fa
Feedback
ግጥም ሲጥም - Gitem Sitem

ግጥም ሲጥም - Gitem Sitem

رفتن به کانال در Telegram

የዘመናችንን ቀለም ያሳያሉ ያልናቸውን የዚህ ትውልድ የስነ ግጥም ውጤቶችን እንጋራ - እናጋራ። ለማካፈል የፈለጋችሁትን በGitem_Sitem ፣ gitemsitem@gmail.com የጸሃፊ ስም እና ርዕስ አክላችሁ ላኩልን። We are all about sharing this generation's poetry. Please email us your pieces gitemsitem@gmail.com

نمایش بیشتر
1 721
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-27 روز
-530 روز
آرشیو پست ها
ከዚህ ከመዋቲው መሐል አዲስ ዓለም አዲስ ሕይወት ከሕይወት ሰፈፍ ወለላ ደግሞ አዲስ ሞት ግን የታባቱ ሕይወት አንዳንዴ በርረን ከማንጨርሰው መንገድ ለቀሰማ አረፍ ብለን ከክንፋችን ብርሃን እየተፋን ስናስበው ሞት የላቀ ጣዕም አለው። ከበተንነው ቅንጣት መሐል ሕይወት ሲያብብ አይቻለሁ! I make things of, sweet flavor But my sweetness is yours [As simple a thing as admiring Can shift the world And the hand that breaks us Is the hand that we hold From the ashes, Comes a new birth And of sweetness of birth Another death] ©Markos

(Inspired by Goethe's "the drop of nectar") I make things of, sweet flavor But my sweetness is yours It would have been selfi
(Inspired by Goethe's "the drop of nectar") I make things of, sweet flavor But my sweetness is yours It would have been selfish to keep you all for my self, I wanted to share you to the world! መዋቲያን መሐል ለጣ'ም የተፈጠርን ኢመውታን አላቂ ላይ የተጣልን ጅምሮች በየቀኑ ከመውደድ ሕይወት ከመውደድ ሞት ልንሰራ እየወደቅን ልናሰራራ ዘፍጥረታችን ቀስሞ ተቀምሶ መብነን ቀፎዬን ለቅቄ ስመጣ ከመኖርሽ ጣዕም ስቀምስ መኖሬን አዲስ ቃና ዘለቀው ብቼዬን ልወድሽ ብትበዢ ቢከብደኝ ጣዕምሽን መሸከም ለዓለም ሁሉ ባጋራሁሽ ዓለም ሁሉ ቢወድልኝ ብዬ ተመኘሁ! I let you pollinate And you wilted. ለካ እጅ ያልነካት ጽጌ ዐይን ይሰብራታል ብትበረክቺልኝ ብዬ ያጋራሁት ዓለም ቀጥፎ መቃብሬ ላይ አኖረሽ ካንቺ ቀስሜ ያጣፈጥኩት ሕይወት ከነለዛው ተረስቷል የታመምንለትን ውበት ሕመማችንን ሳይቀር ሕመሜ ቢሽር ያለ ይታከምበታል ከበላዬ ካረፈ አለት ላይ ቀይ ጽጌ እንቡጥ ቀይ ከበላይዋ ቢራቢሮ ከጣዕሟ የሚጋሩ መዋቲያን የታባቱ ሕይወት አንዳንዴ በርረን ከማንጨርሰው መንገድ ለቀሰማ አረፍ ብለን ከክንፋችን ብርሃን እየተፋን ስናስበው ሞት የላቀ ጣዕም አለው። ከበተንነው ቅንጣት መሐል ሕይወት ሲያብብ አይቻለሁ! መዋቲ ዓለም ውለታ ቢስ ነው ያለመንካት አይቶ ነገሮ ሕልም ይሰብራል ደጃፉ ላይ ለዐይኑ ረሃብ ለዐይኑ ጥም የተከላትን ጽጌ በተከለበት እጁ ይቀጥፋል!

Can we grow together? Grow to be strong enough to let me put my hands on the places you are hurting and to trust you enough to see me angry and sad and resentful. Can we grow together? Grow to be wise enough not to poke each other's wound and worse the pain but instead heal them slowly and wholly. Can we grow together? Grow to find absolute freedom in our world. Grow free from every thing we were molded into believing against our will, grow free from all restraints, Free from rules, Free from society, Free from life, Free from death, Hell! Even grow free from time for it is one hell of a bitch. Can we grow together? Grow in love. I didn't say fall darling because everything that falls gets broken and we're left with only few healthy tendons, we can't afford to be hurt again. Can we grow in love together? Wordgasm Words I cum Talk to me @PoeticMind_bot https://t.me/Wordgasm

ይኸው የግንቦቱ! እንደወትሮው 12 ሰዓት ከ ዜሮ ዜሮ ሲል መመዝገብ እንጀምርና ልክ ከሰላሳ ሲል ዝግጁቱ ይጀመራል መግቢያ ከአንድ ነጻ አራዳ ጋር 50ብር ብቻ! June Edition is here! As
ይኸው የግንቦቱ! እንደወትሮው 12 ሰዓት ከ ዜሮ ዜሮ ሲል መመዝገብ እንጀምርና ልክ ከሰላሳ ሲል ዝግጁቱ ይጀመራል መግቢያ ከአንድ ነጻ አራዳ ጋር 50ብር ብቻ! June Edition is here! As always, we will start signing up performers at 6 PM and show starts at 6:30 Entrance is 50 ETB with free Arada Come and witness - come and perform The stage is open for all!

We are honored to be part of Goethe Institute's 60th anniversary, this Saturday

ድምቀታችን አስቱን በሁለተኛው መጽሐፉ በቅርብ ቀን
ድምቀታችን አስቱን በሁለተኛው መጽሐፉ በቅርብ ቀን

Our own Zertaye at EBS representing Gitem Sitem and Ethiopian slam poetry የኛው ዘርታዬ ግጥም ሲጥምን እና የኢትዮጵያ የግጥም ግጥሚያን ወክሎ በኢቢኤስ ቅዳሜን ከሰዓት ላይ እንዲህ አቅርቦ ነበር

ፍቅር+ናፍቆት=እኔ ስትቀነሽ አንቺ ባዶነቴን ዉሰጅ ዜሮነቴን እንቺ ☝️እርሱ ነዉ☝️ ዳር የለሽ ንጥሻሽ ከሰዉ ዳር ቢያወጣኝ ከአለም ጥግ ቢወስደኝ ከራማሽ እርቆኝ ከህዋሽ ቢያርቀኝ ጭራሹን ናፍቆትሽ እጅጉን ናፈቀኝ ሲያቀብጠኝ ናፈቅሽኝ አሁን ምን ይዋጠኝ¿¡¿¡ ጎንቻ ነኝ ለእሷ የሚታይ ማህተም ©ጎንቻ

[ . . . እናቴ ግንባር ላይ . . . ] ▿ ▿ የከተማ ልጅ ነኝ ፣ የከተማ ሰው ነኝ መርጋት ከ'ኔ ርቆ ፣ የሚያብከነክነኝ “ደኀና ሰንብች እማ”፣ ብያት እንደወጣሁ “ደኀና ሰንብት”ስትል ፣ ተመልሼ መጣሁ ▿ የከተማ ልጅ ነኝ ፣ ዓይኔ የታከተ ወንዝም ይሁን ባቡር ፣ አፉን ከከፈተ ዘው እልበታለሁ ፣ “ቶሎ ንዳው” ብዬ መራመድ ነው ሕይወት ፣ እግር ነው እጣዬ “ቡና አፍዪ መጣሁ” ፣ ብያት እንደወጣሁ አፈር ሊስማት ሲል ፣ ተመልሼ መጣሁ ▿ የከተማ ልጅ ነኝ ፣ ባሻ ወልዴ ችሎት ቁልቁል እንደ ዝናብ ፣ ሽቅብ እንደ ጸሎት ወዲያም ወዲህ ብዬ ፣ ለገላዬ ስጥር ፈርሶ ሚጠብቀኝ ፣ የመንፈሴ ቅጥር ▿ ግጥም ▹ ድሎት ▹ሥዕል ውበት ▹ ዕውቀት ▹ገንዘብ ፍለጋ ስማስን ከሞቷ ጋር እኩል ፣ ከቤቷ ደረስን ከፍቶኛል አልዋሽም “የሷ ልጅ ነህ?” ሲለኝ ፣ በመልካችን ቅጂ ልጅ አልሆንኩላትም ፣ እናት ሆናኝ እንጂ ▿ የከተማ ሰው ነኝ ፣ ሄዳለሁ መጣለሁ ሰው ይጎርፋል ወዲህ ፣ እኔ ደበቃለሁ ራሴ'ንኳ ሳይጠና ፣ ያኔ እንደወጣሁ በቁንጮ ሸኝታኝ ፣ ዛሬ በጢም መጣሁ ▿ የሚያበራ ግንባር ፣ ሽብሽብ ቆዳ ሆኖ ያለ ተክለጻዲቅ ፣ ታሪክ ተሸምኖ ገለሥላሳ ጠጉሯ ፣ ሽበት ተተክቶ ጡሌ አንገቷ ታጥፎ ፣ መራቀቋ ጠፍቶ ይቻት ያቺ እናት . . . ያሳደድኳት ሕይወት ፣ በየብስ በሰማይ ስትሞት አየኋት ፣ እናቴ ግንባር ላይ ▹▹▹▹▹▹▹▹▹▹▹▹▹▹▹ . . ለወ.ኃ (ሴት አያት) — ይሁን! © HEnock Bekele https://www.facebook.com/henock.bekele.79

ታላቅ የሙዚቃ ድግስ!!! 💚💛❤️ ፲ ዓመት የሙዚቃ የፍቅር የጓደኝነት ጉዞ #ሞሰብ_ባንድ የ10ኛ ዓመት ምስረታ በዓላችንን ግንቦት 8/2014 ዓ.ም. ከቀኑ 11:00 ጀምሮ በ #ኢትዮጵያ_ብሔራዊ_ቲ
ታላቅ የሙዚቃ ድግስ!!! 💚💛❤️ ፲ ዓመት የሙዚቃ የፍቅር የጓደኝነት ጉዞ #ሞሰብ_ባንድ የ10ኛ ዓመት ምስረታ በዓላችንን ግንቦት 8/2014 ዓ.ም. ከቀኑ 11:00 ጀምሮ በ #ኢትዮጵያ_ብሔራዊ_ቲያትር እናከብራለን። በዕለቱም ⭐️መድረክ አጋፋሪ 👉#ግሩም_ዘነበ (#እያዩ_ፈንገስ) ⭐️#ሞሰብ_ባንድ ⭐️#ነጋሪት_ባንድ 👉#ተፈሪ_አሰፋ #Drum 👉#ጆርጋ_መስፍን #Saxophone 👉#ዓብይ_ወ/ማርያም #Piano 👉#እዮስያስ #BaseGuitar 👉#ቴዎድሮስ_አክሊሉ #Piano 👉#ግሩም #Saxphone ⭐️ድምጻውያን 👉#ጠረፍ_ከሳሁን ( #ኪያ ) 👉#ምትኩ_በቀለ (#ቸውሲ) 👉#Surprise ድምጻዊን ጨምሮ ስራዎቻችንን ለታዳምያን እናቀርባለን። 💚💛❤️ መግብያ 200.00 (ሁለት መቶ ብር ብቻ) ትኬቱን በዕለቱ መግቢያ በሩ ላይ ያገኙታል Mobile: +251920326836 +251922842696 E-mail: mosebculturalband@gmail.com Facebook: Moseb Cultural Music Group Youtube: Moseb Cultural Music Band