ግጥም ሲጥም - Gitem Sitem
رفتن به کانال در Telegram
የዘመናችንን ቀለም ያሳያሉ ያልናቸውን የዚህ ትውልድ የስነ ግጥም ውጤቶችን እንጋራ - እናጋራ። ለማካፈል የፈለጋችሁትን በGitem_Sitem ፣ gitemsitem@gmail.com የጸሃፊ ስም እና ርዕስ አክላችሁ ላኩልን። We are all about sharing this generation's poetry. Please email us your pieces gitemsitem@gmail.com
نمایش بیشتر1 721
مشترکین
+224 ساعت
-47 روز
-1530 روز
آرشیو پست ها
cracks between you and me(in my side)
In my side, there is naked bars and parking lot's
There is also air so tin, that could be breath in softly but yet it falt heavy in the inside
There is sky to dark,that will make you wonder if you love the darkness more than your loved once
My side on Sunday
On Sunday, we have a ceremony of visiting the grave yard of dead relationships
Shattered hearts holding black flowers
I think it's because most came to tragic conclusion that love is not enough or good reason to stay together
Or most have been torn apart to many times that the lines do not fit anymore
Or most become to fragile to believe in love or second chance
Or, or you had to kiss a fool and some how you let the kiss to fool you
Or you meet people that are the most successful lier's
My side on Saturday,
Every Saturday there is an event held at the East side, with the title of "the art of slipping away from loved once"
You would walk-in, but your pride will be the Rob that tie's you up and you will fall on your self seem
Every Saturday, you would buy more hate, more disgrace with cheeper price and if you lucky even for free
Every Saturday, you would buy dead flowers to represent your soul
Every Saturday, you would buy sleeping pills, to avoid the day light
And from Friday to Monday after midnight,
There is a game where your memories play tag with your soul
Sometimes they play during the day and anxiety tie's you to bed
Your body and your mind become a broken Maze
There will be no way out so you slip in to the darkness slowly then you become the darkness itself.
My side, there is only grave yard of broken heart and dark souls.
@freetalkk
ሠላም ሠላም ጤና ይስጥልን ፣ ቅዳሜ ጥቅምት 28 ቀን 2013 (ከቀኑ 10:00 ጀምሮ) የመስመር ላይ (ኦንላይን) ግጥማዊ ቅዳሜ እናስተናግዳለን! ይህ ምናባዊ የጥበብ መድረክ ለሁሉም ሰው ክፍት ነው።
"ዙም" ላይ ይቀላቀሉ ወይም በፌስቡክ ቀጥታ ይመልከቱን! ለማንበብ ፍላጎት ካለዎት አስቀድመው በውስጥ መስመር መልዕክት በመላክ ያሳውቁን፡፡ እንደ ሁልጊዜው ሁሉ ያለ ቋንቋ፣እድሜ እና ርዕስ ገደብ አምስት ደቂቃ ይኖርዎታል። እዚያው እንገናኝ!
https://us02web.zoom.us/j/71147805916
Hey everyone, this Saturday, November 7th at 4pm, we will host online Poetic Saturdays! Virtual Poetry is open to everyone. Call in and join by Zoom or watch live on Facebook! If you're interested in reading, let us know beforehand or, if you join in on Zoom, send us a private message. As always, you'll have five minutes and we encourage all languages, all ages, and all topics. See you there!
https://us02web.zoom.us/j/71147805916
#HerStories is an evening of poetry and prose that promotes augmenting the voices and perspectives of Ethiopian women through the written word. An annual event, #HerStories features multigenerational women writers of various backgrounds and experiences. This year, the program will take place on November 6th at the Alliance Ethio Francaise under the theme #Herresillience.
@Earuyan solutions is a social justice and impact-driven feminist social enterprise supporting organizations and individuals to promote gender equality and transformative feminist leadership.
Warming: the event will be held indoors. For sanitary reasons, audience will be limited to more or less 30 people, on a first-come first-served basis. The event will be streamed live as well. Link will be shared on the Facebook event page.
Please bring your ID to get in Alliance.
The event was made possible thanks to the support of Yefikir Design, Creations by Dina and Mems Studio.
ልዩ የቁርጥና ክትፎ ድግስ
ቅዳሜ ጥቅምት 28
ከ10:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ምሽቱ 5:00 ሰዓት jalud,didi gaga,aman kiyamo,aseged eshetu ይቀውጡታል በቀነኒሳ ሆቴል
🙏 @GIONEVENTT
መግብያ :- ቀድሞ ለሚገዙ
ለአንድ ሰዉ 600 ብር እራትን አካቶ
ለጥንዶች 1000 ብር እራትን አካቶ
በሩ ላይ ለሚገዙ
ለአንድ ሰው 800 እራትን አካቶ
ለጥንዶች 1200 እራትን አካቶ
ቲኬት :-
*ቀነኒሳ ሆቴል
*ሮሚ በርገር
* ቦስ ሬስቶራንት
ከመንበሩ ሳልደርስ
ባፍላው ስዝለፈለፍ፣
ከእልፍ ጋር ስሰለፍ፣
እንደ እረመጥ ስር አመድ፣
በእኩይ ስሽመደመድ፣
ሰናዩም ላይቀናኝ
ዳግም ላይመለስ መረን ለቆ ሄዷል፣
ጎኔን ሽባ አድርጎኝ
በእቶን ሞጅሮኝ ብርሃኔ ጠፍቷል።
"ወይ ጉድ ...?
ጥሞና የለኝ
ከንቱነት አዝየ በብኩን አለሜ እድሞነሞናለሁ፣
ለማይሞላ ሙሉ
ስጋየ ተቀፎ ውስጤ ተሰንጎ ደሞ እባዝናለሁ።
እህህህ እላለሁ
ከአድማሱ በታች
አምባው ተሳልቆብኝ ምፀቱን ሲለቀው፣
የራማው ይስቃል
ጉሙን አጣቅሶ እየሰበቀው፣
የልቦናየን ደጃፍ እየወተወተው
እየነረተው።
ጀምበር ስታዘግም
ማየት ያልታደለ ቅዋ አልባ ገደኛ፣
ይበለኝ እኔንስ
ጥበብ ያለበስኩኝ አልፎ መንገደኛ።
ይበለኛ
ሀሰትን አቅልሜ
በሀጥያት ስሸመን በወበቁ ንዝረት፣
ጨለማ እንዲወርሰው
የእውነትን አድባር ለሸንጎ ሰጠሁት።
ለግዝት ዳረኩት
"ወይ ጉድ....?
ክብሬ እድፍ ሆኖ
ቃለ ነበልባሉን እያኮላሸሁ፣
ኪዳኑን ሳልጨርስ ከቅዳሴው ሸሸሁ።
ከመድህን ወልድ
ከአባ መሀሪ እልፍኙን ሳልወርስ፣
ከመንበሩ ሳልደርስ
ፀዳሌም እረግፏል
ከምድር ስላጋ ከምድር ስተሻሽ፣
እንከላወሳለሁ
በድን ተሸክሜ በእድሜየ አመሻሽ።
እንጃልኝ ዘንድሮ
ፍርሀት ሲውጠኝ፣
ፍርሀት ሲንጠኝ፣
አምድ አልባ ሆኛለሁ መንፈስ ሲለውጠኝ፣
ብቻ
መዳኔንም እንጃ ?
ሆዴን ባር ባር አለው እንደ እህል አመሰው፣
ነፍሴ ለዝየራ
ወታ ከንፋለች ዳግም ላትመለስ ሲኦልን ልትቀምሰው፣
አወይ ሰው፣
ሰው መሆን እዳ ነው፣
ፀፀትን አርግዞ ባክኖ መስለምለም ነው።
አወይ ሰው
ሀብታሙ ፍቃዴ
ብርድ አሟሟቅ
ውርጭ ነበር
ቀዝቃዛ ዓየር
ንፋስ ነገር
ብርዳም ዘገር
ቁርፍድ ቆዳዬን ተርትሮ
ስንጥር አካሌን ገፍትሮ
እኔን ከላዬ አባርሮ
ልብ የሚያፍን ምትሃት ሰውነቴን ሲነዝራት
የሚያጀግን ፍርሃት ከንፈሬን ቃል ሲነጥቃት
መድረሻ ያጣ እጄ ጣዕም ሲለቅም ተግቶ
የኦርዮን መቀነት ንጹህ ሰማይ ላይ ጎልቶ
ያገኘኋትን ሜሮፒ ይዣት ልጠፋ ስዳረስ
ክንፌ አልታዘዝ ብሎ ጨረቃ አድርሻት ስመለስ
. . . ውርጭ ነበር
ብርድ ነገር
አገላብጦ እየገረፈ ሙቀቷ ላይ ሲያምሰኝ
ቁሩን ዓየር እየሳበች ግለት ትንፋሿን ሲያምገኝ
አንዴ ተሳምኩኝ ብሎ የእጇ ቀጭ ሲወረዛ
ካይን ገባሁኝ ብሎ ልቧ ምቱን ሲያባዛ
አይኗን በቅጡ ሳላየው ጠረኗ ውስጤ ተደፋ
እሷን ካላየሁበት አይኔም ቢጠፋ ይጥፋ
ብዬ ባቀፍኳት ሰዓት
ቀዝቃዛ ዓየር ያዘለ ውርጫም ንፋስ የበዛበት
ብርዳም ነበረ ቀኑ ጥቅምት የጠቀመበት
እያነቀኝ ሲወጣ ከልቤ ውስጥ ሾላልኮ
ቀልቤ እትት ሲላት ከአቅሏ ጋር ተንሾካሽኮ
የይለፍ ቃሉን ስነግራት ጣቶቿን ቆልፌ ይዤ
ግማሽ አካሏን አንቅቼ ግማሽ አካሌን ደንዝዤ
ስትለምነኝ ስለምናት
‘ተው እንኑር’ ‘ተይ እንሙት’
‘ተው እንኑር’ ‘ተይ እንሙት’
‘ከመኖር ብዙ አለ ካለመኖር እረፍት’
‘ከመኖር ነውር አለ ካለ መኖር እፍረት’
. . . ሁሉን ቋሚ ፍጡር
በቀስት የምቀውር
ተገኘሁኝ ዛሬ አይኔን እስክታወር
ዳስሼ ስሳከር
. . . ብርድ ነበር
ውርጭ ነገር
በራድ ንፋስ ቀዝቃዛ ዓየር . . .
‘አሁን’ ከየት ተከሰተች ይሄ ሙቀት የት ነበረ
ልቦች ተጠራሩ እንጂ የታል አንዳች የደረበ?
ከቁሩ እና ከውርጩ ከስንቱ ጉድ አውጥታኝ
የተሰጠኝን ሳልጠግበው ባልተሰጠኝ ሲከፋኝ
እጄ እንደተሸለመ ለነካበት ተባርኮ
በከንፈሬ የዳበስኩት መውደጃዋን ነበር’ኮ
ምኑ ጋር ፎረሽኩና ዘልቄ ከሷ ያልገባሁ
አንዱን ሳንጨርሰው ስለ ድጋሚው ሰጋሁ
በሆነው፣ በሚሆነው እና ሊሆን ባለው መሃል ተጥጄ
ከነበልባል ነዳድ ትኩሳት ግለቷ በርጄ
እሷን ሸኝቼ ስመለስ ወደ በረዶ ቤቷ
እኔ ቤቴን አጣሁት የት አባቴ የት አባቷ
ምን ሊቆጨኝ ምን ሊቆጫት ታሪክ ጽፈን ነፍሳችን ላይ
ብርዱን ስንሞቅ ቀንቶ ሰማይ
ሰይፈ ተማም 2013
#ሰይፈተማም #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ
Less than a week before our virtual meeting!!! To book your place, simply send your full name, email address and the art form you produce to @Mahlet_mairegu!!!
♡ Home is what you fight for ♡
I have been stuck, a little taken aback
I look around, I feel the pain
I feel the sickness, I feel the shame
What is it to be alive? What does it mean when you're not fine?
•
Let me explain how I feel. . .
Told how to act, how to speak perhaps how to surrender
Many define it as a form of good behavior
Sometimes I wonder, when is it ever enough? When is it ever going to end?
First observation then comes manipulation
The other well it's easy, authentication for the better of the situation
I shudder, I stutter looking at their face
I feel like screaming, I feel unsettled, I am unsettled
•
I went outside that day, wanted to be thrown, away,,, far away
A sound from a far tickled my earlobes
It felt right, nothing ever felt right
Want to change, mop the floors
Want to wake up, on the side of a shore
One touch, for a fear
Body warm, eyes full of tears
Felt the noises, heard all the stories
•
Let me adjust my memory,
Collect all the dust, understand their ways
correct all the pieces, Better will come,
Behold! and do as told
Feelings are overrated
To feel, I shallnot
To flee, I can not
To ask, I better not
Forget, oh well! I guess not
•
So what if I pretend?. . .please no pity
Words don't fill me
Not here to please or be pleased
Only dreamed to be free
Chose to wade in the water
How can I renege? I still want to feel the pain
Getting out sounds like a fairytale
Hhmmm,,,,,I'll treat myself and meet my saviour on the other side
Perhaps I'll leave my pain for him to find
Nothing changes either ways
I'm still stuck in this place
The only place I get to see
The only space I get to fill
•
I have done it before
Tried to let go
Tried to feel the light
Not expecting, to end up with such fight
•
Change doesn't come that easily,
it's easier to adapt than heal
You see, I'd rather share than tell
Seek, you'll get attention
Speak, you'll bring destruction
A simple sequence,,,,,, I was put
A simple rule,,,,,,, I thought
A simple order,,,,,, I never fought
•
In the day, I abide
In the night, I fly
The only time I touch the sky
The only space, I carry my pride
The only place, I speak my mind
I am fine,,,,, well, for now
This here is just fine,,,
I still go outside, to seek away
If not for long, a minute is okay
I won't know when,,,, I won't know how
My place is here, I shall use it somehow.
.
Written by: Deborah Dessalegn
Date: December 28th, 2019
Place: HerStories @allianceethio_francaise
Event: A night of performing arts #HERStories #AllianceEthio-Francaise
#Deborah_Dessalegn #gitemsitem #poeticsaturdays
ከወደድኩኝ ቆየሁ
አብዝቶ ከመታ ልቤ ተደናግጦ ከተደናበረ
ስንቱ ልብ ተስሞ
ስንቱ ተስለምልሞ
ስንቱ ድኖ ታሞ
ስንቱ ተሰበረ
ጊዜ ጥሎኝ መጣ ወዳለሁበት ቀን ባዶ እጁን አንግቦ
ከወደድኩኝ ቆየሁ የሚለውን ልቤን ሊጎበኝ አስቦ
በመኖር ዛላ ውስጥ በቀናት ስንጥር ላይ
ከመንጋጋ መሃል የተሰነቀረች የስጋ ፍንቃይ
ጎርጉሮ እያወጣ ጨጓራዬ እንዲድን ከአንጀቴ እንዳትገባ
ለዓይኖቼ ይልካል ውበትን ዘጋግኖ ለልቤ አበባ
ያማረ በሙሉ የተንቆጠቆጠ እንዴት ይወደዳል
የተወደደ እንጂ ቢዝረከረክ ሁላ ሁል ጊዜ ያምራል
በልጅነት መንገድ ከመንጻት ነጽቼ መጓዝ ከዘነጋሁ
ድፍን ነፍፍፍ ዓመቴ እንደ ልቤ ደጃፍ እኔም ከተዘጋሁ
ከተፍለቀለኩኝ ካማረብኝ በጣም ኮርኩሬ ዘልዬ
ከተሽሞነሞንኩኝ ዓለምን ‘ረስቼ ዕቃ ዕቃ ነው ብዬ
ህጻናት አቅፌ ‘ባፋቸው አውርቼ ከተኮለታተፍኩ
‘አዋቂነት’ ንቄ እልፍ ሳቅ ካደመ’ኩ ቆየሁኝ ከወደድኩ
ብዙ ጊዜ ሆነኝ ከተንተፋተፍኩኝ ሌቱ እስከሚነጋ
መቀነት ፈትቼ ወኔ ከታጠኩኝ አልጋ እስከሚናጋ
ኮረዳ ኮርጄ ውቤ ውዴ ብዬ ለምኜ አባብዬ
ፎግሬ አፏግሬ ከደረቷ መሃል እንባ አቀባብዬ
ያላትን ሰልቤ የኔን አስረክቤ ከተሞዳሞድኩኝ
እንዲሆኑ ሆኜ አይሆኑ ሳልሆነው ቆየሁ ከወደድኩኝ
ሰይፈተማም
#ሰይፈተማም #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ
የመኖር ልክሽ አዙሪት
የታል አምሳያሽ
ምትክ እና ልክ የሚሆንሽ
ምንስ ብለው ሲጠሩሽ
አንቺን
እራስሽን
ነሽ?
በምን ይለካል መኖር በድህነት ከብሮ ከብዶ
በምን ይጸድቃል ካህን በሼኪው ልጅ ፍቅር አብዶ
እንዴት ይመቸው ሴጣን ብርሃንሽ ላይ ጸዳል በዝቶ
እንዴት ይዝለቀው ብርሃን ጽልመትሽ ላይ ሞት በርክቶ
ቢሸፍን ቢከልል አንቺን ችሎ የሚደብቅ
የትኛው ጋራ ነው የትኛው መቀመቅ
ደሞስ ያልታየ ሁሉ እንደሌለ ተቆጥሮ
ስለታየም ደሞ ብቻ የሌለው አለ ተብሎ
መኖርና ማኖር በተምታቱባት ኗሪ ዓለም
ከኖሩስ እንዳንቺ ነው እንዳንቺው ደሞ ካልኖሩም
ሰይፈተማም
#ሰይፈተማም #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ
የሰውነት ነገር
አለባብሶ ማረስ ከራስ ጋር ፉክክር
.
ቀኝ ረግጧል ሲባል ግራው እየሳተ
ቆሞ መሄድ ቀርቶ በድን ተጎተተ
'በ'ምነት የታነፀው' ትልቁ ደረጃ
ድንገት ተደልድሎ
ደመነፍስ ሰፈፈ ባለማወቅ ታጅሎ
ያለማወቅ ዑደት የደመነፍስ ምሪት
ዕውር ግስጋሴ ተዓምረ ቅፅበት
እገደል አፋፍ ላይ እንዳለች አንዲት ነፍስ
አንዲት ብኩን ህይወት
መርገጫዋን ሳታይ የፊቷን ስትሻ
ድ....ፍት!
(የጌታነህ ልጅ)
#የጌታነህ_ልጅ #Yegetaneh_lij #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ
ደመና ጎመራ
ከአድማስ ከሩቅ ካ'ፋፉ ላይ
የወይዛዝርት የጥጥ ፈትል መስሎ የሚታይ
ሰማይ ሊስም ከተራራው አናት ወጥቶ ሲፍገመገም
ደግሞ ሲወድቅ ÷ ደግሞ ሲተም
እንደ እሳተ ጎመራ ፅንስ ካ'ብራኩ እንደተገኘ
በነጭ ቀለም ሲጎመራ
በዝምታ ሲያስፈራራ
ዥንጉርጉሩን የእናቱን ሆድ
በአንዱ ሲያምን÷ በአንዱ ሲክድ
እንደ'ሳቱ ለዓይን ሳይከብድ
የተጠጋውን ሳያነድ
ግን.....በክህደት እሱን መስሎ
የቅርብ ሩቅ ሆኖ ሰውን አቂሎ
በአየር ተንሳፎ ÷ ተራራን ተጫምቶ
ደመና ጎመራ ጨሰ ተድበልብሎ÷ ከሰማይ ተነስቶ ÷ ከተራራው ወቶ
ህሊና ሙሉጌታ
#ህሊና_ሙሉጌታ #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #gitemsitem #poeticsaturdays
ይህ ፎርም የአራዳ መዝገበ-ቃላት ለማዘጋጀት እንዲረዳ የቀረበ ነው።እባክዎ ቃል፣ ሐረግ ወይም አባባል ይፃፉ። ትርጉም ይጨምሩ።
ለትብብርዎ እናመሰግናለን::
https://forms.gle/x6GGoKoS5CKWi6kf7
Scar's
If I could I would sacrifices my soul, my being just to avoid falling for you
If I could I would cut my eyes out just to avoid seeing you smile
If I could I would die earlier before meeting you
I am afraid of height and falling too but some how in some ways I fall for you
Not knowing what would happen at the bottom
Whether I land on my feet or break my back,
That is how much I trusted you
I touched you infinity,
I tattooed you deep in my heart,
I wispered you to the stars, I treated you like the rarest thing in the earth,
I had butterflies in my stomach,
I was good to you
Loving you was the last thing I done
And I was good at it
Most of the times I smile
And gave you a thousand second chances, just to prove I am wrong and you right
I did Olympic worth back flip and believe you are the one
One, you left me
One, you used me
One, like you never had memories of me even the little you had , that is a big may be, you scattered them like the stars
One, sometimes when I see a couples in the streets I wish it would have been us
One, one, you smile with her like I never existed
One, I hate her
Ten, I hope she smiles with your jokes but you would remember me instead of her
Nine, I hope she would feel my infinity touch's, smell my perfume on your body and leave you
Eight, may be then you would want to know how I get my scar's
Seven, you would want to know how time heal the pain and what would you do when those days come, when you don't feel like yourself, when it is upside down
Six, you would wander, when you feel worthless, you would wander,
How I get my scar's
Five, see I ripped you out of my heart, I ripped you out of my smile,
I spoke to you in to my shadows, so you would vapor to thin air
See, I stopped my heart so i could breath again
Four, see I swallowed my pride, but it clues back to my mouth
Three, to her, to the random girl you start dating, I think I saw her in your smile but I cried and washed her too
Two, see I scratched you, from my chest, i used my finger nails
One, that is how I gat my scar's.
One , that is how I smile everyday
One , that is how l smile everyday
🦋🦋🦋🦋
@freetalkk
አንሶሻል ዘለዓለሜ
አካል ሥጋ ጠቦሻል
ረቂቅ ነፍስ በግዘፍሽ
ከአንቺ በልጦ ምን ይዘሻል?
(ጥልመት ድ'ቅድቅ
ብርሃን ድ'ብቅ
እ'ርስት
ዝን'ግት
.
ሕዋ ዐይንሽ ላይ
ንጋቴን ልታጋፍሪበት
ያንቺን ጀንበር መሸበት....
ዝም
ዝም
ዝም
ጭልም!)
አንቺን አልፌ ሁሉን
ሁሉን ሳልፈው ተመለስሁኝ
መኖሪያሽ ነኝ የምለው
ለካስ ነዋሪሽ ነበርሁኝ
(አድማስ እኔ
ብርሃኔ እ'ጥፍ
ጥልመት አንቺ ጥ'ልፍ
ብ'ርር
ክ'ንፍ!
አልነገሩኝ አልተረዳሁ
ስበት ብርሃንን እንዲያሸንፍ!
ሳብሺኝ! ል'ጥፍ!
ቦግ...እልም
ዳግም ዝም!)
ዘለዓለሜ አንሶሽ
መሆኔ ጠቦሽ
ከእኔ ገዝፈሽ
እኔን ያዝሺኝ።
ጥልመትሽ ሁሉን ቢሞላ
አድማስ ሙሉ አበራሺኝ።
..ተንጸባረቅሁ
..ነገሥሁብሽ!
(የማይሆንን አደረግነው
በቅጽበት ሁሌን ኖርነው
...ከዕለታት ጠይም
መልከ መልካሙ ላይ
ሁሉን የሚያህልን
አንድ ነጥብ ሰማይ
አቅፈነው አደርን
ነቅተን ሕልሞች ሆንን
አንቺን አልፌ ዓለሙን
ዓለሙን ሳልፍ ተመለስሁ
አንቺን ሳልፍ - አንቺ ሁሉን
ቀኔ ሲያልፈኝ
አንቺ ሁሌ - አንቺ አሁን
ሆንሁሽና ሆንሁት ሁሉን!
ከዕለታት አንቺ ዕለት
ሰማዩን አቀፍሁት
ተሸከምሁ ሁለንታ
ደቃቃ አሁን ላይ
ዘለዓለም ተረታ...)
አንሶሻል ዘለዓለሜ
(በማን ዐይን ተመዝኖ)
ጠቦሻል ሥጋ አካሌ
(በማን አንጻር ተነጻጽሮ)
የመውደዴን ልኬት
ከመዘንሽው በእነሱ አቅም
ከአሁን ሌላ አልወድሽም
(በእነሱ ዘለዓለም
አሁን የለም!)
ማርቆስ ዘመንበረ ልዑል
#ማርቆስ_ዘመንበረ_ልዑል #MarkOs #ግጥምሲጥም #gitemsitem #ግጥማዊቅዳሜ #poeticsaturdays
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
