الفوائد/Al fawaid/ አልፈዋኢድ
رفتن به کانال در Telegram
السلام عليكم ورحمة الله وبركاته እንኳን ወደ አል-ፈዋኢድ ቻናል በሰላም መጡ! እዚህ የተለያዩ ደርሶችን፣ ማስታወሻዎችን፣ ቲላዋዎችን እና መልእክቶችን ያገኛሉ። ቻናሉን በመከታተል እና ለሌሎች በማስተላለፍ ተጠቃሚ ይሁኑ። "በመልካም ነገር ላይ ያመላከተ እንደ ሰሪው ነው" https://t.me/fawaid_00
نمایش بیشترکشور مشخص نشده استدسته بندی مشخص نشده است
226
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز
آرشیو پست ها
የማለዳ መልእክት
#17
ዚክርعَنْ أَبِي الدَّرْدَاءِ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُ قَالَ: قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ: "أَلَا أُنَبِّئُكُمْ بِخَيْرِ أَعْمَالِكُمْ، وَأَزْكَاهَا عِنْدَ مَلِيكِكُمْ، وَأَرْفَعِهَا فِي دَرَجَاتِكُمْ، وَخَيْرٍ لَكُمْ مِنْ إِنْفَاقِ الذَّهَبِ وَالْوَرِقِ، وَخَيْرٍ لَكُمْ مِنْ أَنْ تَلْقَوْا عَدُوَّكُمْ فَتَضْرِبُوا أَعْنَاقَهُمْ وَيَضْرِبُوا أَعْنَاقَكُمْ؟" قَالُوا: بَلَى يَا رَسُولَ اللَّهِ. قَالَ: "ذِكْرُ اللَّهِ تَعَالَى". (رواه الترمذي وابن ماجه وأحمد) ከአቢ ደርዳእ በተላለፈ ሐዲስ እንዲህ ብሏል: የአላህ መልእክተኛﷺ እንዲህ ብለዋል: “ከስራዎቻችሁ ሁሉ በላጭ የሆነውን(ስራ) አልነግራችሁም!?; ይህ(ስራ) የሁሉ ተቆጣጣሪ የሆነው አላህ ዘንድ የጠራ የሆነ፤ ደረጃችሁን ከፍ የሚያደርግ፤ የወርቅ እና ብር ሰደቃ ከመስጠት ለናንተ የተሻለ የሆነ፤ ጠላቶቻችሁን ተገናኝታችሁ አንገታቸውን ከምትመቷቸው ወይም አንገታችሁን ከሚመቷችሁ የተሻለ የሆነ!?» ሶሓቦችም; “እንዴታ! ንገሩን እንጂ የአላህ መልእክተኛ ሆይ!” አሉ; የአላህ መልእክተኛምﷺ : «ከፍ ያለውን አላህ ማውሳት(ዚክር ማድረግ) ነው።» አሉ። ቲርሚዚይ ኢብኑ ማጀህ እና አሕመድ ዘግበውታል።
የዕለተ ረቡእ የአደብ ተከታታይ ትምህርት ክፍል - 3
የ الآداب العشرة/ አስሩ አደቦች ማብራሪያ
الْأَدَبُ الثَّانِي: إِذَا دَخَلْتَ عَلَى أَحَدٍ فَاسْتَأْذِنْ، وَاقِفًا عَن يَمِينِ الْبَابِ أَو يَسَارِهِ، فَإِنْ أَذِنَ لَكَ دَخَلْتَ، وَإِن قِيلَ لَكَ ارْجِعْ فَارْجِعْ.ሁለተኛው አደብ: አንድ ሰው ጋር ስትገባ ከበሩ በቀኝ ወይም በግራ በኩል ቆመክ አስፈቅድ፤ ግባ ከተባልክ ግባ፤ ተመለስ ከተባልክ ተመለስ።
ማብራሪያ፦
ይህ አደብ
የማስፈቀድ አደብ
በመባል የሚጠራ ሲሆን በውስጡ
አራት(4)
ነጥቦችን ይዟል; 1ኛው. إِذَا دَخَلْتَ عَلَى أَحَدٍ فَاسْتَأْذِنْ/ አንድ ሰው ጋር ስትገባ አስፈቅድ የሚለው አ.ነገር ሲሆን;
-.
ከዚህም በተለምዶ ዝግ ሆነው ወይም ተንኳኩቶ ፈቃድ ተጠይቆ የሚገባባቸው ክፍሎች፣ ቢሮዎች እና መሰል ቦታዎችን ይመለከታል(ልቅ ተደርገው ሰዎች ያለፈቃድ ገብተው መገልገል የሚችሉባቸው ቦታዎችን አያካትትም)
2ኛው. وَاقِفًا عَن يَمِينِ الْبَابِ أَو يَسَارِهِ/ በግራ በኩል ቆመክ አስፈቅድ የሚለው አ.ነገር ሲሆን;
-. ከበሩ ፊት ለፊት መቆማችን ሊያስከትል የሚችለውን ያለ አግባብ ማየት የሌለብንን ነገር ማየትን ያስቀራል።
3ኛው. فَإِنْ أَذِنَ لَكَ دَخَلْتَ/ ከተፈቀደልክ ግባ የሚለው አ.ነገር ሲሆን;
-. ከመግባት በፊት ፈቃድ መሰጠት እንዳለበት ይጠቁማል።
4ኛው. وَإِن قِيلَ لَكَ ارْجِعْ فَارْجِعْ/ ተመለስ ከተባልክ ተመለስ የሚለው አ.ነገር ሲሆን;
-. ተመለስ የተባለ ሰው ካልገባው ብሎ ችክ ሊል ወይም ቅር ሊሰኝ እና መሰል ያልተገቡ ድርጊቶችን ሊፈፅም እንደማይገባ እንይዛለን።
* በጥቅሉ አንድ ሰው ጋር ለመግባት ስናስፈቅድ 3 አይነት ምላሾች አሉ
፦ 1, ፈቃድ ማግኘት -
በዚህ ጊዜ እንገባለን
2,ዝምታ -
እንመለሳለን
3, ተመለስ መባል -
እንመለሳለንhttps://t.me/fawaid_00
የማለዳ መልእክት
#16
ዚክርعَنْ عَائِشَةَ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهَا قَالَتْ: كَانَ النَّبِيُّ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ يَذْكُرُ اللَّهَ عَلَى كُلِّ أَحْيَانِهِ» رواه مسلم وأبو داوود والترمذي وابن ماجة ከዓኢሻህ በተላለፈ ሐዲስ, እንዲህ ብላለች: ነቢዩﷺ አላህን በሁሉም ሁኔታቸው ያወሱ(ዚክር ያደርጉ ነበር» ሙስሊም፣ አቡ ዳዉድ፣ ቲርሚዚይ እና ኢብኑ ማጀህ ዘግበውታል።
የዕለተ ማክሰኞ የፊቅህ ተከታታይ ትምህርት ክፍል - 3
ዉዱእን የሚያበላሹ ነገሮች
ሶስት ናቸው። እነሱም፦
1. ከሁለቱ ሀፍረተ ገላዎች የሚወጣ ነገር
2. ዓቅል በእንቅልፍ፣ እብደት፣ ራስን በመሳት ወይም በስካር ምክንያት ከጠፋ
3. የግመል ስጋ መብላት ናቸው።
https://t.me/fawaid_00
"كَبِّرُوا لِيَبْلُغَ تَكْبِيرُكُمْ عَنَانَ السَّمَاءِ،ተክቢራችሁ የሰማይ ጣሪያ እስከሚደርስ ድረስ ተክቢራ አድርጉ
كَبِّرُوا
فَإِنَّ
اللَّهَ
عَظِيمٌ
يَسْتَحِقُّ
الثَّنَاءَአላህ ትልቅ ነው ሊመሰገን እና ሊወደስ ይገባዋል እና ተክቢራ አድርጉ
أَكْثِرُوا
مِنَ
الْأَعْمَالِ
الصَّالِحَةِ،መልካም ስራን አብዙ
وَتَزَوَّدُوا
مِنْ
سَاعَاتِ
هَٰذِهِ
الْأَيَّامِ
وَلَيْلِهَا،በነዚህ ቀናት እና ለሊቶች ያሉ ሰአታትን መልካም ስራን ተሰነቁባቸው
فَهِيَ
تِجَارَةٌ
رَابِحَةٌ.ምክንያቱም ይህ(መልካም ስራ) አትራፊ ንግድ ነው
وَاعْلَمُوا
أَنَّ
لِلَّهِ
تَعَالَىٰ
نَفَحَاتٍለአላህ የእዝነትና የችሮታ እድሎች እንዳሉት እወቁ
فَاسْتَكْثِرُوا
مِنَ
الصَّالِحَاتِ، ስለዚህ መልካም ስራን አብዙ
وَتَطَهَّرُوا
مِنْ
دَنَسِ
الْمَعَاصِي
وَالسَّيِّئَاتِ . ከወንጀል እና ከመጥፎ ስራ ቆሻሻም ፅዱ إِنَّ الْعُمْرَ لَا يَعُودُ، ያለፈ እድሜ አይመለስም وَالْمَوْسِمَ لَا يَدُومُ. እነዚህ የመልካም ስራ እድሎችም አይዘወትሩም وَتَزَوَّدُوا فَإِنَّ خَيْرَ الزَّادِ التَّقْوَىٰ ۚ وَاتَّقُونِ يَا أُولِي الْأَلْبَابِ. " «(የመልካም ስራን ስንቅ) ተሰነቁ፤ ከስንቆች ሁሉ በላጩ አላህን የመፍራት ስንቅ ነው፤ እናንተ የልቦና ባለቤቶች ሆይ! እኔን ፍሩኝ»
የማለዳ መልእክት
#15
ምድብህ/ሽን ምረጥ/ጪ
{{يٰأَيُّهَا الَّذِينَ ءَامَنُواْ اتَّقُواْ اللَّهَ وَلْتَنظُرْ نَفْسٌ مَّا قَدَّمَتْ لِغَدٍۖ وَاتَّقُواْ اللَّهَۚ إِنَّ اللَّهَ خَبِيرٌۢ بِمَا تَعْمَلُونَ}}
«እናንተ ያመናችሁ ሰዎች ሆይ! አላህን ፍሩ፤ ነፍስ ሁሉ ለነገ(የቂያመህ ቀን) ያዘጋጀችውን ትመልከት፤ አላህን ፍሩ! አላህ በምትሰሩት ነገር የውስጥ አዋቂ ነው»
-. አላህን መፍራት ማለት ያዘዘውን መታዘዝና የከለከለውን መራቅ ማለት ነው። -. ቂያማህ ቅርብ መሆኑን ሩቅ አርገን እንዳንዘናጋ እየተነገረን ነው። -. የሰው ልጅ ለዚህ ቀን ያዘጋጀውን ነገር ከአሁኑ መመርመር እንዳለበት ጥቆማ አለ። -. አላህ የውስጥ አዋቂ ስለሆነ የምንሰራውን ስራ ለአላህ ብቻ አጥርተን መስራት እንዳለብን ተጠቁሟል።{{وَلَا تَكُونُواْ كَالَّذِينَ نَسُواْ اللَّهَ فَأَنسَىٰهُمْ أَنفُسَهُمْۚ أُوْلَٰٓئِكَ هُمُ الْفَٰسِقُونَ}} «እንደነዚያ አላህን በመርሳታቸው የተነሳ ነፍሳቸውን ያስረሳቸው እንደሆኑ ሰዎች አትሁኑ፤ እነሱ አመፀኞች ናቸው»
-.
አላህን መርሳት ማለት፦ ትልቅነቱን መርሳት፤ ትእዛዙን እና ክልከላውን ችላ ማለት ማለት ነው። -. ነፍሳቸውን አስረሳቸው ማለት፦ ለራሳቸው እንዳያስቡ ይልቁንስ የማትጠቅም እና አላቂ በሆነችው ዱንያ እንዲጠመዱ አደረጋቸው ማለት ነው።{{لَا يَسْتَوِىٓ أَصْحَٰبُ النَّارِ وَأَصْحَٰبُ الْجَنَّةِۚ أَصْحَٰبُ الْجَنَّةِ هُمُ الْفَآئِزُونَ}} «የእሳት ሰዎች እና የጀነት ሰዎች አይገናኙም; የጀነት ሰዎች እነሱ ናቸው ድልን የተጎናፀፉት»
-.
አላህን የረሱ ሰዎች የእሳት ተብለው ሲገለፁ አላህን ፈርተው ለነገ የተዘጋጁ ሰዎች የጀነት እና ትልቅን ድል የተጎናፀፉ ተብለዋል
የዕለተ ሰኞ የዓቂዳ ትምህርት ክፍል - 3
نواقض الإسلام - እስልምናን የሚያበላሹ ተግባራት
النَّاقِضُ الثَانِي: مَن جَعَلَ بَيْنَهُ وَبَيْنَ اللهِ وَسَائِطَ، يَدْعُوهُمْ، وَيَسْأَلُهُمُ الشَّفَاعَةَ، وَيَتَوَكَّلُ عَلَيْهِمْ كَفَرَ إِجْمَاعًا.2ኛው እስልምናን የሚያበላሽ ተግባር፦ ከአላህ እና ከእሱ መካከል ወሳኢጥ ያደረገ; እነሱን(ወሳኢጦቹን) የሚለምን፤ ምልጃ(ሸፋዓህ) የሚጠይቅ፤ በነሱ የሚመካ ሰው; በሁሉም ዑለሞች ስምምነት መሰረት ከእስልምና ይወጣል(ይከፍራል)። ማብራሪያ፦ «مَن جَعَلَ بَيْنَهُ وَبَيْنَ اللهِ وَسَائِطَ»: ወሳኢጥ(وَسَائِطَ) የሚባለው በአንድ ባሪያ እና በአላህ መካከል የሆነን ነገር የሚያደርስ ሲሆን; ለሁለት ይከፈላል፦ 1ኛ. ሸሪዐው የደነገገው ማድረስ፦ ይህን ስራ የሚሰሩት ነቢያት፣ መልእክተኞች እና የነሱ ወራሽ የሆኑት ዑለሞች ሲሆኑ; የአላህን ትእዛዝና ክልከላ ወደ ባሮች ያደርሳሉ(በማስተማር)። ይህ ሸሪዓችን የደነገገው ሲሆን ይህም ያስተባበለ(አልቀበልም ያለ) ይከፍራል። 2ኛው. ሺርክ የሆነው ማድረስ፦ ይሄ ከላይ እንደተጠቀሰው ለአላህ ብቻ የሚገቡ አምልኮዎችን ከአላህ ውጪ ላሉ አካላት በመስጠት(በነሱ በኩል ካለሆነ አላህ አይሰማኝም እና መሰል ምክንያት በማቅረብ) ወደ አላህ ለመቃረብ መሞከር ሲሆን ይሄ ሺርክ ነው። «يَدْعُوهُمْ» ዱዐእ ዒባዳአ ሲሆን ; ሁለት ክፍሎች አሉት: 1ኛው. «دعاء العبادة» የአምልኮ ዱዐእ፦ ለአላህ የተለያዩ አምልኮዎችን በመፈፀም ምንዳቸውን ከአላህ መፈለግ ማለት ነው። 2ኛው. «دعاء الطلب» የጥያቄ ዱዐእ፦ የምንፈልገውን ነገር ቀጥታ አላህን የምንጠይቅበት(ማረኝ፣ ጀነት አስገባኝ… ) የዱዐእ አይነት ነው።
እነዚህ ሁለቱንም የዱዐእ አይነቶች ከአላህ ውጪ ላለ አካል መስጠት ሺርክ ነው።«وَيَسْأَلُهُمُ الشَّفَاعَةَ» ሸፈዐህ(ምልጃ የሚጠየቀው አላህ ብቻ ሲሆን; ከአለአህ ውጪ ላለ አካል መስጠት ሺርክ ይሆናል። «وَيَتَوَكَّلُ عَلَيْهِمْ» ተወኩል፦ በሸሪዐ የተፈቀዱ ሰበቦችን ከማድረስ ጋር በአላህ መደገፍ እና ነገሮችን ወደሱ ማስጠጋት ሲሆን; ከአላህ ውጪ ላለ አካል መስጠት ሺርክ ይሆናል። ይቀጥላል… https://t.me/fawaid_00
የማለዳ መልእክት
#14
ذو الحجة ٧/ዙል ሒጃህ 7
عَنْ عَبْدِ اللَّهِ بْنِ قُرْطٍ، عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ: "إِنَّ أَعْظَمَ الأَيَّامِ عِنْدَ اللَّهِ تَبَارَكَ وَتَعَالَى يَوْمُ النَّحْرِ، ثُمَّ يَوْمُ الْقَرِّ"رواه أحمد وأبو داوود.
ከዐብዲላህ ኢብኑ ቁርጥ በተላለፈ ሓዲስ የአላህ መልእክተኛ እንዲህ ብለዋል: «ከቀናት ሁሉ አላህ ዝንድ በላጩ የውሙ ነሕር ነው(ዙል ሒጃህ 10)፤ ከዛም የውሙል ቀር ነው(ዙል ሒጃህ 11)»አሕመድና አቡዳውድ ዘግበውታል።
ማስታወሻ፦ የውሙ ነሕር ማለት የእርዱ ቀን ማለት ሲሆን; ሑጃጆችም ሆኑ ሌሎች ሙስሊሞች በዛ ቀን የተለያዩ ትላልቅ ዒባዳዎችን ስለሚፈፅሙ ነው በላጭ የተባለው ተብሏል። የውሙል ቀር ማለት ደግሞ የማረፊያው ቀን ማለት ሲሆን; ሑጃጆች በ10ኛው ቀን የተለያዩ ዒባዳዎችን ከፈፀሙ በኋላ ሚና ሄደው ድንኳኖቻቸው ላይ የሚያርፉበትና የሚረጋጉበት ስለሆነ ይህ ስያሜ ተሰጥቶታል።
ሳዑዲ ላይ ጨረቃ በመታየቷ የዙልሒጃ ወር ነገ(ሰኞ) አንደኛው ቀን ነው የሚሆነው፤ በዚህም መሰረት 9ኛው(የዓረፋ ቀን) ቀጣይ ሳምንት ማክሰኞ ይሆንና ረቡእ ዒድ ይሆናል
የማለዳ መልእክት
#13
ذو الحجة ٦/ ዙል ሒጀህ 6
عن أبي قتادة رضي الله عنه، أن النبي ﷺ سُئِلَ عَن صَوْمِ يَوْمِ عَرَفَةَ فَقَالَ:«صِيَامُ يَوْمِ عَرَفَةَ، أَحْتَسِبُ عَلَى اللهِ أَنْ يُكَفِّرَ السَّنَةَ الَّتِي قَبْلَهُ، وَالسَّنَةَ الَّتِي بَعْدَهُ».رواه مسلم
ከአቢ ቀታደህ በተላለፈ ሐዲስ ነቢዩ ﷺ የዓረፋህ ቀን(9ኛውን የዙል ሒጃህ ቀን) ስለመፆም ተጠይቀው «የዓረፋን ቀን መፆም; አንድ አመት ያለፈን፤ አንድ አመት የሚመጣን ወንጀል ያስምራል ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ» ብለዋል። ሙስሊም ዘግበውታል።
ማስታወሻ፦ የዓረፋ ቀን የሚገኘው ከፊታችን ባሉት የዙል ሒጃህ 10 ቀናት ውስጥ መሆኑ የነዚህን ቀናት ደረጃ ትልቅነት ይጠቁመናል።
Repost from "زاد المعاد" ዛዱልመዓድ- የነገው ስንቅ
ማስታወሻ
ነገ ቅዳሜ (ግምቦት 8/ 2018) የዙልቀዕዳ የመጨረሻ ቀን ሊሆን ስለሚችል ኡድሒያ የማረድ እቅድ ያለው ሰው ከሰውነቱ መነሳት የሚያስፈልጋቸው ፀጉሮችንና ጥፍሩን ዛሬ እና ነገ እስከ ከመግሪብ በፊት ባሉ ሰዓቶች አስቀድሞ ማንሳት ይጠበቅበታል።
ነቢዩ صلى اللہ عليہ وسلم
"የዙልሒጃ ወር ጨረቃን ካያችሁ ከእናንተ ውስጥ ኡዱሒያ ለማረድ የሚያስብ ሰው ፀጉሩንና ጥፍሩን ከመቁረጥ ይታቀብ" ብለዋል።
ዛዱል መዓድ
https://telegram.me/ahmedadem
የማለዳ መልእክት
#12
ذو الحجة ٥/ ዙል ሒጀህ 5
عَنْ عَبْدِ اللَّهِ بْنِ عُمَرَ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُمَا، عَنِ النَّبِيِّ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ قَالَ: "مَا مِنْ أَيَّامٍ أَعْظَمُ عِنْدَ اللَّهِ وَلَا أَحَبُّ إِلَيْهِ الْعَمَلُ فِيهِنَّ مِنْ هَذِهِ الْأَيَّامِ الْعَشْرِ، فَأَكْثِرُوا فِيهِنَّ مِنَ التَّهْلِيلِ وَالتَّكْبِيرِ وَالتَّحْمِيدِ"
(رواه أحمد)
ከዐብዱላህ ኢብኑ ዑመር (ረዲየላሁ ዐንሁማ) እንደተወራው የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦ "ከእነዚህ (ከዙልሒጃ) አስር ቀናት ይልቅ አላህ ዘንድ መልካም ስራዎች ላቅ ያለ ደረጃ የሚያስገኙበት እና ይበልጥ የሚወደዱበት ሌሎች ቀናት የሉም። ስለዚህ በእነዚህ ቀናት ውስጥ ተህሊል (ላ ኢላሀ ኢለላህ)፣ ተክቢር (አላሁ አክበር) እና ተሕሚድ (አልሀምዱሊላህ) ማለትን አብዙ።"
ማስታወሻ፦ ሐዲሱ ለአይ የተጠቀሱት ተህሊል፣ ተክቢር እና ተሕሚድ አባባል፦ «الله أكبر الله أكبر، لا إله إلا الله الله، اكبر الله اكبر، ولله الحمد» ማለት ነው።
የማለዳ መልእክት
#11
ذو الحجة ٤/ ዙል ሒጀህ 4
عَنْ جَابِرِ بْنِ عَبْدِ اللَّهِ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُمَا، عَنِ النَّبِيِّ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ أَنَّهُ قَالَ: «أَفْضَلُ أَيَّامِ الدُّنْيَا أَيَّامُ الْعَشْرِ» - يَعْنِي عَشْرَ ذِي الْحِجَّةِ - قِيلَ: وَلَا مِثْلُهُنَّ فِي سَبِيلِ اللَّهِ؟ قَالَ: «وَلَا مِثْلُهُنَّ فِي سَبِيلِ اللَّهِ، إِلَّا رَجُلٌ عُفِّرَ وَجْهُهُ بِالتُّرَابِ»رواه البزار وصححه الألبانيከጃቢር ቢን ዐብዱላህ (ረዲየላሁ ዐንሁማ) እንደተወራው፤ የአላህ መልዕክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦ «ከዱንያ ቀናት ሁሉ በላጮቹ (የዙልሒጃ) አስሩ ቀናት ናቸው።» «በአላህ መንገድ (ከሚደረግ ጂሃድ) ጋርም ቢሆን አይስተካከሉም?» ተብለው ተጠየቁ። እሳቸውም፦ «አዎ! በአላህ መንገድ ከሚደረግ ጂሃድም ጋር ቢሆን አይስተካከሉም፤ ፊቱ በአፈር የተለወሰ (የተሰዋ) ሰው ቢሆን እንጂ» በማለት መለሱ። በዛር ዘግበውታል አልባኒይ ሶሒሕ ብለውታል።
የዕለተ ረቡእ የአደብ ተከታታይ ትምህርት ክፍል - 2
የ “ الأدب العشرة " / አስሩ አደቦች ማብራሪያ
የኪታቡ ፀሓፊ፦ الشيخ صالح العصيمي/ሸይኽ ሷሊሕ ዑሶይሚይ
الْأدَبُ الْأَوَّلُ: إِذَا لَقِيتَ مُسْلِمًا فَيسَلِّمْ عَلَيْهِ قَائِلًا: «السَّلَامُ عَلَيْكُمْ وَرَحْمَةُ اللهِ وَبَرَكَاتُهُ»، وَإن سَلَّمَ عَلَيْكَ فَقُلْ «وَعَلَيْكُمُ السَّلَام وَرَحْمَةُ اللهِ وَبَرَكَاتُهُ».የመጀመሪያው አደብ፦ ሙስሊምን ስትገናኝ «አሰላሙ ዐለይኩም ወራሕመቱላሂ ወበረካቱህ» በማለት ሰላምታን አቅርብ፤ ሰላምታ ከቀረበልክ «ወዐለይኩም ሠላም ወራሕመቱላሂ ወበረካቱህ» በማለት መልስ።
ማብራሪያ
፦ የመጀመሪያው አደብ
የሰላምታ አደብ
ሲሆን በውስጡ ሶስት ነጥቦችን ይዟል። እነሱም፦ 1. «ሙስሊምን ስትገናኝ…ሰላምታን አቅርብ» የሚለው አ.ነገር ማንኛውንም ሙስሊም ስንገናኝ ሰላምታ ማቅረብ ሱና መሆኑን መገናኘት እስከተባለ ድረስ በአካልም ይሁን በሌላ(እንደ ስልክ) ያለውንም ያካትታል። 2. ሰላምታ ለማቅረብ የምንጠቀመው አ.ነገር “አሰላሙ ዐለይኩም ወራሕመቱላሂ ወበረካቱህ» ነው። 3. ሙስሊሞች ሰላምታ ሲያቀርቡ ሰላምታን መመለስ ግዴታ ሲሆን የምንመልሰውም «ወዐለይኩም ሠላም ወራሕመቱላሂ ወበረካቱህ» በማለት ነው።
ማስታወሻ
-.
ሰላምታን ማቅረብ ሱና ሲሆን ሰላምታን መመለስ ግን ግዴታ ነው። -. በፅሁፍ ሰላምታን በምናቀርብ ጊዜ አሳጥሮ መፃፍ የተከለከለ ነው።https://t.me/fawaid_00
የማለዳ መልእክት
#010
ذو الحجة ٣/ ዙል ሒጃህ 3
عَنِ ابْنِ عَبَّاسٍ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُمَا، قَالَ: قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ: «مَا مِنْ أَيَّامٍ الْعَمَلُ الصَّالِحُ فِيهَا أَحَبُّ إِلَى اللَّهِ مِنْ هَذِهِ الْأَيَّامِ» - يَعْنِي أَيَّامَ الْعَشْرِ - قَالُوا: يَا رَسُولَ اللَّهِ، وَلَا الْجِهَادُ فِي سَبِيلِ اللَّهِ؟ قَالَ: «وَلَا الْجِهَادُ فِي سَبِيلِ اللَّهِ، إِلَّا رَجُلٌ خَرَجَ بِنَفْسِهِ وَمالِهِ، فَلَمْ يَرْجِعْ مِنْ ذَلِكَ بِشَيْءٍ»رواه البخاري وأبو داوود والترمذي وابن ماجة.ከኢብኑ ዐባስ በተላለፈ ሐዲስ እንዲህ ብለዋል: የአላህ መልእክተኛ እንዲህ ብለዋል: «መልካም ስራዎች ይበልጥ አላህ ዘንድ ተወዳጅ የሚሆኑበት ቀን እንደነዚህ አስርቱ ቀናት(የዙልሒጃህ) የለም።» አንቱ የአላህ መልእክተኛ በአላህ መንገድ ላይ ጂሀድ ማድረግም ቢሆን? ብለው ሲጠይቋቸው; «ነፍሱንም ገንዘቡንም ይዞ ወጥቶ ያልተመለሰ ሰው ሲቀር ከጂሀድም ቢሆን» ብለዋል” ቡኻሪ፣ አቡ ዳውድ፣ ቲርሚዚይ እና ኢብኑ ማጀህ ዘግበውታል።
ከሐዲሱ
-. በነዚህ ቀናት መልካም ስራን ማብዛት እንደሚገባ፣ ደረጃው ከፍ ያለ መሆኑ ስለተጠቀሰ -. በሐዲስ ከተጠቀሱት ውጪ የተለየ ዒባደህ በነዚህ ቀናት ውስጥ እንደሌለ( የትኛውንም ስራ መስራት ተብሎ ነው የተጠቀሰው)
የዕለተ ማክሰኞ የፊቅህ ተከታታይ ትምህርት ክፍል - 2
የዉዱእ ማእዘናት
ስድስት ናቸው። እነሱም፦
1. ፊትን መታጠብ፦ መጉመጥመጥ እና በአፍንጫ ውሀን ማስገባትም ይካተታል።
ፊት የሚባለው፦ በቁመት፦ ከፀጉር መብቀያ - አገጭ ሲሆን ወደ ጎን ከጆሮ ጫፍ - ጆሮ ጫፍ ነው።2. እጅን ማጠብ፦ ክርን/ክንድንም ጭምር 3. ሙሉ ራስን ማበስ፦ ጆሮዎችም ይካተታሉ 4. እግርን ማጠብ፦ ቁርጭምጭሚትም ጭምር 5. ቅ/ተከተል መጠበቅ 6. በዉዱእ አካላት መካከል ማከታተል(አንዱን የዉዱእ አካል ካጠቡ ቡሀላ ሳይቆዩ ወደ ቀጣዩ መሄድ)
ማስታወሻ
፦
የዉዱእ ሸርጥ(መስፈርት)
፦
ማለት ዉዱእ ከመጀመራችም በፊት ልንፈፅመው የሚገባ ተግባር ሲሆን ከዚህ ተግባር አንዱ ከጎደለ ያደረግነው ዉዱእ ትክክል አይሆንም
የዉዱእ ማእዘን
፦
ማለት ዉዱእ ስናደርግ የምንፈፅማቸው ተግባራት ሆነው በምንም ሁኔታ ልንተዋቸው የማይገባ እና እነሱን የተወ ዉዱኡው የሚበላሽበት ተግባራት ናቸው።
የማለዳ መልእክት
#009
ذو الحجة ٢ - ዙል ሒጃ 2
عَنْ جَابِرٍ رضي الله عنه أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ ﷺ قَالَ: "أَفْضَلُ أَيَّامِ الدُّنْيَا أَيَّامُ الْعَشْرِ" رواه ابن حبان والبزار وأبو يعلىከጃቢር በተላለፈ ሐዲስ የአላህ መልእክተኛ እንዲህ ብለዋል: «ዱንያ ላይ ካሉ ቀናቶች በላጩ አስርቱ(የዙልሂጃ) ቀናት ናቸው።» ኢብኑ ሒባን፣ በዛር እና አቡ የዕላ ዘግበውታል
የዕለተ ሰኞ የዓቂዳ ትምህርት ክፍል - 2
نواقض الإسلام - እስልምናን የሚያበላሹ ተግባራት
النَّاقِضُ الْأَوَّلُ - الشِّرْكُ فِي عِبَادَةِ اللهِ تَعَلَى وَالدَّلِيلُ قَولُهُ تَعَلَى {إِنَّ اللهَ لَا يَغْفِرُ أَن يُّشْرَكَ بِهِ وَيَغْفِرُ مَا دُونَ ذَلِكَ لِمَن يَشَاءُ، وَمَن يُّشْرِكْ بِاللهِ فَقَدِ افْتَرَى إِثْمًا عَظِيمًا} سورة النساء، وَمِنْهُ الذَّبْحُ لِغَيْرِ اللهِ تَعَلَى كَمَن يَذْبَحُ لِلْجِنِّ أَوْ لِلْقَبْرِ.የመጀመሪያው እስልምናን የሚያበላሽ ተግባር፦ አላህን በማምለክ ላይ ማጋራት ነው። ማስረጃውም እንዲህ የሚለው የአላህ ቃል ነው፦ {አላህ በሱ ያጋራን አይምርም፤ ከዛ(በአላህ ላይ ማጋራት) ውጪ ያለን ወንጀል ለፈለገው ሰው ይምራል፤ በአላህ ላይ ያጋራ ሰው ትልቅ ወንጀልን ሰርቷል} ሱረቱ ኒሳእ -. ከሺርክ ምሳሌዎች መካከል ከአላህ ውጪ ላለ አካል ማረድ ነው። ልክ እንደ ጂን ወይም ቀብር ላሉት ማረድ ማለት ነው። الشرك - ማለት የሆነን የአላህ ሐቅ ከአላህ ውጪ ላለ አካል መስጠት ማለት ነው። العبادة - ማለት አምልኮ ማለት ሲሆን፤ አላህ የሚወደው ማንኛውም ንግግር እና ተግባር መጠሪያ ስም ነው። ሺርክ የመጀመሪያ ደረጃ የተጠቀሰበት ምክንያት፦ ጉዳቱ ከፍተኛ ስለሆነ እና ብዙ ሰዎች ጋር ተሰራጭቶ ስለሚገኝ ነው ። ከሺርክ ጉዳቶች መካከል -. አላህ አይምረውም -. ትልቅ ወንጀል ነው -. ትልቅ ጥመት ነው -. ጀነትን እርም ያደርጋል -. ጀሀነም ያስገባልም ያስዘወትራልም -. ትልቅ በደል ነው
ማስታወሻ፦
አላህ ሺርክን አልምርም ሲል ሺርክን የሰራው ሰው ተውበት ሳያደርግ የሞተ ከሆነ ነው፤ እንጂ እዚህ ዱንያ ላይ አላህ የማይምረው ወንጀል የለም።https://t.me/fawaid_00
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
