fa
Feedback
Dn Abel Kassahun Mekuria

Dn Abel Kassahun Mekuria

رفتن به کانال در Telegram

ይህ ኦርቶዶክሳዊ የሆኑ የተለያዩ ትምህርቶችን የሚያገኙበት በባለቤቱ የተከፈተ ቻነል ነው። ይወዳጁን ለፌስቡክ ገጽ https://www.facebook.com/AbelKassahunMekuria12?mibextid=ZbWKwL ለyoutube https://youtu.be/s6Cn-jMYjrk?si=Tw7lXr62xkGQtL9_ ለInstagram https://www.instagram.com/abelkassahunm?igsh=OW

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام Dn Abel Kassahun Mekuria

کانال Dn Abel Kassahun Mekuria (@dnabel) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 18 564 مشترک است و جایگاه 4 261 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 1 873 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 18 564 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 19 سپتامبر, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 44 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 2 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 36.08% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 15.84% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 6 697 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 2 940 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 189 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
ይህ ኦርቶዶክሳዊ የሆኑ የተለያዩ ትምህርቶችን የሚያገኙበት በባለቤቱ የተከፈተ ቻነል ነው። ይወዳጁን ለፌስቡክ ገጽ https://www.facebook.com/AbelKassahunMekuria12?mibextid=ZbWKwL ለyoutube https://youtu.be/s6Cn-jMYjrk?si=Tw7lXr62xkGQtL9_ ለInstagram https://www.instagram.com/abelkassahunm?ig...

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 20 سپتامبر, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کرده‌اند.

18 564
مشترکین
+224 ساعت
+147 روز
+4430 روز
آرشیو پست ها
የትውልዱን ሕሊና በዕውቀትና በጥበብ የሚያንጹት የተወዳጁ መምህር መጋቤ ሐዲስ እሸቱ አለማየሁ መንፈሳዊና ማኅበራዊ ትምህርቶች በ"ሠሌዳ ሚዲያ" መድረክ በኩል ለአድማጮችና ለተመልካቾች መቅረብ መጀመራቸው አገልግሎቱን በስፋት ለማዳረስ ተጨማሪ ዕድል እንደሚሆን ታምኖበታል። ሠሌዳ ሚዲያ በመጋቢ ሐዲስ እሸቱ አለማየሁ የተመሠረተ የዲጂታል ሚዲያ መድረክ ሲሆን መንፈሳዊ፣ ማኅበራዊ እና ባህላዊ ጉዳዮች ላይ በማተኮር እውነትን፣ ጥበብንና ኦርቶዶክሳዊ ዕሴቶችን የሚያለመልምና ትውልድን የሚያጎለብት የዕውቀት ምንጭ እንዲሆን ታስቦ ሥራ ጀምሯል። ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሕያው ቃሉ "ምን እንድትሰሙ፥ ተጠበቁ"(ማርቆስ 4፥24)  እንዳለው፥ ሠሌዳ ሚዲያ አድማጭና ተመልካቾች የሚያዩትንም ሆነ የሚሰሙትን በመጠኑና በጥንቃቄ እንዲመርጡ ለሚያሳስበው የዘመኑ የነፍስ ጥሪ ምላሽ የሚሆኑ የጠሩ እና የተመረጡ ይዘቶች የሚቀርቡበት ነው፡፡ በሠሌዳ ሚዲያ፡- Ø  መንፈሳዊ ትምህርቶችና ስብከቶች፣ Ø  የማኅበረሰብ ጉዳዮች ዳሰሳዎችና ትንተናዎች፣ Ø  የባህልና የዕሴት አንጸባራቂ አንድምታዎች፣ Ø  ከምሁራን፣ ከሃይማኖት አባቶችና ከባለሙያዎች ጋር የሚደረጉ ጥልቅ ውይይቶችና ቆይታዎች Ø  ሌሎችም መንፈሳዊና ማኅበራዊ ርእሰ ጉዳዮች በሚዛናዊነትና በኃላፊነት ስሜት ይቀርባሉ፦ ይህን የዕውቀትና የጥበብ ማዕድ ለመካፈል በማኅበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይወዳጁን፤ ለብዙኃኑ ተደራሽ እንዲሆንም አጋር በመሆን ሰብስክራይብና ሼር በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ! YouTube:ሠሌዳ ሚዲያ TikTok: @seledamedia Instagram: seledamedia Facebook: Seleda Media ሠሌዳ ሚዲያ - ምን እንድትሰሙ ተጠበቁ። ### Youtube https://www.youtube.com/@seledamedia.megabehadiseshetu Tiktok http://www.tiktok.com/@seledamedia Instagram https://www.instagram.com/seledamedia/ Facebook https://web.facebook.com/profile.php?id=61591554360962

+++ "ልጆቼ ከመሸ ተገናኘን" +++ ያኔ የገዳሙ መጋቢ የነበሩት አባ ተጠምቀ በጭንቀት ተውጠዋል። ከአቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ እግር ስር ወድቀው "ግድ የልዎትም አባ የዛሬው ጉዞ ይቆይዎ። እኔ ጥሩ ሕልም አላየሁም። እባክዎ እግርዎን ከዚህ ቤት አያንሡ፤ እንደው እባክዎ" እያሉ ይለምኗቸዋል። አቡነ ጎርጎርዮስ ግን ወደ መቂ ጊዮርጊስ ለአገልግሎት ለመሄድ ቆርጠው ተነሥተው ነበርና ሳልሄድ አላድርም ብለው እምቢ አሉ። በእርግጥ በዚያች የጉዞ ቀን ምን ሊሆኑ እንደሚችሉ ቀድመው ሳይረዱት ቀርተው አይመስልም። ምክንያቱም "ዛሬ ጥሩ ሕልም አላየሁምና አይሂዱ" ላሏቸው አባ ተጠምቀ " እኔስ ብሆን አንዳች ምልክት ያላየሁ ይመስልሃል። ዛሬ ጠዋት ሱሬን ስታጠቅ ሰባት ጊዜ መልሶ ሲፈታብኝ ነበር" ሲሉ መልሰውላቸዋል። ይሁን እንጂ በመቂ የሚገኝ እጅግ ሕመም የጸናበት አንድ የሚያውቁት ክርስቲያን ስለ ነበር ከራሳቸው ሕይወት ይልቅ ለዚያ ሰው ነፍስ ዋጋ ሰጥተው "ኸረ ሳላቆርበው እንዳይሞትብኝ" እያሉ አባ ጎርጎርዮስ ወደ መኪናው ፈጥነው ወጡ። ነገር ግን ከዚያ መኪና በሕይወት አልወረዱም። ከአዲስ አበባ ሕዝብ ጭኖ ከመጣ ተሽከርካሪ ጋር እርሳቸው ያሉበት መኪና ተጋጭቶ እሑድ ኃምሌ 22 ቀን ጠዋት አንድ ሰዓት ገደማ እኛ ደግ እና ባለ ብዙ ራእይ አባት አረፉ። ብፁዕነታቸው ከማረፋቸው ከአንድ ሳምንት በፊት በአላጌ ሕፃናት አምባ የልጆች ማሳደጊያ ተገኝተው በዚያ ቦታ ለሚሠራ ቤተ ክርስቲያን መሠረት ካኖሩ በኋላ "ሰው የሚፈልገውን ከሠራ የሚጠብቀው ሞቱን ነው" ብለው ተናግረው ነበር። በውስጣቸውም የነበረው የአገልግሎት እሳት ገና እየተቀጣጠለ ቢሆንም በዚህች ምድር የሚቀራቸው የእንግድነት ዘመን ግን ጥቂት መሆኑን ስለተረዱ በዚያ ለነበሩት መንፈሳዊ ልጆቻቸው እየደጋገሙ "ልጆቼ ከመሸ ተገናኘን" ይሏቸው ነበር። ከዚህች ክፋት ከነገሠባት ዓለም ጠልቀው ፈጣሪያቸው ካለበት መንፈሳዊ አገር የሚወጡበት ጊዜ መቃረቡን ቀድመው የተረዱ አባት ነበሩ። አቡነ ጎርጎርዮስ ከዘመናቸው ቀድመው የኖሩ፣ ትውልዱ ሃይማኖቱን ያቆዩለትን አባቶች እንዲያውቅና የኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ እምነቱንም ታሪክ ከመሠረቱ ተረድቶ ቤተ ክርስቲያኑን እንዲያፈቅር በቃልም በመጽሐፍም የተጉ አባት ናቸው። ቅዱስ አባታችን የነበሩበትን ዘመን አልፎ በሚሄደው ተራማጅ አሳቢነታቸውና ለቤተ ክርስቲያን ሁለንተናዊ ዕድገት ያሳዩት በነበረው ትጋት አሁን ላይ ላሉትና ወደ ፊትም ለሚነሡ በእውነት ለሚደክሙ ቅን አገልጋዮች ሁሉ ትልቅ አርአያ ይሆናሉ። የአገልግሎት ድካማቸው በረከት በሁላችን ላይ ይደርብን። እኛንም የአባቶቻችን ልጆች ያድርገን!!! (*የያኔው አባ ተጠምቀ የአሁኑ ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ሣልሳይ የምሥራቅ ሸዋ አገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ናቸው።) ዲያቆን አቤል ካሣሁን ሐምሌ 22፣ 2014 ዓ.ም. (የብፁዕነታቸው የዕረፍት ቀን) ዝዋይ (ብፁዕነታቸው ብዙ ሥራ በሠሩበት ክፍለ አገር ሆኜ)

በእኛ ላይ ሊደርሱ ካሉ ክፉ አደጋዎች የዳንባቸውን ጊዜያቶች እስኪ እናስተውል። ከእነዚያ አስከፊ ሁኔታዎች ተአምር በሚመስል መንገድ የተረፍንባቸውንና ‹ለጥቂት እኮ ነው…› እያልን የምናስታውሳቸውን ሰ
በእኛ ላይ ሊደርሱ ካሉ ክፉ አደጋዎች የዳንባቸውን ጊዜያቶች እስኪ እናስተውል። ከእነዚያ አስከፊ ሁኔታዎች ተአምር በሚመስል መንገድ የተረፍንባቸውንና ‹ለጥቂት እኮ ነው…› እያልን የምናስታውሳቸውን ሰዓታት እስኪ ለአፍታ ደግመን እናስባቸው። በእነዚያ የጭንቅ ጊዜያቶች ሁሉ የታደገንን የጠባቂ መልአካችንን የተዘረጋች ክንድ እናያለን፡፡ የቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ ደቀ መዝሙር የነበረው ቅዱስ ፖሊካርፐስ በጠባቂ መልአኩ አማካኝነት እንዴት ከሞት በተአምር ሊተርፍ እንደ ቻለ ይናገራል፡፡ ቅዱሱ አብሮት በአገልግሎት ከሚረዳው ዲያቆን ጋር በጉዞ ሳሉ ቀኑ ስለመሸባቸው መንገድ ዳር ካለ አንድ ትንሽ ቤት ገብተው ይተኛሉ፡፡ በእኩለ ሌሊትም የፖሊካርፐስ ጠባቂ መልአክ በሕልሙ ተገልጦ ‹ፖሊካርፐስ ሆይ ሊፈርስ ነውና ፈጥነህ ይህንን ቤት ለቅቀህ ውጣ› እያለ ሶስት ጊዜ አስጠነቀቀው፡፡ ፖሊካርፐስ ራእዩን እንዳየ ያንን ቤት ለቆ በፍጥነት ወጣ፡፡ ወዲያውም ቤቱን እያየው በፊቱ ፈራርሶ ወደቀ፡፡ እርሱም ሊመጣበት ከነበረው ሞት በጠባቂ መልአኩ አማካኝነት ዳነ፡፡ እንኳን ለጠባቂያችን ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሰን! መልካም በዓል ይሁንልን! ዲያቆን አቤል ካሳሁን abelzebahiran@gmail.com

የቤተ ክርስቲያን ትምህርት እና ሥርዓት እንዴት አሁን ያለበትን ዓይነት ቅርጽ ሊይዝ ቻለ? በዚህ ሂደት ውስጥስ በቤተ ክርስቲያን የተካሄዱ ዓለማቀፉዊ ጉባኤያት (Ecumenical Councils) ድርሻቸው ምን ነበር? ይህን አጠር ባለ መንገድ ለመረዳት “ጉባኤ ኒቅያ” የተሰኘውን ሦስት ክፍሎች ያሉትን ተከታታይ ትምህርት ከማስታወሻ ጋር እንድትመለከቱ እጋብዛለሁ። https://youtu.be/Epd_EC5diLI?si=JlViJ7yVxsPkpyHA

የልደት ቀኔን አስመልክቶ በጎ ምኞታችሁን እና ምርቃቶቻችሁን እንደ ወንዝ ላፈሰሳችሁልኝ ሁሉ፣ እግዚአብሔር እንደ ወንዝ የሚፈስ ሰላሙን ይስጣችሁ። አምላከ ጳውሎስ ያክብርልኝ!
+1
የልደት ቀኔን አስመልክቶ በጎ ምኞታችሁን እና ምርቃቶቻችሁን እንደ ወንዝ ላፈሰሳችሁልኝ ሁሉ፣ እግዚአብሔር እንደ ወንዝ የሚፈስ ሰላሙን ይስጣችሁ። አምላከ ጳውሎስ ያክብርልኝ!

ፀሐይ ናላ በምታዞርበት እና ሁሉም ለማረፍ ወደ አልጋው በሚሽቀዳደምበት በቀትር ሰዓት አብርሃም ግን በድንኳኑ ደጃፍ ላይ ተቀምጦ እንግዳ በተስፋ ይጠባበቅ ነበር።(ዘፍ 18) በዚህ የቃጠሎ ጊዜ (ስድስ
ፀሐይ ናላ በምታዞርበት እና ሁሉም ለማረፍ ወደ አልጋው በሚሽቀዳደምበት በቀትር ሰዓት አብርሃም ግን በድንኳኑ ደጃፍ ላይ ተቀምጦ እንግዳ በተስፋ ይጠባበቅ ነበር።(ዘፍ 18) በዚህ የቃጠሎ ጊዜ (ስድስት ሰዓት) መንገድ ላይ የሚገኝ ሰው ወይ ምንም ማረፊያ የሌለው ምስኪን ነው፣ አለዚያ ደግሞ እንደዚያች ሳምራዊት ሴት ከሰው የተገለለ ብቸኛ ነው።(ዮሐ 4፥6) አብርሃም ድንኳኑን ያሰናዳው ያማረ ለለበሱ፣ ብድር ለሚመልሱ፣ በመልክም በገንዘብም ዓይን ውስጥ ለሚገቡ ሰዎች ሳይሆን፣ ሰው ለሸሻቸው መጠጊያ ለሌላቸው እና በፀሐይ ንዳድ እየተንገበገቡ ማረፊያ ፈልገው ለሚዞሩ አስታዋሽ አልባ ምስኪኖች ነበር። አብርሃም በደጁ የሚያልፉ ምስኪን እንግዶቹን “ና እስኪ” ብሎ በማቃለል ቃል አይጠራቸውም። እየሮጠ ወደ እነርሱ ሄዶ “ጌቶች (እመቤት) እባካችሁ ወደ ቤቴ ግቡልኝ” ብሎ በትሕትና ይለምናቸዋል እንጂ። ይህንን ግን በምን አወቅን? በሦስት ሰዎች ተመስለው ወደ ቤቱ ቅድስት ሥላሴ በመጡ ጊዜ አብርሃም እነርሱን ያስተናገደበትን መንገድ አይተን ተረዳን። አብርሃም በዚህች ቀን ተዘጋጅቶ ይጠብቅ የነበረው ሰውን እንጂ እግዚአብሔርን አልነበረም። እግዚአብሔር ግን አብርሃም ለምስኪናኑ ያሳይ የነበረው ቸርነቱን አይቶ በቤቱ ሊስተናገድ ወደደ። አብርሃም ለድሆች ሲል በከፈተው በር በኩል በመካንነት ምክንያት የተዘጋውን የሣራን ማኅፀን የሚከፍት የሠራዊት ጌታ ገባለት። የአንተን የብዙ ዓመታት ጥያቄ ለመመለስ እግዚአብሔር ወደ ሕይወትህ የሚገባው፣ ለሌሎች ሰዎች ብለህ በከፈትኸው የመልካምነት እና የቅንነት በር በኩል ነው። ዲያቆን አቤል ካሳሁን ሐምሌ ቅድስት ሥላሴ -2017 ዓ.ም. https://t.me/Dnabel እንኳን አደረሳችሁ!

“ቅዱሱ በሰይፍ ወደሚቀላበት አደባባይ ከደረሰ በኋላ የሞት ጥላ ዙሪያውን ቢከበውም ‹‹የሚያምንብኝ ቢሞት እንኳ ሕያው ይሆናል›› ብሎ የተነገረውን የጌታን ቃል አምኖ የልብሱን ኮሌታ ከፍ በማድረግ አን
“ቅዱሱ በሰይፍ ወደሚቀላበት አደባባይ ከደረሰ በኋላ የሞት ጥላ ዙሪያውን ቢከበውም ‹‹የሚያምንብኝ ቢሞት እንኳ ሕያው ይሆናል›› ብሎ የተነገረውን የጌታን ቃል አምኖ የልብሱን ኮሌታ ከፍ በማድረግ አንገቱን ለሰያፊው አመቻቸ፡፡(ዮሐ 11:25) ወታደሩም በያዘው ሰይፍ የጳውሎስን አንገት ከሰውነቱ ለየው፡፡ በቃሉ ትምህርት ምድርን ወደ ገነት የቀየረው፣ የብዙዎችን ስብራት የጠገነው፣ ሙት ያስነሣው፣ ሽባ የተረተረው የጳውሎስ አፍ ለመጀመሪያ ጊዜ ታተመ፡፡ ይህ እንኳን ሰውን ሰማይና ምድርንም የሚያስደነግጥ ክስተት ነው፡፡ ለዚህም ነው ሊቁ በመልክእ ነገሩን ሲያደንቅ ‹‹ጳውልስ ወጴጥሮስ አመ አፉክሙ ተኀትመ፣ ዘበሰማያት ወዘበምድር እስከ ንፍቀ ሰዓት አርመመ ››/‹‹ጳውሎስ እና ጴጥሮስ ሆይ፣ አንደበታችሁ በተዘጋ ጊዜ፤ በሰማይም በምድርም እስከ ግማሽ ሰዓት ዝምታ ሆነ ›› የሚለው፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ሰማዕትነትን በሚቀበልበት ጊዜ በቦታው ላይ የነበሩ የዓይን ምስክሮች እንዳሉት ሞቱም በተአምራት የተከበበ ነበር፡፡ እነዚህም ሰዎች በሰይፍ ከተቆረጠው ከቅዱሱ አንገት ደም እና ውኃ ፈልቋል ያሉ ሲሆን፣ አንዳንዶች ደግሞ ራሱ ሦስት ጊዜ ወደ መሬት እንደ ነጠረችና በእነዚያም ቦታዎች ላይ ውኃ (ጠበል) መፍለቁን ተናግረዋል፡፡” ቅዱስ ጳውሎስ፣ ገጽ፡ 410 ቅዱሱ ሰማዕት ጳውሎስ ሆይ፣ እንደ ኤፌሶን ሽማግሎች ስለ ክርስቶስ የተሰየፈች አንገትህን አንድ ጊዜ አቅፈን እንስመው ዘንድ ብታድለን ምን ነበር?! #ኃምሌ 5 ሮም አደባባይ ላይ!

#ጉዞ ወደ ሮም አደባባይ!
#ጉዞ ወደ ሮም አደባባይ!

በሁሉ ጎዳና ምሳሌ የሚሆን፣ በተለይ ለዚህኛው ትውልድ ቅርብ የሆነ እና ወድቆ በመነሣት ውስጥ ያለውን ተስፋ ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ አንድ ቅዱስ ወደ ሕይወታችሁ የምትጨምሩበትን መጽሐፍ ልጋዛችሁ? ይ
በሁሉ ጎዳና ምሳሌ የሚሆን፣ በተለይ ለዚህኛው ትውልድ ቅርብ የሆነ እና ወድቆ በመነሣት ውስጥ ያለውን ተስፋ ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ አንድ ቅዱስ ወደ ሕይወታችሁ የምትጨምሩበትን መጽሐፍ ልጋዛችሁ? ይኸው “ራእየ ኒፎን” በቀሲስ ታምራት ውቤ። ቀሲስ ታምራ ውቤ ይህን ድንቅ መጽሐፍ በመተርጎማቸው፣ ቅድስና ርቆ እንደ ተሰቀለ ውብ ፍሬ እያጓጓ የማይደረስበት ለሚመስለን ለዛሬ ክርስቲያኖች፣ ዛፉን ዘንበል አድርጎ ፍሬውን የማቅረብ ያህል ነው ድርሻቸውን ተወጥተዋል። ደግሞ የአተረጓጎም ለዛው፣ እና የቋንቋው ውበት ደግሞ አስደናቂ ነው። አንዴ ካነሡት አስቀምጡኝ አይልም። የነገ ሰንበት ሐምሌ 5 - 8:00 ሰዓት ቀጠሯችሁ “ከቅዱስ ኒፎን” ጋር ካልሆነ በቀር ሌላ ከማንም ጋር አይሁን። ቀሲስ ታምራት ውቤ ጥሩ ነፍስ የሚያጠግብ ድግስ ደግሰው እየጠሩን ነው። ብንገኝ ብዙ እናተርፋለን። ቦታ: ቦሌ መድኃኔዓለም ቤ/ክ ትልቁ አዳራሽ

#ጉዞ ወደ ሮም አደባባይ!
#ጉዞ ወደ ሮም አደባባይ!

#ጉዞ ወደ ሮም አደባባይ
#ጉዞ ወደ ሮም አደባባይ

ለቅዱሳን ቤተሰቦቹ የጸሎት መልስ የሆነው፣ ለዚህች ዓለም የሚነድና የሚያበራ መብራት የነበረው፣ የሥጋን ጣዕም ያልቀመሰው ፍጹም ተሐራሚ፣ ተፈጥሮው የሰው ኑሮው የመልአክ የነበረው፣ ዕረፍትን የማያውቅ የበረሃው ሰው የታላቁ ሰማዕት የቅዱስ ዮሐንስ በዓለ ልደቱ ዛሬ ይታሰባል። ቅዱሱ ሰማዕት እንደ ኖኅ ጻድቅ የነበረ፣ እንደ አብርሃም በእግዚአብሔር የተወደደ፣ እንደ ዮሴፍ የታሰረ፣ እንደ አቤል በአመጻ የተገደለ፣ እንደ ሄኖክ አካሄዱን ከአምላኩ ጋር ያደረገ ነው። በመንፈስ ቅዱስ አሳዳጊነት በመላእክት አገልግሎት በበረሃ ያደገው ዮሐንስ ክብሩ እንዴት ያለ ነው? እርሱ እንደ ሕፃናት ባለቀሰ ጊዜ የሚያባብለው ሰው አልነበረም። “አይዞህ ልጄ” እያለች የምታጽናናው እናቱም ገና በልጅነቱ ተለይታዋለች። ነገር ግን እግዚአብሔር ብቻውን በበረሃ አልተወውም። አጥንት በሚያለመልም የመላእክት ምስጋና አረጋጋው። በልዩ ጥበቡም አሳድጎ በመንፈስ እንዲጠነክር አደረገው። የእግዚአብሔር አብን ልጅ ዮሴፍ በናዝሬት (የሰው ልጅ) እንዳሳደገ፣ የዘካርያስን (ለሰውን) ልጅ ዮሐንስን እግዚአብሔር በበረሃ አሳደገ። እንኳን አደረሳችሁ አደረሰን! ዲያቆን አቤል ካሣሁን የመጥምቀ መለኰት ቅዱስ ዮሐንስ የልደት በዓል

#ጉዞ ወደ ሮም አደባባይ
#ጉዞ ወደ ሮም አደባባይ

ኃጢአት ጸሎት የማቋረጥ ውጤት ነው። እውነተኛ ጸሎት ኃጢአትን የማቆም ምልክት ነው። ሰው ኃጢአትን ልምዱ ካላደረገ በቀር እየጸለየ የሚበድል፣ ከአምላኩ ጋር እየተነጋገረ የሚያምጽ የለም። አዳም እጸ በለስን የቆረጠው ከአምላኩ ጋር የነበረውን ንግግር (ጸሎቱን) በማቋረጡ ነው። ይኸውም አዳምን ጠርቶ "ወዴት ነህ?" ባለው በፈላጊው ድምጽ ተረጋግጧል። ዲያቆን አቤል ካሳሁን abelzebahiran@gmail.com https://t.me/Dnabel

ቤተ ክርስቲያን ታመሰግንሻለች!!! "ያዘነች ስትሆን በልጅሽ በወዳጅሽ ትንሣኤ የተጽናናችው፡፡ የተዋረደች ስትሆን በድንግልናሽ ቡቃያ መውጣት ከፍ ከፍ ያለችው ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ታመሰግንሻለች፡፡
ቤተ ክርስቲያን ታመሰግንሻለች!!! "ያዘነች ስትሆን በልጅሽ በወዳጅሽ ትንሣኤ የተጽናናችው፡፡ የተዋረደች ስትሆን በድንግልናሽ ቡቃያ መውጣት ከፍ ከፍ ያለችው ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ታመሰግንሻለች፡፡ በዕለተ ዓርብ ከልጅሽ ቀኝ በፈሰሰው ውኃ ተጠምቃ የውግታቱን ደም ተቀብታ ቅድስት ቤተክርስቲያን ታመሰግንሻለች። የልዑል እግዚአብሔር በግ የተባለ ልጅሽ አማኑኤል የተሞሸረባት መርዓዊ ሰማያዊ የተባለባት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ታመሰግንሻለች" አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ እንኳን እመቤታችን ድንግል ማርያም ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሰን! ዲያቆን አቤል ካሳሁን abelzebahiran@gmail.com https://t.me/Dnabel