fa
Feedback
Dn Abel Kassahun Mekuria

Dn Abel Kassahun Mekuria

رفتن به کانال در Telegram

ይህ ኦርቶዶክሳዊ የሆኑ የተለያዩ ትምህርቶችን የሚያገኙበት በባለቤቱ የተከፈተ ቻነል ነው። ይወዳጁን ለፌስቡክ ገጽ https://www.facebook.com/AbelKassahunMekuria12?mibextid=ZbWKwL ለyoutube https://youtu.be/s6Cn-jMYjrk?si=Tw7lXr62xkGQtL9_ ለInstagram https://www.instagram.com/abelkassahunm?igsh=OW

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام Dn Abel Kassahun Mekuria

کانال Dn Abel Kassahun Mekuria (@dnabel) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 18 535 مشترک است و جایگاه 4 431 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 1 815 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 18 535 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 16 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -41 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 7 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 36.98% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 13.55% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 6 853 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 2 511 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 183 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
ይህ ኦርቶዶክሳዊ የሆኑ የተለያዩ ትምህርቶችን የሚያገኙበት በባለቤቱ የተከፈተ ቻነል ነው። ይወዳጁን ለፌስቡክ ገጽ https://www.facebook.com/AbelKassahunMekuria12?mibextid=ZbWKwL ለyoutube https://youtu.be/s6Cn-jMYjrk?si=Tw7lXr62xkGQtL9_ ለInstagram https://www.instagram.com/abelkassahunm?ig...

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 17 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کرده‌اند.

18 535
مشترکین
+724 ساعت
+217 روز
-4130 روز
آرشیو پست ها
ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን፣ በአማን ተንሥአ! ዛሬ የዕብራውያን መልእክት ሐተታ ትምህርት አይኖረንም። ቸር ያገናኘን።

"ወደ ገሊላ ይቀድማችኋል" ማቴ 28፥7 ጌታችን ሞትን ድል አድርጎ ከተነሣ በኋላ ለደቀ መዛሙርቱ ብዙ እና ጥቂት ሆነው ሳለ በተለያየ ጊዜ ራሱን ገልጦ አሳይቷቸዋል። አሁን ደግሞ አስቀድሞ በሴቶች በኩል "ወደ ገሊላ ይቀድማችኋል" ብሎ ያስነገረውን ትንቢት ሊፈጽም፣ ዓሣ ለማጥመድ ወደ ገሊላ ባሕር ለወረዱ ለጴጥሮስና ለስድስቱ ወንድሞቹ የተገለጠበትን ሦስተኛ ታሪክ ዮሐንስ ይጽፍልናል።(ዮሐ 21፥1) ቅዱስ ጴጥሮስ "ሰላም ለእናንተ ይሁን" የሚለውን የትንሣኤውን ጌታ ድምጽ ከሰማ ፣ የተጠራጠረው ቶማስ እጁን በጎኖቹ አግብቶ "ጌታዬ አምላኬ" ብሎ ሲያምን ከተመለከተ በኋላ "ዓሣ ላጠምድ እሄዳለሁ" ብሎ ሲናገር እናገኘዋለን።(ዮሐ 21፥3) ክርስቶስ ተላልፎ በተሰጠበት በሐሙስ ምሽት ከእሳት ዳር ተቀምጦ ያደረገውን ሊረሳውና ራሱን ይቅር ሊል ስላልቻለ፣ ጌታው ቀድሞ የሰጠውን የወንጌል መረብ ተወና የዓሣውን መረብ ጨብጦ ወደ ገሊላ ባሕር ሮጠ።(ማቴ 4፥19) በኃጢአት ምክንያት የተሰማው ኃፍረትና መሸማቀቅ ሐዋርያነቱን ትቶ በድሮ ማንነቱ ውስጥ ራሱን እንዲደብቅ አደረገው። የካደን ማን ለምስክርነት ይፈልገዋል በሚል ዓይነት ስሜት ለወንድሞቹ "ዓሣ ላጠምድ እሄዳለሁ" አላቸው። ደስ የሚለው ነገር ግን ይህን አስቀድሞ የሚያውቅ ይቅር ባይ አምላኩ ጴጥሮስን "በገሊላ ቀድሞት ነበር"። በበደሉ ተሸማቆ የተወውን ሐዋርያነት ሥልጣን በፍቅሩ መማለጃነት መልሶ ሊሰጠው፣ አይገባኝም ብሎ ያስቀመጠውን የወንጌል መረብ ዳግመኛ ሊያሲዘው በገሊላ ባሕር ዳር ቀደመው። እኛም አንድ ኃጢአት ይኖረናል። መርሳት ያልቻልነው፣ ንስሐ እንኳን ብንገባበት ራሳችንን ይቅር ለማለት የተቸገርንበት፣ "ከዚህ በኋላማ..." እያሰኘ የድሮ መረብ አስይዞ ወደ ገሊላ የሚመልስ አንድ በደል ይኖረናል። ነገር ግን ጌታ ለቅዱስ ጴጥሮስ እንዳደረገው ለእኛም እንዲሁ ያደርጋል። ከባሕሩ ዳር ይጠብቀናል፣ "ትወደኛለህ" ብሎ ይጠይቀናል፣ ከዚያ በማይለወጥ ፍቅሩ ወልውሎ ሰንግሎ አፍረን ወደ ሸሸነው መንፈሳዊነት ይመልሰናል። +++ ጌታችን በገሊላ ይቀድመናል! +++ ዲያቆን አቤል ካሳሁን ግንቦት 6/ 2015 ዓ.ም. አዲስ አበባ

ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን፣ በአማን ተንሥአ፤ ሰላም እንዴት አረፈዳችሁ፣ የዛሬው ክፍል ሰባት ትምህርታችን ከምሽቱ 3:00 ሰዓት ላይ ይጀምራል። በዛሬው ትምህርታችን ከምዕራፍ አምስት እስከ አሥር ያሉት
ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን፣ በአማን ተንሥአ፤ ሰላም እንዴት አረፈዳችሁ፣ የዛሬው ክፍል ሰባት ትምህርታችን ከምሽቱ 3:00 ሰዓት ላይ ይጀምራል። በዛሬው ትምህርታችን ከምዕራፍ አምስት እስከ አሥር ያሉትን ንባቦች እንድንረዳ የሚያደርገንን የሊቀ ካህናትነትን ትርጉም፣ የኦሪቱን የመሥዋዕቱን ጉድለት፣ የሐዲስ ኪዳኑን መሥዋዕት ፍጹምነት በስፋት የምናነሣ ይሆናል። እንደ ተለመደው ምዕራፍ ስድስትን አንብበን እንገናኝ። መገናኛችን: Telegram: https://t.me/Dnabel Tiktok: https://www.tiktok.com/@dnabelkassahun?_r=1&_t=ZS-94eT9fhoVaX የZoom አማራጭ: https://us06web.zoom.us/j/86200559976?pwd=oIBuOuJyqdjlNTbXs8SdoVirTUw67U.1

ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን፣ በአማን ተንሥአ፤ ሰላም እንዴት አረፈዳችሁ፣ የዛሬው ክፍል ሰባት ትምህርታችን ከምሽቱ 3:00 ሰዓት ላይ ይጀምራል። በዛሬው ትምህርታችን ከምዕራፍ አምስት እስከ አሥር ያሉት
ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን፣ በአማን ተንሥአ፤ ሰላም እንዴት አረፈዳችሁ፣ የዛሬው ክፍል ሰባት ትምህርታችን ከምሽቱ 3:00 ሰዓት ላይ ይጀምራል። በዛሬው ትምህርታችን ከምዕራፍ አምስት እስከ አሥር ያሉትን ንባቦች እንድንረዳ የሚያደርገንን የሊቀ ካህናትነትን ትርጉም፣ የኦሪቱን የመሥዋዕቱን ጉድለት፣ የሐዲስ ኪዳኑን መሥዋዕት ፍጹምነት በስፋት የምናነሣ ይሆናል። እንደ ተለመደው ምዕራፍ ስድስትን አንብበን እንገናኝ። መገናኛችን: Telegram: https://t.me/Dnabel Tiktok: https://www.tiktok.com/@dnabelkassahun?_r=1&_t=ZS-94eT9fhoVaX የZoom አማራጭ: https://us06web.zoom.us/j/86200559976?pwd=oIBuOuJyqdjlNTbXs8SdoVirTUw67U.1

+++ "በስሙ ጥራው" +++ ሰይጣን የሰው ልጆችን የክፋት እስረኛ ከሚያደርግበት ዘዴው አንዱ ኃጢአትን "ኃጢአት" ብለን እንዳንጠራት ማለሳለስ ነው። ከዚያ ይልቅ መልካም በሚመስልና ቢሰማም ብዙ በማይቆረቁር ስም እንድንጠራው ያደርገናል። ለምሳሌ በትዳር ሳይወሰኑ እንዲሁ ከአገኙት ጋር በዝሙት መውደቅ "ነጻ ፍቅር" ("free love")፣ በሚስት እና በባል ላይ መሄድ ደግሞ "ባለጉዳይ"ነት (affair) ተሰኝተዋል። ይህን የሚያደርጉትም ኃጢአቱን ያለ ምንም መሳቀቅ መሥራት እንዲችሉ ስሙን ያሳምሩታል። ሰው የትኛውንም ኃጢአት ከመስራቱ በፊት ኃጢአቱን የሚጠራበት ስም ይለያል። ኃጢአትን የምንጀምረው በጎ ዓላማ እና ጥሩ ስም ያለው አስመስለን ነው። የሚሰክረው ከስካሩ በፊት ምን ልታደርግ ነው? ቢሉት "ልዝናና ነው" ይላል። የሚሳደበውና የሚራገመውም ከስድቡ በፊት ምን ልታደርግ ነው? ቢሉት "ልመክር" ወይም "እርማት ልሰጥ ነው" ይላል፤ ሌሎቹንም እንዲሁ። ጌታችን በመሰለው የጠፋው ልጅ ምሳሌ ላይ ያለውን ልጅ ከአባቱ ቤት ከመውጣቱ በፊት "ለምን ንብረት ተካፍለህ ከአባትህ ቤት ርቀህ ትሄዳለህ?" ብለን ብንጠይቀው፣ "ዓለምን ለማየት" ይላል እንጂ "ኃጢአት ስላማረኝ" እንደማይል ጥርጥር የለውም። ከኃጢአት መራቅ ትፈልጋለህ? እንግዲያስ ልታደርግ ያሰብከውን ክፋት በስሙ ጥራው። አታድበስብስ፣ አታለስልስ፤ በቃ ኃጢአት ነው። ስለዚህ አትጀምረው። ገብተኽበትም እንደሆነ ስሙን እያሽሞነሞንክ ራስህን አትዋሸው። በደል እንደ ሆነ አምነህ በትክክለኛው ስሙ እስክትጠራውና እስክትጋፈጠው ድረስ መድኃኒት የለህም። መዝሙረኛው ዳዊት በኦርዮ ሚስት ተሰነካክሎ ከወደቀ በኋላ ዳግመኛ የተነሣው "አንተን ብቻ በደልሁ፥ በፊትህም ክፋትን አደረግሁ" ብሎ መጸለይ በጀመረ ጊዜ ነው።(መዝ 51፥4) ዲያቆን አቤል ካሳሁን ሐምሌ 2፣ 2014 ዓ.ም. ሻሸመኔ https://t.me/Dnabel

ሥጋዊ ኃይልና ጉልበት በሕመም ይደክማል። ጽኑዕ ደዌ ብርቱ ክንድን ልምሾ ያደርጋል። የታጠከው የጉብዝና ኃይል በእድሜህ አመሻሽ ይፈታል። ደዌ የማያደክመው እድሜ የማያጠፋው ጉልበት "ኃይለ እግዚአብሔር
ሥጋዊ ኃይልና ጉልበት በሕመም ይደክማል። ጽኑዕ ደዌ ብርቱ ክንድን ልምሾ ያደርጋል። የታጠከው የጉብዝና ኃይል በእድሜህ አመሻሽ ይፈታል። ደዌ የማያደክመው እድሜ የማያጠፋው ጉልበት "ኃይለ እግዚአብሔር" ነው። ብዙ ድንቅ ያደረጉና የዓለምን አስፈሪ ነገሮች የታገሉ ታላላቅ ቅዱሳንን ተመልከት። እንደ ቅዱስ ቂርቆስ ያሉ ሰውነታቸው ያልጸና ሕፃናትን፣ እንደ ቅዱስ ጳውሎስ በራስ ምታት፣ በጎን ውጋትና በቁስል የሚሰቃዩ የደዌ ሰዎችን፣ ከአናብስት ጋር እንደ ተፋለመው ቅዱስ አግናጥዮስ ያሉ አረጋውያንን ታያለህ። የተሻለ እንዳገለግል ይህ ደዌ ቢርቅልኝ፣ ጉልበቴ ቢመለስልኝ አትበል። የሰውነትህ ድካም በአንተ የሚሠራውን የእግዚአብሔርን ኃይል ሊያስቆመው አይችልም። ዓለምን በወንጌል ያጠመቀው እና ከሁሉ ይልቅ የደከመው ሐዋርያ ታማሚው ጳውሎስ መሆኑን አትርሳ። +++ "አቤቱ ጕልበቴ ሆይ፥ እወድድሃለሁ" መዝ 18፥1 +++ ዲያቆን አቤል ካሳሁን https://t.me/Dnabel https://youtube.com/channel/UCRvatZyeFOJtXnAjZSOdrZg

+++ ቶማስን አድርገኝ +++ ሞት ያጠላበት ነው ኑሮዬ ዘወትር ገና አልተከበረም ትንሣኤህ እኔ ጋር ስቃይህን ዘንግቷል ብኩን ኅሊናዬ ደምህ እንዳልዋጀው ነው ነገረ ሥራዬ መነሣትህን ያዩ ተነሥቷል ቢሉኝም እኔ ዓይነ ስውሩ ምንም አላየሁም ይኸው ነው ሕይወቴ ምንም እንዳላየ በትንሣኤው ብርሃን እንዳልተጎበኘ እባክህ ጌታዬ! ቶማስን አድርገኝ እጆችህን ልዳብስ አምኜ ለመኖር" የእኔም ተራ ይድረስ ጣቶቼ ይንኩና የጎን ውግታትህን ስዘከረው ልኑር ሕማም ትንሣኤህን ዲያቆን አቤል ካሳሁን abelzebahiran@gmail.com

ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን፥ በአማን ተንሥአ፤
ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን፥ በአማን ተንሥአ፤

ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ እና ዮሐንስ ዘደማስቆ ሐዋርያው ጴጥሮስ ጌታ በዐረገ በዓመቱ (34 ዓ.ም.) ቅዱሱን እሳት በመቃብሩ ስፍራ ማየቱን ጽፈዋል። ይህ ተአምር አሁን እስካለንበት ዘመን የቀጠለ ሲሆን፣ ሁል ጊዜም በትንሣኤ በዓል ዋዜማ ቅዳሜ ቀን ይታያል። ስለዚህ የሚያስደንቅ ተአምር ብዙ የማያምኑ ሰዎች በራሳቸው መንገድ ለማጣራት ሞክረዋል። እስኪ ከእነዚህ ውስጥ አንዱን ታሪክ ላጫውታችሁ። በአንድ ወቅት እንዲህ ሆነ… ዕለቱ ቅዳሜ ጠዋት 4 ሰዓት የትንሣኤ ዋዜማ ነው። የእስራኤል አይሁድ ፖሊሶች እና የከተማዋ ከንቲባ ይህ እሳት ይፈልቅበታል የተባለውን የጌታን መቃብር እውነትነት ማረጋገጥ ስለ ፈለጉ በውስጡ ለእሳቱ መነሣት ምክንያት የሚሆኑ ተቀጣጣይ ነገሮች ካሉ በሚል ለሁለት ሰዓታት ያህል ሦስት ጊዜ ጥብቅ ፍተሻ አደረጉ። ግን ምንም ሊያገኙ አልቻሉም። ቀጥሎም ሁለት መቃብሩን የሚጠብቁ ሙስሊሞችን በማምጣት ልክ የቀድሞዎቹ አይሁድ የጌታን መቃብር እንዳተሙ እነርሱም መቃብሩን ዘግተው በሰም እንዲያትሙት አደረጉ። ይህንም ተከትሎ በቦታው የነበሩ አረብ ክርስቲያኖች ቱርክ እስራኤልን በተቆጣጠረችበት በ13ኛው ክፍለ ዘመን ከቤተ ክርስቲያን ውጭ በየትኛውም ቦታ ቢሆን እንዳይዘምሩ የተከለከሉትን ቆየት ያለ ዝማሬ በኅብረት ከፍ ባለ ድምፅ መዘመር ጀመሩ። መዝሙሩም:- “እኛ ክርስቲያኖች ነን። ለብዙ መቶ ክፍለ ዘመናትም ክርስቲያኖች ነበርን። እስከ ዘላለምም እንዲሁ እንሆናለን፣ አሜን!” የሚል ነበር። እኩለ ቀንም ሲሆን የግሪኩና የአርሜንያው ፓትርያርክ፣ የግብፁ ሜትሮፖሊታንት እንዲሁም ቀሳውስት እና ዲያቆናት ወደ ታተመው የክርስቶስ መቃብር መጡ። ከብዙ ጸሎት እና ምስጋናም በኋላ የታተመው የክርስቶስ መቃብር እንዲከፈት አደረጉ። ፓትርያርኩም ሞጣህቱን ብቻ አስቀርተው ከላይ የለበሱትን ልብሰ ተክህኖ በማውለቅ በክርስቶስ የዕድሜ ቁጥር ልክ ሦስት 33 ያልበሩ ሻማዎችን ይዘው ጨለማ ወደ ነበረው መቃብር ገቡ። ምእመናኑም ከውጭ ሆነው በአንድ ድምፅ ኪርዬሌይሶን (አቤቱ ይቅር በለን) እያሉ በመዘመር ይጠባበቁ ጀመር። ወደ ቅዱሱ መቃብር ገብተው የነበሩትም የግሪኩ ፓትርያርክ ያን በሰው ያልተቀጣጠለ እና የክርሰ‍ቶስን የትንሣኤ ብርሃን የሚያበሥረውን አምላካዊ እሳት ይዘው ብቅ አሉ። ይህን ጊዜ ጎልጎታ በእልልታ ተሞላች የቤተ ክርስቲያኑም ደወል በሐሴት ይደወል ጀመር። ትንሣኤከ ለእለ አመነ ብርሃነከ ፈኑ ዲቤነ እንኳን አደረሰን!!! https://youtu.be/OGyzCFZO0VY?si=2ptLkHV_WD5rYRvY ዲያቆን አቤል ካሳሁን abelzebahiran@gmail.com

የጠሉህን ሳትወድድ፣ መከራ ያከበዱብህን ተቀይመህ፣ ስለ አሳዳጆችህ ሳትጸልይ እንዴት ጣቶችህን አመሳቅለህ የመስቀል ምልክት ትሠራለህ? በጣቶችህ ያለው መስቀል ጠላት የተወደደበት፣ ለሰቃልያን በቃል የማ
የጠሉህን ሳትወድድ፣ መከራ ያከበዱብህን ተቀይመህ፣ ስለ አሳዳጆችህ ሳትጸልይ እንዴት ጣቶችህን አመሳቅለህ የመስቀል ምልክት ትሠራለህ? በጣቶችህ ያለው መስቀል ጠላት የተወደደበት፣ ለሰቃልያን በቃል የማይነገር ትዕግስት የታየበት፣ ተሳዳቢ የተመረቀበት፣ ለሚወጉ ምሕረት የተደረገበት የፍቅር አውድማ ነው። ሰውን ለመወንጀል በቀሰርከው ጣትህ እንዴት መልሰህ የይቅርባነት ምልክት የሆነውን መስቀል ለመሥራት ሌላው ጣትህን አግድም ታስተኛለህ? እያማተብህ አትጥላ፣ እያማተብህ አትፍረድ፣ እያማተብህ አትቀየም፣ እያማተብህ አትርገም። "ገብረ ሰላመ መስቀሉ" - "በመስቀሉ ሰላምን አደረገ" ዲያቆን አቤል ካሳሁን https://t.me/Dnabel abelzebahiran@gmail.com

“ገብረ ሰላመ በደመ መስቀሉ” “በመስቀሉ ደም ሰላምን አደረገ” እንኳን አደረሳችሁ! ዛሬ የዕብራውያን መልእክት ሐተታ ትምህርት አይኖረንም።
“ገብረ ሰላመ በደመ መስቀሉ” “በመስቀሉ ደም ሰላምን አደረገ” እንኳን አደረሳችሁ! ዛሬ የዕብራውያን መልእክት ሐተታ ትምህርት አይኖረንም።

ይስሐቅ በሞሪያ ተራራ ሊሠዋ ሲሄድ የምትወደው እና እንደ ዓይኗ የምትሳሳለት እናቱ ከእርሱ ጋር አልነበረችም። አብርሃምም ኀዘኗን ማየት ስለ ፈራ ከእግዚአብሔር ስለ ተቀበለው ከባድ ትእዛዝ ለሣራ አልነ
ይስሐቅ በሞሪያ ተራራ ሊሠዋ ሲሄድ የምትወደው እና እንደ ዓይኗ የምትሳሳለት እናቱ ከእርሱ ጋር አልነበረችም። አብርሃምም ኀዘኗን ማየት ስለ ፈራ ከእግዚአብሔር ስለ ተቀበለው ከባድ ትእዛዝ ለሣራ አልነገራትም። የይስሐቅ ቤዛው ክርስቶስ ግን ያ ሁሉ ጅራፍ ሲወርድበት፣ ደሙ በየመንገዱ እንደ ውኃ ሲፈስ፣ በገመድ አስረው እየጎተቱ ሲጥሉትና ምራቃቸውን እየተፉ ሲዘባበቱበት እናቱ ድንግል ማርያም አይታለች። አንድ ልጇ ላይ ብዙ የሆኑ አይሁድ እና ሮማውያን ተባብረው ሲጨክኑበት በዓይኗ በብረቱ ተመልክታለች። ወደ መሬት ወድቆ በረገጡት ጊዜ በስቃይ ከሚቃትት ልጇ ጋር ዓይን ለዓይን ተያይታለች። ለልጅም ለእናቱም ቢሆን ከዚህ ዕለት በላይ የሚከብድ ምን ዓይነት የኀዘን ቀን ሊኖር ይችላል? በዚህ ምድር እንደ አምላካችን ክርስቶስ የሰቃየ እንደ እመቤታችን ማርያምም ያዘነ ማንም የለም! ዲያቆን አቤል ካሳሁን https://t.me/Dnabel

ነገ አርብ ነው። ነገ ስቅለት ነው። ነገ የይቅርታ ቀን ነው። እስኪ ይህ ምሽት ሳያልፈን ይቅር እንባባል!!! ይቅርታ!

photo content

በሕማማት እነዚህን መዝሙራት አለመስማት እጅግ ያስቆጫል። ወንድማችን ጸጋ ልብ ድረስ ሰርስሮ የሚገባ እና በደንብ የታሸ የንስሐ መዝሙር ይዞልን መጥቷል። ይህ ከጸጋ ካልሆነ ከምን ሊሆን ይችላል? እስኪ ስሙና ፈትኑኝ!!! https://youtu.be/fEtOXPn3YUk?si=k3QX9F_uoHYaeCMC

ስለ ሁላችን መዳን የተፈጸመው የክርስቶስን ሞቱን ለምናስብበት እና “በሞቱ ለምንመስልበት” ሰሙነ ሕማማት እንኳን አደረሰን። “ኃይልየ ወጸወንየ ውእቱ እግዚእየ” “ኃይሌ እና መጠጊያዬ እርሱ ጌታዬ ነው
ስለ ሁላችን መዳን የተፈጸመው የክርስቶስን ሞቱን ለምናስብበት እና “በሞቱ ለምንመስልበት” ሰሙነ ሕማማት እንኳን አደረሰን። “ኃይልየ ወጸወንየ ውእቱ እግዚእየ” “ኃይሌ እና መጠጊያዬ እርሱ ጌታዬ ነው” https://t.me/Dnabel