fa
Feedback
ግጥም ሲጥም - Gitem Sitem

ግጥም ሲጥም - Gitem Sitem

رفتن به کانال در Telegram

የዘመናችንን ቀለም ያሳያሉ ያልናቸውን የዚህ ትውልድ የስነ ግጥም ውጤቶችን እንጋራ - እናጋራ። ለማካፈል የፈለጋችሁትን በGitem_Sitem ፣ gitemsitem@gmail.com የጸሃፊ ስም እና ርዕስ አክላችሁ ላኩልን። We are all about sharing this generation's poetry. Please email us your pieces gitemsitem@gmail.com

نمایش بیشتر
1 721
مشترکین
-124 ساعت
-37 روز
-1630 روز
آرشیو پست ها
ይኸው የግንቦቱ! እንደወትሮው 12 ሰዓት ከ ዜሮ ዜሮ ሲል መመዝገብ እንጀምርና ልክ ከሰላሳ ሲል ዝግጁቱ ይጀመራል መግቢያ ከአንድ ነጻ አራዳ ጋር 50ብር ብቻ! June Edition is here! As
ይኸው የግንቦቱ! እንደወትሮው 12 ሰዓት ከ ዜሮ ዜሮ ሲል መመዝገብ እንጀምርና ልክ ከሰላሳ ሲል ዝግጁቱ ይጀመራል መግቢያ ከአንድ ነጻ አራዳ ጋር 50ብር ብቻ! June Edition is here! As always, we will start signing up performers at 6 PM and show starts at 6:30 Entrance is 50 ETB with free Arada Come and witness - come and perform The stage is open for all!

We are honored to be part of Goethe Institute's 60th anniversary, this Saturday

ድምቀታችን አስቱን በሁለተኛው መጽሐፉ በቅርብ ቀን
ድምቀታችን አስቱን በሁለተኛው መጽሐፉ በቅርብ ቀን

Our own Zertaye at EBS representing Gitem Sitem and Ethiopian slam poetry የኛው ዘርታዬ ግጥም ሲጥምን እና የኢትዮጵያ የግጥም ግጥሚያን ወክሎ በኢቢኤስ ቅዳሜን ከሰዓት ላይ እንዲህ አቅርቦ ነበር

ፍቅር+ናፍቆት=እኔ ስትቀነሽ አንቺ ባዶነቴን ዉሰጅ ዜሮነቴን እንቺ ☝️እርሱ ነዉ☝️ ዳር የለሽ ንጥሻሽ ከሰዉ ዳር ቢያወጣኝ ከአለም ጥግ ቢወስደኝ ከራማሽ እርቆኝ ከህዋሽ ቢያርቀኝ ጭራሹን ናፍቆትሽ እጅጉን ናፈቀኝ ሲያቀብጠኝ ናፈቅሽኝ አሁን ምን ይዋጠኝ¿¡¿¡ ጎንቻ ነኝ ለእሷ የሚታይ ማህተም ©ጎንቻ

[ . . . እናቴ ግንባር ላይ . . . ] ▿ ▿ የከተማ ልጅ ነኝ ፣ የከተማ ሰው ነኝ መርጋት ከ'ኔ ርቆ ፣ የሚያብከነክነኝ “ደኀና ሰንብች እማ”፣ ብያት እንደወጣሁ “ደኀና ሰንብት”ስትል ፣ ተመልሼ መጣሁ ▿ የከተማ ልጅ ነኝ ፣ ዓይኔ የታከተ ወንዝም ይሁን ባቡር ፣ አፉን ከከፈተ ዘው እልበታለሁ ፣ “ቶሎ ንዳው” ብዬ መራመድ ነው ሕይወት ፣ እግር ነው እጣዬ “ቡና አፍዪ መጣሁ” ፣ ብያት እንደወጣሁ አፈር ሊስማት ሲል ፣ ተመልሼ መጣሁ ▿ የከተማ ልጅ ነኝ ፣ ባሻ ወልዴ ችሎት ቁልቁል እንደ ዝናብ ፣ ሽቅብ እንደ ጸሎት ወዲያም ወዲህ ብዬ ፣ ለገላዬ ስጥር ፈርሶ ሚጠብቀኝ ፣ የመንፈሴ ቅጥር ▿ ግጥም ▹ ድሎት ▹ሥዕል ውበት ▹ ዕውቀት ▹ገንዘብ ፍለጋ ስማስን ከሞቷ ጋር እኩል ፣ ከቤቷ ደረስን ከፍቶኛል አልዋሽም “የሷ ልጅ ነህ?” ሲለኝ ፣ በመልካችን ቅጂ ልጅ አልሆንኩላትም ፣ እናት ሆናኝ እንጂ ▿ የከተማ ሰው ነኝ ፣ ሄዳለሁ መጣለሁ ሰው ይጎርፋል ወዲህ ፣ እኔ ደበቃለሁ ራሴ'ንኳ ሳይጠና ፣ ያኔ እንደወጣሁ በቁንጮ ሸኝታኝ ፣ ዛሬ በጢም መጣሁ ▿ የሚያበራ ግንባር ፣ ሽብሽብ ቆዳ ሆኖ ያለ ተክለጻዲቅ ፣ ታሪክ ተሸምኖ ገለሥላሳ ጠጉሯ ፣ ሽበት ተተክቶ ጡሌ አንገቷ ታጥፎ ፣ መራቀቋ ጠፍቶ ይቻት ያቺ እናት . . . ያሳደድኳት ሕይወት ፣ በየብስ በሰማይ ስትሞት አየኋት ፣ እናቴ ግንባር ላይ ▹▹▹▹▹▹▹▹▹▹▹▹▹▹▹ . . ለወ.ኃ (ሴት አያት) — ይሁን! © HEnock Bekele https://www.facebook.com/henock.bekele.79

ታላቅ የሙዚቃ ድግስ!!! 💚💛❤️ ፲ ዓመት የሙዚቃ የፍቅር የጓደኝነት ጉዞ #ሞሰብ_ባንድ የ10ኛ ዓመት ምስረታ በዓላችንን ግንቦት 8/2014 ዓ.ም. ከቀኑ 11:00 ጀምሮ በ #ኢትዮጵያ_ብሔራዊ_ቲ
ታላቅ የሙዚቃ ድግስ!!! 💚💛❤️ ፲ ዓመት የሙዚቃ የፍቅር የጓደኝነት ጉዞ #ሞሰብ_ባንድ የ10ኛ ዓመት ምስረታ በዓላችንን ግንቦት 8/2014 ዓ.ም. ከቀኑ 11:00 ጀምሮ በ #ኢትዮጵያ_ብሔራዊ_ቲያትር እናከብራለን። በዕለቱም ⭐️መድረክ አጋፋሪ 👉#ግሩም_ዘነበ (#እያዩ_ፈንገስ) ⭐️#ሞሰብ_ባንድ ⭐️#ነጋሪት_ባንድ 👉#ተፈሪ_አሰፋ #Drum 👉#ጆርጋ_መስፍን #Saxophone 👉#ዓብይ_ወ/ማርያም #Piano 👉#እዮስያስ #BaseGuitar 👉#ቴዎድሮስ_አክሊሉ #Piano 👉#ግሩም #Saxphone ⭐️ድምጻውያን 👉#ጠረፍ_ከሳሁን ( #ኪያ ) 👉#ምትኩ_በቀለ (#ቸውሲ) 👉#Surprise ድምጻዊን ጨምሮ ስራዎቻችንን ለታዳምያን እናቀርባለን። 💚💛❤️ መግብያ 200.00 (ሁለት መቶ ብር ብቻ) ትኬቱን በዕለቱ መግቢያ በሩ ላይ ያገኙታል Mobile: +251920326836 +251922842696 E-mail: mosebculturalband@gmail.com Facebook: Moseb Cultural Music Group Youtube: Moseb Cultural Music Band

እንደ ብርቱ ምዕመን ፥ እንደ በቃ ወልይ ቀኝ ብቻ ሲሆን የአህዛብ መስተሐልይ በግራ አውለኝ ብለህ ወደ አምላክህ ፀልይ ። ጊዜህን አትግድል ፥ ከአቅምህም አትጉደል ስትፈልግ አቻህን ፤ አንዳንዴ ህብረ
እንደ ብርቱ ምዕመን ፥ እንደ በቃ ወልይ ቀኝ ብቻ ሲሆን የአህዛብ መስተሐልይ በግራ አውለኝ ብለህ ወደ አምላክህ ፀልይ ። ጊዜህን አትግድል ፥ ከአቅምህም አትጉደል ስትፈልግ አቻህን ፤ አንዳንዴ ህብረት ካላዋጣህ ሞክረው ብቻህን ። አትችልበትም ወይ ? እንዲሁ በሰውነት ያለ መንግስት አዋጅ ራስን መዳኘት ሃይማኖት ሳይኖርህ ፈጣሪህን ማግኘት ከወተት ነጥሎ ገነትን መመኘት ? የሸረሪት መንጋ ድሮች አሰባስቦ አንበሳን ሲያጠምደው እስኪ አንተም ሰው ሆነህ በዜማህ አላምደው ውደደው ውደደው በፖለቲካ አቋም ድርጅት ማቋቋም ኮሚቴና ተቋም እንደ እህል ተዘርቶ በየ ስፍራው ሲናኝ ልክ እንደ መናፍቅ ፥ የከተማ መናኝ ከዓለም ተነጥለህ ፥ ከዓለም ጋ ተገናኝ ። © Hab HD

We will be having an open mic poetry and music session at the Easter Bazaar at Sabegn Concept Store on the eve. Come join us
We will be having an open mic poetry and music session at the Easter Bazaar at Sabegn Concept Store on the eve. Come join us checkout the venders and jam with us!