ግጥም ሲጥም - Gitem Sitem
رفتن به کانال در Telegram
የዘመናችንን ቀለም ያሳያሉ ያልናቸውን የዚህ ትውልድ የስነ ግጥም ውጤቶችን እንጋራ - እናጋራ። ለማካፈል የፈለጋችሁትን በGitem_Sitem ፣ gitemsitem@gmail.com የጸሃፊ ስም እና ርዕስ አክላችሁ ላኩልን። We are all about sharing this generation's poetry. Please email us your pieces gitemsitem@gmail.com
نمایش بیشتر1 721
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-77 روز
-1830 روز
آرشیو پست ها
Meet our musician who possesses various creative sides.
Checkout her works here 👉🏾https://www.youtube.com/watch?v=gznrO3wHb4o&list=RDgznrO3wHb4o&start_radio=1&t=0
#rekik_asegidew #ረቂቅ_አሰግደው #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #ጥዑምግጥም #ምግባርሲራጅ
አለ? ምልክት?
ላለመኖር ማስረገጫ
መኖርን በአንጻር ማስጌጫ?
ይገኛል ትርጉም?
ነፋስ ከሚወዘውዘው
ዐይኔ ከሚያየው ጀርባ
የለም እያልኩሽ ስላለው?
በማለም ሽንቁር ሾልኬ
ግልገል ሞቴን ተመርኩዤ
ከሐሳብ ቁልል መሐል
አለመኖርን መዝዤ
ስመላለስበት ባነጋ
(ሳውቅ)
ማመኔን ሳይደገፍ
መካድ ብቻውን እንዳይረጋ..
ጎሕ ቀደደ
እውኔ ብርሃን ሲያርፍበት
ሕልሜ ጥላ አረቀቀ
የካድሁትን ሆኜ ተነሳሁ
ያመንሁት ከእጄ ወደቀ
(እንዲህ እናምናለን
ስለማሰብ ሐሳብ ሆነን
ስለመፍጠር ተፈጥረን
ሕልሞቻችን እንዲያልሙ
መገፋት ደግፏቸው
ተቃርኖዎች እንደቆሙ...
እንዲህ እናምናለን
ስናምን እንክዳለን..
በማየት በማወቅ ብርታት ስልሽ
ከዚህ መለስ ህይወት የለም
የቱ ህይወት? ከየት ወዲያ?
ብለሽ ብትጠይቂ
መጥራት ህይወት አልፈጠረም?
በተቃርኖ እርቅ ጠራን
እንዲህ ክደን ማመን ዘራን!)
ግልገል ሞቴን ተንተርሼ
ነፍስ ስለመዝራት አስባለሁ
(ነጋ! ነቃሁ ብዬሽ ነበረ?)
ይሄን እየነገርኩሽ መምሸቱን ረስቻለሁ
(ስለማወቅ ስንታመም
መርሳት ደስታ አልሆነም?)
(ቃል ብርሃን ሆኖ ሕዋው ልብ ላይ ፈስሶኣል። እታች፥ ምድር እንደሕያው ዐይኖቼን በብልጭታው ተክዬ
እንዲህ ነን አይደለ?
ወደ'የሉም' ስንጠራ
ሰማይ ዜማ ልንሰራ
ግጥም ሆነን ልናበራ?
ባይ'ረዱን
የማይታይ ይቅር
የምንታይን ካዱን)
ጎሕ ቀደደ ዳግመኛ
በሄድሁበት ዞሬ መጣሁ
መኖሬ ላይ ሕይወት አጣሁ
አየሽ?
መንገድ መድረስን ሲረታው?
(ሕልሜና ዕውኔ መሐል የነበረች ስስ መጋረጃ ተገፈፈች። ነፋሱ የገፋት ቅጠል ተንሳፋ ፊቴ ላይ አረፈች... ሕይወት መገለጥ ሆነ!
ምን ነበረ የለም ያልኩሽ...?
እንዲህ እናምናለን
በማመን እንክዳለን!
በማየት በማወቅ ብርታት ስልሽ
ከዚህ መለስ ህይወት የለም
የቱ ህይወት? ከየት ወዲያ?
ብለሽ ብትጠይቂ
መጥራት ህይወት አልፈጠረም?
በተቃርኖ እርቅ ጠራን
እንዲህ ክደን ነፍስ ዘራን!)
በጀርባዬ ተንበልብዬ
ዐይኖቼን ሕዋው ልብ ላይ ተክዬ
እንደሌለሁ
እንደሌለሽ ይሄንን እውነት ስረሳ
(ብልጭ ያልነው እኛ አይደለን?)
ግጥሞች ሆነን ስንነሳ?
(እንረሳለን
እንጂ..
ካየነው ጀርባ አለን!)
ለ Migbar Siraj
#ማርቆስ_ዘመንበረ_ልዑል #ምግባርሲራጅ #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #ጥዑምግጥም
Meet the published poet, Andu. He will be hosting the show in a way you've never seen before.
@andugetachewpoetry
https://www.youtube.com/channel/UCJI2mmHpHddlQJabYGekFEw
#andugetachew #andu #gitemsitem #poeticsaturdays
የእነዚህን ግጥሞች ሰናኝ ሰው ስም እና የመጽሐፏን ርዕስ ቀድመው ያወቁ ሶስት ሰዎች የአየር ሰዓት ሽልማት ያገኛሉ።
ፍንጭ፦
ከበቂ በላይ ፍንጭ ተሰጥቷል
@seifdman
https://t.me/seifetemam
#ግጥምሲጥም
Meet the poet who is also a Yoga Instructor and a Vegan Chef. Lela will be with us this Saturday!
የዮጋ አሰሪና የቬጋን ምግብ ባለሞያ የሆነችውን ገጣሚ ተዋወቁልንማ
#ሌላ #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #ጥዑምግጥም
#lela #lelamisikir #gitemsitem #poeticsaturdays
Gitem Sitem presents you the marvelous Migbar Siraj and his works along with other outstanding poets.
Poetry, Music, Campfire, Foods and Drinks and so much more.
ግጥም ሲጥም የዘንባባ መጽሐፍ ደራሲ ምግባር ሲራጅን ከሌሎች እጹብ ገጣሚያን ጋር ይዛላችሁ መጥታለች!
ስነ-ግጥም፣ ሙዚቃ፣ የእሳት ዳር ጨዋታዎች፣ ምግብና መጠጥ እንዲሁም ሌሎች መዝናኛዎች አሉን።
https://t.me/seifetemam
በገለጥነው የኛው ቀለም
ጥዑም ግጥም እናጣጥም
#ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #ጥዑምግጥም #ምግባርሲራጅ
የጋዜጠኛና ገጣሚ ወሰንሰገድ ገብረኪዳን አዲስ መጽሐፍ ለንባብ በቃ ::
" ነጻነት " የተሰኘውና በ 112 ገጾች የተቀነበበው መጽሐፍ ግጥሞችንና ወጎችን ሰብስቦ ይዟል ::
ጋዜጠኛና ገጣሚ ወሰንሰገድ ከዚህ ቀደም " የቃሊቲ ምስጥሮች " የተሰኘ የእስር ቤት ማስታወሻና " ሕዝብ ማለት " የተሰኘ የግጥም መድብል አስነብቦናል ::
ይህን ነጻነት የተሰኘውን የግጥም መድብሉ በመደብራችን እየተሸጠ ነው ::
Join. @jafbok
የምስል ጥበብ ስነ-ግጥምን ስታውቃት. . . !
When photography meets poetry...!
@ribkiphoto
#ርብቃሲሳይ #ribkasisay
#ግጥምሲጥም #gitemsitem
Elias Shitahun:
ምስጢረ ሰው መሆን ከምንመረምር
እስቲ አንዳንድ ጊዜ ከአሜን እንጀምር።
ድረሰቱን ዜማውን መሰደር አቁመን
በትርጉም ከምንሞት ከሀሳብ አድመን
ሁሉ እንዲቃናልን ከደቡብ ከሰሜን
ሁሉን ገታ አርገን እንጀምር ከአሜን።
ያመንከውን አስስ
አሜንን ፍለጋ ሰው ከተሰደደ
እንደመስቀል ችቦ በአንድ ከነደደ
ጨለማ ይቀናል በብርሀን ዳና
ሰማይ ቀን ይመስላል ሰው ሰማይ ነውና።
ያመንከውን ፈልግ ከቶ አታፍነው
ጭስ ያበረታኻል ቆሻሻ ቢደፍነው
ያመንከውን ፈልግ
ከሰው በታች ቀብሮህ መቻልህን ገድሎህ
ያልታደለ ሰቃይ
ያነሰ ይመስለዋል መሬት እንኳን ጥሎህ።
ሰቃይ እንደዚህ ነው
የአለምን ድውይ ስትፈውስ ሰትሽር
ጠላትህ ይነሳል ማዳንህን ሊሽር።
ችቦህን አጠራቅም ደመራህን ለኩስ
በአላማህ መንን በሰው ህብረት መንኩስ
ጠላትህን ቀማው የመጥላቱን አቅም
መውደድህን አወጋው
መውጋትን አያውቅም።
ከሰቃይህ ብለጥ ከክፋት ብርሀን
እሳት ይወለዳል በስንጥሮች መሀል።
ከስንጥሮች ቅሰም የህይወትን ትርጉም
ተጋግዞ መብራት ነው የሚያባረረው ጉም።
ደግ ዛሬ ያለው ነገውን ያምጣል
ሁሉን ተወውና ክፉን ትናንት ጣል
ተገኘሁኝ ብለህ ዛሬ እንድትዘምር
ከመታሰብ ቀጥል ከመጀመር ጀምር።
ምስጢረ ሰው መሆን ከምንመረምር
እስቲ አንዳንድ ጊዜ ከአሜን እንጀምር።
በአርትስ tv እንዲሁም በታላላቅ መድረኮች ላይ የምናውቀው ገጣሚ ኤልያስ ሽታሁን አዲስ የ telegram ቻናል ከፍቷል በመቀላቀል ከጥበብ ማዕህድ ይቋደሱ
👇👇👇👇
@Eliasshitahun
@Eliasshitahun
@Eliasshitahun
ጸልያለሁ
========
እጸልያለሁ ለሰው ልጅ
በሰንሰለት ላለው እጅ
እጸልያለሁ ታትሬ
ህላዌን ያላወቀ አለም
ፍፃሜን እንዳያይ ዛሬ
እጸልያለሁ ጸሎቴን
ኩታዬን በኮት ስቀይር
ስለፈረሰው ቤቴ
ራቤን በም'ራብ ስሰፍር
ስለተራበው ጉልበቴ
ስሜን በሰም ሳሰፍር
ስለነደደው ውበቴ
ከራሴ ወጥቼ
ፀርሃ አርያም
ቅጥሩን ተጠግቼ
የዓይኖቼን ውሃ
በፍቅር አተንናለሁ
እ-ጸ-ል-ያ-ለ-ሁ
እጸልያለሁ ጸሎቴን
ዕለትን በአለት ሲያቆም ሲመትር
ስለደከመው አያቴ
ግንጥልጣይ ገጥሞ ሲቀምር
ስለተሰዋው አባቴ
ነፍስ ላይ ነፍጥ ሲከምር
ስለጠበበው አጎቴ
ከራሴ ወጥቼ
መንበረ ፀባዖት
ቅጥሩን ተጠግቼ
የወዜን ብልጭልጭ
በእምነት እጠርጋለሁ
እ-ጸ-ል-ያ-ለ-ሁ
እጸልያለሁ ለሰው ልጅ
በሰንሰለት ላለው እጅ
እጁ ለሰንሰለቱ ሳይጠብ
ሰንሰለት እጁላይ ሳይቀልጥ
ህላዌን እንዲያየው አለም
ፍፃሜን ተግቶ ከማለም
ሰይፈ ተማም 2008
ከተማችን ውስጥ ባለው የጸጥታ ስጋት ይተነሳ ዝግጅታችንን ወደሚቀጥለው ሳምንት ልናስተላልፍ ተገደናል።
እስካሁን ላሳያችሁን ተነሳሽነት ሁሉ ሁላችሁንም እያመሰገንን ያለንበት ሁኔታ ከአቅማችን በላይ የሆነና በአገር ደረጃ ካሉ ሁኔታዎች ጋር የተገናኘ መሆኑን ተረድታችሁ ይቅርታችሁን እንደምትቸሩን ተስፋ እናደርጋለን።
ተጨማሪ መረጃዎችን የግጥም ሲጥም ገጾች የሚያቀብሏችሁ ይሆናል።
Due to security issues in our city, we are forced to move the event to the 21st of November (next Saturday).
We thank you all for your interest in our event. We hope you understand how the situation is beyond our power and we hope you excuse us.
Please stay tuned to Gitem Sitem's channels for more updates.
ተዋወቁልንማ፣ ይህን ጥዑም ግጥም ሰናኝ! ቴዲ ካሳ በግሩም ግጥሞቹ ቆይታችንን ሊያጥም ተዘጋጅቷል።
#ቴዎድሮስካሳ #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #ምግባርሲራጅ #ጥዑምግጥም
https://www.youtube.com/watch?v=-D-skykujfE
የምግባርን ግሩም የግጥም ቪድዮ ሙናን ተጋበዙልንማ
#ሙና #ምግባርሲራጅ #ሞኢሳ #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #ጥዑምግጥም
መልክዐ ሮዝ
ቅዠቴ..
ቀድሞ
ከማይታረም ግዜ መሀል
ራሳችንን ልናስበልጥ
በየጫካው ስንኮበልል
መመለሻው እንዳይጠፋን
ከየሳሩ ከየዛፉ
ጠረንሽን እየቀባን
አልፈን መጣን::
ጉዱ (ተዐምራቱ)
እጣኔዋ
እጣኒቱ::
ካለፍንበት ስመላለስ
ከዚህ ቀደም ከኔ ቀድመሽ
ያለፍሽበት እየቀባሽ
ከዛፍ ከሳሮቹ
ከሀረግ ከእሾሆቹ
ከመሀከላቸው አንድም አልሸበተ
<ፎስት> እንደቀመሳት
ጠበል ጠዲቅ ሁሉ
ወጣት ነው ዘላለም አንቺን ያሸተተ::
©ምግባር ሲራጅ
#ዘንባባ #ምግባርሲራጅ #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #ጥዑምግጥም
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
