fa
Feedback
አብርሆት

አብርሆት

رفتن به کانال در Telegram

ሀሳቦች ዛሬ ካለንበት የዳፍንት (የጨለማ) አለም ወደ ነገ ወደ ተሻለው ብርሀን የሚመሩን መርተውም የሚያገናኙን ድልድዬች ናቸው። ፡ ለአስተያየቶ፡ @bellalsina @ThomB23

نمایش بیشتر
3 738
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز
آرشیو پست ها
እዛ ማዶ አንድ ሚሪንዳ እዛ ማዶ አንድ ሚሪንዳ እባክህ አንድ ሰው ውሰደኝ ካናዳ . ፕሊስ😑

ዛሬ ማምሻውን አንድ ወደል ቢጤ ጢሙን ያጎፈረ በአንድ እጁ ቆርኪ ያለው ዱላ: በሌላ እጁ ጸናፅል ነገር ይዞ በራችን ላይ መቶ "ቡሄ ና ቡሄ በሉት" ይላል ከዛ እኔም:እንዴ ምነው ብቻህን አልኩት" ከዘዛ እሱ : ሰው አጣሁ😑... (እረ ቢዝነስ አናርገው ባህሉን😅)

የቡቲክ ነገር...😑 እንደው ብርድ ብጤ ሰውነቴን ቢያንዘፈዝፈው : ለብርዱ የሚሆን ኮት ነገር እና : የአዲሳባ አስፓልቶችም ከዝናቡ ፍቅር የያዛቸው ይመስል የዘነበውን በሙሉ አቁሮ እየያዘ ጫማዬ ውስጥ እየገባ በመቸገሬ ጫማ ነገርም ለመግዛት አስቤ ወደ ቡቲክ ጎራ አልኹ። ከትንሽ ቡቲኩ ውስጥ መንጎራደድ በኋላ አይኔ የወደደውን ኮት አነሳሁ እና ድምፄን ጎርነን አርጌ " ይሄኛው ስንት ነው"አልኳት... ቡቲክ የገባውን አይኗ ላይ በተተከለው ሽፋሽፍት መሳይ ነገር እየወጋች የምትሸጥ የምትመስለዋን ልጅ..."ስምንት"አለች : የአይኗን ጭራሮ እያ’ማታች በተሞላቀቀ ድምፅ። ስምንት መቶ ማለትሽ ነው " አልኩ አሁንም ያላግባብ ድምፄን አጎርንኜ...."አይ : ስምንትሺ ማለቴ ነው " አለች እንደ መሳቅ እያደረጋት። ኦው እረ ባክሽ : ጥሩ " አልኩ፥ አሁን ግን እንደቅድሙ የጎረነነ ድምፅ መጠቀሜን እንጃ...። የያዝኩትን ኮት አስቀመጥኩና ከፊቴ በተደረደሩት ጫማዎች ላይ በአይኔ ከዞርኩ በኋላ : አሁንም ደስ ያለኝን ጫማ አንስቼ "እቺስ " አልኩ እቺስ በማለቴ ዋጋው ይቀንስ ይመስል...። አስራ አራት " አለች ከተቀመጠችበት ተንስታ ወደኔ እያዘገመች...u mean 14ሺ ነው ኣ " አልኳት...የራስ ቅሏን በአዎንታ ወዘወዘች። 8ሺ + 14ሺ = 22ሺ.... እኔምልሽ ከባንክ ጋር ማያያዝ ይቻላል እንዴ...ባንኩ መቶ ይክፈልልኝ እና እኔ ደሞ ቀስ ብዬ በፐርሰንት እከፍላለሁ" አልኳት እንጃ ለምን እንደሳቀች : ገለፈጠች ብል ይቀላል በርግጥ። ብቻ አንድ እጇን አፏ ላይ አርጋ መሳቅ ጀመረች። ገለፈጠች ስል ሰማችኝ ይሆን...እንጃ ብቻ...ትስማ ደሞ... ለሁለት ቁሰች እኔስ 24ሺ ብር ብላ ስጠራልኝ ምን አልኳት።ምንም! .... ልጅ እና ፊት ብርድ አይበርደውም " አልኩት ለራሴ..እሷም አንድ እጇን አፏ ላይ ይዛ እየሳቀች: እኔም ሁለት እጄን አናቴ ላይአርጌ እንደመጮህ አሰኘኝ መሰል በለሰለሰ ድምፅ መልካም ቀን ብያት ከገባሁበት ቡቲክ እያዘገምኹ ወጣሁ። .... እኔ ድምፄን ሳጎረንን ለካ ኑሮው በደምብ ጎርኑኖ ኖሯል እናንተዬ። በቲሸርት ዝናብ ሲመታው እንዘጥ እንዘጥ እያለ ሲሮጥ ወይ walk ሲያደርግ መንገድ ላይ ካያችሁ እኔ ነኝ። በዚ ብርድ እና ክረምት በቲሸርት የሚሄደው ጤነኛ ነው ?" ብላችሁ እንዳትታዘቡኝ አደራ !

የቡቲክ ነገር...😑 እንደው ብርድ ብጤ ሰውነቴን ቢያንዘፈዝፈው : ለብርዱ የሚሆን ኮት ነገር እና : የአዲሳባ አስፓልቶችም ከዝናቡ ፍቅር የያዛቸው ይመስል የዘነበውን በሙሉ አቁሮ እየያዘ ጫማዬ ውስጥ እየገባ በመቸገሬ ጫማ ነገርም ለመግዛት አስቤ ወደ ቡቲክ ጎራ አልኹ። ከትንሽ ቡቲኩ ውስጥ መንጎራደድ በኋላ አይኔ የወደደውን ኮት አነሳሁ እና ድምፄን ጎርነን አርጌ " ይሄኛው ስንት ነው"አልኳት... ቡቲክ የገባውን አይኗ ላይ በተተከለው ሽፋሽፍት መሳይ ነገር እየወጋች የምትሸጥ የምትመስለዋን ልጅ..."ስምንት"አለች : የአይኗን ጭራሮ እያ’ማታች በተሞላቀቀ ድምፅ። ስምንት መቶ ማለትሽ ነው " አልኩ አሁንም ያላግባብ ድምፄን አጎርንኜ...."አይ : ስምንትሺ ማለቴ ነው " አለች እንደ መሳቅ እያደረጋት። ኦው እረ ባክሽ : ጥሩ " አልኩ፥ አሁን ግን እንደቅድሙ የጎረነነ ድምፅ መጠቀሜን እንጃ...። የያዝኩትን ኮት አስቀመጥኩና ከፊቴ በተደረደሩት ጫማዎች ላይ በአይኔ ከዞርኩ በኋላ : አሁንም ደስ ያለኝን ጫማ አንስቼ "እቺስ " አልኩ እቺስ በማለቴ ዋጋው ይቀንስ ይመስል...። አስራ አራት " አለች ከተቀመጠችበት ተንስታ ወደኔ እያዘገመች...u mean 14ሺ ነው ኣ " አልኳት...የራስ ቅሏን በአዎንታ ወዘወዘች። 8ሺ + 14ሺ = 22ሺ.... እኔምልሽ ከባንክ ጋር ማያያዝ ይቻላል እንዴ...ባንኩ መቶ ይክፈልልኝ እና እኔ ደሞ ቀስ ብዬ በፐርሰንት እከፍላለሁ" አልኳት እንጃ ለምን እንደሳቀች : ገለፈጠች ብል ይቀላል በርግጥ። ብቻ አንድ እጇን አፏ ላይ አርጋ መሳቅ ጀመረች። ገለፈጠች ስል ሰማችኝ ይሆን...እንጃ ብቻ...ትስማ ደሞ... ለሁለት ቁሰች እኔስ 24ሺ ብር ብላ ስጠራልኝ ምን አልኳት።ምንም! .... ልጅ እና ፊት ብርድ አይበርደውም " አልኩት ለራሴ..እሷም አንድ እጇን አፏ ላይ ይዛ እየሳቀች: እኔም ሁለት እጄን አናቴ ላይአርጌ እንደመጮህ አሰኘኝ መሰል በለሰለሰ ድምፅ መልካም ቀን ብያት ከገባሁበት ቡቲክ እያዘገምኹ ወጣሁ። .... እኔ ድምፄን ሳጎረንን ለካ ኑሮው በደምብ ጎርኑኖ ኖሯል እናንተዬ። በቲሸርት ዝናብ ሲመታው እንዘጥ እንዘጥ እያለ ሲሮጥ ወይ walk ሲያደርግ መንገድ ላይ ካያችሁ እኔ ነኝ። በዚ ብርድ እና ክረምት በቲሸርት የሚሄደው ጤነኛ ነው ?" ብላችሁ እንዳትታዘቡኝ አደራ !

ለኢትዮጵያ አምላቅ ምስጋና አቅርቡ ይላል እንዴ...እንደ ኢትዮጵያ አምላክ ደባሪ የለም እኮ ዋቃን😑

@like #c32aa74adbf6d828f

ድርጊት ፣ ፍላጎት እና ሥነ ልቦና... ፧ ድርጊታችን ከአመለካከታችን ጋር ለምን አልሰመረም... " አመለካከታችን ከድርጊታችን ጋር ቅራኔ ውስጥ መግባት የጀመረው የእኛ አመለካከት በሌሎች ብዙሃኑ ሰዎች ተጽዕኖ ስር ስለሚወድቅ ነው። ማኅበራዊው ተጽዕኖ(ማህበራዊው ስነ ልቦና) በርካታና ተከታታይ ስለሆነ በተግባር አመለካከታችንን ሆነን እንዳንገኝ አድርጎናል፤ ሌላው ቀርቶ ማህበራዊው ተፅዕኖ እጅግ የበረታ ከመሆኑ የተነሳ በጽናት የምናምንበትን እምነት እንኳን አጥቦ የመውሰድ ሃይል አለው ። " / አለን ዊከር / ፧ የሰው ልጅ ድርጊት የሚመራው በምክንያታዊነት ነው ወይስ በፍላጎት...? " የሰዎች ድርጊት የሚቀጣጠለው የራስ ወዳድነት ፍላጎታቸውን ለማርካት ባላቸው ፍላጎት ነው ። ለድርጊታቸውም ምክንያትን የሚያቀርቡት ከድርጊታቸው በፊት ሳይሆን ድርጊቱን ከፈጸሙ በኋላ ነው ። " / አርተር ሾፐን አፐር / ፧ ማህበራዊ ሥነ ልቦና ሁልጊዜ የብዙሃኑ ህዝብ ወቅታዊና አንገብጋቢ ስሜት ስለሆነ ምቹ ሁኔታ እየፈለገ እዚህም እዚያም የሚፈነዳ ክስተት ነው ። የሚቀመረውም ከብዙሃኑ የዕለተለት ኑሮና ተግባር፣ የብዙሃኑን የኑሮና የተግባር ሁኔታዎች እንዲሁም ፍላጎቶች ከሚያንጸባርቁ አስተያየቶች ነው ። ፧ ምንጭ ፦ ፍልስፍና ፩

Repost from 24 DESIGN
#hoody_Tshirts_sweaters_ Size #All Color #Available 🔹 High #Quality Printing 🔹Unbelievable price and half way delivery 🔹Co
+3
#hoody_Tshirts_sweaters_ Size #All Color #Available 🔹 High #Quality Printing 🔹Unbelievable price and half way delivery 🔹Contact for more @ThomB23 #መልዕክዎን_ያስቀምጡ @ThomB23 ስልክ +251942545257 ብዙ አማራጮች ስላሉን በሚፈልጉት ዲዛይን አሁኑኑ ይዘዙን...👌

Repost from 24 DESIGN
photo content
+8

Repost from 24 DESIGN
#hoody_Tshirts_sweaters_ Size #All Color #Available 🔹 High #Quality Printing 🔹Unbelievable price and half way delivery 🔹Co
+3
#hoody_Tshirts_sweaters_ Size #All Color #Available 🔹 High #Quality Printing 🔹Unbelievable price and half way delivery 🔹Contact for more @ThomB23 #መልዕክዎን_ያስቀምጡ @ThomB23 ስልክ +251942545257 ብዙ አማራጮች ስላሉን በሚፈልጉት ዲዛይን አሁኑኑ ይዘዙን...👌

#Seniors #half_life #GC #tshirts_sweaters_hoody_oldschool_AfricaDressHoody👌 All available. #with_modern_unique _Designs 🔹 S
+7
#Seniors #half_life #GC #tshirts_sweaters_hoody_oldschool_AfricaDressHoody👌 All available. #with_modern_unique _Designs 🔹 Size #M #L #xl #xxl #xxxl 🔹 High #Quality Printing 🔹Unbelievable price and half way delivery 🔹Contact us @ThomB23 +251942545257 ብዙ አማራጮች ስላሉን በሚፈልጉት ዲዛይን አሁኑኑ ይዘዙን...👌

የተኩላዎች መንጋ ከደረሰ በኋላ በጎቹን ለመሰብሰብ መጋጋጡ አይበቃም ወይ እረኛው?? ኢትዮጵያ እና ህዝቧ በዚህ አይነት እረኛ መታገድ ከጀመሩ እኮ እነሆ ብዙ አመታትን ቢያስቆጥርም የቅርቡ የ3 አመታቱ ደግሞ በስማም ወወልድ አይጣል ነው።ከረኞቹ ተኩላዎቹን ያስመኛል😑 ዋቃን። እረኛው የሆነ መላ አምጣ ከማለት ይልቅ ተኩላውን አትጨክንብን ማለት ይሻላል። እረ መላ ፍጠር ተው..ተው...ተው !!

ታክሲ ውስጥ ነሺዳ ተከፍቷል... ሹፌሩ ሙስሊም ነው፤ ረዳቱ ክርስቲያን... አንገቱ ላይ ታክሲው በተንቀሳቀሰ ቁጥር ወደፊት ወደኃላ የምትጫወት መስቀል አድርጓል... "የአፍጥር ሰአት እየደረሰ ነው አንድ ቢያጆ ሄደን ገብተህ ታፈጥራለህ" አለው... "አንተ የታባህ ልትሄድ ነው? የመጨረሻ ቀን ነው እኮ አብረን እናፈጥራለን" ዘመዶቼ... ልብሱን እንደለበሰ ያበደ ሰው ያለው እዚህ ነው... መሬት ላይ ያለው ህዝብ እንደወትሮው እየኖረ ነው... እንደውም ሙስሊምና ክርስቲያኑ በጥርጣሬ መተያየት የጀመረው ኢቲቪ የሃይማኖት መቻቻል በሚል ቃል አጅቦ የሙስሊም ቆብ ያደረገ ህፃን ከሆነ ሌላ ህፃን ጋር አስተቃቅፎ ማሳየት ከጀመረ በኃላ ነው... ኢድ ሙባረክ ኢትዮጵያውያን 💛!! @Etsegenet Kebede

Hope is a good thing, may be the best of the things. And good thing never dies. @ThomB23

Dear ችግር, please give me a discount, I am your ቋሚ ደንበኛ

ከአርተር ሾፐንሐወር ፍልስናዎች በጥቂቱ እንጋብዛችሁ... ( አርተር ሾፐንሐወር ሥለ ሰው ልጅ የፍላጎቱ ሎሌነት እና ሥለ ጥበብ በሰጠው ትንታኔ እንዲሁም የ #ኒርቫና እሳቤ አድናቂ እንደነበር በሱ ዙርያ የተፃፉ ጽሑፎች ያስነብቡናል ) ፨ ከሚታወቁ እና ከሚደነቁለት የሱ እሳቤዎች ጥቂቶቹን ጀባ እንበላችሁ... ፩, " አጭር በሆነችው ሕይወት ውስጥ እውነት ረዥም ዕድሜና ተግባር አላት፤ ስለዚህም እውነትን ብቻ እንናገር " ፧ ፪, " ይኽ ዓለም የእኔ(የእኛ) ሀሳብ ነው። ከእኛ ውጪ ያለው ማንኛውም ነገር ሁሉ መኖሩን የምናውቀው በስሜት ሕዋሳታችንና በሐሳባችን ውስጥ በተላለፈልን መልዕክት ብቻ ነው። " ፧ ፫, " አንድን ቁስ አካል ከውጭ በምናየው ነገር ላይ ተመስርተን የተፈጥሮውን እውነታ አውቀነዋል ብንል ራሳችንን እንደማሞኘት ነው። ደረስንበት የምንለው እውነታም ከምስል እና ስም ያለፈ ነገር የለውም። በአጭሩ ነገሮችን ከውጭ ባለው ገጽታቸው በዓይናችን ስለተመለከትናቸው ወይም በእጃችን ስለነካናቸው አወቅናቸው የሚል ድፍረት ባይወጣንስ? " ፧ ፬, " አብዛኛው የሰው ልጅ በብዙ ፍላጎትና በጥቂት እውቀት የተሞላ ነው፤ አዋቂነት ግን ብዙ እውቀት እና ጥቂት ፍላጎት ብቻ ይበቃታል።" ፧ ፭, " እብደት የሚመጣው የስቃይን ትዝታ ለመርሳት በሚደረግ ሂደት ነው፤...ፍርሃቶቻችንን እና ልማዶቻችንን መቋቋም የምንችለው በመርሳት ብቻ መሆኑ ተረጋግጧል፤ ለመርሳት ደግሞ የተሻለው መንገድ እብደት ነው። ካላበድክ ክፉውን ነገር መርሳት የምትችለው ራስህን በመግደል ብቻ ነው። " ፧ ፮, "ብዙውን ጊዜ ከጥበብ የራቁ ሰዎች ምሉዕነት የሚመጣው ከገንዘብ ይመስላቸዋል። ሁሉም ነገር የተሟላለት ሰው ጥበብ ከጎደለችው እንደሱ መከራን የሚቀበል ሰው ያለ አይመስለኝም። የሕይወት መንገድ ሀብት ሳትሆን ጥበብ ነች። " ፧ ፯, " ...ፍላጎቶቻችንን ይበልጥ ባወቅናቸው ቁጥር እኛን የመቆጣጠር ብቃታቸውም እንዲሁ ይደክማል፤ ዓለምን ማሸነፍ ከውስጣዊ ማንነት ይጀምራል የምንለውም ይህንኑ እውነታ ለማሳየት ነው። " ፧ ፰," የብዙዎቹ ምሁራን ችግር የራሳቸው የአስተሳሰብ ድህነት የሚፈጥረው ነው፤ ይኽ ድህነት ደግሞ የሚመጣው የራስን ሀሳብ ጥሎ የሌሎችን ሐሳብ ለመረዳት ከሚደረግ መፍጨርጨር ይሆናል። ስለአንድ ነገር በራሳችን አእምሮ አስበን ሳይሆን ከመጽሐፍት ላይ በማንበብ እንዲገባን ለማድረግ ስንሞክር ሌላው ሰው ስለነገሩ እንዲያስብልን እንደማድረግ ሆኖ ይቆጠራል፤ በዚህም ሂደት የእሱን ሐሳብ በእኛ አዕምሮ እየደገምነው እንገኛለን ማለት ነው።..." ፧ ፱, " አንድ ሰው በማንኛውም መንገድ ለሌላው መስሎ የሚታየው ወይም ለመምሰል የሚሞክረው ነገር ሁሉ እሱ ቁምነገር አይደለም፤ማንኛችንም ብንሆን ለብቻችን ቆመን የምንታይበት ጊዜ ይመጣል፤ ጥያቄው ግን በዚያ ጊዜ ብቻውን ብቻውን ለመቆም ብቃት የሚኖረው ማን ነው? የሚለው ይሆናል። ደስታ ማለት ከራሳችን የምናገኘው እንጂ ከሌሎች የምንቀበለው አይደለም፤ የሰውን ልጅ አእምሮ የሚቀርፀውም ዓለም ሳይሆን ነገር ግን እሱ ዓለምን የሚመለከትበት ዓይን ነው። ስለዚህም በዓለም ላይ የሚኖረውና የሚሆነው ነገር ሁሉ በሰው አእምሮ ቅድሚያ የሚሆን ከሆነ እጅግ አስፈላጊው ነገር የአእምሮ እሳቤ ደረጃን በማሳደግ ይሆናል ማለት ነው። " ፧ ፲, " ያልገባህን እና ያልተረዳህውን ነገር ለማድነቅም ሆነ ለመተቸት አትቸኩል፤ ስራህን ካልተረዳ ሰው የሚሰነዘር አድናቆት ከስድብ አይሻልም። አንድ ዘፋኝ ለደንቆሮዎች በመድረክ ላይ ሲዘፍን ቆይቶ ሲወርድ ቢያጨበጭቡለት ሰደቡት እንጂ አደነቁት አይባልም። አንተም ያልተረዳህውን ነገር ስታደንቅም ሆነ ስትተች ትርጉሙ ይህ ነው። " ምንጭ ፦ " ጥበብ ከጲላጦስ " እንዲሁም "የፍልስፍና መንግድ "መጽሐፍት...

photo content

<< አዎንታዊ አመለካከት ያላቸው ሰዎች ለእያንዳንዱ ችግር መፍትሔ አላቸው። አሉታዊ አመለካከት ያላቸው ሰዎች ደግሞ ለእያንዳንዱ መፍትሔ ችግሮች አሏቸው። አሉታዊ አመለካከት ካለቸው ሰዎች ራ
<< አዎንታዊ አመለካከት ያላቸው ሰዎች ለእያንዳንዱ ችግር መፍትሔ አላቸው። አሉታዊ አመለካከት ያላቸው ሰዎች ደግሞ ለእያንዳንዱ መፍትሔ ችግሮች አሏቸው። አሉታዊ አመለካከት ካለቸው ሰዎች ራቁ። >> / አልበርት አንስታይን /

ሲርበን መንቆለጳጰስ ወይም ቁልምጫ አይደለም የምንፈልገው...ምግብ እንጂ! ሲጠማን ስለ ውሃ ጥቅም እንዲነገረን አይደለም የምንፈልገው...ውሃውን እንጂ! ሲያመን እኔን : እኔን የሚለን አይደለም የምንፈልገው...ህክምና እንጂ! …. መንግስታችን ደሞ ሲርበን በቁልምጫ : ሲጠማን በሆይሆይታ : ሲርበን ደሞ በትት ግትት ማዛጉን ቀጥሏል ... የመኖርያ ቤትን ችግር ለማቃለል ለ3ወር ብትት ግትት ስላልክ መፍትሄ አይሆንም... አረ ወደገደለው እየገባን...ከወሬው ወደ መፍትሄው እንደማለት...!! ✍🏾@JamesB23

ልክ 12ኛ ክፍልን እንደጨረስኩ እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ Engineering ደርሶኝ University ገባሁ(እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ ማለቴ እዚህ እኛ አገር ከሆነ ጊዜ ጀምሮ ተማሪው እንዳለ ወይaccountant ወይ ደሞ ከaccounting የተረፈው Engineer ይሆናል)...University ከገባሁ በኋላ እዛው University ካገኘኋቸው ጓዶች ጋር ምን አይነት Department መምረጥ እንዳለብን የባጥ የቆጡን ቀበጣጥረን ሁላችንንም ያስማማ አንድ ሃሳብ ላይ ደረስን... ሃሳቡም “በደንብ የሚያበላንን(በደንብ ብር የሚያስገኝልንን) field ለመምረጥ ወሰንን...(i hope አብዛኛው ማለት በሚያስደፍር ሁኔታ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚማር የuniversity ተማሪ የሚማርበትን department ስለሚወደው ሳይሆን ቶሎ ስራ የሚያስገኝ እና ቆንጆ ክፍያ ያለውን በማሰብ ነው የሚመርጠው...ልክ እንደሰው ሁሉ እኛም እንዲያ አደረግን፥የምንወደውን ሳይሆን የሚያበላንን ለለመምረጥ ወሰንን...። የሆነ የጀለስ ብራዘር Civil ተመርቆ በ2አመት የራሱ ቤትና መኪና አለው እና Civil ይሻላል "አለ አንዱ:እሱም civil engineer ሆኖ ቤትና መኪና በአጭር ጊዜ ሲያገኝ በምናቡ እየታየው። ሌላኛው ቀጠለ "እረ ባክክህ እኛ ሰፈር አንዱ ጎረቤቴ በCivil ከተመረቀ 3አመቱ ነው : ስራ የሚባል ወፍ፣ እንዲሁ ሰፈር ላይ ተጎልታ ነው የምትለው : ይልቅስ water resource💦 and irrigation በሚባል ፊልድ የተመረቀ የሆነ ጀለስ NGO ገብቶ የሌለ ልጥጥ ሆኗል : በዛ ላይ ፊልዱን ብዙ ሰው አያውቀውም...Bill gates በሆነ interview ላይ አለም ላይ 90% የተሳካላቸው(Successful) የሆኑ ሰዎች በአብዛኛው ሪስክ ቴከር(risk taker) የሆኑ ሰዎች ናቸው " ሲል ሰምቸዋለሁ ብሎ: በማናቀው ዲስኩር ተደስኩረን:ዲስኩሩም ሚዛን ደፍቶ ሰምተነው ወደማናቀው Field የመጀመሪያ ምርጫ አርገነው join አርግን። እንደምንም ተማረንም ተምረንም :ተንዘላዝለንም :ቅመንም:አጭሰንም:ቦርክከንም:ፈርከንም:ተጣብሰንም:በግ ተራም ከስነንም(ስመንም):በድ**ንም፣የብሔር ቦለቲካ ባመጣው መዘዝም ብዙ ጊዜ ሎከር ውስጥ ተደብቀንም:ካፌ ደግመንም ......ብዙ ብዙ ነገር አልፈን እንደምንም አንደማንም ተመረቅን። Reality Vs Expectation ተጋጩልሃ አባቴ...CVያችንን ይዘን በጥላሁን ገሰሰ "ፈልጌ አስፈልጌ" ዘፈን በውስጣችን እያፏጨን : መጀመሪያ በላዳ:ከዛ በTaxi : ከዛ በባስ : ከዛ በባቡር የአዲሳባን ቢሮ በCV ከዳር እስከ ዳር ሞላነው...ከዛማ ብንጠብቅ ብንጠብቅ ስራ የምትባል ወፍ የለችም.... "90% አለም ላይ risk take የሚያረጉ ሰዎች successful ናቸው“ የምትለዋ አባባል ትውስ አለችኝ...ይሄ ሽማግሌ ድሮውንም የአሜሪካዊ አባባል ለኢትዮጵያ አይጠቅምም እያልኩ እየተሳደብኩ : ጓደኛዬንም "አንተን ብሎ አባባል አዋቂ እያልኩ እያማረርኩ : አንተም ብሎ Risk ወሳጅ "እያልኩ እራሴንም እየሰደብኩ....ነፍ ብር ያስገኝልናል ያልነውን ብንማርም ነፍ አበሳ እና ችግር የማያስገኝ ሆኖ ጠበቀን... ኢትዮጵያ ብሎ አገር ደሞ እያልን እያማረርን : በለስ ሲቀናን መላ ሲገኝ ኢትዮጵያ በሚል music club ላይ በስካር ጠምብዘን እየዘለልን...አንዳንዴ እያማረርን :አንዳንዴ ቦለቲካውን እየተነተንን:አንዳዴ እየቆዘምን:በብዙ እየተኛን… ህይወት ቀጥሏል ...ምስጋና ለቸሩ መንግስታችን ይሁንና በCivil የተመረቀም : architect የሆነውም፣ eleኩም(Elec Eng) : ሜኩም(mechanical eng) : ሌላውም ሌላውም እግዚኣብሄር ይመስገን ሁሉም ስራ አሊያዙም..... ደስ ሲል በሰው ስራ አለመያዝ መደሰት...አንደዛ አደል ነገሩ እኛ ጋ..በግል መውደቅን እንጂ አብሮ መውደቅ ብዙ ጊዜ መውደቅ አይመስለንም አይደል... ስለዚህ ምን ይኹን.. almost everything we do is importing...while we are producing thousands of engineering graduates each year .....so እድገትን ከፈለግን I think either we need to be creative like usa, Germany, japan or we need to be adaptive/ጥሩ ኮራጅ መሆን which is reverse engineering መጠቀም like china, india or we have to use natural resources properly like the middle east.... እና specially in engineering ሀኒቨርስቲ ውስጥ we need to learn more skills, We have to learn how things work by reverse engineering....and more about enterprnurship marketing & communication, ካልሆነ ግን ወይ ደህና አርገን አልኮረጅን ወይም ደሞ የፈጠራ ችሎታችን አላሳድገን እንዲሁ በሆነው ባልሆነው ጊዜያችንን እየፈጀን መኖራችንን መቀጠል ነው...። የሆነው ሆኖ ልክ እንደ እኛ ግቢ ገብታችሁ ተመርቀን ቆንጆ ህይወት እንኖራለን ያላችሁ፣ነገር ግን እንደ እድል ሆኖ ያሰባችሁት ነገር መሬት ካለው ተፃሮ ላገኛችሁት...ህይወት መራር ብቶንም : የህይወት ጣእሙም struggle ማረጉ ነውና Don’t give Up : ሁሉም ጥሩ ይሆናል ብላችሁ መበርታት ነው....በራሳችሁ በት በት ካላችሁ ጥሩ ነገር ታገኛላችሁ...don’t wait for luck...we do the same and know we have gud things …And pray 🙏 …