Law studies ⚖️
رفتن به کانال در Telegram
Welcome to Law studies telegram channel ⚖️ This channel is dedicated to helping law students succeed. ✔️ Simple & clear law notes ✔️ Past exam questions & answers ✔️ Key articles & case summaries ✔️ Exam tips & important topics
نمایش بیشترکشور مشخص نشده استدسته بندی مشخص نشده است
347
مشترکین
+224 ساعت
+37 روز
+330 روز
آرشیو پست ها
ከዚህ በፊት በሰ/መ/ቁጥር 249795 ላይ “ሠራተኛዉ በተከታታይ ከ5 ቀናት በላይ ለሆነ ጊዜ ከሥራ ቢቀር እንኳ ከሥራ ለቀረበት ለእያንዳንዱ ቀን አሠሪዉ ማስጠንቀቂያ (Warning in Writing) ሳይሰጥ የሥራ ዉልን ለማቋረጥ እንደማይችል” ተገልጾ የተሰጠው የህግ ትርጉም ተለውጦ “የአዋጅ ቁጥር 1156/2011 አንቀጽ 27(1)(ለ) ድንጋጌ ሠራተኛዉ በዚሁ አዋጅ ከተመለከቱ እረፍቶችና ልዩ ልዩ ፈቃዶች ዉጭ ለአምስት ተከታታይ የሥራ ቀናትና ከዚያ በላይ ለሆነ ጊዜ ከሥራ ላይ ከቀረ የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ (Warning in Writing) መስጠት ሳያስፈልግ የሥራ ዉልን ያለ ማስጠንቀቂያ ማቋረጥ ይቻላል” በሚል ተተርጉሟል፡፡
@law8studies
+2
#Update
የመውጫ ፈተና በድጋሚ በግል ለመፈተን እየተጠባበቃችሁ የምትገኙ አመልካቾች ምዝገባ ከዛሬ ግንቦት 08/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለአምስት ተከታታይ ቀናት ይካሔዳል፡፡
በመሆኑም የመመዝገቢያ ሊንኩን https://exam.ethernet.edu.et በመጠቀምና የተዘረዘሩ መስፈርቶችን በማሟላት ከግንቦት 08-12/2018 ዓ.ም መመዝገብ የምትችሉ መሆኑ ተገልጿል፡፡
የአገልግሎት ክፍያ 750 ብር በቴሌብር በኩል መክፈል የሚጠበቅባችሁ ሲሆን፤ ፈተናውን ለመውሰድ የፋይዳ መታወቂያ የግድ የሚያስፈልግ መሆኑ ተመላክቷል፡፡
የ2018 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ከሰኔ 02-12/2018 ዓ.ም እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት መግለፁ ይታወሳል፡፡
@Law8studies
This helps to explain:
Ethiopia’s strategy against desertification
Drought mitigation
Soil and land restoration
Community participation
Sustainable land management
Use this source for:
Purposes/objectives of the Convention
Principles
Institutional framework
Obligations of member states
COP, Secretariat, CST, CRIC, etc.
Very important Articles:
Article 2 → Objective/Purpose
Article 3 → Principles
Articles 4–6 → Obligations
Articles 22–24 → Institutional framework
+2
በመጪው የትምህርት ዘመን በራስ ገዝነት ሽግግር መመሪያ መሰረት 60 በመቶና ከዚያም በላይ የሚያስመዘግቡ ዩኒቨርስቲዎች ወደ ራስገዝነት እንደሚሸጋገሩ ተገለጸ።
------------------------- // -------------------------
በዛሬው እለት ወደ ራሰ ገዝ ዩኒቨርስቲ ሽግግር የሚገቡ ዩኒቨርስቲዎች የዝግጅት ግምገማ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ለገለልተኛ ገምጋሚ ቡድኑ ተሰጥቷል።
መድረኩ ላይ የተገኙት የከፍተኛ ትምህርት አስተዳደርና መሠረተ ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ ሰለሞን አብርሃ (ዶ/ር) እንደገለጹት ዩኒቨርስቲዎች በአዋጅ ቁጥር1294/2015 መሠረት ወደ ራስገዝነት ሽግግር እንዲገቡ በርካታ ስራዎች ሲሰሩ መቆየታቸውን አንስተዋል።
በተለይም በመጪው የትምህርት ዘመን ዘጠኝ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በተዘጋጀው መሥፈርት መሠረት የራሳቸውን ግለ ግምገማ በማድረግ ለትምህርት ሚኒስቴር ሪፖርት ማቅረባቸውን ጠቁመዋል።
ተቋማቱ ያቀረቡትን ሪፖርት መሠረት በማድረግም የትምህርት ሚኒስቴር ዝግጅቶቻቸውን በሚመለከት ከዩኒቨርስቲዎች በተውጣጡ ፕሮፌሰሮችና ሌሎች ምሁራን ገለልተኛ ግምገማ ለማድረግ ዝግጅት ተጠናቆ ወደ ስራ እየተገባ እንደሆነ ገልጸዋል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ፤ https://www.facebook.com/share/p/1Ft5oDM2q2/
የዲግሪ ሰርተፊኬት ህትመት በአንድ ማዕከል ብቻ ሊከናወን ነው
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተመራቂዎች የዲግሪ ሰርተፊኬት ህትመት በአንድ ማዕከል ብቻ ሊከናወን መሆኑ የትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል።
በሚኒስቴሩ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የአስተዳደርና መሰረተ ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ ሰለሞን አብርሃ (ዶ/ር)እንዳሉት፤ አሰራሩ ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃን ለመከላከል ያለመ ነው፡፡
ከዚህ በፊት ሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጨረታ ባሸነፈ ድርጅት በኩል የተማሪዎችን የትምህርት ማስረጃ የሚያሳትሙበት አሰራር ለሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃ አጋላጭ ሆኖ ቆይቷል ብለዋል፡፡
በመሆኑም ሁሉም የመንግሥት እና የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተማሪዎቻቸውን ዲግሪ በአንድ ማዕከል ብቻ እንዲያሳትሙ ይደረጋል ብለዋል፡፡
አዲሱ ዲግሪ ታትሞ እስኪደርስ ድረስ ትምህርት ሚኒስቴር ዲግሪ ለሚያስፈልጋቸው ተማሪዎች የድጋፍ ደብዳቤ እንደሚጽፍ ገልጸው፤ ህትመቱ በዚህ ዓመት እንደሚጀምር ጠቁመዋል።
በ2017 ዓ.ም የተመረቁ ተማሪዎችን ጨምሮ ከዚህ በኋላ የሚመረቁትም ሙሉ በሙሉ በአዲሱ ስርዓት መሰረት በአንድ ማዕከል የሚታተመውን ዲግሪ ብቻ እንዲወስዱ ይደረጋሉ ብለዋል፡፡
በተመሳሳይ ከ2017 ዓ.ም በፊት ተመርቀው ነገር ግን ዲግሪያቸውን ያልወሰዱ ተማሪዎች በአዲሱ አሰራር ብቻ እንደሚስተናገዱ አመልክተዋል።
@law8studies
በዋስትና ከመፈታት አኳያ አዲሱ የወንጀል ሥነ ሥርዓትና ማስረጃ ሕግ ያመጣቸው አዳዲስ ነገሮች መካከል:-
By Hailu Hasena (Legal Advocate)
1. "ያለ ዋስትና መለቀቅ (Release without bail/unconditional release)" የተሰኘ አዲስ ድንጋጌ አምጥቷል::
በዚህ ድንጋጌ መሠረት ተጠርጣሪው የተጠረጠበትን ወንጀል ስለመፈጸሙ ወይም የተባለው ወንጀል ስለመፈጸሙ አጠራጣሪ (doubtful) በሆነ ጊዜ የወንጀል ምርመራ ጊዜ ቀጠሮ ፍ/ቤትም ሆነ ቀዳሚ ምርመራ አድራጊ ፍ/ቤት ተጠርጣሪውን ያለ ዋስትና እንዲሁ እንዲለቁት ይገደዳሉ:: አንቀጽ 118(4)፣ 137(2)
*በቀድሞው የወ/መሕ/ሥ/ሥ/ቁ. 59(1) እና 93 መሠረት የጊዜ ቀጠሮ እና የቀዳሚ ምርመራ ፍ/ቤቶች ተጠርጣሪው ወንጀል ስለመፈጸሙም ሆነ ወንጀሉ ራሱ ስለመፈጸሙ ቢጠራጠሩም ስንኳ ተጠርጣሪውን የግድ ዋስትና እንዲያስይዝ ወይም በማረፊያ ቤት እንዲቆይ እንዲያዙ ይገደዱ ነበር:: በአዲሱ መድብለ ሕግ ያ አሠራር ተሽሯል::
*ይህ ድንጋጌ በተለይ ለሚታፈሱ ወይም በመመሳጠር በፍ/ብሔር ወይም ወንጀል ባልሆነ ጉዳይ ለሚታሰሩ ሰዎች ይህ ትልቅ የሕግ ጥበቃ የሚያደርግ ነው::
*ስለዚህ የተያዙ ሰዎች የሚለቀቁባቸው መንገዶች እነዚህ ናቸው—ያለ ዋስትና መለቀቅ፣ ያለ ገደብ መለቀቅ፣ በራስ ዋስትና መለቀቅ፣ በንብረት ዋስትና መለቀቅ፣ በሰው ዋስትና፣ በገንዘብ ዋስትና መለቀቅ፣ በተጨማሪ ዋስትና መለቀቅ::
*ስለሆነም ከእንግዲህ የጠበቆች ሥራ የታሰረን ሰው በዋስትና ማስፈታት ብቻ ሳይሆን ያለ ዋስትና ማስፈታትንም ይጨምራል::
*Note: በፍ/ቤት መደበኛ ክስ (charge) የተከፈተ ከሆነ ያለ ዋስትና የመለቀቅ ጉዳይ አይነሣም::
2. በሕግ ዋስትና የሚያስከለክሉ ወንጀሎች (non-bailable crimes)
* በሞት የሚያስቀጡ ወንጀሎች፣ ወይም
* በ ≥15 ዓመት ጽኑ እሥራት የሚያስቀጡ ሰው የሞተባቸው ወንጀሎች ብቻ እንዲሆኑ የተደነገገ ስለሆነ በእንደዚህ ዓይነት ወንጀሎች ውጭ ያሉ ወንጀሎች በሙሉ በሕግ ዋስትና የማያስከለክሉ ወንጀሎች (bailable crimes) ሆነዋል:: አንቀጽ 138(2,3)
ስለሆነም:-
➡️ስለሆነም በሕግ ዋስትናን በማይከለከልባቸው ወንጀሎች በመሉ ተጠርጣሪዎች/ተከሳሾች በዋስትና የመለቀቅ መብት አለው::
➡️በዕድሜ ልክ ወይም የጽኑ እሥራት ጣሪያ በሆነው በ25 ጽኑ እሥራት የሚያስቀጣ ወንጀል ብቻውን ዋስትናን አያስከለክልም::
➡️በማንኛውም የሙስና ወንጀል የተጠረጠረ/የተከሰሰ ሰው በሕግ ዋስትናን አይከለከልም—all corruption crimes have become bailable.
ከዚህ ቀደም በዐዋጅ ቁ. 434/1997 (በዐዋጅ ቁ. 882/2007 እንደተሻሻለ) አንቀጽ 4(1) መሠረት "ከ10 ዓመት በላይ በሚያስቀጣ የሙስና ወንጀል የተጠረጠረ ወይም የተከሰሰ ሰው በዋስትና አይለቀቅም በማለት ከ10 ዓመት በላይ የሚያስቀጡትን ለይቶ non-bailable corruption crimes ተደርጎ የነበረው ድንጋጌ ቀሪ (abolished) ተደርጎአል::
➡️በአደገኛ ቦዘኔነት ዐዋጅ ቁጥር 384/96 አንቀጽ 6(3) "በአደገኛ ቦዘኔነት ተጠርጥሮ የተያዘ ሰው በዋስትና አይለቀቅም:" ተብሎ በወንጀል ዓይነት ዋስትና ይከለከል የነበረው (categorical bail denial) ዘፈቀዳዊ ነው ተብሎ በዚህ ዐዋጅ ተሽሮአል::
➡️በሕግ ዋስትና የማያስከለክሉ ወንጀሎችን (bailable crimes) አስመልክቶ ዋስትና መብት (right) ሲሆን ዋስትና ሊከለከልም ሊፈቀድም የሚችለው በዳኞች ፍቅድ ሥልጣን (judicial discretion) ነው::
ፍቅድ ሥልጣኑ የሚመራባቸው መርኆዎችም ደግሞ "ዳኛው ተጠርጣሪውን/ተከሳሹን በዋስትና ይለቃል የሚል ግምት (presumption of release on bail) ይወሰዳል:"፤ "ዋስትናን በሁኔታ የሚያስከለክሉ ሁኔታዎችም አይኖሩም: ተብሎ ይገመታል::"
"ዋስትናን ለመከልከል የሚያበቁ ልዩ ሁኔታዎች በጠባቡ እና ለተከሳሽ/ተጠርጣሪ በሚጠቅም መልኩ ይተረጎማሉ:" የሚሉ ናቸው—ከተመድ የሰብኣዊ መብቶች የዋስትና መብት ትርጉም አኳያ::
ለምሳሌ:- ተጠርጣሪው በዋስ ቢወጣ ሌላ ወንጀል ይፈጽማል ወይም ማስረጃ ያጠፋል ወይም በተፈለገ ጊዜ አይቀርብም ወይም ቋም አድራሻ የለውም ወይም መውጣቱ ለኅ/ሰቡ ደኅንነት ያሰጋል ወይም የዋስትና ግዴታውን አይወጣም ወዘተ. የሚል ግምት አይያዝም::
ስለሆነም መርማሪ ፖሊስ ወይም ዐቃቤ ሕግ እነዚህን መርኀዊ ግምቶች ለማስተባበልና ለመሠረታዊ መብቶች (የነጻነት መብት፣ ንጹሕ ሆኖ የመገመት መብት) የሥነ ሥርዓታዊ ጥበቃ የሆነውን የዋስትና መብት ለመቃወም ሕጋዊ፣ በቂ እና አሳማኝ ምክንያት ያለ መሆኑን በቂ ማስረጃ በማቅረብ ማስረዳት ይኖርበታል::
3. የድኅረ ጥፋተኝነት ፍርድ ዋስትና (Post-conviction bail) የተሰኘ አዲስ ድንጋጌ አምጥቷል::
አንቀጽ 301(2)
ይህ ድንጋጌ ተከሳሹ በተከሰሰበት ወንጀል ጥፋተኛ ነህ ተብሎ ከተፈረደበት በኋላ የቅጣት ውሳኔ እስኪተላለፍበት ድረስ ባለው ጊዜ በዋስትና እንዲቆይ የሚያደርግ ነው::
ይሁንና ይህ ዋስትና የሚሠራው ወንጀሉ በመቀጮ ብቻ የሚያስቀጣ ሲሆን ነው::
እንደሚታወቀው በነባሩ የወ/ሕ/ሥ/ሥ መሠረት ዳኞች የፈረዱበትን ማንኛውንም ሰው ቅጣቱ እስኪወሰን ድረስ 'ታስሮ' እንዲቆይ ያዙ ነበር—በጣም ጥቂት ሰብኣዊነት ላይ የተመሠረተ ልዩነት ቢኖርም::
ለዚህ እንደ ምክንያት ይጠቀስ የነበረው የዋስትና መብት ንጹሕ ሆኖ ከመገመት መርኅ ጋር ብቻ የተቆራኘ ስለሆነ ተከሳሹ ጥፋተኛ ሲባል መብቱም ዐብሮ ቀሪ ይሆናል፣ ጥፋተኛ ከተባለ በኋላ በዋስትና ቢወጣ ሊጣልበት የሚችለውን ቅጣት ፈርቶ ላይቀርብ ስለሚችል የሚጣለው ቅጣት አፈጻጸም ችግር እንዳይገጥመው የሚል ግምት በመያዝ ነበር::
ይሁንና ሁለቱም ምክንያቶች የተሳሳቱ እና የሕግ ፍልስና መሠረት የሌላቸው ስለሆኑ በሥሡ ለማረም ተሞክሯል::
*ለምሳሌ በፌስታል ዐዋጅ ቁ. 1383/2017 አንቀጽ 25(1/ሀ) ሥር ፌስታል በመጠቀም ወይም ለመጠቀም ይዞ በመገኘት ወንጀል ተከሶ የጥፋተኛነት ፍርድ የተሰጠበት ተከሳሽ የቅጣት ውሳኔ እስኪሰጥ ድረስ በማረፊያ/በማቆያ ቤት እንዲቆይ አዲሱ ሕግ አይፈቅድም
አንድ የመንግስት ሰራተኛ በተከሰሰበት የዲስፕሊን ጥፋት ምክንያት ከስራ እንዲሰናበት ካልተወሰነበት በስተቀር ከስራ በታገደበት ወቅት ሳይከፈለው የቀረው ደመወዝ የሚከፈለው ስለመሆኑ ። ቅፅ 24 መዝገብ ቁጥር 161880
በአዲሱ የፌዴራል መንግስት ሠራተኞች አዋጅ ቁጥር 1353/2024 (2025) መሰረት፡
የመንግስት ሰራተኛ በዲስፕሊን ጥፋት ምክንያት ከስራ ሲታገድ፣ በእግዱ ጊዜ ደመወዙ ሊቆም ይችላል።
በመጨረሻ ከስራ እንዲሰናበት ውሳኔ ካልተወሰነበት (ወይም ውሳኔው ካልተረጋገጠ)፣ በእግዱ ወቅት ያልተከፈለው ሙሉ ደመወዝ ያለ ወለድ መከፈል አለበት።
@law8studies
https://t.me/exitetbot?start=ref_1819391277
I've been studying with Exit ET and it's amazing! 🎓
Join me and get 5 bonus free questions:
ትዕዛዝ፣ ብይን፣ ፍርድና ውሳኔ
===================
ትእዛዝ (order ) ,,,ብይን ( Ruling ) ,, ፍርድ (Judgement ),,ዉሳኔ ( Decision /Decree )
እነዚህ አራት ቃላት በሕግና በፍርድ ቤት የሥራ ሂደት ዉስጥ ተመሳሳይ ቢመስሉም የራሳቸው የሆነ የተለየ የሕግ ትርጉምና ደረጃ አላቸው ,,,,,,,,
1, ትእዛዝ ( Order )
" ትእዛዝ " ማለት አንድ የፍርድ ቤት ክርክር ከመጀመሩ በፊት ወይም በሂደት ላይ እያለ ፍርድ ቤቱ አንድን ነገር እንዲደረግ ወይም እንዳይደረግ የሚሰጠው መመሪያ ነው ።
ባህሪው
ጉዳዩ መዝጋት ወይም መጨረስ ሳይሆን ለሂደቱ መቀላጠፍ የሚሰጥ ነው ።
ለምሳሌ :
"ይህ ንብረት ለጊዜው እንዳይሸጥ እንዳይለወጥ ታግዶል " ወይም " ተከሳሽ ለቀጣይ ቀጠሮ ምስክሮች ይዞ ይቅረብ " የሚሉ መመሪያዎች ትእዛዝ ይባላል ።
2, ብይን ( Ruling )
" ብይን" የሚሰጠው በክርክሩ ሂደት ዉስጥ ለሚነሱ መከራከሪያ ነጥቦች ( Interlocutory matters ) ምላሽ ለመስጠት ነው ።
ባህሪው
ዋናው የክርክር ዉጤት ( ማን አሸነፈ ? ማን ተሸነፈ ?) ሳይሆን በመሀል የሚነሱ የህግ ክርክሮችን ለመወሰን ነው ።
ለምሳሌ ;
" ፍርድ ቤቱ ይህንን ክስ ለማየት ስልጣን አለው / የለዉም " ወይም " ክሱ በይርጋ ይታገዳል / አይታገድም " የሚለው ዉሳኔ ብይን ይባላል ።
ብይን ብዙ ጊዜ ክርክሩን አያበቃዉም ይልቁንም ሂደቱን ይቀጥላል ።
3, ፍርድ ( Judgement )
" ፍርድ " ማለት ፍርድ ቤቱ የቀረበለትን ማስረጃዎች መርምሮ ; የግራ ቀኙን ክርክር ሰምቶና መዝኖ የሚሰጥ የመጨረሻ ድምዳሜ ነው ።
ባህሪው
ፍርድ ቤቱ በጉዳዩ ላይ የደረሰበትን የሐቅና የህግ ድምዳሜ በዝርዝር የሚያስቀምጥበት ሰነድ ነው ።
ለምሳሌ ;
" ከሳሽ የንብረቱ ባለቤት መሆናቸውን ፍርድ ቤቱ አረጋግጧል "
የሚለው ሰነድ ፍርድ ነው
4,ዉሳኔ ( Decision /Decree )
" ዉሳኔ " በፍርድ ላይ ተመስርቶ የሚሰጥ ተግባራዊ ትዕዛዝ ነው ።
በፍርድ መደምደሚያ ላይ " በዚህ መሠረት ",,,,,,,,,ተብሎ የሚቀመጠው ነጥብ ነው ።
ባህሪው
በፍርድ የተረጋገጠውን መብት ወይም ግዴታ ለይቶ የሚያስቀምጥና ተፈፃሚ የሚሆን ነው ።
ለምሳሌ ;
ፍርዱ " ከሳሽ ባለቤት ናቸው " ካለ,,,,,
ዉሳኔዉ " ተከሳሽ ቤቱን ለከሳሽ በአንድ ወር ጊዜ ዉስጥ ያስረክቡ" የሚለው የመጨረሻ ትዕዛዝ ነው ።
ማጠቃለያ / ልዩነት
/ቃል/ ትኩረት / መቼ ይሰጣል ?
# ትእዛዝ
ለስራ ሂደት መመሪያ መስጠት
በማንኛውም ጊዜ
# ብይን
በመሀል ለሚነሱ መከራከሪያዎች መልስ መስጠት
በሂደት ላይ
# ፍርድ
ማስረጃ መዝኖ ድምዳሜ ላይ መድረስ
በክርክሩ ማብቂያ
# ዉሳኔ
መብትና ግዴታን ለይቶ መወሰን
በፍርድ መጨረሻ
#ጠበቃ እስከዳር አወቀ
"""""""""""""""""""""""""""""""
ሰባት (7) ዳኞች በተሰየሙበት ችሎት የተሰጠ አስገዳጅ የሰበር ውሳኔ: መዝገብ ቁጥር 236212
ከዚህ ቀደም በሰ/መ/ቁጥር 50835 “በአንድ መዝገብ ላይ የተሠጠ ውሳኔ ከተፈፀመ በኋላም ቢሆን በውሳኔው መብቱ የተነካበት 3ኛ ወገን በሌላ መዝገብ ላይ ክስ አቅርቦ መብቱን ማስከበር ይችላል “ በሚል እንዲሁም
በሰ/መ/ ቁጥር 67127 “በፍርድ ቤት የተሰጠው ውሳኔ መብቴን ይነካል የሚል ሰው በዚያው መዝገብ ላይ የመቃወም አቤቱታ አቅርቦ መብቱን ማስከበር ከሚችል በቀር ዉሳኔዉ በአፈጻጸሙ ከተቋጨ በኋላ በሌላ መዝገብ ላይ አዲስ ክስ ማቅረብ አይችልም፤ በእንደዚህ ዓይነት ሁኔታ የቀረበ ክስ ተቀብሎ ውሳኔ መስጠትም መሠረታዊ የሕግ ስህተት ነው” በሚል የተሰጡት አስገዳጅ ውሳኔዎች ተሻሽለዋል፡፡
ሰባት (7) ዳኞች በተሰየሙበት ችሎት በመዝገብ ቁጥር 236212፡
“አንድ ሰዉ መብቱን የሚነካ ዉሳኔ የተፈጸመ እንደሆነ አዲስ ክስ በማቅረብ መብቱን ማስከበር የሚችለዉ፣ ከአቅም በላይ ወይም በቂ በሆነ ምክንያት ዉሳኔዉ ከመፈጸሙ በፊት መብቱን የሚነካ ዉሳኔ ስለመኖሩ ማወቅ ባለመቻሉ ወይም በተመሳሳይ ምክንያት መቃወሚያ ማቅረብ ያልቻለ መሆኑ ሲረጋገጥ ነው” ተብሎ ተሻሽሎ ተተርጉሟል፡፡
@law8studies
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
+1
#ETHIOPIA #WTO
የነዳጅ መኪናዎች ይገቡ ይሁን ?
የኢትዮጵያ መንግስት ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት (WTO) አባል ለመሆን የምታደርገውን ጥረት ለማሳለጥ ሲል በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች ላይ ጥሎት የነበረውን የማስመጣት እገዳ ሊያነሳ እንደሚችል ዘ ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል።
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ላይ በተካሄደው 7ኛው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት የሥራ ቡድን ስብሰባ ላይ እንደገለጹት የነዳጅ የተሽከርካሪዎች አመጣጥ ገደብ በድጋሚ ከሚታዩ ጉዳዮች መካከል አንዱ ነው።
ሚኒስትሩ ለሥራ ቡድኑ አባላት ፤ " የአሮጌ ልብሶች ማስገባት ላይ የነበረውን እገዳ አንስተን ከድርጅቱ (WTO) መስፈርቶች ጋር በሚጣጣም መልኩ ተግባራዊ በሚሆን የጉምሩክ ቀረጥ ተክተነዋል። አባልነቱ ከመጽደቁ በፊት በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች እና ባለሦስት እግር ተሽከርካሪዎች ላይ ያለውን ገደብ በተመለከተም ተመሳሳይ አካሄድ ለመከተል አስበናል " ማለታቸውን ጋዜጣው ዘግቧል።
የፌደራል መንግስት በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች ወደ አገር እንዳይገቡ እገዳ የጣለው እ.ኤ.አ በ2024 መጀመሪያ ላይ ሲሆን ይህም ኢትዮጵያ ወደ ኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች (EV) ለማድረግ ያቀደችው የኃይል ሽግግር አካል ነበር። ሆኖም የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት መስፈርቶች የነዳጅ ተሽከርካሪዎች ዳግም እንዲገቡ ሊያደርጉ ይችላሉ።
በንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ፥ የዓለም አቀፍ ንግድ ተደራዳሪ የሆኑት አቶ ታገስ ሙሉጌታ ለሪፖርተር ጋዜጣ እንደገለጹት፣ የድርጅቱ ሕግጋት ኢትዮጵያ እገዳውን እንድታነሳ ቢያስገድዳትም ይህ ማለት ግን አሰራሩ ወደ 2024ቱ ነባራዊ ሁኔታ ይመለሳል ማለት አይደለም።
አቶ ታገስ ፤ " በዓለም ንግድ ድርጅት መስፈርት መሠረት አገራት የንግድ ልውውጥን መገደብ አይችሉም። አባል መሆን ከፈለግን ምርቶች እንዳይገቡ መከልከል አንችልም። የሸቀጦች ነጻ ዝውውር የድርጅቱ መሠረታዊ መመሪያ ነው። ሚኒስትሩም በቀጣይ እርምጃዎች ኢትዮጵያ በተሽከርካሪዎች ላይ ያለውን ገደብ እንደምታነሳ መግለጽ ፈልገው ነው " ብለዋል።
" ይህ ማለት ግን የነዳጅ መኪኖች ወደ ኢትዮጵያ እንዲገቡ ሙሉ በሙሉ እንፈቅዳለን ማለት አይደለም " ያለቱ አቶ ታገስ " የነዳጅ መኪኖች መግባታቸውን ተስፋ የሚያስቆርጡ ሌሎች እርምጃዎችን እንወስዳለን። የገንዘብ ሚኒስቴር እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ወደፊት በዚህ ላይ ተወያይተው ይወስናሉ " ብለዋል።
" የአካባቢ ጥበቃ ስጋቶች እና እንደ ታክስ ያሉ እርምጃዎች የነዳጅ መኪኖችን ማስገባት ተስፋ ለማስቆረጥ ሊቀርቡ ይችላሉ። ስለዚህ እገዳው ለድርድር ሲባል ሊነሳ ይችላል እንጂ በቴክኒክ ደረጃ የነዳጅ መኪኖች እንዲገቡ ሙሉ በሙሉ ይፈቀዳል ወይም ወደ ቀድሞው ሁኔታ እንመለሳለን ማለት አይደለም " ሲሉ አስረድተዋል።
ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅትን ለመቀላቀል የጀመረችው የ23 ዓመታት ጥረት ባለፈው አንድ ዓመት ውስጥ እስክግ ትልቅ እድገት አሳይቷል።
ካሳሁን (ዶ/ር) ድርድሩ አሁን " ወሳኝ ምዕራፍ " ላይ መሆኑን ገልጸዋል።
እ.ኤ.አ በመስከረም 2025 ከተካሄደው ስብሰባ በኋላ በአባላት የቀረቡ ጥያቄዎችን ለመመለስ ጥረት እየተደረገ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ከ10 ያነሱ የሁለትዮሽ ስምምነቶች ብቻ መቅረታቸው ተነግሯል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህ መረጃ ያገኘው ከሪፖርተር እንግሊዝኛ ጋዜጣ ነው።
ሚያዚያ 24 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
