✞✞✞ ቅዱሳን ዘ ኢትዮጵያ ✞✞✞
✞ቅዱሳን ዘ ኢትዮጵያ ✞ ♦♦♦ኢትዮጵያውያን ቅዱሳን♦♦♦ ❇ የዚህ ቻነል አላማ ❇ ▶ ▶ ▶ ከኢትዮጵያ የተገኙ የቅዱሳን አበው እመውን (አባቶች እና እናቶች) የቅዱሳንን ስም ፡ የተጋድሎ ህይወት ፡ ፍሬ በጥቂቱ ማስተላለፍ ማስተማር ነው፡ ➕ የቅዱሳን <ቅድስና>የብፅዕና የቅድስና ተጋድሎ ታሪክ ገድል ቃልኪዳን እንገብይ እንምሰላቸውም፡፡ ዕብ ፲፫÷፯-፱ @kidusan_Z_ethiopia
نمایش بیشتر- مشترکین
- پوشش پست
- ER - نسبت تعامل
در حال بارگیری داده...
در حال بارگیری داده...
‹‹ ዳግሚት ሔዋን / ሁለተኛይቱ ሔዋን ›› ምሳሌ 17 [ ምሳሌያት በእንተ ወላዲተ አምላክ ] እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በቅዱሳን ሊቃውንት አንደበት ዳግሚት ሔዋን እየተባለች ትገለጻለች ፤ በቅድስት ቤተ ክርስቲያንም ትመሰገናለች ፡፡ በቀዳሚት ሔዋን ፈንታ አማናዊት እመ ህዋን ናትና ፤ ሁለተኛ ስለመሆኗ ዳግሚት ስንላት ፤ አማናዊት የህያዋን እናት ስለመሆኗ ደግሞ አዲሲቱ ሔዋን እንላታለን ፡፡ ‹‹ ወሠመየ አዳም ስማ ለብእሲቱ ሔዋን እስመ ይእቲ እሞሙ ለሕያዋን - አዳምም ለሚስቱ ሐየዋን ብሎ ስም አወጣላት የሕያዋን ሁሉ እናት ናትና ›› ዘፍጥረት 3 ፣ 20
‹‹ የገነት ዛፍ እና ሰባተኛይቱ ተራራ ›› ምሳሌ 3 [ ምሳሌያት በእንተ ወላዲተ አምላክ ] ‹‹ በኵይናተ እሳት ዘይነድድ ዘየዐቅበኪ ሱራፊ ወአጼነወ መዓዛኪ ሔኖክ ጸሐፊ ጽጌ ዕፀ ገነት ማርያም ዘኢትትነገፊ - ሱራፊ መልአክ የእሳት ጦርን ይዞ የሚጠብቅሽ መዓዛሽንም ጸሐፊ ሔኖክ ያሸተተ የማትነግፊ የማትጠፊ የገነት ዛፍ ቅድስት ድንግል ማርያም ›› ማሕሌተ ጽጌ / አባ ጽጌ ድንግል ‹‹ ይህ ያየኸው ራሱ የጌታን ዙፋን የሚመስለው ረጅም ተራራ ቅዱስና ታላቁ የዘለዓለም ንጉሥ የክብር ጌታ ምድርን በበጎ ሊጎበኛት በወረደ ግዜ የሚቀመጥበት ዙፋን ነው ›› (ሙሉ ይነበብ / ሙሉ ይደመጥ) መጽሐፈ ሔኖክ 7 ፣ 1 – 22