እዝራ ካሳሁን / Ezra Kassahun
رفتن به کانال در Telegram
260
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز
آرشیو پست ها
#ezra 21/3/16 @melos3 @melos3የሁልጊዜ ከራስ ጋር ከባዱ ሙግትና ጭቅጭቅ በተደረገብንና በደረሰብን በደል ላይ ያለን አመለካከት ይመስለኛል። ፧ በተለይ በህይወታችን ውስጥ ትልቅ ቦታ በሰጠናቸው ሰዎች የደረሰብን ክህደት እንዲሁም ክህደቱን ተከትለው የሚመጡ የመከራና የስቃይ ጊዜአት የስብራቱን ክብደትና ህመም ስለሚያብሱት ወቅቱን የምናልፈውና ከማዕበል ወጀቡ የምንተርፍ አይመስለንም። ፧ የሆነው ሆኖ እናልፈዋለን ግን! ሰው አይደለን ምንም ቢሆን ያጠፋ ሊቀጣ የበደለም ሊክስ ግድ ነው የሚል እምነት ስላለን ከምንም በላይ ደሞ ለክፋት ያለን ተጋላጭነት ከተፈጥሮአችን ጋር የሚስማማ ስለሆነ ከበቀል እሳቤ ማምለጡ ይከብደናልና። ፧ ለዛም ነው ከራሳችን ጋር ያለብን ሙግት ፈጣሪን ❝እኔ ልበቀል ወይስ አንተን ልጠብቅ❞ ብለን እንድንጠይቅ የሚያስገድደን።
ለውጥ፦ በህልውናው ውስጥ ያሉ ክስተቶች እና የአዳዲስ ልምዶች መገለጥ ብዬ አምናለሁ። የእውነታን ተለዋዋጭ ተፈጥሮን የመመርመር ትጋትንም ያጠቃልላል። የሁለቱን ዓለሞች ቁሳዊና ግዑዝ እንዲሁም መንፈሳዊ ገጽታዎችንም ያካትታል።
ለዛም ነው ለውጥ «ዛሬ የሚሆን ነው» የሚለው ፅንሰ-ሀሳብ ከምክንያታዊነት ፣ ከግዜ እና የሁሉም ከሚባሉት ነገሮች ጋር ያለው ትስስር ቀጣይነት ባለው ከእለት ተእለት የሰው ልጅ ግንዛቤዎች ጋር በእጅጉ የተቆራኘ ነው ብዬ የማስበው።
ለውጥ የሚለው ፅንሰ-ሀሳብ አመለካከታችንን ግምት ውስጥ በማስገባት ስለ ቆራጥነት እና ነፃ ምርጫ ጥያቄዎችን እንድናነሳ የሚገፋፋን ይመስለኛል። ከዚህም ባሻገር ❝አስቀድሞ የተወሰነ የምክንያት እና የውጤት ሰንሰለት ነው ወይስ ውጤቱ የዝግጅቱን ሂደት በቀረፁ የዘፈቀደ እና የግለሰብ ቅንጣጢት (ስሜት ፥ ልምድ ፥ እውቀት እንዲሁም የራስ ማንነትና ፍላጎት) የተዋጀ ነው ? የሚልን አንኳር ነጥብ በማንሳት በሜታፊዚክስ እና ሥርዓተ ውስጥ ያለውን የእውነታን ተፈጥሮና ጥበብ እንዴት እንደምንረዳ የሚመረምር ሆኖ ይታየኛል።
ስለ ለውጥ ማሰላሰል ብቻውን በቂ ባይሆንም የለውጥ ሀሳብ በራሱ ኦንቶሎጂያዊ አስተያየቶችን ግን ያመጣል። እንደ የሕይወት ዓላማ፣ የንቃተ ህሊና ተፈጥሮ እና ለተከሰቱት ክስተቶች የምንሰጠውን ትርጉም በመሳሰሉ የህልውና ጥያቄዎች ላይ በማተኮር ስለ ራሳችን መሠረታዊ ተፈጥሮ እንድናጠነጥንና ለመረዳት እንድንጥር ይገፋፋናል። በግለሰቦች፣ በህብረተሰብ እና በሰፊው ኮስሞስ መካከል ያለውን ትስስር እንድንመረምር ይጋብዘናል።
በመጨረሻ ለውጥ ወደ ሕልማችን እንቆቅልሽ እና ውስብስብ ነገሮች እንድንገባ ይጋብዘናል። የምኞታችንን ነጸብራቅን ይለካል ፤ ውስጠ-ግንዛቤን ይፈትሻል ፤ በጊዜን ዑደት የእኛን መሻሻል በድርጊት ሚዛን ይሰፍራል ፤ ምክንያታዊነትን በመወሰን አቅማችን ውስጥ ያለውን ቦታ ይገመግማል ፤ ነፃ ምርጫን እንዲሁም ዓላማን መሰረት በማድረግ በእውነታው ውስጥ ያለንን ቦታ እንድንገነዘብ ያበረታታል ብዬ አስባለው።
እናንተስ?
#Ezra 17/3/16
@melos3
@melos3
ስኬት የእውነተኛ ስሜቶች እና የተገሩ ታሪኮችን መታያ መድረክ ነው። በልብ ውስጥ ያለን ሀሳብ በስራ በማስተጋባት የማይጠፋ ምልክት በዓለም ላይ ማኖር ደሞ መገለጫው ነው።
ወደ መታያ መድረኩም ሆነ ወደ መገለጫው ፥ መንገዱ ትግል የሚበዛበት ቢሆንም መዳረሻው ፤የጉዞው ፍፃሜ ግን ነፍስን የሚማርክ የደስታ ዜማ ነው።
ስኬት የተጋላጭነት አትሮንስም ነው። ለሁሉ የተሰጠ ግን ሁሉም የማያገለግልበት።
ያለ ፍርሃት ራስን የመግለጽ ፥በፈጠራ ችሎታ ማሰላሰልን የመቀስቀስም ሂደት ነው። እንዲሁም መንፈስን የሚያንቀሳቅስ እና ጊዜን የሚሻገር ስሜትን ወደ ተጨባጭ ውበት የመቀየር ጥበብ ነው።
ለዚህ እውነት ስንቶቻችን ዝግጁ ነን?
@melos3
#Ezra 14/3/16
❝እንቁጣጣሽ❞
፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧
ባለፉት አመታት፣ወራት እንዲሁም ቀናት ውስጥ አውቄም ሆነ ሳላውቅ አስቀይሜዎት ከሆነ ይቅርታ እየጠየኩኝ፦
፧፧፧፧፧፧፧
አዲሱ ዓመት በሁሉም የህይወት ገጽታዎች ከፍ የሚሉበት፥የተጀመረ ጉዞዎ መልካም ፍጻሜ የሚያገኝበት ፣የሰላም ፣የደስታ፣ የፍቅር፣ የጤና እንዲሁም የተድላ ዓመት እንዲሆንልዎ ከልብ እመኛለሁ።
፧፧፧፧፧፧፧
መልካም አዲስ ዓመት!!
🌼🌼🌼
"2016 ዓ.ም"
ዛሬ እንደ ወትሮው ኣይደለም ! መሰላቸት አይበታለው። ደክሞታል። ማሰብ ከዛ መቀበል አልያም አለማሰብ ከዛ አለመቀበል ብቻ የሆነ መደምደሚያ ላይ ቢደርስም መንገዱ ይሁን ሁኔታው ታክቶታል።
፧
< ምንሆነኻል እዝራ > አልኩት ሲያወራ ከቀለለው ብዬ
፧
< ምንም > አለኝ እያቅማማ .....
፧
በዚህ መሐል ያዘዝነው ወተት ተከታይና ነጣ ያለ ማኪያቶ ከተወለወለው ጠረጴዛ ላይ በግሩም ትህትና በየአቀማመጣችን ትይዩ ተቀመጠልን።
፧
ማኪያቶዬን አንድ ሁለቴ ከሳብኩኝ በኋላ < ንገረኝ እንጂ እኔና አንተ የምንደባበቀው ነገር ኣለ? >
፧
< የለም > ወተቱ ላይ ለማጥቆሪኣነት የመጣለት ቡና እየጨመረ
፧
< እዝራ ወንድሜ ኣንተ ዝም ስትልና ሲከፋህ አይቼ ኣላውቅም እንዲህ ስትሆን ይጨንቃል > ሳቅና ጨዋታው ለምጄ ምጥ የሆነ ፊት ሲያሳየኝ ግራ ገብቶኝ...፤
፧
ዝም እንዳለ ነው < ትዝ ይልኻል የሆነ ጊዜ ሳቢ የሌለ ጠሮብን አንዱን ዘብ'ነይ ሊፍት አጠቃቀም አሳይተን ስምንተኛ ፎቅ ላይ አድርሰን ከመለስነው በኋላ የትራንስፖርት የተቀበልነው > እየሳኩኝ........
፧
ኣልሳቀም! ፈገግም ኣላለም < ትናንት ማታ ቤቴን ዘግቼ አነባው አለቀስኩ እናቴ ማህፀን ውስጥ እንደ ነበረኝ አቀማመጥ ጥቅልል ኩርምት ብዬ ተንሰቀሰኩኝ ምክንያቱም በሙሉ ሀይሌ ሞክሬ ስላጣው።.... ለፍተህ መና ፣ ደክመህ ከንቱ ሲሆን ምላሹ ያብከነክናል ፤ ከመብሰልሰል ላልተርፍ ስቃዩ እንደ ሞኝ እንደ ጅል አደረገኝ እንባዬን ልፅፈው ሞከርኩኝ እንባ ግን እንዴት ይፃፋል ? በልብ የደበቁት ከአይን ይነበብ የለ በእንባ እየተሞላው በለሆሳስ ከራሴ ጋር ስለማውራቴ ትራሴ ምስክር ነው ፤ ከመተኛቴ በፊት ብዙ የነገርኩት አንዳንዴ በእንባ አንዳንዴ በሳቅ የተዋበ ታሪክ አለኝና ......>
፧
ደነገጥኩ < ምንሻ ነው ? > አልኩት ብርቱው ወዳጄ ፤ ጠንክሮ የሚያጠነክረኝ ፤ ጀግኖ የሚያጀግነኝ መኮማተሩ አመመኝ ፤ መሰበሩ ጎዳኝ ፥ አብሬው እየኖርኩ እያጣሁት እንደነበር ሳሰብ .....፤
፧
ድንጋጤው አለቀቀኝም ፥ ሁኔታዬን ችላ ባይለውም መተንፈስ ነበረበትና በዝምታ አብሬው እንደሆኑኩ ጉንጬን አሰረጎድኩ ፥ ቀጠለና
፧
< መኖር ትርጓሜው በየግል የሚገለፅ ይመስለኝ ነበር ፤ መንገዱን ማሳመር እንጂ አንድ እስትንፋስ ለሁሉም ነው ፥ በፆታና ተያያዥ ጉዳዮች እንከፋፈል እንጂ መሰረታዊ ስርዓቱ የሚቀየር አይደለም ብቻ ከፍታ ፍለጋ እራሳችንን እያጣን ነው። ቀላል ህይወት ፣ ቀላል ኑሮ ፣ ቀላል አስተሳሰብ ትርጉሙ አልገባንም ወይም ገብቶን ችላ እያልነው ነው >
፧
ብሞግተው ደስ ባለኝ ግን ተውኩት ፥ ምክንያት አጥቼም አይደለም ወይም ስሜታዊ ሆኜ አልያም ሀሳብን በሀሳብ ለመሞገት እውቀትም ድፍረትም አጥቼ ሳይሆን አንዳንድ ነገሮች ፤ ህመሞች ፤ ስሜቶች ፤ እውነት ስለሚያገዝፉ መልሳቸው ዝምታ ብቻ ነው።
፧
በእንባ የተሞሉ አይኖቹ ማልቀስን ቢሹም በትግል መልሷቸው ፤
< መበርታት አለብኝ። እንደ ፋኖስ ብርቱ መከለያ ያስፈልገኛል። ምክንያቱም የንፋሱ ብርቱ መሆን ለኩራዝ ቢከብድ እንጂ የፋኖሱን ብርኻን አያጠፋም ፤ ደሞም የእስካሁኑ ይበቃል። ፍፁም ፍፁምነት የለም እውነትን መቀበል አለብኝ ፤ እየሸሸው እስከ መቼ ? ማብቃት አለበት ፤ ብቸኛ ነኝ። አንተም እንደዛው። አይመስለኝም እንጂ አሳ እራሱ ያለቅሳል ኮ' ባህር ግን አያውቅም ልክ እንደዚህ ብቸኝነቴም በሰዎች የተሞላ ነው።>
፧
እውነት ነው ብቸኝነታችን በሰዎች የተሞላ ነው!
#Ezra kassahun
6/13/15
@melos3
@melos3በህፃን ልጅ የተያዘች ትንሽዬ ወፍ ፥ ልጁ የወፏ ስቃይ አይገባውም። ወፏን በመያዙ እየተደሰተ ፥ እየተጫወተ ነው። እንድታመልጠውም አይፈልግም ፤ እሷም ማምለጥ አትችልም መዳፉ ብርቱ ነው ካላት ጉልበት አንፃር ፤
የኔም ልብ እንደዛ እንደሆነ ይሰማኛል። ምክንያት ቢያገኝ እንኳ ከመዳፏ መኖሩም መሞቱም ሰላም አይሰጠውም። ያስጥሉኛል ብዬ የሄድኩባቸው መንገዶች ሁሉ እንኳን እሷን ሊያስረሱኝ ይቅርና መዳረሻቸው ፥ የጉዞው መጨረሻ እርሷ ጋር ነው።
አይገርምም አውቃለሁ መራሩ እውነት ግን መጥላት በማትችለው ሰው እንደመፈተን ከባድ ነገር የለም።
....የሆነው ሆኖ ነፍስ ዋጋ የሚሰጧትን ትዘነጋለች!
#Ezra kassahun
28/12/15
@melos3
@melos3
ሽኝት፦
-----
ለወራት ስያሜ የወቅት መልካቸው
ስያሜ መጠሪያ ለየ' ባህሪያቸው
እኔ የኔ ምላት አንተ ያችሁት ያልካት
< ፀሀይ >
ይቺ የቀን ዶቃ..........፤
በምስራቅ ብቅ ባይ
ለውድቅቱ ሽኝት ከጴጥሮስ ንሰሀ
መልዕክቱ ተቀባይ ፥
ለእለተ' አሀዱ ንጋትን አብሳሪ...፤
ደሞሞ ለምሽት ጅማሬ ለሰማይ ንጣፉ
ጠይም መልክ ቀቢ ብርሀንን አሳሪ
ይቺ የእግዜር ምስጢር
በምስራቅ ፈንጥቃ...........፤
ለሁሉ በልኩ ተስፋን አስንቃ
ደሞ ወደ ኣመሻሽ ከጎጆዋ' ልትከትም
በምዕራብ ምትሸሸው
ስለምንስ ይሆን አቅጣጫው
ከሁለት የሆነው ?
ይህ ነገር የዘመን ስፍር የህይወት ልክ ነው ?
የዕድሜ ሁለት ጫፎች ምንና ምን ናቸው ?
ሁሉ እንደ ጀንበር ነው ?
ሰውስ' እንደ ፀሀይ ገፀ' ፈረቃ ነው ?
_=___
*ዝናብ ነበርና አብርሆት ቤተመጻሕፍት ለመሄድ ከአልጋዬ መውጣት ብፈልግም እንቅልፍ ተጨምሮበት ድካሜ ባባሰው ጊዜ የተፃፈ ነውና። አውቃለው ምንም እንደማያገባችሁ ፥ አሁን ግን አብርሆት ነኝ። 🙂
#ዛብሎን
ዕዝራ ካሳሁን
4/11/15
@melos3
< ተፈጥሮአችን ይገርመኛል > አለኝ እንዳዘዘው ብቻ ሳይሆን እንደሚፈልገው የተሰራለትን ማኪያቶ ፉት ብሎ ካጣጣመው በኋላ....፤
< እንዴት > አልኩት በስራ ብዛት የዛለውን መንፈሴን ለማነቃቃት በወረደ ቡና የተከሸነውን እስፕሪሴን እየጠጣው ....፤
< ዲፎልት ተፈጥሮአችን ህልም ማለም ነው ፥ ለማለም የሚያስፈልጉንን ግብአቶች ደሞ በቀን ውሎአችን እንሰበስባለን። > ደግሞ ደጋግሞ ማኪያቶውን እየሳበ....፤
< እሺ > አልኩት የቡናው ጥንካሬ የፈጠረውን ከባድ ምሬቴ እንደምንም ችዬ....፤
< ምነው ? ይመራል እንዴ > ኣለኝ የፊቴ ገፅታ መቀየሩን ኣይቶ....፤
< አዎ ... ለነገሩ እዚህ ሀገር ከመኖር አይብስም ፥ እንደው ካነሳኸው ኣይቀር አንዱ የሙሉ ጊዜ ስራህ ምንድነው ቢሉት « ኢትዮጵያ ውስጥ መኖር » > ሁለታችንም ሳቅን ፥ በሀቅ መሳቅ ፡ በእውነት መገልፈጥ ኣይ ጊዜ....፤
< ኣይ እዝራ ትኩስ ነገርን ሁሉ ያለ ስኳር እየጠጣህ መረረኝ ብትል ፤ ህይወት እሬት እሬት አለኝ ብለህ ብታማርር ማን ይሰማኻል > ለማለት የፈለገው ገብቶኛል ፥ ልብህን ክፍት አድርገው ምናምን የሚባሉ የደራሲ ቃላቶችን እየተጠቀመ ስለ « ሊዲያ » ሊያነሳብኝ ነው ....፤
< እውነት ነው ... ይልቅ የጀመርከውን ጨዋታ ጨርስልኝ > እሱ ሽሽት የሚለውን እኔ ስያሜ ያጣሁለትን ጉዳይ ባናወራውስ ከሚል ዝምታ በኋላ....፤
< መልካም ፥ ድካምን በተፈጥሮ የጊዜ ስሌት ስለምንቀምር በብርሀን የስም ቅያሬ ባንፈልግም እናርፋለን ፥ እናሸልባለን ። የተገታንበት ነገር ኣለ። እእእ...የተፈጥር ገዢ ለተፈጥሮ ተገዢ ነን። ይህን ኣልፈን ወደ ህልማችን ወደ ማለማችን እንመለሳለን።>
< ሊሆን ይችላል ፥ ህልማችን የትናት ግን ዛሬ የሚኖር ነው ፥ በነገ ጊዜ ውስጥ ህልም የለም የመታገስ ሌላኛው ገፅ ነው ያለው እሱም 'መጠበቅ' ነው > እያልከኝ ያለኸው....፤
< አዎ >
ማኪያቶው ለመጨረሻ ጊዜ አንስቶ ጨለጣት....፤
< እንዴት > ተከተልኩት....፤
< የህይወታችን ፍቺ በሁለት ፅንፍ እንዳለ አምልኮ ነው። አንድም ሙሴን መጠበቅ ፤ አንድም ለብቸኛ ነፍሳችን ከፍርሀት መዳኛ ሌላ አምላክ መፈለግ። > ፈገግ አለ....፤
< ለምን ? >
< በመታገስ ውስጥ ያለው ጥበቃ ያደክማል ድካም ደግሞ ያሰለቻል።> አስተናጋጇን ጠራትና ሂሳብ ከፈለ። < ስልክህ እየጠራ ነው እኔ ላይ ማፍጠጡን ትተህ አንሳው ፤ ሊዲያ ትሆናለች >....፤
< የት ናቹ >....፥
< መገናኛ አማንጋ ነን >....፥
< መጣው ጠብቁኝ >....፥
< ማነው ሌላ ማኪያቶ እንድጠጣ የሚያደርገኝ ቅዱስ ሰው > አለኝ የምጠላትን የነገር ፈገግታ ፈገግ እያለ....፤
< ሳሚ ነው ፡ ከስራ ገና አሁን እየወጣ ነው መሰለኝ > ሳምሪ ሁለት ማኪያቶ ... እ ኖርማል አድርጊው....፤
#ዛብሎን
ዕዝራ ካሳሁን
3/11/15
@melos3
እሷን መውደድ ማለት ፦ በልጅነት ብስክሌት እንደመለማመድ ነበር። ያ ልጅነት... በጉጉት የተሞላው የአፍላነት እድሜ ፤ ንፁህ የዋህነት።
፥
ስለማመድ መውደቅ አይታክተኝም ግን እያንዳንዱ እርምጃዬ በፍርሀት የተሞላ ነበር ... በመቻል ውስጥ የማገኘውን ደስታ የማይረታ ፍርሀት ፥ ግን ደሞ ፍርሀት ፍርሃት ነው ፤ እንደሚነሳ የሚያውቅ ሰው መውደቅ ስለምንድነው የሚፈራው ?
፥
ለዛ እድሜዬ ፥ ለዛ የማፍቀር ስሜት ከባድ ጥያቄ ነበር። የከበደኝ ማቅለል መሻት እልኸኛ አድርጎኝ ስለነበር የጥያቄዬን መልስ ፈለኩ..ፈለኩ..አገኘሁት..፤
፥
ሳገኘው ግን ፍላጎቴ ሞቶ ነበር! ምንም አልመሰለኝም። ለምን?....እ...
ከማግኘቴ በላይ ፍለጋዬን ወድጄው ወይስ ያረፈደ ማግኘት ሆኖ አስጠልቶኝ? አላውቅም.....!
፥
ሌላ ጥያቄ ፤ ሌላ ፍለጋ......፣
#ዕዝራ ካሳሁን
9/9/15
@melos3
@melos3
ስሚኝማ'
ያ ማንነቴ አልናፈቀኝ መሰለሽ! ያ አንቺ የምትወጂው!
ለህልሜ የማይመሽብኝ፥ስኳትን፣ስታትር መንጋቱ ትዝ የማይለኝ፥
ለማረፍ በመጓዝ የሚመጣው (ሌላ መንገድ የለማ')
ብርሀን እና ጥላን ጊዜ ብሎ የሚጠራው!
እ እሱ።
ዕዝራ ካሳሁን
1/9/15
@melos3
