fa
Feedback
SOZO YOUTH

SOZO YOUTH

رفتن به کانال در Telegram

Helping young Christians pursue purity, purpose, relationships, and spiritual maturity. » YOUTUBE https://www.youtube.com/@sozopodcast » TIKTOK https://www.tiktok.com/@s.o.z.o For comment: @inbox_sozo P.O.BOX 387 /1033 ADDIS ABABA

نمایش بیشتر
5 794
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز
آرشیو پست ها
. 🙏 ምክር ለግሱኝ 🙏 እባካቹ  የተወደዳቹ  SOZO FAMILY የምክር አግልግሎት  ከእናንተ እፈልጋለው ወንድማቹ  D.  እባላለው። ከዩኒቨርሲቲ   ተመሪቄ ከመጣሁኝ  1ዓመት ከ3ወር ሁኖኛል እግ/ር ይመስገን ከተመረኩኝ በ3ኛው ወር ላይ ስራ ያዝኩት። ይሁን እንጂ የምወዳት ጓደኛዬ ማለትም 3 ዓመት ሙሉ በፍቅር ዐለም ከእርሷ ጋር አሳለልፈናል። እዛው ዩኒቨርሲቲ ነው የተዋወቅነው ፡ በፍቅር ወስጥ ሳለን ስለ ወደፊት ሕይወታችን ብዙ ነገሮችን አወርተናል። ይህውም፡ በጣም እንደምትወደኝ  ፡ እኔም እንደምወዳት  ቃልገብቼላት ፡ ደግሞ ከሁለታችን አንዳችን ቀድሞ ስራ ከያዝን  እንደምንጋባ ተነጋግረን ነበረ፡፡ ነገር ግን በመሀሉ ቸግር ተፈጠረ  ይኸውም ሀገራችን ይራራቅ ስለነበር ከምርቃት በኋላ በስልክም  ይሁን በአካል ላገኛት ብሞክር አልቻልኩም  በጭራሽ ጠፋች፡፡ እኔም እንደ ካደችኝና ቃሏን እዳጠፈች  ገባኝ ፡፡ በዚህም ምክንያት  ተፀፀትኩኝ። ከሌሎች ሴቶች ጋር የማይሆን ተግባር ወስጥ ገባሁት ፡ ከነሱም ጋር  ሴክስ  ጀመርኩት ፡ ወንዶች ጓደኞቼን ለመሸሽ ሞከርኩት ፡ ጓደኞቼ አብረውኝ ያገለግሉ  ስለነበር  በጣም ይቆጡኝ ነበር። እኔም የተፈጠረውን  ነገር  ለማንም  አልተናገርኩም ግን ሕይወቴ  ሐጥዓት ላይ  መሆኑ ይፀፅተኛል  የእግ/ር ፀጋ  እንዲረዳኝ ፡ ከዚህም  ሕይወት  ለመውጣት እፈልጋለው ፡፡  ምን ትሉኛላችሁ??????? ለምክራችሁ ይህን link ተጠቀሙ👉@ORUsoon ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖     [ https://t.me/sozo_purity ]

1.ጉልበቱን የሚሰጥ ••• ዛሬ ባለንበት አለም ብዙዎቻችን ደክመናል። መደበኛ መርሀ ግብሮችን ለማድረግ የሰነፍን፡ ሌሎችን ለመርዳት የሰነፍን፡ እርባና ቢስ በሆኑ ነገሮች ራሳችንን አጥምደን በዙርያችን
1.ጉልበቱን የሚሰጥ ••• ዛሬ ባለንበት አለም ብዙዎቻችን ደክመናል። መደበኛ መርሀ ግብሮችን ለማድረግ የሰነፍን፡ ሌሎችን ለመርዳት የሰነፍን፡ እርባና ቢስ በሆኑ ነገሮች ራሳችንን አጥምደን በዙርያችን ያሉ መልካም ነገሮችን ለመቃኘት የደከምን ሆነናል። ወደዚ መልካም መስመር ለመመለስ አቅማችንን ከየትኛውም ጊዜ በላይ መጠቀም መቻል አለብን። ••• ታዲያ በእንደዚህ አይነት ጊዜ አንድ ሰው ጉልበቱን አሳልፎ ሲሰጥ የኢየሱስን ልግስና ያሳያል። ከራሱ ውጪ ለሌላ ሰው አእምሯዊ፣ ስሜታዊ እና አካላዊ አቅሙን ከሚሰዋ ሰው ጋር ስትጣመሪ፣ ክርስቶስ ስፍር ቁጥር የሌላቸውን ሰዎች ለመፈወስ ሰውነቱን እንዴት እንዳዳከመ መረዳት ትችያለሽ። ሁሉንም ጉልበቱን ከራሱ በስተቀር ለሁሉም ሰጠ ለዚህም ነው ዛሬ ላይ እኔን ጨምሮ ብዙዎቻችን ክርስቶስን የምንወደው። °°°ሴቶች፣ ጉልበቱን ለሌሎች የሚሰጠውን ሰው አግቡ፣ የተጠራንበት አንዱ ምክንያት ለሌሎች እንድንተርፍ ነውና ለሌሎች የሚተርፍ ነገር ያለ ስስት የሚያደርግ ወንድ ላንቺ የማይተርፍበት ምንም ምክንያት አይኖርም! 2.ጊዜ የሚሰጥ ወንድ አግቡ ••• ምንም ነገር ለማድረግ ጊዜ የለንም– አዎ በማወቅም ይሁን ባለማወቅ አንዳንዶቻችን ጊዜያችንን መስጠት ያለብን ነገር እያለ በሌላ ከንቱ በሆኑ ተግባራት ራሳችንን አጥምደን እንገኛለን። በዚህ ሁሉም በየፊናው እየሮጠ ጊዜ የለኝ በሚልበት ጊዜ ለግንኙነታችሁና በዙርያው ላሉ መልካም ተግባራት ጊዜውን የሚሰጥ ወንድ ባል ማድረግ መታደል ነው። ነገ ላይ ለቤተሰቡ ጊዜ መስጠት እንዳለበት ያውቃልና። [ እህቴ፣ ጊዜውን ለመልካም ነገር አሳልፎ የሚሰጠውን ሰው አግቢው! ]

. ሴቶች የሚሰጥ ወንድ አግቡ ••• ማግባት ያለብሽን ወንድ ዓይነት በተመለከተ ብዙ ምክሮችን ልታገኚ ትችያለሽ። በተለይ ስለ ነገ የትዳር ህይወትሽ በዙርያሽ ያሉ ወዳጆችሽን ስትጠይቂ በዋናነት ከታች
.             ሴቶች የሚሰጥ ወንድ አግቡ ••• ማግባት ያለብሽን ወንድ ዓይነት በተመለከተ ብዙ ምክሮችን ልታገኚ ትችያለሽ። በተለይ ስለ ነገ የትዳር ህይወትሽ በዙርያሽ ያሉ ወዳጆችሽን ስትጠይቂ በዋናነት ከታች ከተዘረዘሩ ምክሮች ቢያንስ አንዱን አስተናግደሽ ታውቅያለሽ ብዬ አስባለው። "ወደ ቤተ ክርስቲያን መሄዱን አረጋግጪ። (በነገራችን ላይ የትኛው ቤተ እምነት ነው? የትኛውን የመጽሐፍ ቅዱስ አፈታት ይጠቀማል?)" "ጥሩ ደሞዝ የሚያስገኝ ሥራ ቢኖረው ይሻላል። ወደፊት ​​አንቺንና ልጆቻችሁን መደገፍ ይኖርበታል።" "ከንዴታም ወንድ ተጠንቀቂ። ንዴቱን  ሊቆጣጠረው ካልቻለ ነገ ላይ በስሜታዊነት ፣ ተሳዳቢ ወይም በአካል ላለመተናኮሉ ዋስትና የለሽም። አንዴ ካገባሽ እና ምናልባትም ልጆች ከወለድሽ በኋላ እነዚህ ባህርያት ከባድ ናቸውና።" "እናቱን...እና አዛውንቶችን እንዴት እንደሚይዛቸው አስተውይ።  እነዚህ ባህሪያቶቹ ነገ አንቺን የሚይዝበትን መንገድ ያንፀባርቃሉና።" °°°አንዲት ሴት እራሷን በፍቅር ልታስር የምትፈልገውን ወንድ ስታገኝ  እነዚህን ላይ ማመዛዘን አለባት። ቤተ ክርስቲያንን፣ ታታሪነትን፣ ራስን መግዛትን እና ሴቶችን፣ አረጋውያንን እና ሌሎችን ሁሉ ከፍ አድርጎ መመልከት ይገባዋል። ••• ሆኖም፣  ግልጽ ባይሆንም ምክሬ ቀላል ነው፡  ሴቶች የሚሰጥ ሰው አግቡ። በበለፀገ አውድ፣ የራሱን የሚሰጥ ወንድ እንድታገቢ ሀሳብ አቀርባለሁ። [ ምን ምንድነው መስጠት ያለበት? የዛሬው ርዕሳችን ነውና ይህን መልዕክት ለወዳጆቻችሁ እያጋራችሁ አብራችሁኝ ቆዩ...]

4. የእግዚአብሔርን ህልውና አብልጠን እንድንፍልግ ዓላማ ቢስነት ሊሰማን ይችላል " የሕይወትን መንገድ አሳየኸኝ፤ ከፊትህ ጋር ደስታን አጠገብኸኝ፥ በቀኝህም የዘላለም ፍሥሐ አለ።"(መዝ 16:11፤) ••• አላማ የለሽነት ስሜት ከተሰማን፡ከደከመን እና የህይወትን መንገድ ማወቅ ከፈለግን የእግዚአብሔርን ፊት መፈለግ አለብ።                  ✅ ይቀላቀሉን ⤵️ ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖     [ https://t.me/sozo_purity ]

3. ሌሎችን የማስታጠቅ አቅም እንድናገኝ አላማ ቢስነት ሊሰማን ይችላል ••• የትላንት ችግሮቻችን ብዙ ጊዜ የነገ አገልግሎታችን ይሆናሉ። እግዚአብሔር ብዙውን ጊዜ እንድናገለግለው እንደጠራን ሰዎች በፈተና እንድናልፍ ያደርገናል። ሰዎችን ለመርዳት በሚገባ የታጠቁ ሰዎች ብዙውን ጊዜ በብዙ መከራ ውስጥ ያለፉ ናቸው። ለምሳሌ፡ (ቲቶ 2:3-5)ን ስታናይ ጳውሎስ አሮጊት ሴቶች ወጣት ሴቶችን እንዲረዷቸው ካዘዛቸው በኋላ፡ (ቲቶ 2:6) ላይ ቲቶ በወጣት ወንዶች ላይ እንዲያተኩር ነግሮታል፤ ምናልባትም ቲቶ ከታናናሾቹ ጋር የበለጠ ዝምድና ስላለው ሊሆን ይችላል እንዲህ የታዘዘው። °°°  ብዙ ጊዜ እግዚአብሔር በተመረጡ ፈተናዎች አሳልፎን ለተወሰነ አገልግሎት ያስታጥቀናል። ጳውሎስ ክርስቲያን ከመሆኑ በፊት እጅግ በጣም ሕጋዊ ሰው ነበር፣ ነገር ግን ሌሎች ሰዎች ጸጋን እንዲረዱ እግዚአብሔር ጠራው (ፊልጵስዩስ 3፡2-11)። ••• ዓላማ እንደሌለህ ከተሰማህና እንዴት በመንፈስ መሪነት ነፃነት እንደምታገኝ ስትማር፣ ሌሎች ሰዎችም ዓላማ ቢስነትን እንዲዋጉ ለመርዳት እግዚአብሔር እንዲህ በአላማቢስነት እንድትሰቃይ ሊፈቅድልህ ይችላል።                  ✅ ይቀላቀሉን ⤵️ ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖     [ https://t.me/sozo_purity ]

2. ጥሪያችንን ለይተን እንድናውቅ አምላክ ዓላማ የለሽነት ስሜት እንዲሰማን ሊያደርግ ይችላል ••• አንዳንድ ጊዜ አምላክን ለማስደሰት እየሞከርን እና በጸጋው እንደተሸፈንን አውቀን በክርስቶስ አጠቃላይ ሰላም ሊኖረን ይችላል። ነገር ግን እግዚአብሔር በዚህ ምድር ስንመላለስ እንዲኖረን ያደረገንን ጥሪ ጥርት ባለ መልኩ አለማወቃችን ልባችንን ሊያውክ ይችላል። °°° “ዓላማ” እና “ጥሪ” የሚሉትን ሀረጎች በተለያየ መንገድ እጠቀማለሁ። አላማ እግዚአብሔር ለህይወታችን ያለው አጠቃላይ ግብ ነው። እንደ ክርስቲያኖች, ሁላችንም አንድ አላማ አለን - "እግዚአብሔርን ለማክበር " ግን እያንዳንዳችን በህይወታችን ሁሉ የተለያዩ ጥሪዎች አሉን። ••• "መጠራት" የሚለውን ቃል የምጠቀምበት መንገድ እግዚአብሔር አሁን እንድታደርጉት የሚፈልገው ተግባር ነው። ይህ በህይወት ዘመን ሁሉ ሊለወጥ ይችላል እና ብዙ ነገሮችን በተመሳሳይ ጊዜ እንድናደርግ ልንጠራ እንችላለ። ለምሳሌ፣ የአንዳንዶቻችን ጥሪ ጥሩ እጮኛ፣ ጥሩ ሚስት፣ ጥሩ አባት፣ ትጉ ሰርራተኛ፣ ጎበዝ ተማሪ እንድሆን እና ኢየሱስን ከፍ የሚያደርግ ይዘት መፍጠር ሊሆን ይችላል። ነገር ግን ትምህርት ስንጨርስ  ወይም ስራ ስንቀይር ጥሪያችንም እንደየሁኔታው ይቀየራል። ••• በዚህ ሁሉ፣ አላማ የለሽ እንደሆናችሁ ከተሰማችሁ፣ እግዚአብሔር ጥሪያችሁ የበለጠ ግልጽ እንዲሆንላችሁ እያደረገ ሊሆን ይችላል። ምናልባት ጥሪያችሁን እንድትቀይሩ ወይም ተግታችሁ እንድትሰሩበት እየተናገረም ሊሆን ይችላል። ••• በጥሪያችሁ እየተጋችሁ መሆኑን የምታውቁበት አንዱ መንገድ ለሌሎች መትረፍ የሚችልና ደስተኛ የሚያደርጋችሁ መሆኑ ነው። ጥሪ ፍሬ እንዳለው አንዘንጋ! ለምሳሌ፣ የጳውሎስ ስብከት ሌሎችን ጠቅሞናል፣ ይህን ማድረጉ ያስደስተው ነበር፣ እንዲሁም ጥሩ ነበር (1 ቆሮንቶስ 9:16)። [ ዛሬ በአዲስ አመት ጅማሬ ጥሪያችሁ ምንድነው? ማለት እወዳለው። ]                  ✅ ይቀላቀሉን ⤵️ ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖     [ https://t.me/sozo_purity ]

1. ፈቅደን አላማ ቢስ ከሆንን እግዚአብሔር የአላማ ቢስነት ስሜት እንዲሰማን ያደርጋል! ••• አንዳንዶቻችሁ “እግዚአብሔር ዓላማ ቢስነት እንዲሰማህ እያደረገ ነው” በሚለው ሐረግ ትንሽ ሊያናድዳችሁ ይችላል። °°° መንፈስ ቅዱስ በእኛ ውስጥ ተገቢ የሆነ የእምነት ስሜት እንደሚያመጣ ክርስቲያኖች ብዙ ጊዜ እንረሳለን (ዮሐንስ 16፡8)። √ ለምሳሌ፦ ለአንድ ነገር በድብቅ ሱሰኛ ከሆናችሁ፣ እግዚአብሔር ንስሐ እንድትገቡ ለማነሳሳት የጥፋተኝነት ስሜት እንዲሰማችሁ ያደርጋል። ከክርስቲያን ማህበረሰብ እራሳችሁን እየገለላችሁ ከሆነ፣ መንፈስ ቅዱስ የብቸኝነት ስሜት እንዲሰማችሁ ያደርጋል ይህም ህብረትን እንድትፈልጉ የሚያነሳሳ መንገድ ነው። °°° በተመሳሳይ፣ ህይወታችሁን ዓላማ በሌለው መንገድ እያኖራችሁ ከሆነ እና በእርግጥ ዓላማችሁን ካላሟላቹ፣ አምላክ ዓላማችሁን በተመለከተ መመሪያ እና ግልጽነት ለማግኘት እንድትነሳሱ ያደርጋችኋል። ብዙ ሰዎች ጠቃሚ፣ ትርጉም ያለው ሕይወት እየመሩ እንደሆነ እየተሰማቸው ዓላማ የለሽ፣ ትርጉም የለሽ ሕይወት መኖር ይፈልጋሉ። ••• እግዚአብሔር ፈጽሞ አይዋሽም (ቲቶ 1፡2)። ዓላማ የለሽነት ከተሰማችሁ፣ ዓላማ የለሽ ስለሆናችሁ ሊሆን ይችላል። እግዚአብሄር ትክክለኛ ወደሆነ መስመር ሊከተን አሉታዊ ስሜቶችን እንዲሰማን ሊያደርግ ይችላል።  (1ኛ ዮሐንስ 3፡19-24)። በአጠቃላይ. . . እግዚአብሔር አቅጣጫችንን እና አላማችንን እንድናገኝ የዓላማ አልባነት ስሜትን ይጠቀማል።

አላማ የለሽ ስሜት ለምን ይሰማናል? √ እግዚአብሔር ሁሉን ያውቃል( 1ኛ ዮሐንስ 3፡20)። መጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሔርን ጥበብ ብንለምን እንደሚሰጠን ይናገራል(ያዕቆብ 1፡5)። እንዲሁም በቃሉ እግዚአ
አላማ የለሽ ስሜት ለምን ይሰማናል? √ እግዚአብሔር ሁሉን ያውቃል( 1ኛ ዮሐንስ 3፡20)። መጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሔርን ጥበብ ብንለምን እንደሚሰጠን ይናገራል(ያዕቆብ 1፡5)። እንዲሁም በቃሉ እግዚአብሔር የሰላም አምላክ እንጂ የሁከት አምላክ እንዳልሆነ ተነግሮናል (1ኛ ቆሮንቶስ 14፡33)። ••• ታዲያ አምላክ አቅጣጫ እንዲያሳየን ብንጠይቅም አንዳንድ ጊዜ በሕይወታችን ውስጥ ዓላማ የለሽ እና ግራ የተጋባ ስሜት እንዲሰማን ለምን ፈቀደ? የዛሬ ርዕሳችን ነው. . . .⤵️

🌼[ውድ ሶዞ ቤተሰቦች] እንኳን ለአዲሱ አመት በሰላም አደረሳቹ!🌼 🌼 2015 እቅዶቻችሁ እና በውስጣችሁ ያኖራችሁት ግብ መሬት ወርዶና አካል ለብሶ የምታዩበት. . . ተሳካልኝ የምትሉበት. . . በምስጋና ውዳችሁን ከፍ የምታደርጉበት. . . ዘመን ይሁንላችሁ!

የተቃራኒ ፆታ ጓደኝነት ፅንሰ ሐሳብ መነሻ ••• የተቃራኒ ፆታ ጓደኝነት አሁን የመጣ ሀሳብ ወይም ሰይጣን እኛን ለማጥመድ ብሎ የፈጠረው ሳይሆን በእግዚአብሔር የዘላለም ፕሮግራም ውስጥ የነበረ ደግሞም ኃጢያት ወደ ምድር ከገባ በኋላ ምንም እንኳን የዘላለም ዕቅድነቱ ቢቀርም የእግዚአብሔር መልካም ሐሳብ ሆኖ የቀጠለ ነው፡፡ ••• ለአዳም እግዚአብሔር እጅግ በጣም ብዙ ነገሮችን ሰጥቶታል ለምሳሌ ምንም የማይጎድልበትን መኖሪያ (ኤድን ገነት)፣ በጣም ብዙ አይነት ዝርያ ያላቸውን እንስሳት፣ ለመብላት ደስ የሚያሰኙ ፍራፍሬዎችን፣ ወዘተ... ነገር ግን ይሄ ሁሉ ሲሆን ለአዳም እንደ እርሱ ያለ ረዳት አልተገኘለትም ነበር :: (ዘፍ 2፤20) ለመጀመሪያ ጊዜ አዳም የተሟላ የደስታ ኑሮ መኖር የጀመረው እንደ እርሱ ያለች ረዳት ሔዋን ስትፈጠርለት ነበር፡፡ ••• እንደውም እግዚአብሔር ከአዳም የጎን አጥንቱ ላይ ወስዶ ሔዋንን በመፍጠር ወደ አዳም ሲያመጣት በሚገርም ሁኔታ ከየት እንደመጣች እንኳን ማንም ሳይነግረው በቀጥታ እንዲህ ነበር ያለው “አዳምም አለ፦ ይህች አጥንት ከአጥንቴ ናት፥ ሥጋም ከሥጋዬ ናት እርስዋ ከወንድ ተገኝታለችና ሴት ትባል። ስለዚህ ሰው አባቱንና እናቱን ይተዋል፥ በሚስቱም ይጣበቃል ሁለቱም አንድ ሥጋ ይሆናሉ።” (ዘፍ 2፤23-24) ይሄ የሚያሳየን የሴትና ወንድ ጓደኝነት የሰይጣን ፈጠራ ወይም ደግሞ የሰዎች ስሜት ብቻ የፈጠረው ሳይሆን ከጅምሩ የእግዚአብሔር መልካም ሐሳብ እንደነበረ ነው፡፡ ••• እንደዚህ መልካምና ደስ የሚያሰኝ ለጥቅማችንም የተፈጠረ ሆኖ እያለ ግን አዳም በሰራው ኃጢያት ምክንያት ሰው ስለወደቀ ሰይጣንም ለክፉ ስራው ማስፈፀሚያነት ይጠቀምበት ጀመር፡፡ እኛ ክርስቶስ ኢየሱስን አምነን ከመንፈስ ቅዱስ ዳግም የተወለድን ቅዱሳን በሙሉ ለየት የሚያደርጉን ነገሮች ውስጥ አንዱ በሰይጣን ተበላሽቶ ከወደቀው ዓለም የተዋጀንና በአዲሱ አዳም (ኢየሱስ) የዘር ግንድ የገባን መሆናችን ነው፡፡ ••• የወደቀውና የተበላሸው ዓለም ውስጥ ያሉ ሰዎች የራሳቸው የሆነ የአኗኗር ስርአትና የሚመሩበት ሕግ (መልካምም ሆነ ክፉ) እንዳላቸው ሁሉ እኛም ደግሞ የሚገዛንና ስርአት የሚያስይዘን የህይወት መንፈስ ሕግ አለን፡፡ ••• ስለ ሰው ለሚፈጠርብን ማንኛውም ጥያቄ መልስ የምናገኘው መሪያቸን ከሆነው መፅሐፍ ቅዱስ ብቻ እና ብቻ ነው፡፡ እግዚአብሔር ሰውን ሲፈጥር ሴት እና ወንድ እርስ በርስ እንዲፈላለጉ እና እንዲፋቀሩ የሚያደርግ ስሜት በውስጣቸው አስቀምጧል፡፡ ••• እንግዲህ የተቃራኒ ፆታ ጓደኝነትና የትዳር ዲዛይነር እግዚአብሔር ከሆነ፤ እንዴት በቅድስና እንደምንይዘው የሚያሳይ ደግሞ መንገድ አለው ማለት ነው፡፡ ••• ታዲያ ፈጣሪችን የሆነው እግዚአብሔር እንተዳደርበት ዘንድ የሰጠን ማኑዋል መፅሐፍ ቅዱስ ነው እንጂ ስለኛ አፈጣጠር የማይመለከተው አካል አቅጣጫ ሊያሳየን አይችልም፡፡ መቼ? ••• የፍቅር ጓደኝነትን ለመጀመር ትክክለኛ ጊዜውን ማወቅ እጅግ በጣም አስፈላጊ ነው፡፡ የብዙ ሰዎች ጓደኝነት ትዳር ላይ ሳይደርስ ከሚፈርስባቸው ምክንያቶች ውስጥ አንዱ ያለጊዜው መጀመሩ ነው፡፡ ጓደኝነትን ያለጊዜ በመጀመር ከሚደርሱት ጉዳቶች ውስጥ ደግሞ ዋነኛው የቅድስና ችግር ነው፡፡ ከእነዚህ ሁሉ ችግሮች ለመዳን የፍቅር ጓደኝነትን ከመጀመራችን በፊት አሁን ትክክለኛ ጊዜው ነውን? ብለን ራሳችንን መጠየቅ ይኖርብናል፤ ምን መጠየቅ ብቻ እርግጠኛ የሆነ መልሱንም ማወቅ አለብን!! ••• ጊዜ አለመጠበቅ የሚያመጣውን ጉዳት በሚገባ ያስተዋልን እንደሆነ “ታዲያ እንዴት ነው ጊዜውን ማወቅ የምንችለው?” የሚል ጥያቄ ወደ አእምሮአችን ይመጣል፡፡ ••• የዘጠኝ ዓመት ሕፃን ልጅ ፍቅረኛ ልያዝ ወይ ብላ ብትጠይቃችሁ በእርግጠኝነት የምትመልሱላት መልስ አንቺ እኮ ገና ሕፃን ልጅ ነሽ ፍቅረኛ ለመያዝ ትንሽ ማደግ አለብሽ የሚል ነው፡፡ ነገር ግን አንድ የሀያ አምስት አመት ኮረዳ ተመሳሳይ ጥያቄ ብትጠይቃችሁ ህፃን ነሽ እደጊ አትሏትም ወይም ደግሞ እንዴት በሀያ አምስት ዓመትሽ አትሏትም ይልቁንም ልጁ ማነው? ክርስትያን ነው ወይ? ባሕርይው ምን ዓይነት ነው? እና ሌሎችንም ጥያቄዎችን በመጠየቅ ለማጣራት ነው የምንሞክረው፡፡ ከዚህ የምንረዳው የፍቅር ጓደኝነትን መያዝ ወይም አለመያዝ የሚወሰነው በእድገታችን ነው ማለት ነው፡፡ እድገት ምንድን ነው? በእድሜና በአካለመጠን የመግዘፍ ብቻ ወይስ አርቆ የማሰብና የማስተዋል መጠን? ክፍል እየቆጠሩ መመረቅ ብቻ ወይስ በማህበራዊና ስነልቦዊ ዕውቀት መራቀቅ?፣ እድገት ምንድን ነው? ስንት ዓይነት እድገት አለ? እድገት የሚለካው ሁሉን አቀፍ በሆነ አዎንታዊ የለውጥ መጠን ነው፡፡ አንድ ሰው ሀያ እና ሀያ አንድ አመት ስለሞላው ብቻ አድጓል ማለት አንችልም፡፡ በትምህርት ልቆ ዶክተር ኢንጂነር ቢባል ይህ ብቻውን የእድገቱ ማሳያ ሊሆን አይችልም፡፡ እድገት ዘርፈ ብዙ፣ መጠነ-ሰፊና፣ እና ሁሉን አቀፍ አዎንታዊ የለውጥ መጠን ነው፡፡ የፍቅር ጓደኝነትን ከመጀመራችን በፊት በቅድሚያ ሁለንተናዊ የሆነ እድገታችንን መመርመር መቻል አለብን፡፡ ይህን ስናደርግ ትክክለኛ ጊዜው ይሁን አይሁን መወሰን ቀላል ይሆንልናል፡፡

✨✨✨✨✨✨ተለቀቀ✨✨✨✨✨✨ Excited!! 💯💯 መንፈስ ቅዱስ | ASTUECSF choir new Gospel music video View - Like - share - Subscribe to Our YouTube Channel on YouTube https://youtu.be/4q-0mWC-Hsw on telegram @astuecsf on insta @astuecsf2k19 on fb @astuecsf2k

✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ ዛሬ ጠዋት 4፡00 በ ASTU YOUTUBE channel ይለቀቃል። Excited!! 💯💯 መንፈስ ቅዱስ | ASTUECSF choir new Gospel music video View
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ ዛሬ ጠዋት 4፡00 በ ASTU YOUTUBE channel ይለቀቃል። Excited!! 💯💯 መንፈስ ቅዱስ | ASTUECSF choir new Gospel music video View - Like - share - Subscribe to Our YouTube Channel on YouTube https://www.youtube.com/channel/UCm48BEH7GumfTuvFWPMAS3w on telegram @astuecsf on insta @astuecsf2k19 on fb @astuecsf2k

የ ፖርኖግራፊና የ masturbation ሶስት ዋና ዋና ውሸቶች ውሸት 1: "ይሄ የመጨረሻህ ነው" ••• ምንም ያህል ጊዜ የፖርኖግራፊ ፊልም ብታይ 'ይሄ ለመጨረሻ ጊዜ የምታየው ነው' የሚል የውሸት ድምፅ አለ፡፡ የመጨረሻህ እንደሆነ ስላመንክ ወደ ድህረገፁ ስትገባ ወይም ዳውንሎድ ስታደርግ ለሰው መናገር አለብኝ ብለህ አታስብም ምክንያቱም 'የመጨረሻ ጊዜህ ነው' :: ፖርኖግራፊ ይህ የመጨረሻህ ነው ብሎ ካሳመነህ ለማንም ችግርህን አታወያይም ማንም አይፀልይልህም ማንም አይረዳህም:: መጨረሻ የሌለው መጨረሻ:: ውሸት 2: "በፈለግከው ጊዜ ማቆም ትችላለህ" ••• ፖርኖግራፊና masturbation እንዲህ ይሉሃል :-" እኛ በሌሎች ትዳሮች ላይ ፣ ሌሎች ጓደኞችህ ላይ፣ ሌሎች ቤተሰቦች ላይ ፣ ሌሎች የቤተክርስቲያን አገልጋዮች ላይ ያደረሰውን ውድቀት ታውቃለህ......አንተ ግን 'ሱስ አልያዘህም' ፡፡ በፈለግከው ጊዜ ማቆም ትችላለህ፡፡ በዚያ ላይ ሌሎች ላይ የሚያደርሰውን አይነት ተፅእኖ አንተ ላይ አያደርስም፡፡ ህይወትህን ፣ ትዳርህን ፣ ቤተክርስቲያንህን ፣ አገልግሎትህን አይጎዳም፡፡ አንተ ነህ እንጂ የምትቆጣጠረው እሱ አይቆጣጠርህም፡፡ " ውሸት3: "ትግልህን ለሰው መናዘዝ ብዙ ዋጋ ያስከፍልሃል፡፡ " ••• ፖርኖግራፊና masturbation በሚስጥር እንድትኖር ነው ሚፈልጉት፡፡ ብቻህን ስትሆን የምታደርጋቸው ነገሮች ስለሆኑ ሁሌ ብቻህን ብትሆን ፣ጓደኞች ባይኖሩህ ደስ ነው የሚላቸው፡፡እነዚህ ክፉ ነገሮች የመናዘዝን ዋጋ ችግሩን ከመደበቅ ዋጋ ጋር አመዛዝነህ የመደበቅ ዋጋ ቀላል እንደሆነ እና ብዙ ህመም እንደሌለው ሊያሳምኑህ ይጥራሉ፡፡ በሰዎች ያለህን ተቀባይነት ታጣዋለህ የሚል ድምፅ ያሰማሉ፡፡ ነገር ግን ሃጢያትህን አለመናገር ከዛ ቀንበር እንዳትወጣ ያደርግሃል፡፡ ••• እውነቱ ግን ይህ ነው "እርስ በርሳችሁ በኃጢአታችሁ ተናዘዙ። ትፈወሱም ዘንድ እያንዳንዱ ስለ ሌላው ይጸልይ፤ የጻድቅ ሰው ጸሎት በሥራዋ እጅግ ኃይል ታደርጋለች።" (የያዕቆብ መልእክት 5:16) •○• ከላይ የተዘረዘሩትን ውሸቶች የምታምን ከሆነ ከዚህ እስራት ለመውጣት የምታደርገውን ትግል ተራራ ያደርግብሃል፡ እግዚአብሄር በእነዚህ ድርጊቶች ተበሳጭቶ ፊቱን እንዳዞረብህ ሚሰማህ ከሆነ ተሳስተሃል፡፡ እንደውም ከዚህ እስራት እንድትወጣ እየታገለልህ ነው፡፡ 《ጌታ ኢየሱስ የሞተውና ሞትንና ሃጢያትን ያሸነፈው አንተን በሃጢያት ላይ አሸናፊ ሊያደርግህ ነው:: 》

Behind every sinful act, unbelief in God's promises is rooted in it. መጋቢ John Piper በአንድ ስብከቱ ላይ ስለ lust እየተናገረ እንዲህ አለ "you are not addicted"። ይህንንም ለማብራራት እንዲህ ሲል አንድ ምሳሌ ተናገረ " በውስጥህ ልትቋቋመው የማትችለው ክፉ ምኛት(lust) እንደተቆጣጠረህ ተሰማህና ያን መሻትህን ተከትለህ nude picture ለማየት ወሰንክ። ልክ ምስሉን ልትመለከት ስትል በድንገት አንድ ሰው የባለቤትህ አንገት ላይ ቢላ ሊያርዳት እንዲያመቸው አስተካክሎ ይዞ፣ 'ይህን ምስል የምትመለከት ከሆነ እገላታለሁ' ቢልህ፣ ያለ ጥርጥስ ምስሉን መመልከትህን ትተዋለህ። ወይ ደግሞ በሌላ በኩል፣ ምስሉን ልትመለከት ስትል አንድ ሰው ወደ አንተ መጥቶ 'ይህን ምስ የማትመለከት ከሆነ አንድ ሚሊዮን ብር እሰጥሃለሁ' ቢልህ አሁንም ምስሉን መመልከት ትተዋለህ።" ይህን የPiperን ንግግር ያመጣሁት አንድ መልዕክት ለማስተላለፍ ፈልጌ ነው። ከላይ በጠቀስኩት ምሳሌ ላይ እንዳያችሁት "አንድ ሚሊዮን ብር እሰጥሃለሁ" የተባለውን ተስፋ እውን እንደሆነ ስላመነ ያንን ምስል ላለመመልከት ጨክኗል።አስቡት ይህ ምድረዊና ሀላፊ ጠፊ ነው። ለእኛ እግዚአብሔር በክርስቶስ የሰጠን ተስፋ ከዚህ እጅግ የላቀ ነው። ደግሞም እውንና የሚፈጸም ነው(አንዳንዱም ባመንን ጊዜ ተፈጽሟል)። ታዲያ ይህ ተስፋ እውን ብለን ያመንን እንደሆነ የኃጢአትን ግብዣ ለመግፋት አቅም እናገኛለን።ለኃጥያትም ማታለል በቀላሉ እጅ አንሰጥም። እኛ ግን በእግዚአብሔር የተገባልንን ተስፋ ከማመን ይልቅ ኃጢአት የሚሰጠንን የጊዜያዊ ደስታ ተስፋን በማመን በኃጢአት እንዘፈቃለን። እርግጥ ነው በዚህ ዓለም ስንኖር ፈተናው ቀላል አይደለም። ነገር ግን ኃጢአት ከሚሰጠን የጊዜያዊ ደስታ ተስፋ ይልቅ እግዚአብሔር በክርስቶስ የገባልን የዘላለሙ ተስፋ ይልቃልና “ሸክም የሚሆንብንን ሁሉ፣ በቀላሉም ተብትቦ የሚይዘንን ኀጢአት አስወግደን በፊታችን ያለውን ሩጫ በጽናት እንሩጥ።” — ዕብራውያን 12፥1 (አዲሱ መ.ት)። በእርጥ እንዲህ ስል የኃጢአትን ፈታን እያቀለልኩ አይደለም። ነገር ግን በዚህ ሁሉ ውስጥ የሚረዳን የእግዚአብሔር ጸጋ አለ። እግዚአብሔር እምነታችንን ይጨምር። “ሙሴ ካደገ በኋላ፣ የፈርዖን የልጅ ልጅ መባልን በእምነት እምቢ አለ።” — ዕብራውያን 11፥24 (አዲሱ መ.ት) Via- Natty Alex

ከፖርኖግራፊ እና Masturbation ሱስ መውጫ መንገዶች “ይህ ሱስ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ እኔንም በእጅጉ ያጠቃኝ ነበር፡፡ ይህን ደግሞ ከእኔ ውጭ ማንም አያውቅም፡፡ ከዚህ ወጥመድ ለመውጣት ብዙ ታግያለው፡፡ ዛሬ በቃ ከዚህ በኋላ አጠገቡጋ አልደርስም እልና ነገ ገና ሳይነጋ እንደገና ሳፈጥ ራሴን አገኛለሁ፡፡ እንደዚህ እያልኩ ብዙ ታገልኩ አልቻልኩም፡፡ ነገር ግን አንድ ቀን በምማርበት ካምፓስ ፌሎሺፕ መሪዎች ጉባኤ ላይ ከዚህ ሃሳብ ጋር ተያይዞ አጭር ውይይትና የእርስ በርስ ፀሎት ተደረገ እኔም ችግሬን ተናገርኩ በዛው ተፀለየልኝ፡፡ ጌታም ነፃ አወጣኝ እኔም ደግሜ ላለመመለስ በራሴ አቋም መያዝ ጀመርኩ ለእንደዚህ አይነት ሃሳቦች ከሚጋብዙኝ ነገሮች ሁሉ መራቅ ጀመርኩ፡፡ እስካሁንም እራሴን ገዝቼ ተቆጥቤም አለሁ፡፡ ወደፊትም ጌታ ይረዳኛል ብዬ አምናለሁ፡፡”- ናርዶስ ••• በዚህ ሱስም ውስጥ ያሉ ክርስቲያኖችም ከዚህ አንፃር በቤተ ክርስትያን ካለው መገፋት እና ኃፍረት የተነሳ መፍትሄን ከመፈለግ ያፈገፍጋሉ። ይህም ግለሰብ በቤተክርስትያን አገልግሎት ወይም መሪነት ቦታ ካለ ነገሮችን የበለጠ የተወሳሰቡ ይሆናሉ። በኋላ እግዚአብሄር ፍርድ ፊት ከመቅረብ ዛሬ ላይ በሰው ፍርድ ውስጥ ማለፉ የተሻለ ነው። ••• በጌታ ፊት ቀርበው በነጋታው ያንን ነገር እያደረጉ ይገኛሉ፡፡ በዚህ ተደጋጋሚ አሰልቺ አካሄድ መጨረሻ ላይ ተስፋ ቆርጠው ለማቆም የሚያደርጉትን ጥረት እርግፍ አድርገው ይተዉታል፡፡ ከፖርኖግራፊ ሱስ ለመውጣት የምትፈልጉ ወገኖች ከዚህ ቀጥሎ የቀረቡትን ተግባራዊ ነጥቦች ብትከተሉ መልካም ነው፡፡ ወረቀትና እስኪብርቶ ይዛቹ ለተቀመጡት ጥያቄውች በጽሁፍ መልስ እየሰጣቹ እለፉ። 1. እግዚአብሔር እንደሚወደን አስበን ንሰሐ እንግባ ••• በዚህ ሱስ ውስጥ የገቡ ሰዎች እግዚአብሔር እንደሚጠላቸውና እንደሚጸየፋቸው ያስባሉ።እንዲህ አይነቱ ሃሳብ ሰዎችን የሱሱ ባሪያ አድርጎ ለማኖር ሰይጣን ይጠቀምበታል።እውነታው ግን እንደዚህ አይደለም።በእናንተና በሐጥያታቹ መካከል ልዩነት አለ። እግዚአብሔር ሐጥያትን ይጠላል። ሐጥያተኛን ግን ይወዳል። እናት የልጅዋ ልብስ ቢቆሽሽ ለልጅዋ ያላት ፍቅር እንደማይቀየር እግዚአብሔርም በለእናንተ ያለው ፍቅር አይቀየርም። ከዚህ ህይወት ወጥታቹ ወደ እርሱ ለመምጣት ብትወስኑ እጆቹን ዘርግቶ ይቀበላቹሃል። በቀራንዮ ላይ የፈሰሰው የኢየሱስ ደም ከሐጥያታቹ ሁሉ እንደሚያነጻቹ አምናቹ በእግዚአብሔር ፊት ንሰሐ ግቡ። ”የልጁም የኢየሱስ ክርስቶስ ደም ከኃጢአት ሁሉ ያነጻናል።”1ዮሐ 1፡7 ••• የኢየሱስ ክርስቶስ ደም ስለ አለም ሁሉ ስለፈሰሰ በእግዚአብሔር ፊት ይቅር የማይባል ሐጥያት የለም። 2. አምነን እንፀልይ ••• የሰው ልጅ በራሱ ጥረት ከሐጥያት መውጣት አይችልም።የእግዚአብሔር ጸጋ ሲያግዘው ግን የማይቻለውን ችሎ በቅድስና አሸብርቆ መኖር ይቻለዋል። እስከ ዛሬ በግል ጥረታቹ ከዚህ ሱስ መውጣት ስላልቻላቹ ተስፋ ቆርጣቹ ሊሆን ይችላል። ጸጋው ግን ጣልቃ ገብቶ አዲስ ህይወት ሊሰጣቹ ይችላል።ይህ ደግሞ የሚሆነው “እኔ ደካማ ስለሆንኩ የሚረዳኝ ጸጋ ይሰጠኝ”ብሎ በጸሎት እግዚአብሔርን በመለመን ይሆናል። መውጣት እንደሚቻል አለምማመን በራሱ ሰንሰለት ነው። የእግዚአብሔር ጸጋ ታሪክን እንደሚቀይር ከዚህ ህይወት መውጣት እንደሚቻል እመኑ። ምክንያቱም ከሐጥያት አስወጥቶ ቅዱስ የሚያደርግ ሰዎችን ሁሉ የሚያድን የእግዚአብሔር ጸጋ ተገልጦአልና፤ቲቶ 2፡11-13 3. ቀስቃሽ ነገሮችን እንለይ ••• ከዚህ በታች ያሉትን ጥያቄዎች ለራሳቹ መልሱ። ¤ በብዛት ፖርኖግራፊ የምታዩት ወይም ራስን በራስ ለማርካት ምትነሳሱት የትኛው ሰአት ላይ ነው? ¤ ለመጨረሻ ጊዜ ፖርኖግራፊ ያያችሁት ወይም Masturbate ያረጋቹት መቼ? ¤ ፖርኖግራፊ ከመመልከታቹ ወይም Masturbate ከማድረጋቹ በፊት ምን አይነት ስሜት(mood) ላይ ነበራቹ?  ቀስቃሽ ነገሮቻቹ ምንድን ናቸው? ¤ ስሜትን የሚያነሳሱ የሙዚቃ ክሊፖች ወይንስ ፊልሞች? አንዲት እህት ፖርኖግራፊ ይዘት ያላቸውን ነገሮች የምታገኘው ከፌስ ቡክ ላይ ነበር።ከዚህ ህይወት ሙሉ ለሙሉ መውጣቷን እስክታረጋግጥ ድረስ ፌስቡክ መጠቀሟን አቆመች። ከዚህ በፊት የሰበሰባችሁት ፊልምና ማንኛውም ነገር አሁኑኑ አጥፉ።ገፋፊ ነገሮችን ከእናንተ ለማራቅ ወስኑ። ኢንተርኔት መጠቀም ማቆም ካለባቹ አድርጉት።መጠቀም ካለባችሁም ሰዎች በተሰበሰቡበት ቦታ ተቀመጡ። ••• ወደ ፖርኖግራፊ የሚገፋፋቹ ጭንቀት ከሆነ ከጭንቀት መውጫ ሌሎች መንገዶችን ፍጠሩ። 4. እንታገል ••• ከዚህ ሱስ መውጣት ሂደት ነው። ለማቆም ከወሰናቹ በኋላ እንኳን ልትቸገሩና እስከ ዛሬ ያያችሁት ፊታቹ ላይ እየመጣ ልትጨነቁ ትችላላቹ። ይሄ ማለት ከዚህ ህይወት አልተላቀቃችሁም ማለት አይደለም። ቡና ለረጅም ጊዜ ጠዋት መጠጣት የለመደ ሰው ሊያዛጋው እንደሚችል ማለት ነው። አዕምሮአችን ወደ ቀደመው ቦታ እስኪመለስ ከማንኛውም ሱስ ስንወጣ የምናልፍበት ጤናማ ሂደት ነው። ዋናው በጦርነቱ ተሸንፎ እጅ አለመስጠት ነው። ጸንታቹ በታገላቹና የሚፍልገውን እስከነሳችሁት ድረስ ሱሱ በእናንተ ላይ ያለውን አቅም ያጣል።ከመገባችሁት ግን ያድግና ይውጣቹሃል። 5. ስሜቶቻችንን እንቆጣጠር ••• ፖርኖግራፊ ማየት ሶስት ደረጃዎች አሉት።እነሱም ስሜት/Emotion/ሐሳብ/Thought/-ተግባር/Action/ናቸው።vስሜት የምንለው የመጀመሪያው ደረጃ ጭንቀት፣ መከፋት ወይንም ፖርኖግራፊ የማየት ፍላጎት ሊሆን ይችላል። ከዛ ነው ፖርኖግራፊ የማየት ሐሳብ የሚመጣው። መጨረሻ ላይ ሁሉም ወደ ተግባር ይቀየራል።ስለዚህ ራሳችሁን መቆጣጠር የምትችሉት ገና ስሜት ሲሰማቹ ነው። ••• አንድ ወንድሜ እንዲህ አይነት ስሜት ሲሰማው ስፖርት እንደሚሰራ አጫውቶኛል።ይህ ስሜት ሲሰማቹ ምን ብታደርጉ ጥሩ ነው? 3 ነግሮችን ጻፉና የሚስማማችሁን ነገር አድርጉ። 6. ብቸኝነትን እናስወግድ ••• ለረጅም ሰአት ብቻችሁን ላለመሆንና ጊዜያችሁን ከቤተሰብና ከወዳጆቻችሁ ጋር ለማሳለፍ ሞክሩ። በተቻለ መጠን ቀናችሁን በተሻለና ትርጉም ሊሰጥ በሚችል ነገር ላይ አውሉት። እንደ ስፖርት መስራት መጽሐፍት ማንበብ ወደ ቤተ ክርስቲያን መሄድ ያሉ አዳዲስ ልምዶችን አዳብሩ። እስኪ ከዛሬ ጀምሮ ልታዳብሩት የምትችሉት 5 ልምምዶችን ጻፉ። 7. በአዕምሯችን እንለማመድ ••• ተግባራችን የሐሳባችን ውጤት ነው። እስኪ አይናችሁን ጨፍኑና ፖርኖግራፊ የማየት ስሜት ሲሰማቹና እምቢ ብላቹ ተቃውማቹ በተቀራኒው መልካም ነገር ስታደርጉ በአዕምሯችሁ ስላቹ ይሄን በተደጋጋሚ ተለማመዱ። 8. ተስፍ አንቁረጥ ••• ከዚህ ህይወት ለመውጣት በምታደርጉት ጥረት ውስጥ መውደቅና መነሳት ሊያጋጥማቹ ይችላል። ተስፋ ሳትቆርጡ ከስህተታቹ ተምራቹ እንደ አዲስ በብሩህ ተስፋ ነገን አሻግራቹ ተመልክቱ። 9. ግልጽ እንሁን ••• ብዙ ሰው በጉዳዩ ላይ ማውራት ስለሚያሳፍረው እርዳታም ለማግኘት ይቸገራል።ከዚህ ህይወት ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለመውጣት ከፈለጋቹ ሊረዳቹ ለሚችል ለአንድ ሰው በግልጽ ችግራችሁን መናገር ይኖርባቹሃል።

አዲስ ወደ ዩኒቨርሲቲ የምትቀላቀሉ ተማሪዎች ስለ ምትገቡበት ዩኒቨርሲቲ እና ስለ ተማሪዎች ፌሎሺፕ መረጃ ለማግኘት ከስር ያለውን ማስፈንጠርያ በመጠቀም የEvaSU ቴሌግራም ቻናል ላይ ማግኘት ትችላላችሁ። https://t.me/EvaSUE58

"ባል ለሚስቱ የሚገባትን ያድርግላት፥ እንደዚሁም ደግሞ ሚስቲቱ ለባልዋ። ሚስት በገዛ ሥጋዋ ላይ ሥልጣን የላትም፥ ሥልጣን ለባልዋ ነው እንጂ፤ እንዲሁም ደግሞ ባል በገዛ ሥጋው ላይ ሥልጣን የለውም፥ ሥልጣን ለሚስቱ ነው እንጂ። "...... 1ኛ ቆሮ 7:3-4 "አዲስ ሚስትም ያገባ ሰው ወደ ጦርነት አይሂድ፥ ነገርም አይጫኑበት፤ ነገር ግን አንድ ዓመት በቤቱ በፈቃዱ ይቀመጥ፥ የወሰዳትንም ሚስቱን ደስ ያሰኛት።" (ኦሪት ዘዳግም 24:5) አያችሁ የግብረ ስጋ ግኑኝነት እርካታ ባል ለሚስቱ ሚስትም ለባሏ የምትሰጠው እንጂ ሰው ከሌላ ቦታ ከራሱም ቢሆን ሊያገኘው የሚገባ እርካታ አይደለም፡፡ የግብረ ስጋ ግኑኝነት እርካታ በትዳር ውስጥ ባለ መኝታ ብቻ የሚገኝ ከእግዚአብሔር የተሰጠ ስጦታ ነው፡ ስለዚህ ባልና ሚስት በአንድነት ሲፀልዩ " እግዚአብሄር ሆይ ስለሰጠኸን ድንቅ ስጦታ እናመሠግንሃለን" ማለት አለባቸው፡፡ •○• ከዚህ ውጪ ያለ የፆታዊ ግንኙነት እርካታ በሙሉ ሀጢያት ነው፡፡ □ ራስን ማርካት masturbation ይባላል፡፡ □ ከትዳር ውጪ የሚደረግ አብሮ መተኛት ማመንዘር ይባላል፡ □ ሁለት ያላገቡ ወይም ያልተጋቡ ጥንዶች አብረው ቢተኙ ግልሙትና ይባላል፡፡ ሌሎችም አሉ፡፡ ••• በእነዚህ ነገሮች እግዚአብሄር ምንም ቦታ የለውም፡፡ ይልቁንም በዚህ ነገር ውስጥ ያለው ዲያቢሎስና የራሳችን የሀጢያት ተፈጥሮ ነው፡፡ ስለዚህ በነዚህ ነገሮች ሁሉ ራሳችንን መግዘት አለብን፡፡ " ትዕግሥተኛ ሰው ከኃያል ሰው ይሻላል፥ በመንፈሱም ላይ የሚገዛ ከተማ ከሚወስዱ ይበልጣል። " (መጽሐፈ ምሳሌ 16:32) ••• ይሄ ማለት ከላይ በተነሱት ጉዳዮች ላይ ንፁህ መሆን የቻለ ሰው መልካም ባል /ሚስት ፣ መልካም አባት /እናት እንዲሁም በመንፈሳዊ ነገር ያደገ ይሆናል፡፡ የምንኖርበት ማህበረሰብና ዘመን በነዚህ ጉዳዮች ንፁህ እንድንሆን አይረዳንም፡፡ ነገርግን መፅሐፍ ቅዱስ ሲናገር "በዚህ ሁሉ ግን በወደደን በእርሱ ከአሸናፊዎች እንበልጣለን።" (ወደ ሮሜ ሰዎች 8:37) ይላል፡፡

ለ. ልቅ የሆኑ የወሲብ ፊልሞችና ምስሎች - PORNOGRAPHY ••• በቅርቡ በወጣው ጥናት መግለጫ መሠረት ሰክስ (Sex) ብለው ከመጠይቁ ወይም (search) ከሚያረጉ ሀገራት መካከል ኢትዮጲያ አምስተኛዋ ናት፡፡ እንግድህ ከዚህ መረጃ ራሱ በመነሳት ምን ያህል ኢትዮጲያ ውስጥ እሄ ጉዳይ አሳሳቢ እንደሆነ መገመት ቀላል ነው፡፡ Pornography (ልቅ የሆኑ የወሲብ ፊልሞች) ከየትኛውም ሱስ የከፋ፣ከየትኛው አደንዝዥ ዕፅ ፣ለምሳሌ ከኮኬይን(cocaine) ይልቅ ሱስ የመሆን እድል አለው ፣ይህም የሚሆነው ፊልሞቹን በምናይበት ወቅት አይምሮዋችን ኢንዶርፊን(Endorphin) የተባለውን ሆርሞን ስለሚለቅ ከምናየው ነገር ጋር በሱስ እንደሚያጠብቀን እንሆናለን ማለት ነው ፡፡ ••• ትክክል ነው ፣ የወሲብ ቀስቃሽ ፊልሞችን ማየት አንዱ ችግር ይህ ነው ፣ ፊልሞቹ እጅጉኑ ሱስ መሆን ደረጃ ላይ ሲደርስ ለሴት ልጅ ክብር አለመስጠት እና እጅግ የወረዱ የስሜት መወጫ አድርጎ በማሰብ ፣ ደካማ በሆኑ ህጻናት እና የአይምሮ ህሙማን በሆኑ ሰዎች ላይም ጥቃት ለማድረስ ይዳርጋል፡፡ ማንኛውም ክርስቲያን እግዚአብሄር ኃጢያትን ጨምሮ ማናቸውንም ነገር ማሸነፍ እንደሚችል፤ ሁሉን ቻይ እንደሆነ እና ክርስቶስም ማናቸውንም ፈተና ልንቋቋም የምንችልበት ፀጋ እንደሰጠን ቢያምንም በፖርኖግራፊ ሱስ እየታገለ ያለ ክርስቲያን ግን ይህን እውነት መጠራጠር ይጀምራል። የፖርኖግራፊ (Pornography) መዘዞች ••• ፖርኖግራፊ (Pornography) መመልከት የሚያስከትለው እጅግ በጣም ብዙ መዘዞች አሉት። ከፖርኖግራፊ መዘዞች ዋነኛውና አሳሳቢው ራስን በራስ ማርካት ወይም Masturbation ወደሚባለው ልምምድ በተለይም እኛ ወጣቶችን መጋበዙ ነው፤ ሌሎቹን ደግሞ ከስር መመልከት እንችላለን፡፡ ••• በአጠቃላይ መንፈሳዊ፣ ስነ-ልቦናዊና ማህበራዊ ጉዳቶች ያስከትላል፡፡ እስኪ የተወሰኑትን በዝርዝር እንመልከት። ከእግዚአብሔር ይለያል በክርስቶስ የተጠራነው ንፁህ እና ቅዱሳን እንድንሆን እንደመሆኑ በድብቅ የምንሰራቸው ማናቸውም ኃጢያቶች በመንፈሳዊ ሕይወታችን እንድንደክም ያደርጉናል። በፖርኖግራፊ ሱስ ላለ ሰው መፀለይ፤ ቃሉን ማንበብ እና ከሌሎች ክርስትያኖች ጋር ህብረት ማድረግ ከባድ ይሆናል። ••• በዚህ ሱስ ከተጠቁ ወገኖቼ በተደጋጋሚ ከሚሰሙት ድምጾች ዋነኛው፤ “መጸለይ አልቻልኩም፤ ቤተ ክርስቲያን መሄድ ከበደኝ፤ ምክንያቱም ፊቴ ላይ የሚመጣው የተመለከትኩት ፖርኖግራፊ ነው” የሚል ነው። ሀሳብ ከሌላው ሰው የተደበቀ ስለሆነ ብዙ ትኩረት ባይሰጠውም ተጨባጭ ሀጢያት ከመሆን አያግደውም። ••• ፖርኖግራፊ መመልከት ኃጢያት መሆኑ ግልፅ ነው። ጌታችን ኢየሱስ “ወደ ሴት ያየ ሁሉ የተመኛትም ያን ጊዜ በልቡ ከእርስዋ ጋር አመንዝሮአል” (ማቴዎስ 5:28) እንዳለ እናስታውስ። ••• እኔ ፖርኖግራፊ አይቼ በፍጹም አልመኝም የሚል ይኖር ይሆን? የስጋን ፈቃድ እየፈፀሙ ክርስቶስን ለማምለክ መሞከር ትርፉ ብቸኝነት፤ ተስፋ መቁረጥ እና ውድቀት ነው። ፖርኖግራፊ መንፈሳዊ ሕይወትን የሚያኮላሽ ነው። ሰው መንፈሳዊነቱን ካጣ ደግሞ ምንም ነገር ቢያገኝ አይረካም። ፖርኖግራፊ ዋና ነገሮቻችንን ያሳጣናል። ድብርት/ጭንቅት ያመጣል ፖርኖግራፊ ውስጥ የገባ ሰው ያለበት ሕይወት ትክክል እንዳልሆነ ያውቃል። ስለዚህ ከባድ የሆነ ጭንቀት ይሰማዋል። ብዙ ሰዎች በዚህ ምክንያት ሀፍረት ስለሚሰማቸው በራስ መተማመናቸውን ያጣሉ። ስለዚህ በከባድ የድብርት ስሜት ውስጥ ሆነው ራሳቸውን ከሰው ያገላሉ። Masturbation (ራስን በራስ ማርካት) ••• መጀመሪያ masturbation የሚለውን ቃል እናብራራ ቀጥተኛ የአማርኛ አቻ ፍቺ እንዳለው ባናውቅም "ራስን ማስደሰት" ወይም "ራስን ማርካት" የሚል ትርጓሜ ልንሰጠው እንችላለን፡፡ በአብዛኛው ክርስቲያናዊም ሆነ ከክርስቲያናዊ ባልሆኑ የጥናት ስራወዎች ከ95-97% የሚሆኑ ታዳጊዎች የመራቢያ አካላቸውን የመነካካትና በዛም ውስጥ ጥሩ ስሜትን የሚያገኙበት ደረጃ ውስጥ እንደሚያልፉ ለማወቅ ተችሏል፡፡ ••• ይህ ልምምድ ከ 9-12 ባለ ዕድሜ ክልል ውስጥ ሊከሰት ይችላል፡፡ ይህ ክፉ ሀሳብ የሌለበት ራስን የመነካካትና ጥሩ ስሜትን መፈለግ ቅጣት ይገባዋል ብዬ አላስብም፡፡ ይልቁንም በዚህ ሰዓት ይሄ ልጅ የሚያስፈልገው አጠገቡ በመሆን ፆታዊ ጉዳዮችን ለዕድሜው በሚመጥን መልኩ የሚያስተምረው ፥ እግዚአብሄር ለምን ሰውነታችንን በዚህ መልኩ እንደፈጠረው እንዴትስ ይህን ሰውነቱን ለእግዚአብሔርም ለራሱም አእምሮ በሚመች መልኩ መያዝ እንዳለበት የሚነግረው ወላጅ ነው፡፡ “እንግዲህ፥ ወንድሞች ሆይ፥ ሰውነታችሁን እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝና ሕያው ቅዱስም መሥዋዕት አድርጋችሁ ታቀርቡ ዘንድ በእግዚአብሔር ርኅራኄ እለምናችኋለሁ፥ እርሱም ለአእምሮ የሚመች አገልግሎታችሁ ነው። (ሮሜ 12 ፥ 1-3) ያለበለዚያ ግን ይሄ ልጅ ራሱን በመነካካት ጥሩ ስሜትን ከማግኘት ያልፍና ወደ Masturbation ይሻገራል፡፡ ይሄንም በተደጋጋሚም ማድረግ ይጀምራል፡፡ ይህ ልምምድ ከጊዜ በኃላ ሱስ ይሆናል፡ በቀን ውስጥ ከ 2-14 ጊዜ ሊደጋግመው ይችላል፡፡ ይህ ሁኔታ በሂደት የሚያዩትን ወይም የተመኙትን ነገር በተግባር ለማውጣት ማለትም ግብረስጋ ግንኙነት ለመፈፀም መንገዶችን ወደ መፈለግ ይደርሳል፡፡ ይሄ ልምምድ ሁልጊዜም ፀፀት ፣ ሀዘን ፣ አሰልቺነት ፣ ጭንቀት ፣ ፍራቻና ራስን የማጥፋት ሀሳቦችን ከኃላው ያስከትላል፡፡ እግዚአብሄር ሁላችንንም ሲፈጥረን ፆታዊ ግንኙነትን የሚፈልግ ደግሞም ያንን ፍላጎት የሚቀሰቅስ ነገር ሲያጋጥም ምላሽ የሚሰጥ ሰውነትን ፈጥሮልናል፡፡ ሆኖም እግዚአብሄር ስለ ፆታዊ ግንኙነት በራሳችን ፈልገን እንድናገኝ ዝም ብሎ አልተወንም፡፡ መመሪያ እርሱም መፅሀፍቅዱስ ነው፡፡ ይህ መመሪያ እንደፈለጉ በስሜታቸው ከሚኖሩት እንስሳት ይለየናል ፡፡ የግብረስጋ ግንኙነት ፤ የእግዚአብሔር ቃል እንደሚለው ፤ በአንዲት ሴት እና በአንድ ወንድ መሀል በሚደረግ የአንድነት ጋብቻ ውስጥ ብቻ ሊኖር የሚገባ ነው፡፡ ይህም ማለት ሚስት ለባሏ የምትሰጠው ባልም ለሚስቱ የሚሰጣት ለጋራ እርካታ የሚሆን መልካም ተግባር ነው፡፡ ይህ እግዚአብሄር ሁላችንም ለትዳር አጋሮቻችን ብቻ እንሰጠው ዘንድ የሰጠን ስጦታ ነው፡፡ በመሆኑም በትዳር ውስጥ ያለ የግብረ ስጋ ግኑኝነት ደስታ ሰላምና ፍቅር እንጂ በምንም መልኩ ጉዳት አይፈጥርም፡፡ ልክ እንደ masturbation ፀፀት ፣ ሀዘን ፣ አሰልቺነት ፣ ጭንቀት ፣ ፍራቻና ራስን የማጥፋት ሀሳቦችን ከኃላው አያሰከትልም፡፡ •○• እስከዛሬ ድረስ "እግዚአብሄር በ masturbation እየባረከኝ ነው" የሚል አንድም ሰው አላጋጠመኝም፡፡ ምክንያቱም ከእግዚአብሔር መንፈስ ዳግም የተወለደ ማንም ሰው ከ masturbation ጋር ተከትለው የሚመጡት እንደ ጭንቀት ፣ ፍርሃትና ብቸኝነት የመሳሰሉት ነገሮች ከእግዚአብሔር ጋር ያለውን ግንኙነት መልካም አያደርጉለትም፡፡ ••• በመፅሐፍ ቅደስ ውስጥ የግብረ ስጋ ግኑኝነት ራስን ማርካት እንደሆነ ተደረጎ በየትኛውም ቦታ አልተጠቀሰም፡፡

የ ወ ጣ ቶ ች ጠ ላ ት (ዓ ይ ን) "ዓይንህ ብታሰናክልህ አውጥተህ ከአንተ ጣላት፤ ሁለት ዓይን ኖሮህ ወደ ገሃነመ እሳት ከምትጣል ይልቅ አንዲት ዓይን ኖራህ ወደ ሕይወት መግባት ይሻልሃል።" ማቴ 18: 9 √ አይንህን አውጥተህ ጣላት ማለት በሆነ ስለታማ ነገር አውጣት ማለት ነው? አይደለም ፡፡ ጌታ ኢየሱስ በዚህ ክፍል እየተናገረ ያለው ነገር እንዲህ ነው፡ አይንህ መልካም ያልሆነውን ነገር አይታ ከምታሰናክልህ ጭራሽ ማየት ባትችል ይሻልሃል !! ይህም ማለት በሌላ አነጋገር አይንህን የሥጋ ፈቃድ ለማድረግ የሚገፋፋህን ነገር ለማየት ከምትጠቀምበት ይልቅ ማየት የተሳነው ሰው ብትሆን ይሻልሃል ማለት ነው፡፡ እነዚህ የስጋ ፈቃድን ለማድረግ ሊገፋፉ የሚችሉ ነገሮች ምን ምን ሊሆኑ ይችላሉ ከታች በደንብ እናያቸዋለን፡፡ ስለዚህ በአይንህ ስለምታየው ነገር በጣም መጠንቀቅ አለብህ፡፡ √ ምን አይነት መፅሃፍ ወይም መፅሄት ነው የምታነበው ? √ ኢንተርኔት ስትጠቀም አላስፈላጊ ምስሎች ወይም ጽሁፎች ይመጡብሃል ? √ የምታያቸው ቪዲዮ ወይም ፊልሞች ምን አይነት ናቸው ? ••• መፅሃፍ ቅዱስ ስለ ዓይን እንዲህ ይላል "የሰውነት መብራት ዓይን ናት። ዓይንህ እንግዲህ ጤናማ ብትሆን፥ ሰውነትህ ሁሉ ብሩህ ይሆናል፤" (ማቴ 6: 22) ፡፡ አይንህን እርኩሰት ባለማየት ጤናማ አድርጋት የዚያኔ ለመላ ሰውነትህ ከዚያም አልፎ ተርፎ ለነፍስህ ጤንነትን ታድላለህ፡፡ ወይም በዚህ ክፍል እነደሚናገረው ብርሃን ይሆናል፡፡ ••• መፅሀፍ ቅዱስ ሲናገር... “ዓለምን ወይም በዓለም ያሉትን አትውደዱ፤ በዓለም ያለው ሁሉ እርሱም የሥጋ ምኞትና የዓይን አምሮት ስለ ገንዘብም መመካት ከዓለም ስለ ሆነ እንጂ ከአባት ስላልሆነ፥ ማንም ዓለምን ቢወድ የአባት ፍቅር በእርሱ ውስጥ የለም።”(1 ዮሐንስ 2 ፡ 15-16፤) "የአይን አምሮት" ብዙ የመዝናኛ እና የክፋት ኢንዱስትሪ ዋነኛው የገቢ ምንጭ የሚያገኙት በዚህ ነገር ነው፡፡ በዚህ መንገድ ለአንድ ክርስቲያን ወገን ይቀርባሉ "እስኪ እየው "በማለት እንዲያይ ያደርጉታል ፡፡ √ ጦርነቱ ያተኮረው በነብስ ላይ ሲሆን አይን ደግሞ ተግባሯን በመቀጠል ያለምንም ጥርጣሬ እና ያለምንም ገደብ በትኩረት መመልከትን ትጀምራለች፡፡ መፅሀፍ ቅዱስ ሲናገር ... “ሲኦልና ጥፋት እንዳይጠግቡ፥ እንዲሁ የሰው ዓይን አይጠግብም።” (ምሳሌ 27 ፤ 20) ••• አይናችን በተፈጥሮ ለአደጋም ሆነ ለተለያዩ ነገሮች እጅግ በጣም ቅርብ የሰውነታችን ክፍል ነች፡፡ በመጠኑ አነስ ያለ ንፋስ ቢነሳ ቶሎ ብለን ጆሮአችንን አንይዝም አይናችንን እንጨፍናለን እንጂ፡፡ ዘመኑ ደግሞ የዓይን ነው፡ ማለትም አብዛኛው የዘመናዊነት መጠቀሚያ ነገሮች የሚመጡት በዓይን በኩል ነው፡፡ ከነዚህም መካከል ዋነኞቹ ፡- ሀ. ፊልም ለ. ልቅ የሆኑ የወሲብ ፊልሞችና ምስሎች (Pornography) ሐ. ማህበራዊ ድረ-ገፆች (social media) ናቸው፡፡ ሀ. ፊልም ••• ፊልም አንዱና ዋነኛው የዓይን ወጥመድ ነው፡፡ የአንዳንድ ፊልሞች ዓላማቸውን ለመናገር ባንደፍርም ግን በውስጣቸው ስለያዙት ይዘት ግን ብናወራ ስለያዝነው ርዕስ ይበልጥ ግልፅ ይሆንልናል፡፡ ፊልም የሰውን ስሜት የመቆጣጠር ትንሽ የማይባል ጉልበት አለው፡፡ ለዚህም ነው ከኬጂ ህፃናት ጀምሮ እስከ ጎልማሶች ያለን ሰዎች በዚህ ሱስ ተጠምደን መላቀቅ ያቃተን፡፡ የፊልም ጥቅሙን ለመናገር ቢከብደንም ስለጉዳቱ ግን ብዙ ማለት እንችላለን ፡፡ ••• በርግጥ ጠቃሚ ፊልሞች እነዳሉ መርሳት የለብንም፡፡ ለምሳሌ መንፈሳዊ ፊልሞች፣ ትምህርታዊ ፊልሞች፡፡ በሌላ በኩል ግን ዓለማዊ ፊልሞችን በተለይም በአሁኑ ዘመን የሚለቀቁ ፊልሞችን ብንመለከት ከላያቸው ሲታዩ ምንም የማይመስሉ ነገር ግን በውስጣቸው እጅግ አደገኛ ወጥመድን የሚያጠምዱ መሆናቸው የታወቀ ነው፡፡ በተለይ ክርስቲያኖችን ያነጣጠሩ መሆናቸው ደግሞ አሳሳቢ እየሆነ መቷል፡፡ አዎ ! ፊልሞችን ማየት እናቁም ማለታችን አይደለም ነገር ግን ፊልም የምንመለከት ሰዎች ከታች የተዘረዘሩትን ጥያቄዎች ሁሌም በዓዕምሯችን ልናሰላስለው ይገባል፡፡ √ እያየነው ያለው ፊልም ምን ዓይነት ነው? √ ከጀርባው ምን ሚስጥር አለው? √ ለእኔ በምን መልኩ ሊጠቅመኝ ይችላል? √ ከክርስትና አንፃር ምን ችግር ያመጣል? √በቀን ለቀን ውሎዬ ላይ ምን ተፅኖ አለው ? √በባህሪዬ ላይ ለውጥ ሊያመጣ ይችላል ? ••• ፊልም ለትዳር መፋታትም እንደ አንዱ ምክንያት ሊወሰድ ይችላል፡፡ ፊልም ጊዜ ይበላል ስለዚህ ከዕለት ስራችን ያስተጓግለናል፡፡ ተማሪዎችን ከማቦዘኑም ያለፈ ለቤተሰብ ጊዜ እንዳንሰጥ ያደርገናል፡፡ ፊልም የባህሪይ ለውጥ ያመጣል፡፡ አመጸኞች ያደርገናል፡፡ ፊልም አመለካከታችንን ይለውጣል፡፡ ኑሮ ዜይቤያችን ንግግራችን አኳኋናችን አመለካከታችን ፊልም ውስጥ ካየነው አክተር እና የፊልሙ ደራሲ በፊልሙ ካሰፈረው ሃሳብ ጋረ የተመሳሰለ ይሆናል፡፡ ታዲያ ይህን ሁሉ ተፅኖ ካመጣብን ፊልምን አዘውትረን እንይ ወይ??? መልሱን ለናንተው፡፡

ዩኒቨርሲቲ እና ኮሌጅ ከመቀላቀላችሁ በፊት ማወቅ ያለባችሁ... [ ሰላም ወንድማችሁ ነኝ። እጅግ ተጠፋፍተናል አውቃለው። ጌታ ቢፈቅድ በቅርቡ በአዲስ ነገር በሰፊው እንገናኛለን፡ እስከዛ ግን አዲስ ወደ ዩኒቨርሲቲ እና የግል ኮሌጆች ከምትገቡት ጋር እንዳንተላለፍ ከዚህ በፊት ከተዘጋጀ መልዕክት አጠር እያደረኩ አካፍላችኋለው።] እነዚህን የትምህርት ተቋማት እንደ ክርስቲያን ስንቀላቀል ማድረግ ያለብን... በተጠራንበት መጠራት መመላለስ “እንግዲህ በጌታ እስር የሆንሁ እኔ በተጠራችሁበት መጠራታችሁ እንደሚገባ ትመላለሱ ዘንድ እለምናችኋለሁ፤ (ኤፌ.4፡1) ••• በተጠራንበት መጠራት መመላለስ የሚለው ሃሳብ በርካታ ነገሮችን ይይዛል: ከታች ለመግለጽ የተሞከረው በጣም በጥቂቱ ነው እነዚህም :— በብርሃን መመላለስ ፣ መልካሙን ሥራ በመስራት መመላለስ ፣ ከአህዛብ ጋር ባለመተባበር መመላለስ ...ብዙ ብዙ ማለት ይቻላል፡፡ በብርሃን መመላለስ “እናንተ የዓለም ብርሃን ናችሁ።” ማቴ 5:14 ••• ብርሃን የተደበቀውን ይገልጣል ___ክፉ የሚያደርግ ሁሉ ብርሃንን ይጠላልና፥ ሥራውም እንዳይገለጥ ወደ ብርሃን አይመጣም፤ (ዮሐ 3፡20)፡፡ ብርሃን ከጨለማ ጋር ትብብር የለውም ፡፡ ብርሃን ጨለማን ያሸንፋል እንጂ ለጨለማ እጅ አይሰጥም ፡፡ ብርሃን ከጨለማ ጋር በአንድ ቦታ በፍጹም ሊቀመጡ አይችሉም ፡፡ ሁሌም ብርሃን አሸናፊ ነው፡፡ በብርሃን የሚኖር ሰው ወይም ብርሃን በእጁ ያለው ሰው ወይም እራሱ ብርሃን የሆነ ሰው በሄደበት ሁሉ መብራቱን ያበራል እንጂ ሊደብቀው አይችልም፡፡ መብራቱን ስለፈለገ ሳይሆን የሚያበራው እራሱ ብርሃን ስለሆነ ሊደብቀው ስለማይችልም ጭምር ነው ፡፡ በተራራ ላይ ያለች ከተማ ልትሰወር አይቻላትም።(ማቴ 5: 14 ) መልካሙን ሥራ በመስራት መመላለስ “እኛ ፍጥረቱ ነንና፤ እንመላለስበት ዘንድ እግዚአብሔር አስቀድሞ ያዘጋጀውን መልካሙን ሥራ ለማድረግ በክርስቶስ ኢየሱስ ተፈጠርን።”(ኤፌ 2 :10 ••• ሰው ስለ እኛ ያለው አመለካከት መልካም ብቻ እንዲሆን ማድረግ አለብን፡፡ “___በጌታ ፊት ብቻ ያይደለ ነገር ግን በሰው ፊት ደግሞ መልካም የሆነውን እናስባለንና።” (2 ቆሮ 8 ፡ 21)ይላልና፡፡ በእግዚአብሔር ፊት ሞገስን ያገኘ ሰው ሁሌም በሰው ፊት ሞገስን ያገኛል ማለት አይደለም ምክኒያቱም አንዳነድ ሰው ክፉ ነውና፡፡ ••• በሌላ በኩል ደግሞ በሰው ፊት ሞገስን ያገኘም ሁሉ በጌታም ፊት ሞገስን ያገኛል ማለት አይደለም፡ ኃጥአትን በማድረግ በሰው ፊት መክበር አለና፡፡ ከዚህ ሃሳብ ጋር ተያይዞ መናገር ምፈልገው ነገር ቢኖር ለእኛ ለክርስቲያኖች የሚሻለን ግን ሁሌም በጌታ ፊት ሞገስን ያገኘ በመልካም ስራ የተሞላ ኑሮ መኖር ነው፡፡ በሰው ፊት ከመክበር በጌታ ፊት ሆኖ እግሩ ስር መሆን እንኳ የተመረጠ ነውና፡፡ መልካሙ ሥራ ምንድነው ? √ በዋናነት ወንጌል ነው √ የእግዚአብሔር ፈቃድ ያለበት ፡ √ መጨረሻው በፍጹም ወደ ሃጢአት የማያመራ ነገር ሁሉ መልካም ሥራ ነው፡ √ ሌላውን የሚያንጽ እንጂ የማይጎዳ ነው (የጌታ ፈቃድ አለበት) ለምን በመልካም ሥራ መመላለስ አስፈለገ ? √ የተፈጠርነው ለመልካም ሥራ ብቻ ስለሆነ ___”እኛ ፍጥረቱ ነንና፤ እንመላለስበት ዘንድ እግዚአብሔር አስቀድሞ ያዘጋጀውን መልካሙን ሥራ ለማድረግ በክርስቶስ ኢየሱስ ተፈጠርን።”(ኤፌ 2 :10) √ በእኛ መልካም ሥራ እግዚአብሔር ሰለሚከብር ___ “ስለሚመለከቱት ስለ መልካም ሥራችሁ፥ ክፉ እንደምታደርጉ በዚያ እናንተን በሚያሙበት ነገር፥ በሚጎበኝበት ቀን እግዚአብሔርን ያከብሩት ዘንድ በአሕዛብ መካከል ኑሮአችሁ መልካም ይሁን።”( ጴጥ 2 : 12 ) “መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማያት ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ እንዲሁ በሰው ፊት ይብራ።” (ማቴ 5: 16) ከአህዛብ ጋር ባለመተባበር መመላለስ “ከማያምኑ ጋር በማይመች አካሄድ አትጠመዱ፤ ጽድቅ ከዓመፅ ጋር ምን ተካፋይነት አለውና ብርሃንም ከጨለማ ጋር ምን ኅብረት አለው፡”(2 ቆሮ 6 ፡ 14 ) ••• ይህን ሃሳብ ከመወያየታችን በፊት ስለ ህብረት ጥቂት ግንዛቤ ብንጨብጥ ሃሳቡን በይበልጥ ለመረዳት ያስችለናል፡፡ ህብረት ፡— •• ሁለትና ከዚያ በላይ አካላት የታቀፈ ቡድን ነው ••• በመተባበር ለአንድ ዓላማ የሚሯሯጥ ቡድን ነው ••• በርካታ የተለያዩ አመለካከቶች ተዋህደው ተቻችለው የሚቆዩበት ቦታ ነው ••• የሃሳብ መደጋገፍ አለበት ••• በህብረት ውስጥ የሌላውን አመለካከትና ህይወት መካፈል የግድ ነው ••• በህብረት ውስጥ ሌላው አዘውትሮ የሚጠቀመውን ነገር መልሶ መጠቀም የግድ ነው (ለምሳሌ ፡ — ንግግር፣ አለባበስ፣ የመሳሰሉት ) ••• መጽሐፍ ቅዱስ እንደ ክርስቲያን ከላይ ከተጠቀሱት ነጥቦች ከአህዛብ ጋር በአንዳቸውም ተካፋዮች እንዳንሆን ያስተምረናል፡፡ በአጭሩ እኛ ወጣቶች ከማያምኑ ጋር የጠበቀ ህብረት/ ጓደኝነት እንዳይኖረን እና ከህብረታቸው እንድንወጣ ይፈልጋል፡፡ “ከመካከላቸው ውጡና የተለያችሁ ሁኑ ርኵስንም አትንኩ ይላል፤ ሁሉንም የሚገዛ ጌታ።”(2 ቆሮ 6 ፡ 17) ከአህዛብ መለየት አስፈለገ ? ••• የእግዚአብሔር ትዕዛዝ ስለሆነ “...ፍሬም ከሌለው ከጨለማ ሥራ ጋር አትተባበሩ፥__ ”( ኤፌ 5 ፡ 11) √ ብርሃን ከጨለማ ጋር ህብረት ስለሌለው “ብርሃንም ከጨለማ ጋር ምን ኅብረት አለው” ( 2 ቆሮ 6 ፡ 14 ) √ የአህዛብን ህይወት ወደመጋራት እና ወደመለማመድ ሊወስደን ስለሚችል የአህዛብ ህይወት ምን ዓይነት ነው? “እነርሱ ባለማወቃቸው ጠንቅ በልባቸውም ደንዳንነት ጠንቅ ልቡናቸው ጨለመ፥ ከእግዚአብሔርም ሕይወት ራቁ፤ ደንዝዘውም በመመኘት ርኵሰትን ሁሉ ለማድረግ ራሳቸውን ወደ ሴሰኝነት አሳልፈው ሰጡ።” ( ኤፌ 4 ፡ 18 ) አህዛብ ፡ — √ ያለ ክርስቶስ ናቸው √ ያለ መንፈስ ቅዱስ ናቸው √ የስጋቸውንና የልቦናቸውን ፈቃድ የማድረግ ህይወት አላቸው “የሥጋችንንና የልቡናችንን ፈቃድ እያደረግን፥ በሥጋችን ምኞት በፊት እንኖር ነበርን እንደ ሌሎቹም ደግሞ ከፍጥረታችን የቁጣ ልጆች ነበርን።”(ኤፌ 2 ፡ 3) ••• ከአህዛብ ጋር ህብረት ባለማድረግ መመላለስ ማለት ወደ አህዛብ አለመቅረብ ማለት አይደለም ፡፡ ነገር ግን የአህዛብን የኑሮ ዘይቤ ወዲያ በመተው በክርስቲያኒያዊ የኑሮ ዘይቤ መመላለስ ማለት ነው ፡፡ እኛ ክርስቲያኖች ከአህዛብ የሚለየን ሃጢአት ባደረግን ጊዜ የሚወቅሰን ሃይል አለ እሱም መንፈስ ቅዱስ ይባላል፡፡ ይህ መንፈስ ድንገት ተሳስተን እራሳችንን በሃጢአት ልምምድ ውስጥ ብናገኝ ተጸጽተን በይቅርታ እንድንመለስ ያደርገናል፡፡ ይህ መንፈስ ከሌለው ሰው ጋር ገደቡን ያለፈ ግንኙነት ወይም ህብረት ማድረግ ደግሞ ለምን ያህል የከፋ ተጽኖ እንደሚዳርግ መገመት አያዳግትም፡፡