በረከተ እስጢፋኖስ | Saint Stephen's blessings
رفتن به کانال در Telegram
نمایش بیشتر
8 431
مشترکین
-324 ساعت
-197 روز
-8030 روز
آرشیو پست ها
በደብረ ዘይት ሳምንት መጨረሻ ቆየት ያለ ስለ ጌታችን ምጽአት የተሰበከ አጭር ስብከት ተጋበዙልን!
የሚያስተምረን፣ የሚመክረን፣ የሚገሥጸን አምላካችን እግዚአብሔር ስሙ የተመሰገነ ይሁን።
በጳጕሜን ወር በመካነ ቅዱሳን አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያን በዲያቆን ዮሐንስ ደረጀ የተሰጠ ትምህርት ነው።
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
+2
+ ከመልካም ነገር አለማጣት +
...................................................
ብዙ ሰው ትልቅ ዋጋ የሚሰጠው ነገር እናንተ ጋር ስለሌለ ቆጭቷችሁ አያውቅም? እግዚአብሔርን ለምን አሳጣኸኝ ብላችሁ አማራችሁትስ አታውቁም?
ዓለም ሁሉ መልካም ነው ብላ የተስማማችበትን ሀብት እና ዝነኝነትን ስላላገኛችሁ ተናዳችሁ አታውቁም?
በተቃራኒው ደግሞ እነኚህ በዓለም ዋጋ የሚሰጣቸው ጉዳዮች ስላሏችሁ ኮርታችሁ ታውቃላችሁ? "እኔን እግዚአብሔር ከሌላው ሰው ይልቅ መልካም አድርጎልኛል" ብላችሁ አስባችሁስ ታውቃላችሁ?
እንግዲያውስ አንድ የሚያጽናና እና የሚያስጠነቅቅ ቃል ላስታውሳችሁ!
ቅዱስ ዳዊት እንዲህ ይላል:-
"እግዚአብሔር በቅንነት የሚሄዱትን ከመልካም ነገር ሁሉ አያሳጣቸውም"
- መዝ ፹፫ (፹፬) ፥ ፲፩
የምታደርገውን ነገር ሁሉ በቅንነት እስካደረከው ድረስ ላንተ መልካም የሆነን ነገር ሁሉ ልታጣው አትችልም። ደሃ ሆነህ፣ ብዙ ነገር ጎድሎህ ብትኖር፣ ነገር ግን ልብህ ቅን ከሆነ አጣሁት ብለህ የምታስበው ሀብት ላንተ መልካም አልነበረም ማለት ነው።
ምክንያቱም በቅንነት እየተጓዝክ ላንተ መልካም የሆነን ነገር እግዚአብሔር ሊያሳጣህ አይችልም።
በበሽታ እና በሕመም ብትሰቃይ፣ ልብህ ግን ቅን ከሆነ፣ ያጣኸው ጤና ላንተ መልካም ነገር አልነበረም ማለት ነው።
በድሎት እና ተድላ ደስታ እየኖርክ፣ መልካም ነገር ሆኖልኛል ብለህ እያሰብክ፣ ቅንነት ከሌለህ ደግሞ ያገኘኸው ሀብት መልካም እንደሆነ እርግጠኛ መሆን አትችልም።
በሀብት እና ዝና ተከበህ፣ ብዙ ሰው እየቀናብህ ብትኖር እንኳን ልብህ ቅን ካልሆነ ግን ያገኘኸው ባዕለጸግነት ብዙ ሰው መልካም ነው ብሎ ስለተስማማ መልካም ነው ብለህ ማረጋገጥም አትችልም።
የልባችንን ቅንነት እስካረጋገጥን ድረስ፣ ለእኛ ከራሳችን በላይ የሚያስብልን እግዚአብሔር የሚረባንን መልካም ነገር ሁሉ አያሳጣንም!
...................................
ዲያቆን ዮሐንስ ደረጀ
መጋቢት 09/2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
....................................
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
እምቢም እኮ መልስ ነው | "NO" is also an answer
.
.
ይህን ቪድዮ ተመልከቱት
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://vt.tiktok.com/ZSuQw6fcA/
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
እምቢም እኮ መልስ ነው! | "NO" is also an answer!
.
.
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
.
Follow and share our tiktok page!
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://vt.tiktok.com/ZSuQw6fcA/
+2
+ ይማርህ አይመራመርህ! +
..........................................
በነገራችን ላይ ሰው ሲያስነጥስ "ይማርህ" ብቻ አይባልም።
ከዕለታት በአንድ ቀን በጉንፋን እየተሰቃየሁ በኃይለኛው ሲያስነጥሰኝ አንዷ ወዳጄ እንደማንኛውም ሰው "ይማርህ" ብላ መረቀችኝ። "አሜን" ብዬ ስመልስላት "አይመራመርህ" ብላ ጨመረችልኝ።
ሰው ሲያስነጥስ "ይማርህ" የሚባለው የልብ ምቱ በሚያስነጥስበት ጊዜ ለቅጽበት ስለሚያቆም ነው። ይህች አስተዋይ እህቴ "አይመራመርህ" ብላ የጨመረችው ደግሞ እግዚአብሔር ኃጢአትህን አይመራመርህ፣ አይተሳሰብህ አይቁጠርብህ ማለቷ ነው።
እውነቷን ነው። እግዚአብሔር እያንዳንዷ ኃጢአታችንን ቢቆጥርብን፣ ቢመራመረን፣ ቢቆጣጠረን ምን እንሆን ነበር?
በጌታ ቅዳሴ ላይ ዲያቆኑ ብዙ አስፈሪ ልብን ቀጥ የሚያደርጉ ትእዛዛትን ሲያውጅ ሰምተነው ይሆናል።
ይ.ዲ:-
"የአሳብ ነውር ያለበት ቢኖር አይቅረብ!
"አሳቡ ድውይ የሆነ ቢኖር ይራቅ!
" ኃጢአትን የሚሠራ ንጹሕም ያልሆነ ቢኖር ይወገድ!
"በኃጢአት የወደቀ ቢኖር አይርሳ፣ የማይረሳ ነውና!
"ከኢየሱስ ትእዛዝ ልዩ የሆነ ቢኖር ይከልከል!!"
ደግነቱ ፈርተን እንዳንሸሽ ቤተ ክርስቲያን እዚያው በምንመልሰው ተሰጥዖ ታጽናናናለች እንጂ ይህን ሰምቶ ማን ይቆም ነበር?
ዲያቆኑ እንዲህ እያለ ሲያውጅ በሚታወጁት ሁሉ ኃጢአቶች ተዘፍቀን የምንኖረው እኛ እንዲህ ብለን እንመልሳለን።
"አቤቱ እንደ ቸርነትህ ነው እንጂ እንደ በደላችን አይሁን"
ወገኖቼ! የእግዚአብሔር ቸርነት ሆኖ እንጂ በየደቂቃው የምናስበው የኃጢአት ሀሳብ ነውራችን እኮ ወደ እግዚአብሔር ባላቀረበን ነበር።
እንደ ቸርነቱ ሆኖ እንጂ ንጹሕ ስላልሆንን፣ ኃጢአት ስለምንሰራ ብቻ መወገድ ነበረብን።
እግዚአብሔር ቸር ሆኖ ኃጢአታችንን ንስሐ ስንገባ ስለሚረሳልን እንጂ እንደ በደላችን ቢሆንማ ኃጢአት የሚረሳ እኮ አልነበረም።
እንደ በደላችን ቢሆንማ እንደ ዳታንና አቤሮን ምድር ተከፍታ ብትውጠን በተገባ ነበር። እንደ በደላችን ቢሆንማ የሰራነው ኃጢአት ሊያስቀስፈን በተገባ ነበር።
እንደ በደላችን ቢሆንማ እሳት ከሰማይ ወርዶ ቢበላን፣ ከምድረ ገጽ ብንጠፋ ለእኛ የተገባ ነገር ነበር።
እግዚአብሔር ግን ቸር፣ መሐሪ፣ ይቅር ባይ ስለሆነ፣ ምሕረቱ መዓቱን እየቀደመ ስለሆነ እንጂ አንዳችንም በሕይወት ባለኖርን ነበር።
የምንተነፍሰው፣ ተኝተን የምንነሳው፣ የምንበላው የምንጠጣው፣ ሁሉን ነገር የምናደርገው እንደ እግዚአብሔር ቸርነት እንጂ እንደ በደላችን ስላልሆነብን ነው። ዓለም እስከአሁን ያልጠፋችው "የእግዚአብሔር ቸርነት ምድርን ስለመላች" ነው። (መዝ ፴፪ (፴፫) ፥ ፭)
"አቤቱ ኃጢአትን ብትጠባበቅ በፊትህ ማን ይቆማል?"
መዝ ፻፳፱ ፥ ፫
እግዚአብሔር አምላክ ይማረን፣ አይመራመረን!!
.................................
ዲያቆን ዮሐንስ ደረጀ
መጋቢት 3/2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
...................................
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
ለረጅም ዓመታት ቤተ ክርስቲያንን ያለ ድካም ሲያገለግል የኖረ፣ በጊዜ ብዛት ያልተለወጠ፣ በቃልም በሕይወትም ያስተምር የነበረ መምህራችን ዘላለም ወንድሙን ዛሬ በክብር እንሰናበተዋለን። የስንብት መርኃ ግብሩም እንደሚከተለው ነው:-
1. በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቃውንት በመምህራነ ወንጌል በሰንበት ትምህርት ቤት ወጣት ዘማርያን እና በበርካታ ምእመናን ታጅቦ ከጠዋቱ 3:00 ጀምሮ እስከ 5:00 ሰዓት ድረስ መስቀል አደባባይ ይደረሳል።
2. ከጠዋቱ 5:00 ሰዓት ጀምሮ በመስቀል አደባባይ የተለያዩ የአሸኛኘት መርሐግብሮች የሚከናወኑ ሲሆን በዚህም ቦታ
ከጠዋቱ 5:00 – 8:00 ሰዓት ድረስ የተለያዩ ክንውኖች ይኖሩናሌ። እነዚህም:-
ከጠዋቱ 5:00 – 5:30 የመርሐ ግብር መክፈቻ እና ጸሎት
ከ5:30 እስከ 6:00 ያሬዳዊ ዝማሬ የዘማርያን ኅብረት ዝማሬ እና ቅኔ ይቀርባል ።
ከ6:00 – 6:15 የመምህር ዘለዓለም ወንድሙ የሕይወት ታሪክ በንባብ ይቀርባል ።
6:15 – 6:40 ከተለያዩ ተቋማት የሚቀርቡ የስንብት መልዕክቶች ይቀርባሉ ።
ከ6:40 – 7:00 ከቤተሰብ እና ከወዳጅ ዘመዶች ስለወንድማችን የሚቀርቡ ምሥክርነቶች በተለያዩ አካላት ይሰጣል።
ከ7:00 – 7:30 የወንጌል መርሐ ግብር ይካሄዳል ።
ከ7:30 – 7:40 በሰንበት ትምህርት ቤቶች እና በዘማርያን የጋራ ዝማሬ ይቀርባል።
ከ7:40 - 8:00 ቃለ ምእዳንና ቡራኬ በብፁዓን አባቶች ይሰጣል
ከቀኑ 8:00 ላይ የመስቀል አደባባዩ መርሐ ግብር ተጠቃሎ ጉዞ ወደ መንበረ ጸባኦት ቅድስት ስላሴ ጉዞ የሚያደርግ ሲሆን ከቀኑ 9:00 ላይ አጭር ጸሎት ተደርጎ ሥርዓተ ቀብሩ የሚፈጸም ይሆናል።
© የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ
+ የጸሎት አጣሪ ኮሚቴ +
+ A committee that filters prayers +
.
.
የበረከተ እስጢፋኖስን tiktok አካውንት follow share እና copy link በማድረግ አገልግሎቱን ይደግፉ!
👇👇👇👇👇👇👇👇
https://vt.tiktok.com/ZSuBA3t92/
+ የጸሎት አጣሪ ኮሚቴ +
+ A committee that filters prayers +
.
.
የበረከተ እስጢፋኖስን tiktok አካውንት follow share እና copy link በማድረግ አገልግሎቱን ይደግፉ!
https://vt.tiktok.com/ZSuBA3t92/
በቃለ እግዚአብሔር እና በጸሎት የንዑድ ክቡር ቀዳሜ ሰማዕት ወሊቀ ዲያቆናት ቅዱስ እስጢፋኖስን ነገ በዚሁ ቤት እንዘክራለን።
በረከተ እስጢፋኖስን አምላካችን ያድለን!
Repost from Deacon Yakob Dereje
+8
እንኳን ለታላቁ ዓቢይ ጾም በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን 🙏
የካቲት 8/2018ዓ.ም
አዲስ አበባ
@Dn_yakob
+2
+ "በርታ ልብህም ይጽና!" +
(መዝ 26 ፥ 14)
.................................................
ተወዳጅ ወንድሜ ሆይ፣ ልብህ የሚከፋበትና የምታዝንበት አንዳች ጉዳይ እንዳለ አውቃለሁ።
አምላክህ ፊት ዘወትር ስትቆም ዕንባህ የሚቀድምበት አንዳች የምታስጨንቅህ ነገርም እንዳለች አይጠፋኝም። የጸሎትህ መልስ እኔ ጋር አይደለምና እኔ ልልህ የምችለው አንድ ነገር ብቻ ነው። "በርታ ልብህም ይጽና፣ እግዚአብሔርንም ተስፋ አድርግ!"
ጸበልና ሐኪም ቤት የምትዘዋወር፣ በሕመም የምትሰቃየው ወንድሜ ሆይ፣ ለነፍስም ለሥጋም ፈውስን የሚሰጥ "ፈዋሴ ዱያን" አምላክ አለህና አይዞህ "በርታ ልብህም ይጽና!"
ፈቃዱ ሆኖ ባያድንህም እንኳን ሕመምህን ለጸጋ ለበረከት የሚያደርግልህ ቸር አምላክ ስላለህ ወንድሜ ሆይ አይዞህ! በርታ ልብህም በአምላክህ ይጽና!
የእኔ ተወዳጅ ወንድም፤ ለምትወዳቸው ሰዎች በችግራቸው ጊዜ መድረስ አቅቶህ፣ እናት አባት፣ ወዳጅ ዘመድ ላንተ ስለከፈሉልህ ዋጋ ውለታቸውን መመለስ አቅቶህ እንደምታዝን አውቃለሁ። ግን አይዞህ! እየሞከርክ ያለውን ሁሉ፣ ድካምህንና ልፋትህን ችላ የማይል ቸር፣ ለጋስ አምላክ አለህና "በርታ ልብህም ይጽና፣ አምላክህንም ተስፋ አድርግ!"
ተወዳጅ ወንድሜ ሆይ፣ ነፃ መውጣት የምትፈልግበት፣ መላቀቅ የምትሻው አንዳች ሱስ፣ ክፉ ልማድ እንዳለም አይጠፋኝም። ከእግዚአብሔር አምላክህ የለየህን ኃጢአት ማራገፍ እንደምትፈልግም አውቃለሁ። አይዞህ! ብትመለስ ኃጢአትህን ይቅር የሚል፣ ከበረዶም ይልቅ ሊያነጻህ የታመነ መሐሪ አምላክ አለህና "በርታ ልብህም ይጽና!"
ተወዳጅ እህቴ ሆይ፣ አንቺም ብትሆኝ የምትከፊበት፣ አንቺና አምላክሽ ብቻ የምታውቁት አንዳች ልብሽን ሰቅዞ የያዘሽ ኃዘን እንዳለብሽ አውቃለሁ። የእግዚአብሔርን መልስ በዕንባና በልቅሶ የምትለምኚበት አንዳች ደጅ ጥናት፣ አንዳች ልመና እንዳለሽም አይጠፋኝም።
እህቴ ሆይ አይዞሽ "ምኞትሽን በበረከቱ የሚያጠግባት፣ ጎልማስነትሽንም እንደ ንሥር የሚያድስ" ኃያል አምላክ ስላለሽ በርቺ ልብሽም ይጽና፣ የሚወድሽ አምላክሽንም ተስፋ አድርጊው!! (መዝ ፻፪ ፥ ፭)
ወዳጅ ዘመድሽን በሞት ተነጥቀሽ፣ ልብሽ ተሰብሮብሽ በኃዘን እና በብቸኝነት የምትኖሪ እህቴ ሆይ፣ አይዞሽ!! "ወላጅ እንደሌላቸው ሕፃናት" ብቻሽን የማይተውሽ፣ "ማቅሽን ቀዶ በደስታ የሚያስታጥቅሽ" የኃዘንተኞች መጠጊያ (ምስካየ ኅዙናን) የሆነ አምላክ አለሽና በርቺ ልብሽም በአምላክሽ ይጽና፣ ይጽናና!! (ዮሐ ፲፬ ፥ ፲፰ ፣ መዝ ፳፱ ፥ ፲፩)
ደግሞስ "ናዛዚተ ኃዘን" የተባለች ኃዘንን የምታረጋጋ እመብርሃን እናትሽ አይደለች? ግድ የለሽም የእኔ እህት አይዞሽ ልብሽም በልጇ ይጽና!!
ይህች ዓለም የደከመቻችሁ፣ ኃዘን በዲበ ኃዘን የሚፈራረቅባችሁ፣ ቀን ከሌሊት ዕንባችሁን የምትዘሩ ተወዳጆች ሆይ፣ አይዟችሁ! ዕንባችንን ከንቱ የማያስቀር፣ የልባችንን ኃዘን የሚያውቅ፣ "ሳንለምነው የሚያስፈልገንን አውቆ የሚሰጠን" ደግ አባት አለንና አይዞን! እንበርታ፣ ልባችንም በእግዚአብሔር ይጽና፣ ተስፋም እናድርገው! (መጽሐፈ ኪዳን)
"እግዚአብሔርን የምታምኑ ሁላችሁ
በርቱ ልባችሁም ይጽና"
~ መዝ 30 ፥ 24
ሁላችንንም እግዚአብሔር አምላክ ያበርታን!!
አሜን!!
.................................
ዲያቆን ዮሐንስ ደረጀ
ጥር 19/2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
...................................
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
Repost from N/a
“ጌታ ቢፈቅድ፥ ብንኖርም ይህን እናደርጋለን፤”
የያዕቆብ መልእክት 4፥15
ሌሎች ወንድሞችና እኅቶቻችንም የቤተሰባችን አካል ሆነው ለተጨነቀች ነፍስ ዕረፍት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ የምንችለውን ሁሉ እናድርግ።
+2
ቤተ ክርስቲያን የእግዚአብሔር ጸጋ ፈስሶባቸው የሚተርፋቸው እጅግ ብዙ አገልጋዮች አሏት። ከእነርሱም መካከል በዚህ ቻናል የምንዘክረውን ንዑድ ክቡር ሊቀ ዲያቆናት ቅዱስ እስጢፋኖስን በስም፣ በማዕረግ እና በሥራ የሚመስለው እጅግ ተወዳጅ ወንድማችን መምህር ዲያቆን እስጢፋኖስ ግርማ ነው።
ዲያቆን እስጢፋኖስ ልክ እንደ ሰማዕቱ ሕግን የተማረ እና የሚያውቅ ተወዳጅ ወንድማችን ነው። ዲያቆን እስጢፋኖስ በአዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ በሕግ (Law) ትምህርት የማዕረግ ምሩቅ፣ የዓለም አቀፍ ሕግ ባለሞያ እና ጠበቃ ነው።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንንም በውብ ስብከቶቹ እና ጽሑፎቹ በአማርኛ እና በእንግሊዘኛ ቋንቋ የሚያገለግል ውድ ወንድማችን ነው።
ከታች የምናስቀምጥላችሁ ቻናል መንፈሳዊ ትምህርቶችን እና ስብከቶችን መምህራችን የሚያጋራበት ስለሆነ ሊንኩን በመጫን እንዲቀላቀሉ እናሳስባለን።
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/Dnestifanos
