cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

Amazing profile picture🙏🌅🌌

Christian profile picture ✝

نمایش بیشتر
ايطاليا16 623زبان مشخص نشده استدسته بندی مشخص نشده است
Advertising posts
173مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

melkam adis amet
نمایش همه...
💁የኔ አለባበስ የኔ ጉዳይ እንጂ የወንዶች አይደለም፡፡ እግዚአብሄርንም ቅር አያሰኘውም 👆ከላይ ያነበባችሁት የአንዳንድ እህቶች ድምፅ ነው፡፡ 👉 ነገርግን በሳይንስም ሆነ በመፅሃፍቅዱስ የተረጋገጠ እውነት ይህ ነው ፡፡ 👁 ወንዶች በብዛት ለዝሙት የሚጋለጡት በአይናቸው በሚያዩት ነገር ነው፡፡ 🤔ታዲያ ከላይ የተባለውን አይነት አስተሳሰብ እህቶች የሚኖራቸው ለምን ይሆን? ምክንያታቸው ልዩ ልዩ ሊሆን ይችላል ሆኖም ግን የብዙዎቹ ምክንያት ከነዚህ ከሁለቱ አይዘልም ፡፡ 1⃣ ወንዶች በእነሱ አለባበስ እንደሚሰናከሉ አለማወቃቸው 2⃣ ቢያውቁም ለወንዶች ከመጠንቀቅ ይልቅ ፋሽን ለመከተል መወሰናቸው 🗝 ነገርግን ሴቶች በመገላለጣቸው ምክንያት አውቀውም ሆነ ሳያውቁ ወንዶች ማሰናከላቸው አይቀሬ እሰከሆነ ድረስ ሁለቱም ምክንያቶች #ከተጠያቂነት_አያድኗቸውም ፡፡ 👇እስኪ ከታች ያለውን ጥቅስ እንይ (ሉቃ 17 ) ------------ 1 ለደቀ መዛሙርቱም እንዲህ አለ፦ መሰናክል ግድ ሳይመጣ አይቀርም፥ ነገር ግን መሰናክሉን ለሚያመጣው ወዮለት፤ 2 ከእነዚህ ከታናናሾች አንዱን ከማሰናከል ይልቅ የወፍጮ ድንጋይ በአንገቱ ታስሮ ወደ ባሕር ቢጣል ይጠቅመው ነበር። -------------- 💯 አየሽ? ለአንዳንዶቹ የቀለለውን ያህል ይህ ጉዳይ በእግዚአብሔር ፊት ቀላል አይደለምና በአግባቡ በመልበስ እና እርቃንን በመሸፈን ወንዶችን በዝሙት እንዳይወድቁ ማገዝ እራስሽንም ከተጠያቂነት ማዳን ያንቺ ሃላፊነት ነው፡፡ 💢 @wongelLeAlem 💢
نمایش همه...
PART 2⃣ 🤝🤝🤝የማላውቀው ሰላምታ ከሰማይ መጣ❗ [ ብታምኑም ባታምኑም እውነቱ አይቀየርም። 12ኛ ክፍል የተአምራት አመት ] ምን እንደተፈጠረ ግራ እስኪገባኝ ሰይጣን ቀስ በቀስ ከእግዚአብሔር ቤት ሲያንሸራትተኝ ቅናት፣ ግራ መጋባት፣ ሰላም ማጣት ውስጤን እየሞላ መጣ። 8ኛ ክፍል እንዴት እንደሆነ በማላውቀው መንገድ ለፊልም ፍቅር የሌለኝ ልጅ፣ የሴክስ ቪዲዮ የማይበት አጋጣሚዎች በሌለበት ሰዓት 8ኛ ክፍል የገባሁበት ት/ቤት ስለ masturbation (ሴጋ) ሲወራ ቀለል ተደርጎ የሚወራበት ቡድን ጋር ከመቀመጥ ብቻ አዲስ ነገር ውስጤ ማደግ ጀመረ። በወሬያቸው ተሳትፌ ባለማወቄና የሚሉትን መረዳት የማልችል ሆኜ በመገኘቴ እዚ ነገር ውስጥ እንዳልገባሁ ቢረዱም እነሱ ግን ሰው ሁሉ ወሲባዊ ነገር እንደሚመኝ ሲያወሩ ቀለል አርገው ስለነበር የምፈተንበት ዕድሜም የደረሰ ይመስል 8ኛ ክፍልን ለመማር ከክረምት የገባሁበት ት/ቤት አስተሳሰቤን የቀረፀ ይመስላል። ወቅቱን በስርዓት አስታውሳለሁ ከመሀል አመት በኋላ ነው ይሄን ነገር የጀመርኩት 👉masturbation (ሴጋ፣ የሴክስ ፍላጎትን እራስ በራስ ማርካት) ጀመርኩ። ለደቂቃዎች በፍትወት እቃጠልና እርካታውን ይዤ መቀጠል ላልችል ያቺ ደቂቃ ስታልፍ ውስጤ መረበሽ ይጀምራል። ዘፈን ማቆም እስከሚያቅተኝ ከውስጤ ጋር ተዋህዶ ሱስ የሆነብኝ ሀጥያት እልፍ ሲልም ማቆም እየፈለኩ ማቆም ያልቻልኩት ባሪያ አርጎ የሚገዛኝ ሀጥያት ሆኖ ሳለ ሰይጣን በቃኝ አያውቅ ከአዲስ ነገር ጋር አስተዋወቀኝ። ዘፈን መስማቴ ሀጥያት ወደማይመስሉ ነገር ግን ህይወቴን የማበላሸት አቅም ወዳላቸው ነገር ይመራኝ ነበር። እንግሊዝኛ ዘፈኖች ብቻ ነበር የምሰማው ዘፈን ከመስማት ብዛት ማፍቀር መመኘት ጀመርኩ፣ ብዙ ዘፈኖች "only God can judge me" (እግዚአብሔር ብቻ ነው ፈራጅ) የሚል ሃሳብ ይዘው ሲዘፍኑ ሃሳቤን እየሞረዱት ሰው የሚለኝን ወዳለመስማት አሳደጉኝ፣ አንዳንድ ዘፈኖች ስለመሳሳም ከመዘፈናቸው የተነሳ ከፍቅር ይልቅ ወደ መመኘት (ወሲባዊ የሆነ ነገርን, lust) ከተቱኝ፣ ሳላስተውል በፊት በጌታ ቤት ሆኜ በመዝሙር አምልኮ የእግዚአብሔርን ህልውና እንደምለማመድ አሁን ስሜቴን የሚገልፅልኝን ዘፈን እየሰማሁ ከመዋሃዴ የተነሳ የሰይጣንን ህልውና መለማመድ ጀመርኩ፣ አንዳንዱ ዘፈን ስድብም እየቀላቀለ የልቤን ያደርስልኝ ነበር። ብቻ ምን አለፋቹ አማረኛም ሆነ እንግሊዝኛ ዘፈን ስሰማ ተመስጬ ሄጄ አንዳንዴ ሳለቅስ ልታገኙኝ ትችላላችሁ። ዘፈን ራሴን ከሰዎች ጋር የማወዳድርበት ነገር ሆኖም አገኘሁት። የግል ት/ቤት እንደሚማር ተማሪ አዳዲስ ዘፈኖችን ማወቅ፣ መሸምደድ፣ በድምፅ መፎካከር፣ ለእንግሊዘኛ ዘፈኖች የሚሆኑ ግጥሞችን መፃፍ ተጀመረ። ግጥሞቹ ከልቤ የሚወጡ ስለነበሩ ማፍቀር እንድመኝ ያረገኝ ዘፈን የምርም የቀረብኩትን ሰው እንዳፈቅር አገዘኝ ከልጁ ጋር ከዘፈን ውጪ ወሬ ኖሮኝ አያውቅም፣ ዘፈን ከመስማት ብዛት የምሰማው ዘፈን አብዛኛው ስለወንዶች የማይረባ ነገር ሲነግረኝ በግዜው በቅርብ የማቃቸው ለወንድ መጥፎ ምሳሌ የሚሆኑም ስለነበሩ ዘፈን የሚለኝን ለማመን አይከብድም ነበር፣ እንዳፈቅር ያገዘኝ ዘፈን እንደሴት ራሴን መጠበቅ እንዳለብኝ ሲያስተምረኝ ሰው ቢሄድ ሰው ይመጣል በሚል ስሌት በእግዚአብሔር መልክ ለተፈጠረ ፍጥረት የረከሰ አስተሳሰብ እንዲኖረኝ ሚናውን ተጫወተ፣ አንዳንድ የእንግሊዝኛ ዘፈኖች ሃሌሉያ hallelujah የሚለውን ቃል እየተጠቀሙ ሲዘፍኑ የእግዚአብሔርን ስም እየጠቀሱ ሲዘፍኑም የእግዚአብሔር ነገር እንዲቀልብኝ ያረጉኝ ነበር፣ ማፍቀር እንድመኝ ያደረጉኝ ዘፈኖች ምን ያህል ውስጤ ባዶ እንደሆነ እንዳስተውል ረድተውኝ ያንን የጎደለውን ቦታ በወንድ መሙላት እንደሚቻል ይነግሩኝ ነበር፣ ቤት ውስጥ ከቤተሰቦቼ ጋር እንደምፈልገው መሆን ስላልቻልኩ የሚወደኝ የሚቀበለኝ አለሁልሽ ለሚለኝ ለየትኛውም ሰው ልቤ ክፍት ነበር። ለማፍቀር ስዘጋጅ አለም በዘፈን ውስጥ ምን አይነት ወንድ እንደሚያስፈልገኝ ስለነገረችኝ ከእግዚአብሔር ለመጠየቅ አላሰብኩም። እግዚአብሔር ያልሞላውን ቀዳዳ ማንም ላይሞላው ነገር ጎዶሎዬን የምሞላ መስሎኝ አንዴ በአለም ፍቅር፣ በmasturbation (ሴጋ)፣ አንዴ ከጓደኞቼ ጋር በማወራው እና በምሰማው የተቃራኒ ፆታ ፍቅር፣ አንዴ በዘፈን፣ የመጣን ሰው ስቀበል የሄደን ስሸኝ፣ ሁሉንም ነገር ያለማስተዋል ሳደርግ ቆየሁ። ጎዶሎዬን ይሞላል ያልኩት ሁሉ ጎዶሎዬን አሰፋው፣ ጥሜን ያረካል ያልኩት ሁሉ ጥሜን ጨመረው፣ ጉሮሮ ውሃ ሲያጣ እንደሚደርቅ ከእግዚአብሔር ህልውና ውጪ ስኖር ከግዜ ወደግዜ የህይወትን ውሃ፣ ፅድቅን፣ ቅድስናን የበለጠ እያጣሁና ውስጤ እየደረቀ ጥማቴን አባሰው። የሚገርመኝ የመጀመሪያ ግዜ ፍቅር እስከሚይዘኝ ድረስ ያለወንድ መኖር እንደሚቻል አውቅ ነበር፣ የወሲብ ፍላጎት አድሮብኝ ራሴን በራሴ ለማርካት በፍትወት መቃጠል እስከምጀምር ድረስ ያለፍትወት መኖር እንደሚቻል አውቅ ነበር፣ ጎዶሎዬን ለመሙላት መተራመስ እስከምጀምር ድረስ በእረፍት መኖር እንደሚቻል አውቅ ነበር፣ መቅበዝበዝ እስከምጀምር ከጌታ ቤት እስክወጣ ድረስ ከእግዚአብሔር ጋር መኖር እንደሚቻል አውቅ ነበር፣ መፀለይ እስከማቆም ድረስ መፀለይ እንደሚቻል አውቅ ነበር፣ ቃል በማነብበት ወቅት መፅሐፍ ቅዱስ ማንበብ እንደሚቻል አውቅ ነበር፣ በእግዚአብሔር ህልውና ውስጥ ስውልና ሳድር ባልተቀደሰ ህዝብ መሀል መቀደስ እንደሚቻል አውቅ ነበር፣ አሁን ግን መኖር ይቻላል እግዚአብሔር ቅርብ ነው ከሱ ጋር ህብረት ማድረግ ይቻላል ያልኩት ህይወት ሁሉ ዳገት ሆኖብኝ ለሰይጣን እንደተፈጠርኩ ማሰብ እንድጀምር አረገኝ። ለሴክስ የነበረኝን ጥማት ራሴን ለማርካት የጀመርኩት ልምምድ፣ ወደድኩት ያልኩትን ልጅ እሱ እንዳይጎዳኝ ከመፍራት የሱን ስሜት ቀድሜ መጉዳት፣ ሰዎችን ማመን አለመቻሌ፣ ያለቅድስና መኖሬ፣ የትምህርት ውጤቴ መቀነስ፣ ብዙ ተስፋ ይዤ ተስፋ ለማረገው ነገር መዘጋጀት አለመቻል፣ ጭራሽ ይኖረኛል ብዬ የማላስበውን ማንነት መያዜ በቀን በቀን ራሴን ወደመጥላት ያሳድገኝ ጀመር። ይቀጥላል. . . #ሼር ⬇️ ይቀላቀሉን ⬇️ ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖ 📩📩 @hiwotkale @hiwotkale 🚀🚀 @hiwotkale @hiwotkale 🚻🚻 @hiwotkale_bot https://t.me/joinchat/S3vhwOnUpABxGbZ3
نمایش همه...
Voice of Heven♥

በእግዚአብሄር ለተወደዳቹና ቅዱሳን ለመሆን ለተጠራቹ በኢቲዮጵያ ላላችሁት,ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን ።✋ ለአስተያየት or ጥያቄ @hiwotkale_bot #new gospel song 👉 #word of God 👉 #christian news And others please join us!!

https://t.me/hiwotkale

PART1⃣ 🤝🤝🤝የማላውቀው ሰላምታ ከሰማይ መጣ❗ [ ብታምኑም ባታምኑም እውነቱ አይቀየርም። 12ኛ ክፍል የተአምራት አመት ] በብሉይ ኪዳን በድምፅ ያወራ አምላክ አሁን ዝምታን መርጦ ነው??? ተወልጄ ያደኩት በክርስትና ጴንጤ የሚለውን ሀይማኖት በሚከተሉ እናትና አባት ነበር። ስሜ የወጣልኝ ገና ከመወለዴ በፊት በማህፀን ውስጥ ሆኜ ነበር። በወቅቱ እናትና አባቴ በገንዘብ የሚቸገሩበት ወቅት ስለነበር ከክርስትና ባለፈ በህክምና ላይ እምነታቸውን ያደረጉ አልነበሩም። እናቴ ታላቅ እህቴንም ታናሽ ወንድሜም እኔንም ቤት ውስጥ ነው የወለደችን። በህክምና ክትትል አድርጋ ስለማታውቅ ሶስታችንም ፆታችን ስንወለድ ነው የታወቀው። ሴት ነኝ፣ ዲቦራ እባላለሁ ስሜ ከመወለዴ በፊት ጌታ ለቤተሰቦቼ ሴት ልጅ እንደምትወለድ እና ስሟም ዲቦራ እንደሚባል በነብይነት ፀጋ እንደምታገለግለው እና መፅሃፍ ቅዱስ ላይ ያለችውን የዲቦራ ፀጋ እንደሚያርፍባት የተነገረላት ሴት ነኝ። ምን ዋጋ አለው ክርስትና ህይወት እንጂ ሃይማኖት ሲሆን አያምርበትም፣ እምነት የግል እንጂ የጀማ ሲሆን አያድንም፣ ጌታ የግል እንጂ የቡድን ሲሆን ፍቅሩ አይገባንም። ልጅ እያለው የማስታውሰውን አብዛኛውን ልጅነቴን ከእግዚአብሔር ጋር በሚገርም ህብረት ነው ያሳለፍኩት። ቤት ውስጥ የፀሎት፣ የቃል፣ የአምልኮ ግዜ ስለነበረን የእግዚአብሔርን መንፈስ እየተለማመድኩ ነው ያደኩት። በ3አመቴ አባቴ መንፈስ (አጋንንት) እየተቃወመ ሲፀልይ የሚያየውን መንፈስ እኔ በጨዋታ መሃል ሆኜ እንኳን ይታየኝ እንደነበር ያወሩኛል እኔ ባላስታውስም (አከራያችን የዛር መንፈስ ያመልኩ ነበር በኋላ ጌታን ቢቀበሉም፤ አባቴ ሲፀልይ ጥቁር ውሻ አይጥ የተለያዩ ነገሮች ይታዩት ነበር እኔ ደሞ እሱ ሲፀልይ የሚያያቸውን እየተጫወትኩ ሳይ ደንግጬ ከተንበረከከበት ስሩ ገብቼ አስነሳው እንደነበር በወሬ እሰማለሁ) ከዛ በኋላም የማየው ነገር ያስደነግጠኝ ስለነበር መቋቋም በምችልበት ግዜ እንዲሰጠኝ ፀልዮ ቆመልኝ ከዛ 12ኛ ክፍል ሆኜ ነው እንደገና መንፈስ ያየሁት ከዛ በፊት አይቼ አላቅም። በልጅነቴ እስከ 6ኛ ክፍል ድረስ በጣም የምፀልይ ቃል የማነብ እና በየግዜው እግዚአብሔር በህልም የሚያናግራት ሴት ነበርኩ። መልክት እየተቀበልኩ ነበር ከህልሜ ምነሳው የሚነግረኝ መልክት ሁሉ ይፈፀም ነበር። ሰው ሁሉ እንደኔ እግዚአብሔር የሚያዋራው ስለሚመስለኝ ህልሜን ለሰው ተናግሬ አላውቅም። ሰዎች ህልም ፍቱልኝ ብለው ለሰው ሲያወሩ ይገርመኝ ነበር እኔ የማየው ህልም እዛው ህልሜ ውስጥ ነበር ተፈቶልኝ የምነሳው። እስከ 6ኛ ክፍል የሚገርም ህይወት አሳለፍኩ ሰላምና ደስታ መኖሪያዬ ነበሩ 6ኛ ክፍል ላይ አንድ ወቅት ቤት ውስጥ ልሳን ስለሚባለው ፀሎት ጥያቄ ማቅረብ ጀመርኩ። ሰው ከእግዚአብሔር ጋር የሚያወራውን ድብቅ ቋንቋ የመናገር ሃይለኛ ጥማት ውስጤ አረፈ። ጌታ እንዲያናግርሽ ጠይቂው ሲሉኝ በእምነትና በፍፁም መፈለግ ውስጥ ለአንድ ሳምንት ይሄን ጥያቄ አቀረብኩ። ልፀልይ በተንበረከኩበት ይሄን ጥያቄ ብቻ ሆነ የማቀርበው። የሆነ ቀን ከወንድሜ እና ከአክስቴ ልጅ ጋር ከልደት ስንመለስ ቤት ውስጥ አምልኮ እና ፀሎት ጨርሰው የመደምደሚያ የምስጋና ፀሎት ላይ ሆነው ደረስን። ወንድሜና የአክስቴ ልጅ ወደ መኝታ ቤት ሲሄዱ ፀሎት ሲጨርሱ በመድረሴ እየተናደድኩ ለምስጋና ተንበረከኩ። አጭር የምስጋና ፀሎት አቀረብኩ ፀሎቱ አልቆ ስነሳ ወደ መኝታ ቤት ሲሄዱ የነበሩት ወንድሜና የአክስቴ ልጅ ቆመዋል አክስቴ ከተንበረከኩበት ስነሳ ትኩር ብላ ተመልክታ በልሳን እንደፀለይኩ ነገረችኝ። ውስጤ በደስታ ቢሞላም እኔ ግን የፀለይኩት ፀሎት ሙሉ ለሙሉ አማረኛ እንደነበር ነበር ማቀው። የፀለይኩት ፀሎት እነሱ ሲሰሙት ሌላ ቋንቋ ሆነባቸው እንጂ እኔ እንደውም ባይነግሩኝ እራሱ የተለየ ፀሎት እንደፀለይኩ አልታወቀኝም ነበር። ፀሎቴ አማረኛ እንደነበር ነግሬ የፀለይኩትን ፀሎት ልደግምላቸውም አስቤ ነበር የሚገርመው በመንፈስ ሆኜ ከልቤ የሆነ ምስጋናን እንዳቀረብኩ ባስታውስም የፀሎቱ ቃላት ያልኩት ነገር ከአይምሮዬ ሙሉ በሙሉ ነው የጠፋው። በጌታ ቤት ሆኜ ድምፁን እና ህልውናውን እንደፈለኩ በማገኝበት በዚ ግዜ የመጨረሻ በህልም የነገረኝ መልክት ከቤቱ ልጠፋ እንደሆነ ነበር። 6ኛ ክፍል የመጨረሻው በእግዚአብሔር ቤት የቆየሁበት ግዜ ላይ አንድ ቀን ህልም አየሁ። 👉 እኔና ወንድሜ የአክስታችንን ልጅ ይዘን ወደምናቀው ከተማ ደብረዘይት እንሄዳለን። በትክክል ያንን ቦታ የምናውቀው አንድ ቀን ከአባቴ እና ከቸርች ሰዎች ጋር በመኪና ሄደን ነው። ለሶስት ቀን እዛ ፀሎት ለማድረግ የቸርች ሰዎች ልጆቻቸውን ይዘው የሄዱበት ፕሮግራም ነበር። በህልሜ ታዲያ እኔም ወንድሜም እንደምናስታውሰው እርግጠኛ ሆነን የአክስታችንን ልጅ ይዘን እንሄዳለን። የያዝነው ታክሲ የደብረዘይት መስሎን ነበር መጨረሻ ብሎ ሲያራግፍ የተሳፈርንበት ታክሲ የናዝሬት እንደነበር ገባን። ናዝሬት ከወረድን በኋላ በፊታችን ሁለት መንታ መንገድ ይታየናል። እኔ በቀኝ ያለው ወደምንፈልገው ቦታ ያደርሰናል ስል እሱ በግራ ያለው ነው ትክክለኛ መንገድ ይለኛል። ከብዙ ክርክር በኋላ ያልኩት መንገድ ልክ እንደሆነ እያወኩ ተለያይተን ላለመሄድ ስንል እሱ ባለው በግራ ሄድን። የአክስታችን ልጅ እኛ በተስማማው ተከተለችን ሙሉ መንገዱን የምንሄድበት መንገድ ልክ እንዳልሆነ እየነገርኩት ርቀን ከሄድን በኋላ "ልክ ነበርሽ አሁን የማንጠፋ መስሎን ጠፋን ይለኛል።" የህልሙ ፍቺ 👉 በመጀመሪያ በወላጆቻችን እና በቸርች የምናውቀው ጌታ እንደነበር እነሱ በሌሉበት ስንወጣ እነሱ ባሉን መንገድ እንደማንሄድ ነበር። 7ኛ ክፍል ዘፈን እንደቀላል ተጀመረ፣ መፀለይ አቆምኩ፣ ቃል ማንበብ አቆምኩ፣ እግዚአብሔርን መፍራቴ መቀነስ ሲጀምር ህልም ማየት መልክት መቀበል የእግዚአብሔርን ድምፅ መስማት እየጠፋ መጣ። ይቀጥላል. . . #ሼር ⬇️ ይቀላቀሉን ⬇️ ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖ 📩📩 @hiwotkale_bot 🚀🚀 @hiwotkale @hiwotkale 🚻🚻 https://t.me/joinchat/S3vhwOnUpABxGbZ3
نمایش همه...
Voice of Heven♥

በእግዚአብሄር ለተወደዳቹና ቅዱሳን ለመሆን ለተጠራቹ በኢቲዮጵያ ላላችሁት,ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን ።✋ ለአስተያየት or ጥያቄ @hiwotkale_bot #new gospel song 👉 #word of God 👉 #christian news And others please join us!!

https://t.me/hiwotkale