች ቢኖሩም አንዱ ሌላውን አይሰማም፣ መስማትም አይፈልግም። ችግሩ ሃላፊነትን የመቀበልና ያለመቀበል ጥያቄ ነው፤ ችግሩ የበቃኝ አልበቃኝ ጥያቄ ነው፤ ችግሩ ችግሩን ያለማወቅ ጥያቄ ነው…ችግሩ የመቻቻል ያለመቻቻል ጥያቄ ነው። መደማመጥ የሌለበት፣ ለነገው ትውልድ የማይታሰብበት የሆዳም ዘመን መሆኑ ነው - ግዙፍ መሰናክል። "ትናንት አንዱ ሌላውን አይናችሁን ጨፍኑ እያለ አሞኘ፣ ዘረፈ፣ በመሣሪያ የበላይነት እየገደለ በሃብት ደለበ። ዛሬ ደግሞ በረጅ ዕጁ፣ በምላሱ፣ በግንባር መጋፈጡን ትቶ አንዱን ከሌላው ጋር እያባላ በህፃናት፣ በአዛውንቶች…እልቂትና ሰቆቃ እየተዝናና እያላመጠ ይጎነጫል።…" • "የዘርሲዎች ፍቅር" በፍቅረማርቆስ ደስታ (133/4) ✨b_lion 🔰Philo's @tebtaewket @tebtaewket
نمایش همه...
"እያንዳንዷ ቃሌ በሚስቴ ፊት ሞገስ እንዲኖራት እፈልጋለሁ። በትዳር ውስጥ በጋራ ጉዳይ ላይ የግል አመለካከት የሚባል ነገር የለም። በሚስቴ ሰውነት ላይ ስለምትደረግ እያንዳንዷ ነገር ያገባኛል። ምክንያቱም 'አንድ አካል አንድ አምሳል ሆናችኋል' ብለው ያጋቡንን ቄስ ተላልፌ ሲመቸን አንድ ላይ ሳይመቸን በየግላችን እንድንዳክር አልፈቅድም። በምንም ነገር 'ስለኔ አይመለከትህም' የምትል ሚስት ወይ በሽተኛ አልያም የትዳር ኃላፊነት ያልገባት መደዴ ሴት ናት። መከባበር በሌለበት ውበት ገደል ይግባ። የስጋ ክምሯ ስላማለለህ ዘለህ አልጋ ላይ ትወድቃለህ፣ ከአልጋህ ስትወርድ ምድርህ እሳት ለብሶ ይጠብቅሃል። ፍቺ ደግሞ በማሕበረሰቡ ጸያፍ ነገር ነውና እያስመሰልክ ትኖራለህ። ማስመሰል ደግሞ ያንገሸግሻል። ራስህን በእሳት ልምጭ መግረፍ በለው። በዚህ ዓይነቱ ኑሮ እንኳን ሚስት ተብዬዋ ያጠለቀችልህ ቀለበት፣ ቀለበት የተጠለቀበት ጣትህም ይቀፍሃል።" "ሚስት ስለእርሱ ሕይወት የት ድረስ እንደሚያገባትና የት ድረስ የእርሱ ጉዳይ እንደማይመለከታት መስመር የሚያሰምር ወንድም ድድብና ከነጓዙ የሰፈረበት ደነዝ ይመስለኛል። … ባልም ለሚስቱ፣ ሚስትም ለባሏ ተገዢ ናቸው። ውልፍት የለም። አንዱ ካለአንዱ ፍላጎት ስንዝር ሊራመዱ አይገባም። ሚስቴ እኔ ላይ በዚህ ምድር ካለ ማንኛውም ሰው በላይ ኃላፊ ነች። እኔ የርሷ ነኝ፣ ርሷም የኔ ናት። ፋሽንም በለው ዘመን አመጣሽ ቅራቅንቦ በጎጆዬ ውስጥ የጥፍር ቁራጭ የሚያክል ቦታ እንዲኖራቸው አልፈልግም። ለምን መሰለህ…ከሦስት ጉልቻ አንዱም ከውጪ አይመጣም፤ አንተ፣ ሚስትህና ፍቅር ብቻ ናችሁኮ ጉልቶቹ…" "የሴት ልጅ ክብር በትጥቅ ትግልም በአደባባይ ጩኸትም አይመጣም! በቤቱ ሚስቱ የገፋችው፣ ፍቅረኛው ያቀለለችው ወንድ ሺ ሕግ፣ ሚሊዮን መመሪያ ቢወጣ ሴትን ያከብራል ማለት ዘበት ነው።" "አባትና እናቱ ሲደባደቡና ባለመከባበር አፍ ሲካፈቱ እያየ ያደገ ሕጻን ባባቱ ሲወጣ እያዩ፣ 'ልጅ የፍቅር ገመድ ነው' ይሉናል። በጥላቻና በመናናቅ ትዳር ውስጥ የበቀለ ሕጻን የፍቅር ሳይሆን የማሕበረሰቡን ሕግና ባሕል ማነቂያ ገመድ ነው! ብዙዎች 'ዘመናዊነት' ፍዳቸውን የሚያበላቸውን ሴቶች ታዘብ እስቲ፣ መነሻቸው ፍቅሩን አሟጥጦ እየተቋሰለ የኖረ ግድ የለሽ ቤተሰብ ነው። ካልተፋቀርን ምን አወላለደን! ልጅ አሻንጉሊት አይደለም! ቃላችንን ማፅናት ሲያቅተን፣ ሥጋ ለበስ ሐውልት ቤታችን ውስጥ ተክለን ልናመልክ ይዳዳናል! 'ልጅ ወለድን' ብለን አንመፃደቅ። በልጆቻችን እናት ካልተደሰትን የልጆቻችንን ግማሽ አንወደውም ማለት ነው። እናቶች ቢሆኑ 'ለልጄ ስል እንዲህ ሆንኩ፣ ለልጄ ስል ተፈለጥኩ…'፤ እስቲ መጀመሪያ ለእኛ ለባሎቻቸው ሲሉ ይፈለጡ፣ ይቆረጡ። የልጅሽ ግማሽ አካል እኛ ባሎች አይደለንም እንዴ? እነዚህ ኮተታም ዘፈኖችና ፊልሞች በቀጥታም በተዘዋዋሪ የወንድን ልክስክስነት ለሴቶቻችን ሲሰብኩ፣ 'ታዲያ ለማን ብለሽ ነው የምትታመኚው' እያሉ ለመደዴነት ሚስታችንን፣ እህታችንን እያዘጋጇት መሆኑን ዘግይቶ ነው የሚገባን።" • "ዙቤይዳ፣ ሚስቴን አከሸፏት" በአሌክስ አብርሃም (179/180) #book #ማጋራት #share @tebtaewket @tebtaewket @tebtaewket @tebtaewket ጠ ብ ታ እ ው ቀ ት
نمایش همه...
ጉራማይሌ የመፅሀፍት መሸጫ ገፅ: መጽሀፍት ዋጋቸው የወረቀት ገንዘብ አይደለም የሰው ልጅ አዕምሮ ላይ መፍጠር የሚችሉት አዎንታዊ ተፅእኖ እንጅ!!!
نمایش همه...
ከዕለታት... ግማሽ ቀን ደራሲ - አሌክስ አብርሃም የገፅ ብዛት - 287 የተለጠፈበት ዋጋ - 180 ብር መሸጫ ዋጋ - 155 ብር @Guramayelie 0912319263 #Free_delivery
نمایش همه...
"አንድን ነገር የምትጠቀምበት አላማ ጥሩ እና መጥፎ የሚል ተቀጥላ ያሰጠዋል። በቃ! ሌላው ቀርቶ ውኃን ለልምላሜና ለጥማት ስንጠቀምበት ስለኖርን ጥሩነቱ ብቻ ይታየን ነበር። ውስጡ ሌላ ኃይል እንዳለ ተረድተን ሐይድሮጂን ቦንብ ስንሰራበት ውኃ መጥፎ ሆነ ማለት ነው? ውኃ ጥሩም መጥፎም አይደለም። ሰው ነው ጥሩ እና መጥፎ የሚለው። ልዩ ተስጥዖ ያላቸውም ሰዎች እንደ ውኃ ጥሩ የሚባልና በመጥፎነት የሚፈረጅ ኃይል ሊወጣቸው ይችላል። አንድ ሰው ከበሽታ መፈወስን እስኪ እንየው። ፈውሱ ጥሩ የሚባለው ከማን አንፃር ሲታይ ነው? ምን አልባት በርስት ለሚከራከረው ሰው ያንን በሽተኛ ማዳን መጥፎ ሊሆን ይችላል። መግደል ደግሞ ጥሩ!…" • "በፍቅር ሥም" በዓለማየሁ ገላጋይ (193/4) 🔰Philo's @tebtaewket @tebtaewket @tebtaewket @tebtaewket ጠ ብ ታ እ ው ቀ ት
نمایش همه...