Sadat_Text_Posts
رفتن به کانال در Telegram
نمایش بیشتر
📈 تحلیل کانال تلگرام Sadat_Text_Posts
کانال Sadat_Text_Posts (@sadattextposts) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 10 532 مشترک است و جایگاه 18 731 را در دسته اخبار و رسانهها و رتبه 3 222 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 10 532 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 04 مارس, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -85 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 0 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 0% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً N/A% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 0 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 0 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 0 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
توضیحی برای کانال ارائه نشده است.
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 05 مارس, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته اخبار و رسانهها تبدیل کردهاند.
10 532
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-207 روز
-8530 روز
آرشیو پست ها
10 532
"ወንጀል ከሱና አያስወጣም " እየተባለ .. ውሸት ፣ ማጭበርበር እና ሌሎችም አስከፊ ወንጀሎች ዉስጥ በግዴለሽነት መነከር አሳፋሪ መባል የሚያንሰው ክፉ ና ፀያፍ ምግባር ነው .. ወቅታችን ላይ ደግሞ ይሄው ክፉ ደዌ ብዙዎችን አጥቅቷል ---- ወንጀል አይጎዳ ይመስል በቀጥታም ባይሆን ባዙሪት ቀላልነቱ ይሰበክ ይዟል - በአንዳንዶቻችን ...
ነብዩን እና ባልደረቦቻቸውን እከተላለሁ የሚል ግለሠብና ወገን ወንጀልን የሚመለከትበት አይን ኢርጃእን የተጎራበተ መሆኑ ወይም የተጎራበተ ሊሆን መቃረቡ ይሳዝናል ...
የአላህን፡ ህግጋቶች ማክበርና አግዝፎ መመልከት የተቅዋ እና የአላህን ቅጣት መጠንቀቅ መገለጫ ነው ...
وَمَن يُعَظِّمْ شَعَائِرَ اللَّهِ فَإِنَّهَا مِن تَقْوَى الْقُلُوبِ
የአላህንም የሃይማኖት ምልክቶች (ትእዛዦች ፣ ክልከላዎች ) የሚያከብር ሰው እርሷ ከልቦች የኾነች ጥንቃቄ ናት፡፡
ተቃራኒው እንዝላልነት የልብን መጥቆር አጉልቶ ይሳያል .....
ዓብዱላህ ኢብኑ መስዑድ ሙእሚን ወንጀልን አግዝፎ እንደሚመለከት፣ ሙናፊቅ ግን እጅጉን አቅልሎና አሳንሶ እንደሚያየው ተናግረዋል .....
በወንጀሎች ላይ መዘውተር የከሃዲያን መገለጫ መሆኑንም ልንዘነጋ አይገባም ... አላህ እነሱን ሲገልፃቸው እንዲህ ይላል
وَكَانُوا يُصِرُّونَ عَلَى الْحِنثِ الْعَظِيمِ
(በታላቅ ኀጢአትም ላይ ይዘወትሩ ነበሩና )
ሌላው ነገር፦ ወንጀል (በተለይ የድብቅ ወንጀል ) መጨረሻን (አሟሟትን) ከሚያበላሹ ነገሮች ውስጥ አንዱ ነውና የዛሬውን ሱና ላይ መሆን ብቻ ሣይሆን የወንጀል ብዛት ሊያስከትል የሚችለውን መንሸራተትና ክፉ ውጤት እናስብ... አላህን እንፍራ ... ወደሱም እንመለስ ።
ጥፋትና ወንጀል ከሁላችንም ሊመነጭ የሚችል መሆኑን አልዘነጋሁም ። ከላይ በተጠቀሰው መጠን ወንጀል ላይ ቸልተኛ መሆን ግን እጅጉን አደገኛ ነው።
አላህ፡ ይመልሰን !
ቻናሉን ይቀላቀሉ። ሌሎችንም ይጋብዙ። መልእክቱን ለሌሎች በማሰራጨት የአጅሩ ተቋዳሽ ይሁኑ።
t.me/Muhammedsirage
10 532
አሸዋ ሜዳ እና ዙርያዋ ላላችሁ፡፡
በአላህ ፍቃድ ከሰኞ እስከ ሀሙስ ሁለት ቀን ለወንዶች፣ ሁለት ቀን ለሴቶች ከቀኑ 10፡45-11፡30 ድረስ በመርከዝ ተውሒድ የኪታብ ቂርዓት ፕሮግራም ይኖራል፡፡ ፕሮግራሙ በዋናነት ቁርዓን ቀርተው ለጨረሱ ወንድም እና እህቶች ይሆናል፡፡ በተለይ ትምህርት ቤት ደርሰው ለሚመለሱ ወጣቶች ታስቦ የተዘጋጀ ፕሮግራም ነው፡፡
በአላህ ፍቃድ የሚሰጡት ኪታቦች ከታች ጀምሮ እይያጠሩ እውቀት መቅሰም ላይ ትኩረት ያደረገ ይሆናል፡፡
በአላህ ፍቃድ ዋና ትኩረታችን መልክተኞች ሁሉ የተላኩበትን ተውሒድ ለኡማው ማድረስ ነው፡፡
የሚቀሩትን ኪታቦች እና የሴቶችና የወንዶች ፕሮግራም አከፋፈልን በተመለከተ በአላህ ፍቃድ በቅርብ ቀን ይለቀቃል፡፡
https://t.me/Tewhide_Merkez
10 532
ለተጨማሪ መረጃዎች እነዚህን የቴሌግራም አድራሻዎች ጆይን በማድረግ ይከታተሉ:‐
① t.me/Tewhide_Merkez
② t.me/IbnuMunewor
③ t.me/SadatKemalAbuMeryem
④ t.me/Muhammedsirage
⑤ t.me/Abulabas
10 532
السلام عليكم ورحمة الله وبركاته
ማስታወቂያ
ተቋርጦ የነበረው ሳምንታዊው የእሁድ ደርስ በአላህ ፈቃድ የፊታችን እሁድ ታህሣሥ 4/2013 ይጀምራል።
🌴 የሚጀመሩት ኪታቦች
① መሳኢሉል ጃሂሊያ – በሙሐመድ ሲራጅ
② መቶ ሐዲሥ – በሳዳት ከማል
③ መንዙመቱል ኢልቢሪ – በአቡል ዐባስ
④ ዶላሉ ጀማዐቲል አሕባሽ – በኢብኑ ሙነወር
🌴 ደርሱ የሚሰጥበት ቦታ
~~~
* አንፎ ድልድይ ከባጃጅ ተራ ወደ ውስጥ ገባ እንዳሉ ኤግልቪው ክሊኒክ ወረድ ብሎ ጣሊያን ውሃ ጋ።
🌴 ደርሱ የሚጀምረው ቀጥታ ጧት 3:00 ስለሆነ በሰዓት እንዲገኙ እናሳስባለን።
የኪታቦቹን ሶፍት ኮፒ እንለቃለን። የምትችሉ ግን ገዝታችሁ ወይም ኮፒ አድርጋችሁ ይዛችሁ እንድትመጡ።
10 532
ለቅፅበት ታክል እንኳን ከብቸኛው ፈጣሪ አላህ ፈላጊ ያልሆነ አንድም አካል የለም። ለዛ ነው ነብዩ ﷺ ለቅፅበት ታክል እኔን ለነፍሴ አትተወኝ ያሉት። ከአላህ ፈላጊ ድሆች መሆናችን አውቀን ወደሱ ብቻ መዋደቃችን ታላቅ አምልኮ ነው።
10 532
የዛሬ ቀን ረቢአል አወል 12 ነብዩ ﷺ የሞቱበት ነው። ይህን ቀን አመታዊ የደስታ ቀን አድርጎ መያዝ ሰይጣናዊ መንገድ ነው። በኢስላም የሙት አመት የሚባልም ነገርም የለም። በኢስላም የታዘዝነውን ብቻ እንስራ። ከክስረት እንጠበቃለንና። ነብዩ ﷺ "ቢድአ ሁሉ ጥመት ነው" ብለዋል።
10 532
የትኛውን መውሊድ?
እንደሚታወቀው በኢስላም የታዘዙት ሁለት አመታዊ በኣላት፣ ኢድ አል-ፊጥር እና ኢድ አል-አድሃ ናቸው፡፡ ኢድ አል-ፊጥር አንድ ቀን ብቻ ሲሆን፣ ኢድ አል አድሃ ደግሞ 4 የበኣል ቀናቶች ናቸው፡፡ ታድያ በሀገራችን ተጨባጭ አላህ 4 ቀን እንዲከበር ያዘዘውን አንድ ቀን ብቻ እያከበርን ያልታዘዝነውን መውሊድ ግን ከአንድ ቀን በላይ በተለያዩ ሰዎች ስም ሲከበር ይታያል፡፡
ለምሳሌ ሀገራችን ላይ በተለያየ ቀናት ከሚከበሩ የመውሊድ አይነቶች ውስጥ
1) የነብዩ መውሊድ፣
2) የአሊ ጎንደር መውሊድ፣
3) የአባድር መውሊድ፣
4) የዳንግላው መውሊድ፣
5) የአብሬት መውሊድ፣
6) የቃጥባሬ መውሊድ፣
7) የአልከሶ መውሊድ፣
8) እና ስፍር ቁጥር የሌላቸው መውሊዶች……
ለምን ይሆን በኢስላም የታዘዝነውን ትተን ያልታዘዝነውን የምንሰራው?
እውነት ይህ ነው የነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ውዴታ?
በፍፁም፡፡
ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “አደራችሁን አዳዲስ ነገሮችን (በዲን ላይ ከመጨመር) ተጠንቀቁ፡፡ ሁሉም አዲስ ነገር ጥመት ነው፡፡” ብለው ሲያበቁ
አሁንም ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “የእኛ ትእዛዝ የሌለበትን ስራ የሰራ ሰው ስራው ተመላሽ ነው (ተቀባይነት አያገኝም፣ ውድቅ ነው)” ብለው ሳለ
ዛሬ እሳቸው ያዘዙትን ትተው ያላዘዙትን የሳቸውንም ይሁን ሌሎች ጥሩ ሰዎች ናቸው ብለው የሚገምቷቸውን የአሊ ጎንደር መውሊድ፣ የአባድር መውሊድ፣ የዳንግላው መውሊድ፣ የአብሬት መውሊድ፣ የቃጥባሬ መውሊድ፣ የአልከሶ መውሊድ እና የመሳሰሉትን እያሉ በውዱ ሃይማኖታችን ላይ ቅጥፈትን ይቀጥፋሉ፣ የክህደት ንግግሮችን መውሊዶች ላይ ይናገራሉ፣ ይጨፍራሉ፣ ይህን አደንዛዥ ቅጠል ያላምጣሉ፡፡
ሱብሃነላህ ይህ በፍፁም ነብዩን መውደድ አይሆንም፡፡ ነብዩን ከማንም በላይ የሚወዱት ሰሃባዎች የነብዩን ፈለግ ህይወታቸው ላይ ተላበሱ እንጂ እንዲህ ልደት እናክብር አላሉም፡፡
ለሙስሊሙ ከታሰብ መውሊድ ብሎ በሺርክ፣ በቢድኣ፣ በጭፈራ እና አደንዛዥ ቅጠል ጫትን መቃም እና ማስቃም ሳይሆን፣ መስጂዶችን ማስፋፋት፣ መድረሳዎች መገንባት፣ እውነተኛውን የነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) አስተምህሮት ማሰራጨት፣ ከሱስ የፀዳ ሃይማኖቱን እና ሀገሩን የሚጠቅም ትውልድ ማነፅ ይጠበቅብናል፡፡
ይሄ እውነተኛ የነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ውዴታ የሚገለፀበት ተግባር ነው፡፡
አላህ ሱናቸውን ከሚከተሉት ከቢድኣ ከሚርቁት ትውልዶች ያድርገን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
10 532
“መውሊድ”፣ “ክሪስማስ”፣ አሹራ….?
*******************************************
ከነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) እና ሰሃባዎቻቸው በላይ አውቀው ነው ወይ?
ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ነብይ ተደርገው በተላኩ ጊዜ ነሷራዎችም (ክርስትያኖች) ይሁዳዎችም ነበሩ፡፡ ነሷራዎች የኢሳንም ልደት ሲያከብሩ ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) የወንድማቸውን ኢሳ ልደት አንድም ቀን አክብረው አያውቁም፡፡ ምክንያቱም በአላህ አልታዘዙምና፡፡ የነብይም ይሁን የሌላ ግለሰብ የልደት በዓል ማክበር የነብያቶች እምነት እስልምና በፍፁም የሚያውቀው አይደለም፡፡ ልደት ማክበር የእስልምና አካልም አይደለም፡፡በሌላ በኩል ሌላኛው ወንድማቸው ነብየላህ ሙሳን (አለይሂ ሰላም) አስመልክቶ የሁዳዎች አሹራን ሲፆሙ አዩ፡፡ ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) የሁዳዎችን ለምን እንደሚፆሙ ጠየቁ “አላህ ሙሳን እና የእስራኢል ልጆችን ከፊርዐውን ነፃ ያወጣበት ቀን ነው” ሲሉ መለሱላቸው፡፡ ነብዩም (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “እኛ በሙሳ ጉዳይ ከናንተ የበለጠ የተገባን ነን” ብለው አሹራን ፆሙ እንዲፆምም አዘዙ፡፡ እንዲያውም ረመዳን ከመደንገጉ በፊት አሹራ በሙስሊሞች ላይ ግዴታ ነበር፡፡ ከረመዳን በኋላ ይሀው እኛም የሳቸውን ፈለግ በመከተል እንፆመዋለን፡፡ ልክ እንደዚሁ ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “ሰኞ ለምን እንደሚፆሙ” ሲጠየቁ “የተወለድኩበት ቀን ስለሆነ እና ቁርዐን እኔ ላይ የወረደበት ቀን ስለሆነ ነው” ብለዋል፡፡ ታድያ ግዴታ ያልሆነ የሱና ፆም አሹራን በአመት አንዴ እንድንፆመው፣ እሳቸው የተወለዱበትን ቀን እና ቁርዓን የወረደበትን ቀን ሰኞ እንዲሁ በሳምንትን አንዴ ሱና ፆም እንድንፆም ነግረውናል፡፡ የሚያሳዝነው አብዛኛው “መውሊድን” አከብራለሁ የሚል ሰው የታዘዘውን በየሳምንቱ የሚፆመውን ሱና ሲፆም አይታይም፡፡ ይልቁንስ ለምሳሌ “የኢስነይን ሰዎች ነን” እያሉ ሰኞ ሰኞ ጉንጫቸውን በአንደንዛዡ ቅጠል ጫት ወጥረው ሲቅሙ እና ሲጨፍሩ የሚውሉ ሸይጧን የተጫወተባቸው አሉ፡፡ በአመት አንዴ ግን ያልታዘዙትን “መውሊድ” ብለው በማክበር “የኢሳ ልደት” ብለው ከሚያከብሩት ሰዎች ጋር ተመሳስለዋል፡፡ የታዘዙትን ትተው ያልታዘዙትን በመስራት ወደ አላህ እዝነት ሳይሆን ቁጣውን ወደሚያከናንባቸው የሰይጣን መንገድ የሚንደረደሩ ሰዎች ምን አለ ቆም ብለው ቢያስቡ?
አላህ እኮ ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለምን) በመከተል እንጂ ውዴታውን እና ምህረቱን ቃል የገባልን ያላዘዙትን በመስራት አይደለም፡፡ ሸይጧን ደግሞ እንዲህ አሳቢ መስሎ ነው ከጥንት እስከዛሬ ሰዎችን ሲያጠም የነበረው፡፡ አላህ ከተንኮሉ ይጠብቀን፡፡
ሌላው ሰሃባዎች አላህ አማኝ፣ እውነተኞች፣ ወድጃቸዋለሁ እያለ ያወደሳቸው….. ከነሱ መንገድ ውጭ ያለን የሚከተል መንገድ የሳተ፣ ጀሀነምም እንደሚገባ አላህ እና መልክተኛው ነግረውን ሲያበቁ፡፡ ለምን ይሆን መውሊድንም ይሁን ሌሎች ተግባራትን በተመለከተ ሰሃባዎች የቆሙበት ቦታ የማንቆመው?
ሰሃባዎች ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) በህይወት በነበሩ ግዜም ይሁን ሞተው አንድም ቀን የማንንም ነብይ ይሁን የረሱልን (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ልደት አክብረው አያውቁም፡፡
ታድያ እኛ ማን ሆነን ነው ሰሃባዎች ያልሰሩትን የምንሰራው? የአላህን ዲን፣ ንፁሁን የነብዩ ሱና በቢድዐ ለማቆሸሽ፣ የሰይጣንን ተልኮ “ነብዩን መውደድ” በሚል ስም ለማሳካት ደፋ ቀና የሚባለው?
እውነት ሰሃባዎች ነብዩን (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ሳይወዱ ቀርተው ነው የነብዩን መውሊድ ያላከበሩት?
ወይንስ እነሱ ለነብያችን (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ያላቸው ውዴታ ሸሪዐ በደነገገው መልኩ በገንዘብ፣ በህይወት መስዋትነት እና በሌላም ስለገለፁ ነው?
እውነታው እነሱ ስለስርዐት አላቸው፡፡ ይህንን ከሰማይ የወረደ ዲን “እኔ እንደሚመስለኝ” እያሉ ሳይዳፈሩ ያንን ንፁህ ምንም ጭማሪ የማይፈልግ ዲን ለእኛ በሰላም አድርሰዋል፡፡ አላህም ወዷቸዋል፡፡ ዛሬ አላህ ዘንድ ገና ፍርድ ያልተሰጠባቸው ሰዎች ይህን ዲን መጥተው በፈለጉ ጊዜ በቀያየሩት ቁጥር እኛ አብረን የምንቀያየረው አላህን ነው የምናመልከው ወይንስ እነዚህ አላህ ያልደነገገውን የሚደነግጉ ዲን አፍራሾች?
መውሊድ የሸሮች ሁሉ መጠራቀሚያ፣ የሙስሊሞችን አንድነት ማፍረሻ፣ የድሆችብ ንብረት መብያ….. እርኩስ ተግባር ነው፡፡ ሙስሊሞች ሆይ! ራቁት፡፡
አይ ሸይጧን በየዘመኑ መጥፎውን ነገር ጥሩ አስመስሎ ስም እየቀያየረ የአደም ልጆችን ያጠማቸዋል፡፡ ወደ እሳትም ይመራቸዋል፡፡ ተመልከቱ አደም እና ሀዋን ያቺን ዛፍ ስሟን አሳምሮ እንዳትበሉ የተባሉትን አስበላቸው ከዛም ስህተት ውስጥ ጣላቸው፡፡ የኑሕን (አለይሂ ሰላም) ህዝቦች በሞቱት 5 ደጋግ ሰዎች ያዘነ መስሎ መቀማመጫቸው ላይ ሀውልት አሰርቶ ገደል ከተታቸው፡፡ የጠፉበትን እርኩስ ተግባር ሽርክ ውስጥ ዘፈቃቸው፡፡ አሁንም ይህን ኡመት “ለነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ያላችሁን ውዴት ልደቱን አክብሩለት” የሚመስል የሰይጣን ሹክታ እዚህ ኡማ ላይ ተሰራጭቶ የሽርክ መነሃርያ የሆነውን መውሊድ እያከበሩ ወደ እሳት ሲነዱ ይታያሉ፡፡ መውሊድ ላይ ከባባድ የሽርክ ቃላትን ከእስልምና አስፈንጥረው የሚያስወጡ የሽርክ ተግባራት ይታያሉ፡፡ ከነዚህም ውስጥ አላህን ትቶ ፍጡራንን መለመን፣ እነሱን ድረሱልን ብሎ መጣራት፣ አላህን ትቶ ለፍጡራን ስለት መግባት እና የመሳሰሉት ናቸው፡፡
አሳዛኙ ደግሞ ጥመቱን እንደሃቅ፣ ሃቁን እንደ ጥመት ቆጥረው “ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም)፣ ሰሀባዎቻቸው፣ ታቢኢኖች፣ አትባኡታቢኢን፣ 4 አኢማዎች፣ ሙሐዲሶች፣ 3 ምርጥ ክፍለ ዘመን እና ትውልድ አላከበረውም” ሲባሉ ሃቁን ከመቀበል ይልቅ ያልታዘዝነውን አንሰራም ያሉትን “ነብዩን የማይወዱ፣ የነብዩ ጠላቶች፣ ወሃብዬች እና ሌላም” ሲሉ ይደመጣሉ፡፡
ከድጡ ወደ ማጡ ይሉሃል ይህ ነው፡፡ ሸይጧን ግን ዛሬ ጥፋታቸውን እያሸበረቀላቸው ዲንን በዲን ስም እንዲንዱ እየገፋፋቸው ነው፡፡
ነሷራችን በነብየላህ ኢሳ (አለይሂ ወሰለም) ላይ ድንበር አልፈው “የአላህ ልጅ ነው” እንዲሉ ያደረጋቸው የሰው እና የጂን ሰይጣናት ናቸው፡፡ ነሷራች ኢሳን ድንበር ያለፉበት ጠልተውት ሳይሆን ወደውት ነው፡፡ ግን ድንበር አለፉ፡፡ ከልክ በላይ ከፍ ከፍ አደረጉት፣ ያላታዘዙትን ልደቱን አከበሩለት፡፡ ከዚህም ኡማ ነብዩን (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) በመውደድ ስም ሸይጧን መንገድ አስቷቸው ልክ እንደነሷራች ያልታዘዙትን ልደት ማክበር፣ ነብዩን (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “መጣ ያለፈው ወንጀላችንን ማረ”፣ “የሁሉ ቀላቢ”፣ “ልቤ ባንቱ በእርሶ ተመካ” እና የመሳሰሉትን የብቸኛ ፈጣሪና ተመላኪ አላህ መብት አሳልፈው ለነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) በመስጠት ታላቁን ማጋራት እና ቢድዐ ሲሰሩ ይታያል፡፡
ሸይጧን መቼም ለሰው ልጎች ከባድ ጠላታቸው ነው፡፡ አላህ ድንበር ከማለፍ፣ ከሽርክ፣ ከቢድዐ እና አላህ ከጠላው ሁሉ ይጠብቀን፡፡ አላህ ወደ ተውሒድ፣ ሱና፣ የሰለፉነ ሷሊሂን አረዳድ፣ እሱ መልካም ወዳለው ሁሉ ይምራን፡፡
የአላህ ሰላት እና ሰላም በነብያት መደምደሚያ፣ በቤተሰቦቻቸው፣ በባልደረባዎቻቸው እና ሃቅ በተከተለ ላይ ሁሉ ይሁን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
10 532
መውሊድ በበፊት አክባሪዎቹ ሲጋለጥ
ከዚህ በታች የምታነቡት መውሊድ የሚሄድ የነበረ ሰው ይፈፅም የነበረውን ሺርክ፣ አላህን ማመፅ፣ የሙስሊሞች ብር ዘረፋ እንዲህ ሲል ያስቀምጠየዋል
እኔ ገጠር ያደኩ ሥሆን በዛን ጊዜ ሥለድን ከቤተሠቦቼ እንኳን አንዳችንም አናቅ፡፡
ታዲያ መወልድ ደረሠና ሥንቃችንን ይዘን በጧት ተነሥተን ወደ ጀማ ንጉሥ መጎዝ ጀመረን፡፡
ይሄንን ቁልቁለት ሸቅበት በሥንት ጉድ ጨርሠን፡፡
ማታ ጀማ ንጉሥ ገባን፡፡
ከዛ ማታ ህዝቡ እደ ጉድ ተሠብሥቧል፡፡
ከዛ መንዙማ ተከፈተ ሤቱም ወንዱም እደ ዲልቂያ ተደበላልቆ እሥክታ ይመታ ጀመረ፡፡
ብቻ እኔ ሥለድኔም ምንም ባላቅ አልጣመኝምና ወደ ዳሡ ሄጂ ተኛሁኝ፡፡
ጧት ቀሠቀሡኝ እና እንሄድ አሉኝ፡፡
የት አልካቸው?
ወረፉ እንያዝ አሉኝ፡፡
ለምኑ?
ሸሆቹ እየመረቁ ነው እኮ አሉኝ፡፡
ሠልፉን ያዘን ከዛ እበራፉ ላይ ሁለት ጥምጣም የጠመጠሙ እየመረቁ የሄንን ብር ለጉድ ሠብሥበውታል፡፡
ከዛም አልፉ ወደ ቤቱ እየተገባ በመሥኮቱ ወደ ውሥጥ ብር ይወረወራል፡፡
እውሥጥ በድቦራ የተሸፈነ ትልቅ ጎራ የሚመሥል አለ፡፡
በዛ በመሥኮት ባለሀጃው መቶ ሥቅሥቅ ብሉ ያለቅሣል፣ ይለምናል፡፡
የሄንን ካደረጋችሁልኝ ኮርማ አቀርባለው፡፡
ብቻ አምልኮ በሙሉ ለፍጡር ይደረጋል፡፡
እኔ በአይኔ ያየሁት ጉዳይ ነው፡፡ ከዛ ለአንድ ጎደኛየ ይሄንን ነገር ነገርኩትና ያማ በድቦራ የተሸፈነው ቀብር ነው አለኝ፡፡
ጀማ ንጎሥ የሽርክ መነሀሪያ መሆኑን አወኩ፡፡
አሏህ ሽቶልኝ ወደ ሣወዲ አምጥቶ ዲኔን አሣወቀኝ፡፡ ጀህልና ወልቅ ብላ ሄደች አልሀምዱሊላህ እና ይሄንን ለመናገር የፈለኩት አንዳንድ ሠዎች መውሊድ እምናከብረው እና ሥናከብር ድሆችን ለማብላት ቁራአን ለመቅራት ወዘተ ይላሉ ወሸት ነው፡፡
የዚህ ወንድም ምስክርነት በዚህ አበቃ፡፡
ከዚህ የምንወስደው ትምህርት ሀገራችን ላይ
- ሱፊዬች የተውሒድ ሰዎች ናቸው እያሉ የሚያጭበረብሩት ውሸት ነው፡፡ ሱፍዬች ይሀው ሺርክ እና ቢድኣን አስፋፊ ናቸው፣
- መውሊድ ላይ ቀብር አምልኮ ይፈፀማል፣
- የድሆች ብር ይበዘበዛል፣
- ለሆዳቸው የደሩ አሊም ተብየዎች ይህንን ጥፋት በማስፋፋት ላይ የመጀመሪያውን ድርሻ ይይዛሉ፣
- መውሊድ ላይ ነብዩን እናወድስበታለን እያሉ የሚያጭበረብሩት ኪስ አውላቂዎች የነሱን ሀብት ለማዳለብ እንጂ ለነብዩ ውዴታ አይደለም፣
- መውሊድ በሃበሻ ዲን ለመስፋፋት አስተዋፅኦ አድርጓል የሚሉን ሰዎች ውሸታሞች ናቸው፡፡ መውሊድ ይሀው ዲንን አፍራሽ ለመሆኑ ሰሜን አካባቢ የሚሰራውን የአይን እማኞች የተናገሩት ከበቂ በላይ ማስረጃ ነው፡፡
አላህ ኡማውን ከማጭበርበር እና በአጭበርባሪዎች ከመጭበርበር ይጠብቀን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
10 532
ለምንድን ነው የኢሳን (አለይሂ ሰላም)፣ የአቡበክር፣ የኡመርን፣ የኡስማንን፣ የአልይን ልደት የማናከብረው?
እነሱ ስሜታቸውን ተከትለው
‹‹የነብዩን (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ልደት የምናከብረው ለሳቸው ያለንን ውዴታ ለመግለፅ ነው፡፡›› ይላሉ
ጥያቄው
ሙስሊም የሆነ ሰው ነብያትን፣ ሰሃባዎችን መውደድ፣ እናት አባቱን መውደድ፣ ኡለማዎችን መውደድ ግዴታው ነው፡፡ ታድያ ከነብያት ውስጥ ለምሳሌ ከ5ቱ የቁርጠኝነት ባለቤት ከሚባሉት ውስጥ የሆነውን ታላቁን ነብይ ኢሳ (አለይሂ ሰላም) ለሱ ያለንን ውዴታ የምንገልፀው የልደት ቀኑን በማክበር ነውን?
በፍፁም
ሰሃባዎችን እንድንወድ ታዘናል፡፡ ታድያ ለምን የአቡበክር ሲዲቅን፣ የኡመርን፣ የኡስማንን፣ የአልይን ልደት አናከብርም?
መልሱም
ስላልታዘዘ እና በዚህ መንገድ ስላልሆነ ለነሱ ያለንን ውዴታ የምንገልፀው፡፡
ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለምን) ከአላህ ቀጥሎ ከነፍሳችን፣ ከልጆቻችንና፣ ከማንም በላይ አስበልጠን መውደድ አለብን፡፡ ለሳቸው ያለንን ውዴታ የምንገልፀው
1) ያዘዙትን ሁሉ አቅም በቻለው መልኩ በመታዘዝ፣
2) የከለከሉትን ሁሉ በመከልከል፣
3) የተናገሩትን ሁሉ እውነት ነው በማለት፣
4) የተዉትን፣ ያላሳዩንን እኛም በመተው፡፡ ምክንያቱም መልካም ሆኖ ያላሳዩን ነገር የለምና፡፡
5) ሰለዋት በማውረድ እና የመሳሰሉትን
እሳቸው በህይወት በነበሩ ግዜ አላህ ዘንድ የተከበረ፣ የተወደደ፣ ቅርብ የተባለው ወንድማቸውን ኢሳን (አለይሂ ሰላም) ልደት ነሷራዎች ቢያከብሩትም እሳቸው ግን አላከበሩትም፡፡ በጣም የሚወዷት ልጃቸው ፋጢማ (ረድየላሁ አንሃ) ልደቷን አክብረውላት አያውቁም፡፡ ምክንያቱም አላህ እንዳላቸው ‹‹ወዳንተ የተወረደልህን ተከተል›› እሳቸው ከአላህ የታዘዙትን ብቻ ነው የሚከተሉት፡፡
በሸሪዐችን አቂቃ የተባለ አንድ ሰው ሲወለድ ደስታችንን በግለጫ፣ ጌታችንን ማመስገኛ ወንድ ልጅ ከተወለደ 2 በግ፣ ሴት ልጅ ከተወለደች 1 በግ ይታረዳል፡፡ አበቃ፡፡
ታድያ ለነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለምና) ለነዛ ውድ ሰሃባዎች የበቃቸው ዲን ለእኛ አይበቃንምን?
ሱና ላይ እንቁም ከሃቅ በኋላ ጥመት እንጂ ሌላ የለም፡፡ ከሱና በኋላ ቢድዐ እንጂ ሌላ የለም፡፡
‹‹እኛ መውሊድን የምናከብረው ለነብዩ ያለንን ውዴታ ለመግለፅ ነው፡፡›› የሚሉ ሰዎች የሚከተሉት ምርጦች
-) ሙሃጂሮች፣ አንሷሮች፣ 10ሩ የጀነት ሙሽሮች፣
-) ታቢኢኖች፣ አትባኡ ታቢኢን፣
-) ኢማም አቡ ሃኒፋ፣ ኢማሙ ማሊክ፣ ኢማሙ ሻፊኢ፣ ኢማሙ አሕመድ፣
-) ኢማሙል ቡኻሪ፣ ኢማሙ ሙስሊም፣ ነሳኢ፣ አቡ ዳውድ፣ ትርሚዚ፣ ኢብን ማጃ፣ እነ ሱፍያን አሰውሪ፣ እነ አብደላህ ኢብን ሙባረክ፣ እና ሌሎችም ፈርጦች አይወዷቸውም ነበርን ልትሉን ነው?
ወይንም እንዴት ውዴታቸውን መግለፅ እንደነበረባቸው አልገባቸውም ወይንም አያውቁም ልትሉን ነው?
ይልቁንስ መውሊድን የጀመሩት የነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም)፣ የሰሃባዎችና፣ የአማኞች ጠላቶች የሆኑት ሺዐዎች ናቸው፡፡ ይህ ብቻ ይበቃናል ሸር ለመሆኑ፡፡
አላህ ሃቁን ይምራን፣ በሃቅም ላይ ያፅናን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
10 532
ነብዩﷺ የሞቱት ቀን?
ከመውሊድ ድግስ እና በአል በአላህ እጠበቃለሁ፡፡
ነብዩﷺ የሞቱት በረቢዓል አወል 12ኛው ቀን ነው፡፡ ዛሬ መውሊድ አክባሪዎች የደስታ ቀን አድርገው የያዙት ነብዩﷺ የሞቱበትን ቀን ነው፡፡ አላህ እኛንም ዝርያዎቻችንንም ከዚህ ሰይጣናዊ ተግባር ይጠብቀን፡፡ ሸሪዓ ያላዘዘውን መስራት እንዲህ አይነት አዙሪት ውስጥ ይከታል፡፡ ሰራሁ ብሎ ከአላህ ጋር መጣላት፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
10 532
በየሳምንቱ ሰኞ እና ሀሙስ ግዴታ ያልሆነ የሱና ፆም መፆም ወደ አላህ የሚያቃርብ እና ኢስላም የሚያውቀው ነው፡፡
አመት ጠብቆ የነብዩንም (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ይሁን የሌላን ግለሰብ ልደት ማክበር በኢስላም ያልተደነገገ ጥመት ነው፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
