መፅሀፍ ቅዱስ
رفتن به کانال در Telegram
17 እንግዲያስ እምነት ከመስማት ነው መስማትም በእግዚአብሔር ቃል ነው። ወደ ሮሜ ሰዎች 10 :17 " ነገር ግን ለዚህ ዓለም ከሚመችና የአሮጊቶችን ሴቶች ጨዋታ ከሚመስለው ተረት ራቅ። እግዚአብሔርን ለመምሰል ግን ራስህን አስለምድ።" (1ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 4:7) @Bible_only https://t.me/Bible_only
نمایش بیشتر1 309
مشترکین
-124 ساعت
-47 روز
+1830 روز
آرشیو پست ها
1 308
“በእኔ ብትኖሩ ቃሎቼም በእናንተ ቢኖሩ የምትወዱትን ሁሉ ለምኑ ይሆንላችሁማል።”
— ዮሐንስ 15፥7
“If ye abide in me, and my words abide in you, ye shall ask what ye will, and it shall be done unto you.”
— John 15፥7 (KJV)
1 308
ዘኍልቁ 6
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁴ እግዚአብሔር ይባርክህ፥ ይጠብቅህም፤
²⁵ እግዚአብሔር ፊቱን ያብራልህ፥ ይራራልህም፤
²⁶ እግዚአብሔር ፊቱን ወደ አንተ ያንሣ፥ ሰላምንም ይስጥህ።
²⁷ እንዲሁ ስሜን በእስራኤል ልጆች ላይ ያደርጋሉ፤ እኔም እባርካቸዋለሁ።
Numbers 6 (KJV)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁴ The LORD bless thee, and keep thee:
²⁵ The LORD make his face shine upon thee, and be gracious unto thee:
²⁶ The LORD lift up his countenance upon thee, and give thee peace.
²⁷ And they shall put my name upon the children of Israel; and I will bless them.
1 308
“አለኝም፦ ተፈጽሞአል። አልፋና ዖሜጋ፥ መጀመሪያውና መጨረሻው እኔ ነኝ። ለተጠማ ከሕይወት ውኃ ምንጭ እንዲያው እኔ እሰጣለሁ።”
— ራእይ 21፥6
“And he said unto me, It is done. I am Alpha and Omega, the beginning and the end. I will give unto him that is athirst of the fountain of the water of life freely.”
— Revelation 21፥6
1 308
“ተቆጡ ኃጢአትንም አታድርጉ፤”
— ኤፌሶን 4፥26
“Be ye angry, and sin not: let not the sun go down upon your wrath:”
— Ephesians 4፥26 (KJV)
1 308
“የመስቀሉ ቃል ለሚጠፉት ሞኝነት፥ ለእኛ ለምንድን ግን የእግዚአብሔር ኃይል ነውና።”
— 1ኛ ቆሮንቶስ 1፥18
“For the preaching of the cross is to them that perish foolishness; but unto us which are saved it is the power of God.”
— 1 Corinthians 1፥18 (KJV)
1 308
ማቴዎስ 15
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁷ እናንተ ግብዞች፥ ኢሳይያስ ስለ እናንተ፦
⁸ ይህ ሕዝብ በከንፈሩ ያከብረኛል፥ ልቡ ግን ከእኔ በጣም የራቀ ነው፤
⁹ የሰውም ሥርዓት የሆነ ትምህርት እያስተማሩ በከንቱ ያመልኩኛል ብሎ በእውነት ትንቢት ተናገረ።
Matthew 15 (KJV)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁷ Ye hypocrites, well did Esaias prophesy of you, saying,
⁸ This people draweth nigh unto me with their mouth, and honoureth me with their lips; but their heart is far from me.
⁹ But in vain they do worship me, teaching for doctrines the commandments of men.
1 308
ማቴዎስ 11
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²¹ ወዮልሽ ኮራዚ፤ ወዮልሽ ቤተ ሳይዳ፤ በእናንተ የተደረገው ተአምራት በጢሮስና በሲዶና ተደርጎ ቢሆን፥ ማቅ ለብሰው አመድም ነስንሰው ከብዙ ጊዜ በፊት ንስሐ በገቡ ነበርና።
²² ነገር ግን እላችኋለሁ፥ በፍርድ ቀን ከእናንተ ይልቅ ለጢሮስና ለሲዶና ይቀልላቸዋል።
²³ አንቺም ቅፍርናሆም፥ እስከ ሰማይ ከፍ አልሽን? ወደ ሲኦል ትወርጃለሽ፤ በአንቺ የተደረገው ተአምራት በሰዶም ተደርጎ ቢሆን፥ እስከ ዛሬ በኖረች ነበርና።
²⁴ ነገር ግን እላችኋለሁ፥ በፍርድ ቀን ከአንቺ ይልቅ ለሰዶም አገር ይቀልላታል።
Matthew 11 (KJV)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²¹ Woe unto thee, Chorazin! woe unto thee, Bethsaida! for if the mighty works, which were done in you, had been done in Tyre and Sidon, they would have repented long ago in sackcloth and ashes.
²² But I say unto you, It shall be more tolerable for Tyre and Sidon at the day of judgment, than for you.
²³ And thou, Capernaum, which art exalted unto heaven, shalt be brought down to hell: for if the mighty works, which have been done in thee, had been done in Sodom, it would have remained until this day.
²⁴ But I say unto you, That it shall be more tolerable for the land of Sodom in the day of judgment, than for thee.
1 308
ማቴዎስ 6
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁵ ስለዚህ እላችኋለሁ፥ ስለ ነፍሳችሁ በምትበሉትና በምትጠጡት፥ ወይም ስለ ሰውነታችሁ በምትለብሱት አትጨነቁ፤ ነፍስ ከመብል ሰውነትም ከልብስ አይበልጥምን?
²⁶ ወደ ሰማይ ወፎች ተመልከቱ፤ አይዘሩም አያጭዱምም በጎተራም አይከቱም፥ የሰማዩ አባታችሁም ይመግባቸዋል፤ እናንተ ከእነርሱ እጅግ አትበልጡምን?
²⁷ ከእናንተ ተጨንቆ በቁመቱ ላይ አንድ ክንድ መጨመር የሚችል ማን ነው?
²⁸ ስለ ልብስስ ስለ ምን ትጨነቃላችሁ? የሜዳ አበቦች እንዴት እንዲያድጉ ልብ አድርጋችሁ ተመልከቱ፤
²⁹ አይደክሙም አይፈትሉምም፤ ነገር ግን እላችኋለሁ፥ ሰሎሞንስ እንኳ በክብሩ ሁሉ ከነዚህ እንደ አንዱ አልለበሰም።
³⁰ እግዚአብሔር ግን ዛሬ ያለውን ነገም ወደ እቶን የሚጣለውን የሜዳን ሣር እንዲህ የሚያለብሰው ከሆነ፥ እናንተ እምነት የጎደላችሁ፥ እናንተንማ ይልቁን እንዴት?
³¹ እንግዲህ፦ ምን እንበላለን? ምንስ እንጠጣለን? ምንስ እንለብሳለን? ብላችሁ አትጨነቁ፤
³² ይህንስ ሁሉ አሕዛብ ይፈልጋሉ፤ ይህ ሁሉ እንዲያስፈልጋችሁ የሰማዩ አባታችሁ ያውቃልና።
³³ ነገር ግን አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ፥ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል።
³⁴ ነገ ለራሱ ይጨነቃልና ለነገ አትጨነቁ፤ ለቀኑ ክፋቱ ይበቃዋል።
Matthew 6
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁵ Therefore I say unto you, Take no thought for your life, what ye shall eat, or what ye shall drink; nor yet for your body, what ye shall put on. Is not the life more than meat, and the body than raiment?
²⁶ Behold the fowls of the air: for they sow not, neither do they reap, nor gather into barns; yet your heavenly Father feedeth them. Are ye not much better than they?
²⁷ Which of you by taking thought can add one cubit unto his stature?
²⁸ And why take ye thought for raiment? Consider the lilies of the field, how they grow; they toil not, neither do they spin:
²⁹ And yet I say unto you, That even Solomon in all his glory was not arrayed like one of these.
³⁰ Wherefore, if God so clothe the grass of the field, which to day is, and to morrow is cast into the oven, shall he not much more clothe you, O ye of little faith?
³¹ Therefore take no thought, saying, What shall we eat? or, What shall we drink? or, Wherewithal shall we be clothed?
³² (For after all these things do the Gentiles seek:) for your heavenly Father knoweth that ye have need of all these things.
³³ But seek ye first the kingdom of God, and his righteousness; and all these things shall be added unto you.
³⁴ Take therefore no thought for the morrow: for the morrow shall take thought for the things of itself. Sufficient unto the day is the evil thereof.
1 308
ማርቆስ 8
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³⁴ ሕዝቡንም ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ጠርቶ እንዲህ አላቸው፦ በኋላዬ ሊመጣ የሚወድ ቢኖር፥ ራሱን ይካድ መስቀሉንም ተሸክሞ ይከተለኝ።
³⁵ ነፍሱን ሊያድን የሚወድ ሁሉ ያጠፋታልና፥ ስለ እኔና ስለ ወንጌል ነፍሱን የሚያጠፋ ሁሉ ግን ያድናታል።
³⁶ ሰው ዓለምን ሁሉ ቢያተርፍ ነፍሱንም ቢያጐድል ምን ይጠቅመዋል?
³⁷ ሰውስ ስለ ነፍሱ ቤዛ ምን ይሰጣል?
³⁸ በዚህም በዘማዊና በኃጢአተኛ ትውልድ መካከል በእኔና በቃሌ የሚያፍር ሁሉ፥ የሰው ልጅ ደግሞ በአባቱ ክብር ከቅዱሳን መላእክት ጋር በመጣ ጊዜ በእርሱ ያፍርበታል።
Mark 8 (KJV)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³⁴ And when he had called the people unto him with his disciples also, he said unto them, Whosoever will come after me, let him deny himself, and take up his cross, and follow me.
³⁵ For whosoever will save his life shall lose it; but whosoever shall lose his life for my sake and the gospel's, the same shall save it.
³⁶ For what shall it profit a man, if he shall gain the whole world, and lose his own soul?
³⁷ Or what shall a man give in exchange for his soul?
³⁸ Whosoever therefore shall be ashamed of me and of my words in this adulterous and sinful generation; of him also shall the Son of man be ashamed, when he cometh in the glory of his Father with the holy angels.
1 308
“እርሱም የሰጠን ተስፋ ይህ የዘላለም ሕይወት ነው።”
— 1ኛ ዮሐንስ 2፥25
“And this is the promise that he hath promised us, even eternal life.”
— 1 John 2፥25 (KJV)
1 308
1ኛ ጴጥሮስ 5
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁶ እንግዲህ በጊዜው ከፍ እንዲያደርጋችሁ ከኃይለኛው ከእግዚአብሔር እጅ በታች ራሳችሁን አዋርዱ፤
⁷ እርሱ ስለ እናንተ ያስባልና የሚያስጨንቃችሁን ሁሉ በእርሱ ላይ ጣሉት።
1 Peter 5 (KJV)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁶ Humble yourselves therefore under the mighty hand of God, that he may exalt you in due time:
⁷ Casting all your care upon him; for he careth for you.
1 308
(የዮሐንስ ራእይ ምዕ. 1)
----------
4-5፤ ዮሐንስ በእስያ ላሉት ለሰባቱ አብያተ ክርስቲያናት፤ ካለውና ከነበረው ከሚመጣውም፥ በዙፋኑም ፊት ካሉት ከሰባቱ መናፍስት፥ ከታመነውም ምስክር ከሙታንም በኵር የምድርም ነገሥታት ገዥ ከሆነ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን። ለወደደን ከኃጢአታችንም በደሙ ላጠበን፥
6፤ መንግሥትም ለአምላኩና ለአባቱም ካህናት እንድንሆን ላደረገ፥ ለእርሱ ከዘላለም እስከ ዘላለም ድረስ ክብርና ኃይል ይሁን፤ አሜን።
7፤ እነሆ፥ ከደመና ጋር ይመጣል፤ ዓይንም ሁሉ የወጉትም ያዩታል፥ የምድርም ወገኖች ሁሉ ስለ እርሱ ዋይ ዋይ ይላሉ። አዎን፥ አሜን።
8፤ ያለውና የነበረው የሚመጣውም ሁሉንም የሚገዛ ጌታ አምላክ። አልፋና ዖሜጋ እኔ ነኝ ይላል።
(Revelation Chap. 1)
----------
4 John to the seven churches which are in Asia: Grace to you and peace, from him who is and was and is to come; and from the seven Spirits which are before his high seat;
5 And from Jesus Christ, the true witness, the first to come back from the dead, and the ruler of the kings of the earth. To him who had love for us and has made us clean from our sins by his blood;
6 And has made us to be a kingdom and priests to his God and Father; to him let glory and power be given for ever and ever. So be it.
7 See, he comes with the clouds, and every eye will see him, and those by whom he was wounded; and all the tribes of the earth will be sorrowing because of him. Yes, so be it.
8 I am the First and the Last, says the Lord God who is and was and is to come, the Ruler of all.
1 308
" ያቤጽም። እባክህ፥ መባረክን ባርከኝ፥ አገሬንም አስፋው፤ እጅህም ከእኔ ጋር ትሁን፤ እንዳያሳዝነኝም ከክፋት ጠብቀኝ ብሎ የእስራኤልን አምላክ ጠራ፤ እግዚአብሔርም የለመነውን ሰጠው። "
(መጽሐፈ ዜና መዋዕል ቀዳማዊ 4:10)
"10 And Jabez made a prayer to the God of Israel, saying, If only you would truly give me a blessing, and make wider the limits of my land, and let your hand be with me, and keep me from evil, so that I may not be troubled by it! And God gave him his desire."
(1 Chronicles 4:10)
1 308
(አማርኛ 1954)“እግዚአብሔር መልካም ነው፥ በመከራ ቀንም መሸሸጊያ ነው፤ በእርሱ የሚታመኑትንም ያውቃል።”
— ናሆም 1፥7
(KJV)“The LORD is good, a strong hold in the day of trouble; and he knoweth them that trust in him.”
— Nahum 1፥7 (KJV)
1 308
(አማርኛ 1954)“ባለጠጎች ደኸዩ፥ ተራቡም፥ እግዚአብሔርን የሚፈልጉት ግን ከመልካም ነገር ሁሉ አይጐድሉም።”
— መዝሙር 34፥10
(KJV)“The young lions do lack, and suffer hunger: but they that seek the LORD shall not want any good thing.”
— Psalms 34፥10 (KJV)
1 308
(አማርኛ 1954)“የእግዚአብሔር ስም የጸና ግምብ ነው፤ ጻድቅ ወደ እርሱ ሮጦ ከፍ ከፍ ይላል።”
— ምሳሌ 18፥10
(KJV)“The name of the LORD is a strong tower: the righteous runneth into it, and is safe.”
— Proverbs 18፥10 (KJV)
1 308
1ኛ ጴጥሮስ 4
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹-² ክርስቶስም በሥጋ ስለ እኛ መከራን ስለተቀበለ፥ ከእንግዲህ ወዲህ በሥጋ ልትኖሩ በቀረላችሁ ዘመን እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ እንጂ እንደ ሰው ምኞት እንዳትኖሩ፥ እናንተ ደግሞ ያን አሳብ እንደ ዕቃ ጦር አድርጋችሁ ያዙት፥ በሥጋ መከራን የተቀበለ ኃጢአትን ትቶአልና።
³ የአሕዛብን ፈቃድ ያደረጋችሁበት በመዳራትና በሥጋ ምኞትም በስካርም በዘፈንም ያለ ልክም በመጠጣት ነውርም ባለበት በጣዖት ማምለክ የተመላለሳችሁበት ያለፈው ዘመን ይበቃልና።
⁴ በዚህም ነገር ወደዚያ መዳራት ብዛት ከእነርሱ ጋር ስለማትሮጡ እየተሳደቡ ይደነቃሉ፤
⁵ ግን እነርሱ በሕያዋንና በሙታን ላይ ሊፈርድ ለተዘጋጀው መልስ ይሰጣሉ።
⁶ እንደ ሰዎች በሥጋ እንዲፈረድባቸው በመንፈስ ግን እንደ እግዚአብሔር እንዲኖሩ ስለዚህ ምክንያት ወንጌል ለሙታን ደግሞ ተሰብኮላቸው ነበርና።
⁷ ዳሩ ግን የነገር ሁሉ መጨረሻ ቀርቦአል። እንግዲህ እንደ ባለ አእምሮ አስቡ፥
⁸ ትጸልዩም ዘንድ በመጠን ኑሩ፤ ፍቅር የኃጢአትን ብዛት ይሸፍናልና ከሁሉ በፊት እርስ በርሳችሁ አጥብቃችሁ ተዋደዱ።
1 Peter 4
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ Forasmuch then as Christ hath suffered for us in the flesh, arm yourselves likewise with the same mind: for he that hath suffered in the flesh hath ceased from sin;
² That he no longer should live the rest of his time in the flesh to the lusts of men, but to the will of God.
³ For the time past of our life may suffice us to have wrought the will of the Gentiles, when we walked in lasciviousness, lusts, excess of wine, revellings, banquetings, and abominable idolatries:
⁴ Wherein they think it strange that ye run not with them to the same excess of riot, speaking evil of you:
⁵ Who shall give account to him that is ready to judge the quick and the dead.
⁶ For for this cause was the gospel preached also to them that are dead, that they might be judged according to men in the flesh, but live according to God in the spirit.
⁷ But the end of all things is at hand: be ye therefore sober, and watch unto prayer.
⁸ And above all things have fervent charity among yourselves: for charity shall cover the multitude of sins.
1 308
ሉቃስ 24
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
² ድንጋዩንም ከመቃብሩ ተንከባሎ አገኙት፥
³ ገብተውም የጌታን የኢየሱስን ሥጋ አላገኙም።
⁴ እነርሱም በዚህ ሲያመነቱ፥ እነሆ፥ ሁለት ሰዎች የሚያንጸባርቅ ልብስ ለብሰው ወደ እነርሱ ቀረቡ፤
⁵ ፈርተውም ፊታቸውን ወደ ምድር አቀርቅረው ሳሉ፥ እንዲህ አሉአቸው፦ ሕያውን ከሙታን መካከል ስለ ምን ትፈልጋላችሁ? ተነሥቶአል እንጂ በዚህ የለም።
⁶-⁷ የሰው ልጅ በኃጢአተኞች እጅ አልፎ ሊሰጥና ሊሰቀል በሦስተኛውም ቀን ሊነሣ ግድ ነው እያለ ገና በገሊላ ሳለ ለእናንተ እንደ ተናገረ አስቡ።
⁸-⁹ ቃሎቹንም አሰቡ፥ ከመቃብሩም ተመልሰው ይህን ሁሉ ለአሥራ አንዱና ለሌሎች ሁሉ ነገሩአቸው።
Luke 24 (KJV)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
² And they found the stone rolled away from the sepulchre.
³ And they entered in, and found not the body of the Lord Jesus.
⁴ And it came to pass, as they were much perplexed thereabout, behold, two men stood by them in shining garments:
⁵ And as they were afraid, and bowed down their faces to the earth, they said unto them, Why seek ye the living among the dead?
⁶ He is not here, but is risen: remember how he spake unto you when he was yet in Galilee,
⁷ Saying, The Son of man must be delivered into the hands of sinful men, and be crucified, and the third day rise again.
⁸ And they remembered his words,
⁹ And returned from the sepulchre, and told all these things unto the eleven, and to all the rest.
1 308
“የመስቀሉ ቃል ለሚጠፉት ሞኝነት፥ ለእኛ ለምንድን ግን የእግዚአብሔር ኃይል ነውና።”
— 1ኛ ቆሮንቶስ 1፥18
“For the preaching of the cross is to them that perish foolishness; but unto us which are saved it is the power of God.”
— 1 Corinthians 1፥18 (KJV)
1 308
ኢሳይያስ 53
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ የሰማነውን ነገር ማን አምኖአል? የእግዚአብሔርስ ክንድ ለማን ተገልጦአል?
² በፊቱ እንደ ቡቃያ ከደረቅም መሬት እንደ ሥር አድጎአል፤ መልክና ውበት የለውም፥ ባየነውም ጊዜ እንወድደው ዘንድ ደም ግባት የለውም።
³ የተናቀ ከሰውም የተጠላ፥ የሕማም ሰው ደዌንም የሚያውቅ ነው፤ ሰውም ፊቱን እንደሚሰውርበት የተናቀ ነው፥ እኛም አላከበርነውም።
⁴ በእውነት ደዌያችንን ተቀበለ ሕመማችንንም ተሸክሞአል፤ እኛ ግን እንደ ተመታ በእግዚአብሔርም እንደ ተቀሠፈ እንደ ተቸገረም ቈጠርነው።
⁵ እርሱ ግን ስለ መተላለፋችን ቈሰለ፥ ስለ በደላችንም ደቀቀ፤ የደኅንነታችንም ተግሣጽ በእርሱ ላይ ነበረ፥ በእርሱም ቍስል እኛ ተፈወስን።
⁶ እኛ ሁላችን እንደ በጎች ተቅበዝብዘን ጠፋን፤ ከእኛ እያንዳንዱ ወደ ገዛ መንገዱ አዘነበለ፤ እግዚአብሔርም የሁላችንን በደል በእርሱ ላይ አኖረ።
⁷ ተጨነቀ ተሣቀየም አፉንም አልከፈተም፤ ለመታረድ እንደሚነዳ ጠቦት፥ በሸላቶቹም ፊት ዝም እንደሚል በግ፥ እንዲሁ አፉን አልከፈተም።
⁸ በማስጨነቅና በፍርድ ተወሰደ፤ ስለ ሕዝቤ ኃጢአት ተመትቶ ከሕያዋን ምድር እንደ ተወገደ ከትውልዱ ማን አስተዋለ?
⁹ ከክፉዎችም ጋር መቃብሩን አደረጉ፥ ከባለጠጎችም ጋር በሞቱ፤ ሆኖም ግፍን አላደረገም ነበር፥ በአፉም ተንኮል አልተገኘበትም ነበር።
¹⁰ እግዚአብሔርም በደዌ ያደቅቀው ዘንድ ፈቀደ፤ ነፍሱን ስለ ኃጢአት መሥዋዕት ካደረገ በኋላ ዘሩን ያያል፥ ዕድሜውም ይረዝማል፥ የእግዚአብሔርም ፈቃድ በእጁ ይከናወናል።
¹¹ ከነፍሱ ድካም ብርሃን ያያል ደስም ይለዋል፤ ጻድቅ ባሪያዬም በእውቀቱ ብዙ ሰዎችን ያጸድቃል፥ ኃጢአታቸውን ይሸከማል።
¹² ስለዚህም እርሱ ብዙዎችን ይወርሳል፥ ከኃያላንም ጋር ምርኮን ይከፋፈላል፤ ነፍሱን ለሞት አሳልፎ ሰጥቶአልና፥ ከዓመፀኞችም ጋር ተቈጥሮአልና እርሱ ግን የብዙ ሰዎችን ኃጢአት ተሸከመ፥ ስለ ዓመፀኞችም ማለደ።
Isaiah 53 (KJV)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ Who hath believed our report? and to whom is the arm of the LORD revealed?
² For he shall grow up before him as a tender plant, and as a root out of a dry ground: he hath no form nor comeliness; and when we shall see him, there is no beauty that we should desire him.
³ He is despised and rejected of men; a man of sorrows, and acquainted with grief: and we hid as it were our faces from him; he was despised, and we esteemed him not.
⁴ Surely he hath borne our griefs, and carried our sorrows: yet we did esteem him stricken, smitten of God, and afflicted.
⁵ But he was wounded for our transgressions, he was bruised for our iniquities: the chastisement of our peace was upon him; and with his stripes we are healed.
⁶ All we like sheep have gone astray; we have turned every one to his own way; and the LORD hath laid on him the iniquity of us all.
⁷ He was oppressed, and he was afflicted, yet he opened not his mouth: he is brought as a lamb to the slaughter, and as a sheep before her shearers is dumb, so he openeth not his mouth.
⁸ He was taken from prison and from judgment: and who shall declare his generation? for he was cut off out of the land of the living: for the transgression of my people was he stricken.
⁹ And he made his grave with the wicked, and with the rich in his death; because he had done no violence, neither was any deceit in his mouth.
¹⁰ Yet it pleased the LORD to bruise him; he hath put him to grief: when thou shalt make his soul an offering for sin, he shall see his seed, he shall prolong his days, and the pleasure of the LORD shall prosper in his hand.
¹¹ He shall see of the travail of his soul, and shall be satisfied: by his knowledge shall my righteous servant justify many; for he shall bear their iniquities.
¹² Therefore will I divide him a portion with the great, and he shall divide the spoil with the strong; because he hath poured out his soul unto death: and he was numbered with the transgressors; and he bare the sin of many, and made intercession for the transgressors.
