fa
Feedback
ግጥም ሲጥም - Gitem Sitem

ግጥም ሲጥም - Gitem Sitem

رفتن به کانال در Telegram

የዘመናችንን ቀለም ያሳያሉ ያልናቸውን የዚህ ትውልድ የስነ ግጥም ውጤቶችን እንጋራ - እናጋራ። ለማካፈል የፈለጋችሁትን በGitem_Sitem ፣ gitemsitem@gmail.com የጸሃፊ ስም እና ርዕስ አክላችሁ ላኩልን። We are all about sharing this generation's poetry. Please email us your pieces gitemsitem@gmail.com

نمایش بیشتر
1 719
مشترکین
-124 ساعت
-47 روز
-1430 روز
آرشیو پست ها
ለማፍቀር ቀጠሮ ሸትታ 'ምትገለማ መርቅዛ 'ምትገማ ወፍፋ ያበደች ጨርቋን ጥላ የሄደች ማንነቷን ስታ ከሆነው ተጣልታ ካልሆነው ተጣብታ ያልሆነውን ሽታ ማስመሰል አብዝታ በመክሰም ለማበብ በመግደል ለማከም በምታደክም አለም ውዴ አንቺን ልወድሽ 'ሚገባ አይደለም ... ... ... ስለዚህ ... በናርዶስ ምዓዛሽ የዝች ቅርናት አለም ሽታዋ ከጠፋ ወይ ሰናይ ፀባይሽ አሽሏት እንደሆን እንዳትቀር ወፍፋ ማስመሰሏን ከሳ እራሷን ስትሆነው ደግሞ ተመልሳ ቀጠሮ ስላለኝ ያንግዜ ልወድሽ አለሜን አክምያት እንዳይረፍድ ባክሽ #seifetemam

ለአባባ ተስፋዬ 2 ያኔ... የፕላስቲክ ኮዳ የሞባይል ካርዱ መንገድ ሳይከመር መስኮትና ጣሪያው በዲሽ ሳይወረር አንድ ቲቪ ብቻ ላንድ ሙሉ ሰፈር አንድ ቲቪ ቻናል ላንድ ሙሉ ሃገር አንድ ሰው ብቻውን ስንቱን ያስቆም ነበር? ኋላ ላይ... እንደ'ውቀት ፍሬ ልጅ ሁሉ እድሜ በላ እንደ አዳም ባነነ ጩጬ ና ፈልፈላ ገባው እንደሌሉ አባባ ተስፋዬ ከስክሪኑ ኋላ ፎገሩኝ እያለ ተካቸው በሌላ ከዛም... ቴሌቭዥኑም ከስቶ እንደእንጀራ ሳሳ ገብስ ወረረው ፈልቶ የአበባውን ማሳ ልጅ ባገሩ በዝቶም ልጅ ሁላ ተረሳ (በአካል ተከስቶም) ለአባባ ተስፋዬ ጠፋ የሚነሳ ከዛም በኋላ... ለገዢው መደብ ጦር ተሰለፉ ልጆች ለአባይ ዘመሩ ጮሁ ለታጋዮች 'ብሔር ብሔረሰቦች' ከ'ዛ በኋላም በኋላ... እነዛን ተወዝዋዥ እጆች እስኪዘክራቸው ታሪክ እስኪገኝ የአባባ ምትክ አዋቂው እንደ ልጅ ይጃጃል ልጅም ይቅበጥ በአዋቂ ልክ ማንም ለማንም አይነሳ እራሱን ያክብር ዘመኑ '1' እና '0'ን ቀምሩ የ'1' እና '0' ነው ቀኑ በሉ ልጆች ደህና ሁኑ ደህና ሁኑ ደህና ሁኑ #seifetemam

ለ አባባ ተስፋዬ 1 'ዛሬ አበባዎች የነገ ፍሬዎች' ብለው ከጠሯቸው ስንቶቹ ረገፉ? ለሳሎን ጌጥነት ስንቶች ተቀጠፉ? እርሶስ ፍሬ ሆነው ተዘርተው አለፉ:: #seifetemam

መስታወተ ጓደኛ ጓደኛ ሲሆን መስታወት 'ራስን 'ሚያሳይ ሲያዩት አንዳ'ንዱ ግን ይለያል የ'ራሱን ምስል ሲያሳዩት ጓደኛዬ ይህ ነው ይላል #seifetemam

ዋጋ የለሽም ምክንያቴን ሁሌም ተረጂው ቢለይብሽም መንገዴ ተመን የለኝም ላንቺ ከቶም አልልሽ ውዴ በዚች ኮተታም አለም ኦና ቤቴን ካሻሽም ውድነት ቢያረክስሽ እንጂ አንቺስ ዋጋ የለሽም #seifetemam

ግጥምጥም የሰበራችሁትን እገጥማለሁ ብዬ ያጣመማችሁትን አቀናለሁ ብዬ እኔው ተሰብሬ እኔው ተጣምሜ ማቅናቴም መግጠሜ በማዝመም ማዝገሜ አወይ ግጥም ጥሜ #seifetemam

እጅ-አዙር አዬ አጤው ቴዎድሮስ እጅግ ተታለለ በነጭ መያዝን ውርደት እንዳላለ ልቡን አጀገነ ያችን ጥይት ሊውጥ በማን ተሰራና በ'ጁ ያለው ሽጉጥ #seifetemam

ያልቃሽ አዋጅ በዚህ ፊት አምላኪ በበዛበት አለም ፊት እንደመቧጠጥ ታላቅ ግድፈት የለም #ፍሰሃ

ወዳጄ ጠጥቶ ጠጥቶ ጠጥቶ ውሃም ይሁን ጠላ ተግቶ ተግቶ ግድግዳ ይጠጋል አጥር ይደገፋል ጀርባ ለሰው ሰጥቶ አጥር ስር ማስለቀስ ህቅም እንኳን ሳይለው ሊከልል ይጥራል የሰውነቱ አካል ሆኖበት ማፈሪያው (ጋሼ Seife ...አስለቃሽህ ወዳጅህን ጠምጄዋለሁ ዛሬ) የጌታነህ ልጅ ሐምሌ 22, 2009

እውነቱን ልንገርሽ (በ ሰይፈ ተማም) እውነቱን ልንገርሽ ከራሴ አስበልጬ አንቺን የምወደው እያለሽ ናፋቂ እየሄድሽ አድናቂ ተራግመሽ መራቂ ልቤን ብጠላ ነው እውነቱን ልንገርሽ ከራሴ አስበልጬ አንቺን እምወድሽ ከፋት ብሎ ሚያምጥ ሳቀች ብሎ ሚያገጥ ኖረሽ የማይወዛ ሄደሽ የማይከሳ ሆኜ ብገኝልሽ አንቺን የምወደው አብልጬ ከራሴ አይንሽን ለማየት ጨረር እማይፈራ አለሽበት ሊደርስ መንገድ ሚሰራ ጣትሽን ለመንካት ጣቱን ሚሰዋ ቃልሽን ለመስማት መናኝ እስከ ህዋ የሆነው አካሌን ብትጠላው ነፍሴ ከማንም አብልጬ አንቺን የወደድኩኝ የወደድሽው ሁሉ... በፍቅር አሳቦ ቅናትን ሰብስቦ ቢያስጨንቀኝ ከቦ (አንቺን ከማስበለጥ) አማራጭ አጣሁኝ ህዳር ፳፬፣ ፪፼፯ ዓም #seifetemam

ግጥም ሲጥም: ቀና ልብ ያልቀጠረውን ሰው ናፍቆ የሚጠብቅ በውድቅት ለሊት ጨረቃን የሚሞቅ ካለም ብርሃናት ላይ ወዳጁን የሚስል በወደደው መጠን መውደዱን 'ሚያክል በደም እና በ'ምነት በተስፋ የጸና ልብስ ይኸውልሽ በፍቅር የቀና #seifetemam

ስብርባሪ.aac2.03 MB

ነገ ዛሬ ዛሬ ሲቻል ለነገ አልኩ ነገም ደርሶ ነገን አከልኩ ከነገወዲያም ደሞ መቶ ነገ ሊባል ሰበብ ሞልቶ ነገ ሲባል ተጎትቶ በነ ነገ ነገር ተወግቶ ባንዱ ነገ ውስጥ ተካቶ እቅድ ተገኘ ሞቶ እምጽ አምጵጽ #seifetemam

ስቆሽሽ በጊዜ እንቅልፍ የጣላችሁ ምነው ዛሬ ደርሶ ፊንፊን ያላችሁ