fa
Feedback
ግጥም ሲጥም - Gitem Sitem

ግጥም ሲጥም - Gitem Sitem

رفتن به کانال در Telegram

የዘመናችንን ቀለም ያሳያሉ ያልናቸውን የዚህ ትውልድ የስነ ግጥም ውጤቶችን እንጋራ - እናጋራ። ለማካፈል የፈለጋችሁትን በGitem_Sitem ፣ gitemsitem@gmail.com የጸሃፊ ስም እና ርዕስ አክላችሁ ላኩልን። We are all about sharing this generation's poetry. Please email us your pieces gitemsitem@gmail.com

نمایش بیشتر
1 721
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-77 روز
-1830 روز
آرشیو پست ها
የገጣሚን በቃሉ ሙሉ " እኔና ክርስቶስ " የተሰኘው የግጥም መድብል ለንባብ በቃ ::
+1
የገጣሚን በቃሉ ሙሉ " እኔና ክርስቶስ " የተሰኘው የግጥም መድብል ለንባብ በቃ ::

ከፊል መልክሽ ዐይን ሸሽቶ ግራጫ ላሁጫ ጠጉርሽ ከሻሽ መሐል ሾልኮ ወጥቶ እዛ ጥግ... አንቺ በግማሽ እየገባሺኝ መረዳቴን በግማሽ መርሳት ልትረቺ እያየሁሽ.. አስታወስሁኝ ዕለት ከእቅፍሽ አንገቴ ፀጉርሽ መሐል ፊቴ.. ነፍሴ ላይ ጠረንሽ አንቺ - ዙሪያዬ እኔ - ውስጥሽ.... መውደቅ ስንረታ ወድቀን አሳላፊያችን ሲያልፈን አስታወስሁ ትዝ አለኝ የረሳሁት ያልረሳኝ ሳውቅሽ የማውቃት ሽበት እንግዳ ነገር ትመስል ከሌላው ዕለት ጎልታ ታይታኝ.. መቼ ማርጀት ጀመርሽ? .. (ጠሩኝ አልሽኝ.. ወዳሉበት የምትወጃቸው ...ተ ከ ተ ል ሻ ቸ ው! መንገድ ያህል ነገር ያለስንብት በእስትንፍስ ፍጥነት ቶሎ ጥድፍ ክንፍ አንዴ ተንፍሶ መኖር ጨርሶ ...ቀድሞ ለመድረስ.... ጠሩኝ አልሽ ጥድፍ (አቤት እንደማለት...) እፍፍፍፍፍ ሸኘሁሽ ሄደሽ ከጨረስሽ... መቼ ነበር ማርጀት የጀመርሽ?) ከፊል አንቺ ጎኔ ጠጉርሽ መሐል የኖረችን አንዲት ሽበት እየቆጠርሁ ጎንሽ እኔ.. ምን ያህል ዘመን እጅሽን ያዝሁ ስንት ዕለታት ተቃቅፈናል? ዘለዓለም ይሁን ሰከንድ ከፍቅራችን በልጦ ጊዜ እኛን ይመዝነናል? ዛሬኣችን ላይ አድፍጦ ዕድሜን የተደገፈ ጠጉርሽን እያየሁ በከፊልሽ ስደመም መቃናችንን እየታከከ ዘጠኝ ሞት መጣ ዘጠኝ ሞት አለፈ... ትዝ አለኝ እንግዳ ያላየሁት እያየሁ የዘነጋሁት ክንዴ መሐል ሆነሽ ከኖርነው የበለጠ አዲስ ረዥም ዕድሜ ወረሰሽ መቼ አረጀሽ? (...እዚያች ከፊልሽ ያረፈችባት እቅፌ መሐል የወደቅሽባት። ወርደ ጠባብ መደብ ላይ ጥላ እየጣሉ "አቤት" እና ስምሽ ተቀምጠዋል... ያን 'ለት ዘጠኙ አለፈ አሥርኛው ገባ... ቤት ለእንግዳ! በሚያልፍበት ቅጽበት እንኳን ያልተረዱት የሚያውቁት ይሆናል ባዳ ደነቀኝ እየፈካሽ ማርጀትሽ መኖር ምልክትሽ መዋቲ የመሆንሽ... "አቤት!" በእስትንፋስ ዕድሜ ስትጀምሪ ማብቃትሽ ያውም መንገድ ያህል ነገር እስካሁን የነበርሽው መሄድሽን ነበር? መቼ ጀመርሽ ማርጀቱን? እፎይ!) -----አስታወስሁ ያልሁሽ ትዝ ያለኝ እንዲህ እየሆንሁ ነው!---- ከፊልሽ ካረፈበት መደብ አንዱን ዕድሜ ብንተራሰው እንግዳ ያላስተዋልሁት እያየሁ የዘነጋሁት ጠጉሬን ሽበት ወረሰው.. (ለግርምቴ ደግሞ ቀለሙ ያንቺን የሚመስል!) ዕድሜዬን መቼ ኖርሁት መምጫ ስጠብቅ እንጂ የሸበትሁት አረጀሁ! ቀትር - ጀንበር በፈካችበት ጥላሽ ቤቴን ሞልቶታል ከአንቺ ጋር የወሰደኝ ዳግም ደጃፌን ይመታል... (ምን ቀረው?) ከፊልሽን መርታት ያቃተው ብርሃን ቤቴ ዘለቀ (በሬን ማን ገፋው? ግባ! ቤት ለእንግዳ) ግማሽ ጥላሽ ሞላኝ ከፊሌ ላይ ወደቀ! አስታወስሁ ዕለት መዘንጋት ረሳሁ (ከመ ጽጌ ረዳ መዓዛኪ ጥዑም ዘያበርሆ ለጽልመት ገጽኪ ግሩም... ዜማ ሆነሽ ፊቴ ሰፈፍሽ) ተፈለቀቀ ከንፈርሽ አሸበሸበ ከፊልሽ.. ስታዜሚ ስትዜሚ መዝሙርሽ ላይ ስሜን ሰማሁ ከመኝታዬ ተራገፍሁ ከፊሌን ይዤ ተነሳሁ... (እፎይ! በእስትንፋስ ዕድሜ ልከ'ተልሽ! ያውም መንገድ ያህል ነገር መጠበቄ መድረሴን ነበር!) ተከተልሁሽ! "አቤት ዓለሜ? ጠራሺኝ መሰል" #𝖊𝖓𝖙𝖗𝖔𝖕𝖞 #𝖒𝖆𝖗𝖐 𝖔'𝖘

©ማርቆስ ዘመንበረ ልዑል

አዬ ሰው ጎስቋላ አዎን...! አውርተነው ነበር ይህንን ሰውነት ይህን የሞት እብለት! ላይዙት ላይጥሉት መሐላ እንዳለበት፤ ያው ሆነለት ያልነው ገላ ላይ ሲያደርጉት እንዶድም እድፍ ነው። ©ዲበኩሉ ጌታ
አዬ ሰው ጎስቋላ አዎን...! አውርተነው ነበር ይህንን ሰውነት ይህን የሞት እብለት! ላይዙት ላይጥሉት መሐላ እንዳለበት፤ ያው ሆነለት ያልነው ገላ ላይ ሲያደርጉት እንዶድም እድፍ ነው። ©ዲበኩሉ ጌታ #ዲበኩሉ_ጌታ #የምድር_ዘላለም #ግጥምሲጥም3 #ግጥማዊቅዳሜ #artinaddis #poetry #poetrylovers

አዬ ሰው ጎስቋላ አዎን አውርተነው ነበር ይህንን ሰውነት ይህን የሞት እብለት! ላይዙት ላይጥሉት መሐላ እንዳለበት፤ ያው ሆነለት ያልነው ገላ ላይ ሲያደርጉት እንዶድም እድፍ ነው ©ዲበኩሉ ጌታ
አዬ ሰው ጎስቋላ አዎን አውርተነው ነበር ይህንን ሰውነት ይህን የሞት እብለት! ላይዙት ላይጥሉት መሐላ እንዳለበት፤ ያው ሆነለት ያልነው ገላ ላይ ሲያደርጉት እንዶድም እድፍ ነው ©ዲበኩሉ ጌታ

We are so honored to have amazing poets like Kalkidan with us along side our headline poet Dibekulu Geta !!! ''I didn't grow
We are so honored to have amazing poets like Kalkidan with us along side our headline poet Dibekulu Geta !!! ''I didn't grow up to be a poet because I loved the art. I am not a writer because I love spilling words. My writing experience never came from a loving place. It came from a place of need. A need to escape, to be alone, to feel out loud, to let go or to just talk to myself without labeling the process. I needed to talk to myself and listen to myself in return. I believe writing a single poem takes a lot of courage. It starts from revisiting your past and ends with acceptance, but a lot goes in between. There is a lot of feeling in there, from love to resent'' - Kalkidan "poetic disruption through bold and uncensored self-expression'' -Everted Check out her amazing poetry collection here at Everted https://t.me/Everted #Kalkidan #Everted #ዲበኩሉ_ጌታ #የምድር_ዘላለም #ግጥምሲጥም3 #ግጥማዊቅዳሜ #artinaddis #poetry #poetrylovers

ተማፅኖ አንተ የማላውቅህ ኃያሉ ዳኝነት - ገናናው ዝግ ሠሚ በማትለይበት ሁሉን ዐካል የሆነክ፤ ብርሃን ጨለማን ዳር ድንበር አስማሚ፤ አንት የተምኔት ዐለም - ንጉስ ምናቤ ሆይ . . . [ከበፊት ያል
ተማፅኖ አንተ የማላውቅህ ኃያሉ ዳኝነት - ገናናው ዝግ ሠሚ በማትለይበት ሁሉን ዐካል የሆነክ፤ ብርሃን ጨለማን ዳር ድንበር አስማሚ፤ አንት የተምኔት ዐለም - ንጉስ ምናቤ ሆይ . . . [ከበፊት ያልታዬ - ያልነበረን ዘር ግንድ] እባክህን ችረኝ! [አዎን———-] አንዲት ቅንጣት ነገር ትንሽ ሚጢጥ ሥልጣን ሰውን፣ ከእግዜር ሰይጣን - ከራሱም ለማስጣል። #ዲበኩሉ_ጌታ #የምድር_ዘላለም #ግጥምሲጥም3 #ግጥማዊቅዳሜ #artinaddis #poetry #poetrylovers

The Human In Us They think they have figured it out, Humans. They believe they have Deconstructed and traced back the univers
The Human In Us They think they have figured it out, Humans. They believe they have Deconstructed and traced back the universe and God himself to the origins. Yet, look at them Enslaving others for a path of freedom. Creating chaos in the name of peace. Taking more lives in hopes they can reduce death... All they do is Destroy themselves. They gather in their circle of pity and mock another Circle of pity [So as I keep doing now..] They've made God Vulnerable, so lonely and insecure... smiling for the Heathen souls they killed and Getting angry at them for being happy. They think they have figured it all out. Yet all that's out there is contradiction. In a world of change, I envy how some are willing to die for somethings that exist in just their minds. But then I would die for You! [Did I just contradicted my self?] In the manner of contradiction God is more human than humans themselves! https://t.me/thegreyspot ©ማርቆስ ዘመንበረ ልዑል ©Markos ©Fasika Kebede

ጭጭ ኡኡኡታ ዝም ጭጭ ምጭጭ ፀጥ እርምም እምምም የተቆለፈበት በውሸት ተገፍቶ የተገራረደ ድምጽነቱ ጠፍቶ የተቸመቸመ ከንግግር እኩል ታናናሽ ህመሞች በዝምታ 'ሚኩል ስንትናስንት ቡራ ብዙ ሺ ከረዩ ላን
ጭጭ ኡኡኡታ ዝም ጭጭ ምጭጭ ፀጥ እርምም እምምም የተቆለፈበት በውሸት ተገፍቶ የተገራረደ ድምጽነቱ ጠፍቶ የተቸመቸመ ከንግግር እኩል ታናናሽ ህመሞች በዝምታ 'ሚኩል ስንትናስንት ቡራ ብዙ ሺ ከረዩ ላንቃዬ ያልነካቸው ልሳኔን ያላዩ እልፍ ኡኡታዎች መዓት ወዮ ወይኔ ቃሌን እየፈሩ 'ሚደፍሩ የኔን ወኔ አሸን 'ኤጭ ወደዛ!' ነፍ 'አልበዛም እንዴ?!' አይሆንምን ከአፌ መቁረጥን ከሆዴ ሰርክ እያዳፈኑ ለእያሪኮ ይመስል የሚያጠራቅሙ ከለሆሳሴ ላይ ጮኸው የሚሰሙ ዝም ያሉ ጩኸቶች ድምጾቼን ለቀሙ ... ዝም እሪሪሪ !!! ... ዝም ኡኡ! ©ሰይፈ ተማም - ግጥም ©ሙኒት ተስፋዬ - ምስል

አበባ ናት ለጋ ቀንበጥ በአረንጓዴ ዘንግነቷ ከሩቅ የምትታይ ውሃን ነሷት የምራቃቸውን ጠብታ እንኳ ነፈጓት ! ጠደቀች አፈር ነሷት የምትደላደለበት ጠደቀች በውበቷ አሰማመረቻቸው በፍቅሯ አቅበጠበጠቻቸው እስትንፋሷን እፍፍ ብላ ህይወት ዘራች የመጣችው በምክንያት ነው ልታኖር ያላኖሯትን ልታደላድል የጎረበጧትን ፍቅር ሆነችላቸው ህይወት ሆነችላቸው ውበት ሆነችላችው ሲሆንላት ፈክታ ፍንድቅድቅ ብላ ደሞ እየጠወለገች እየሞተችም ጠደቀች እየረገፈች ጠደቀች ሞቷም ውበት ነው:: ትገርመኛለች !!! እውነቷን ያሠረችበት ዘመኗ ግን ብዙም አይደል አጃኢብ እላለሁ ሁሌም ሳስባት ! ©መቅደስ ሞገስ #Mekdes_Moges #መቅደስ_ሞገስ #ዲበኩሉ_ጌታ #የምድር_ዘላለም #ግጥምሲጥም3 #ግጥማዊቅዳሜ #artinaddis #poetry #poetrylovers

የፊታችን ቅዳሜ በግጥም ሲጥም 3 ላይ የአሁኑን 'ራስ' አጅበው ጥዑም ግጥም ከሚያቀርቡላችሁ ውስጥ ሁለቱ ፦ ምትኩ ምድሩ እና ቲና በላይ እንኋቸው! ዛሬ ብሔራዊ ትያትር 11፡30 ጀምሮ ብትገኙ ደግሞ
+1
የፊታችን ቅዳሜ በግጥም ሲጥም 3 ላይ የአሁኑን 'ራስ' አጅበው ጥዑም ግጥም ከሚያቀርቡላችሁ ውስጥ ሁለቱ ፦ ምትኩ ምድሩ እና ቲና በላይ እንኋቸው! ዛሬ ብሔራዊ ትያትር 11፡30 ጀምሮ ብትገኙ ደግሞ ምትኩ ምድሩን ለበጎ ዓላማ ግጥም እንካችሁ ሲል ታገኙታላችሁ። https://t.me/GitemSitem #ዲበኩሉ_ጌታ #የምድር_ዘላለም #ግጥምሲጥም3 #ግጥማዊቅዳሜ #ምትኩ_ምድሩ #ቲና_በላይ #poeticsaturdays #Dibekulu_Geta #Mitiku_Midru #Tina_Belay #artinaddis #poetry #poetrylovers

ዘላለም ናፋቂው (በሻሎም ደሳለኝ) በ2012 ዓ፡ም ከወጡ የግጥም መድብሎች ውስጥ "የምድር ዘላለም" የተሰኘው የዲበኩሉ ጌታ መጽሀፍ አንዱ ነው። መፅሀፉ 106 ያህል ግጥሞችን በ202 የገፅ ብዛት ላይ
ዘላለም ናፋቂው (በሻሎም ደሳለኝ) በ2012 ዓ፡ም ከወጡ የግጥም መድብሎች ውስጥ "የምድር ዘላለም" የተሰኘው የዲበኩሉ ጌታ መጽሀፍ አንዱ ነው። መፅሀፉ 106 ያህል ግጥሞችን በ202 የገፅ ብዛት ላይ አስፍሮ ይዟል። በመድብሉ ውስጥ ከቁጥር እንደተኳረፉ የጥንት ዘመን ሰዎች እድሜያቸውን ያላሰሉ ግጥሞች እንዱሉ ሁሉ የልደት ቀናቸው የታወቀ፣ የተቆጠረ፣ የተሰፈረ ድርሰቶችም አሉ። ተቆጠሩም አልተቆጠሩ ፣ ተሰፈሩም አልተሰፈሩ እድሜያቸው የትየለሌ ዘመናቸውም እስከ ዘለዓለም እንዲሆን ተብለው በደራሲው የተሸመኑ ናቸው። በጎጥ ያልታጠሩ ፤ በደም ያልሰከሩ። "ማነህ መዝሙር ያለህ" የተሰኘው ግጥም ይሄን ሃሳቤን ያስረዳልኝ ይመስለኛል። ይሄ ግጥም ከ2005-2008 ዓ፡ም ድረስ ሲገመድ ሲበጠስ ፣ ሲቀጠል ሲበጠስ ቆይቶ እንካችሁ የተባለ ነው። ዘመን - ድንበር የማይጋርደው ምስል በቃሎችህ የምትስል *** በዩኒቨርስ ሰማይ እኩል የወጣህ ፀሐይ ካለህ…አውጣው - ቅኔህ ይታይ… ለአንድ ሉል የሰው ዘር ውል . . . የብርቱ ገጣሚ አገሩ የት ነው? ድንበሩስ? ምናቡ አይደለምን? ነው እንጂ! ገጣሚው መላዕክ ነው። ለመድብሉ ጥሩ ስም አውጥቶለታል ። አልያም ስምን መላዕክ ብቻ አያወጣም ፤ ገጣሚ ጭምር እንጂ። "የምድር ዘላለም"! "እሱ" በተሰኘው ሌላ ግጥሙ ላይ እንዲህ ይለናል… ህግ፣ ሐሳቡን ከዘላለም አቆራኝቶት እየተራመደው ዘመኑን መች ደርሶት። በስንኞቹ ልሳን ገጸ ሰቡ የሚተርክልን ሐሳብ ከዘላለም አቆራኝቶት "የቆመበቱ ወይም የመሻቱ ዘመን ላይ መች ደርሶበት" እያለን ይመስላል። ነገር ግን እሱ ሰም ነው ፤ ወርቁ "ወሰኔ ይህ ዘመን አይደለም ድርሰቴ ዘላለማዊነት ነው" የሚል ነው...

Green Ethiopia will host an exhibition featuring eco-friendly businesses, entrepreneurs, creators and artists at Fendika Cult
Green Ethiopia will host an exhibition featuring eco-friendly businesses, entrepreneurs, creators and artists at Fendika Cultural Center on 16 January 2021. Doors will open at 10:00am. For more information contact +251 92914 3012. @linkupaddis Download and enjoy the January 2021 edition of LinkUp Addis digital magazine: https://bit.ly/3hyyMxI @linkupaddis

በአሁኑ የግጥም ሲጥም 'ራስ' ዲበኩሉ ጌታ ነው። 'የምድር ዘላለም' የተሰኘች ግሩም የግጥም ስብስብ መጽሐፍ አለችው! ስነ-ግጥም፣ ሙዚቃ፣ የእሳት ዳር ጨዋታዎች፣ ምግብና መጠጥ እንዲሁም ሌሎች መዝናኛ
በአሁኑ የግጥም ሲጥም 'ራስ' ዲበኩሉ ጌታ ነው። 'የምድር ዘላለም' የተሰኘች ግሩም የግጥም ስብስብ መጽሐፍ አለችው! ስነ-ግጥም፣ ሙዚቃ፣ የእሳት ዳር ጨዋታዎች፣ ምግብና መጠጥ እንዲሁም ሌሎች መዝናኛዎች አሉን። https://t.me/GitemSitem በገለጥነው የኛው ቀለም ጥዑም ግጥም እናጣጥም የ'ራሱ'ንም የራሳቸውንም ግጥም ሊያቀርቡ እንዲሁም ዝግጅቱን ሊያጥሙ የተዘጋጁት ደግሞ እኚሁላችሁ ! መቅደስ ሞገስ፣ ምትኩ ምድሩ፣ ሊያ አበበ፣ ልዩ ናቃቸው፣ ኪሩቤል ዘርፉ (ድሬ)፣ አናንያ ተሾመ፣ ቲና በላይ፣ ማርቆስ ዘመንበረ ልዑል፣ ቃልኪዳን (Everted), ሻሎም ደሳለኝ፣ አስታወሰኝ ረጋሳ (አስቱ) እና ሌሎችም ትጉንጬ ካፌ እና ሬስቶራንት /Tigunche cafe and Resturant ካዛንቺስ ኢሲኤ መንገድ ከእፎይ ፒዛ ጀርባ Kazanchis ECA road behind Efoy Pizza #ዲበኩሉ_ጌታ #የምድር_ዘላለም #ግጥምሲጥም3 #ግጥማዊቅዳሜ #artinaddis #poetry #poetrylovers

#ዲበኩሉ_ጌታ #የምድር_ዘላለም #ግጥምሲጥም3 #ግጥማዊቅዳሜ #poetry #artinaddis #poetrylovers
#ዲበኩሉ_ጌታ #የምድር_ዘላለም #ግጥምሲጥም3 #ግጥማዊቅዳሜ #poetry #artinaddis #poetrylovers

Open Mic session 📅 January 9, 2021, 3:30-6:00 pm 📍 Jupiter international hotel, Cazaenchis branch 🙏 @Mokaddis It is free,
Open Mic session 📅 January 9, 2021, 3:30-6:00 pm 📍 Jupiter international hotel, Cazaenchis branch 🙏 @Mokaddis It is free, contact Mekonnen @ 0913107115 @eventsethiopia

Advice From 22 Year Old It's 1:37 The coldness woke Me up from sleep Perfect time to Think deep In my 22 years I understood some Things One life is too short To hold onto pain Two Nothing can stop What God has ordained Three If we don't know How to handle our emotions By them we will be enslaved Four We haven't lived If we didn't love And forgived So why we stay comfortable In places we don't belong? We spend more time in darkness As if it doesn't feel wrong As if these life given to us is long Darling, You were made for bigger things It's okay if sadness is what you feel But don't stay there Someone once said "You matter" I hope you believe it Because you do matter And don't be scared if You don't fit in Don't run away if You make a bad decision Learn from your mistakes Don't waste time on what-ifs Don't let your ego ruin good things Learn to let go If it is meant for you It will find you And about others don't be too quick to assume Everyone is fighting their own battles Mostly it had nothing to do with you Love passionately Unconditionally Forgive and without excuse Learn to say sorry Be grateful for what you have Because you didn't know What it means to starve Believe in yourself And also remember You matter -Hermela

ሌላ ዓለም እስኪገኝ *** መኖር ምሬት ምሬት አየር እሬት እሬት፤ መተንፈስ መፈጥፈጥ ከላይ ወደ መሬት። ሰውነት አሳር ነው ሸሸኹት ገላዬን፣ መራመድ ምሳር ነው እራቀኹት መኖሬን። በቃኝ - ደቃኝ ኑሮ! የመቃብር ደወል የእርምጃው ከበሮ። በቃኝ ከዚህ አገር ዲበ ደህና ሰንብት! ሌላ ቀን! ሌላ ዓለም! ሌላ ዘር እስኪብት። ©ዲበኩሉ ጌታ ጥቅምት፣ 27፣ 2013 ዓ.ም።

!?! አጋኖ መጠየቅ ጠይቆ ማጋነን ፣ ተጠየቅ ተመኑን መልሱን አለማመን ፣ የንጋት ጉልበቱ የእውነት ውበት ተመን ። ለተወርዋሪ ኮከብ ዮሐንስ አድማሱ © ዲበኩሉ ጌታ