fa
Feedback
HOP Ministry

HOP Ministry

رفتن به کانال در Telegram

HOP Ministry — Hear. Obey. Practice. A discipleship platform sharing devotionals, revival histories, spiritual biographies, testimonies, and Amharic Christian literature to build Christ-like lives. Based on Luke 11:28.

نمایش بیشتر
کشور مشخص نشده استدسته بندی مشخص نشده است
445
مشترکین
+224 ساعت
+237 روز
+6630 روز
آرشیو پست ها
እንደ እኛ ሳይሳቀቅ የሚኖር፣ የሚያስፈልገውም ሁሉ የሚደረግለት፣ ዘላለማዊ አምላክ መኖርያው የሆነ፣ የዘላለም ክንዶቹም ከሥሩ ያሉት ማን ነው?! 📖 Hear. Obey. Practice. #HOPMinis
+7
እንደ እኛ ሳይሳቀቅ የሚኖር፣ የሚያስፈልገውም ሁሉ የሚደረግለት፣ ዘላለማዊ አምላክ መኖርያው የሆነ፣ የዘላለም ክንዶቹም ከሥሩ ያሉት ማን ነው?! 📖 Hear. Obey. Practice. #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional t.me/hopministry10

አንተን_ተጠግቼ_ኤፍሬም_ዳኜ_with_lyrics_efrem_dagne_old_song128k.m4a5.07 MB

#ሳበን_ከአንተ_ኋላ_እንሮጣለን! ምህረት እና ቸርነት ተከትሎት በሕይወት የኖረ፣ መንገዱም የቀናለት ሰው አረማመዱ፣ አካሄዱ ያስታውቃል። በእሳት ውስጥ አልፎ እዚህ ቢደርስ እንኳ፤ ዛሬ ስለ እሳቱ ኃይል አያወራም፤ በእሳቱ ውስጥ ሲያልፍ አብሮት ስለነበረው፣ ስላዳነውም እግዚአብሔር እንጂ። ሳንሸማቀቅ፣ ሳናፍር፣ እውነት መሆንኽ ገብቶን የምንከተልህ ኢየሱስ። አንተን በዚህች ሕይወት ብቻ ተስፋ አናደርግኽም፤ እስከወዲያኛው ታዋጣናለህ፣ ታዛልቀናለህ። እንደ እኛ ሳይሳቀቅ የሚኖር፣ የሚያስፈልገውም ሁሉ የሚደረግለት፣ ዘላለማዊ አምላክ መኖርያው የሆነ፣ የዘላለም ክንዶቹም ከሥሩ ያሉት ማን ነው?! ኢየሱስ በብርሃንህ ብርሃን አይተናል፤ በቸርነትህ ሕይወት ሆኖልናል። ከእርግጠኝነት ውጪ በሆነች Uncertainty በሞላባት ከንቱ ዓለም አንድ እውነት፣ አንድ ሕይወት፣ አንድ መንገድ ማግኘት፤ ማወቅ፣ እርሱን ታምኖ መከተልም እንዴት መታደል ነው?! መቼ እንደምትጠፋ እና ብርሃኗም እንደሚጨልም በማይታወቅ ዓለም ውስጥ እየኖሩ እውነተኛውን ብርሃን ማወቅ፣ በብርሃኑም ለዘላለም መኖር ምንኛ መልካም ነው?! ትናንት ስፍስፍ ያልንላቸው፣ ልናገኛቸው የጓጓንና የተከታተልናቸው ነገሮች ሁሉ በእጃችን ሲገቡ፦ ጣዕም አጡ፣ ቀለውም ተገኙ። ኢየሱስ አንተ ግን በቀረብንህ ቁጥር በራህልን፣ ፍቅርህም እያደር ጠናብን፣ እየወደድንኽ መኖር ስራችን፣ ተድላችንም ሆነ። ቸር መሆንህን ቀምሰናልና ላንለይህ የፍቅርህ ምርኮኛ ሆነናል። አሁንም አንድ ትሁት ልመና አለን፦ ሳበን ከአንተ ኋላ እንሮጣለን። ታዋጣናለህ፣ ፍቅርህም ያዛልቀናልና አንተን የሙጥኝ እንላለን። ሳበን ከአንተ ኋላ እንሮጣለን! ሳበን ከአንተ ኋላ እንሮጣለን! ሳበን ከአንተ ኋላ እንሮጣለን! ሳበን ከአንተ ኋላ እንሮጣለን! ✍️ መክሊት አየለ 📆 June 15, 2026 #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional

#የእግዚአብሔር_ቃል! የእግዚአብሔር ቃል ለሕይወታችን እና ለትምህርታችን የተጻፈ፣ የተሰጠን ሕያው ቃል ነው። ከእግዚአብሔር ቃል ጋር ጊዜ መውሰድ የእግዚአብሔርን አሳብ መቅዳት ነው፤ የእግዚአብሔርን የልብ አሳብ ማወቅ ነው። “የእግዚአብሔር ቃል ሕያውና የሚሠራ ነውና፤ በሁለት በኩል ስለት ካለው ሰይፍ ሁሉ ይልቅ ስለታም ነው፤ ነፍስንና መንፈስን፣ ጅማትንና ቅልጥምን እስኪለያይ ድረስ ዘልቆ ይወጋል፤ የልብንም ሐሳብና ምኞት ይመረምራል።”   — ዕብራውያን 4፥12 (አዲሱ መ.ት) ✍️ መክሊት አየለ 📆 June 14, 2026 #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional

የእግዚአብሔርቃል.mp32.91 MB

እግዚአብሔር ክፍተታችን፣ ጉድለታችን፤ ሙላታችንም ነው። 📖 Hear. Obey. Practice. #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional t.me/hopministry10

#ክፍተታችንን_በልባችን_ሰሪ_መሙላት! ክፍተታችንን፣ ጉድለታችንን እግዚአብሔር ያውቀዋል፣ ሆነ ብሎም ሰርቶታል፤ ደግሞ እርሱ ብቻ ይሞላዋል፣ በእርሱ ብቻ ይሞላል። ልብን በሚያዝል፣ በሚያጎድል፣ ብርታት በማይሰጥ፣ በሚያደርቅ፣ ወከባ እና ግርግር በበዛበት ዓለም እየኖርን ልባችንን መሙላት፣ ማሳረፍ፣ መደገፍ፣ መጠበቅ የምንችለው በልባችን ሰሪ፣ ሙሉ አድራጊ፣ በክፍተታችን በእግዚአብሔር ብቻ ነው። ክፍተታችን፣ ጉድለታችን እግዚአብሔር፤ የሚሞላው፣ አሳራፊያችንም ያው እርሱ ነው፤ አይደለም ጉድለታችንን ሊሞላው ይቅርና ልባችን ላይ ጠብ ብሎ በማያርሰን ነገር ክፍተታችንን ለመሙላት እንባክን። ይልቁንም ሙላታችን፣ ሁሉ በሁሉ ወደ ሆነው ወደ እግዚአብሔር አብዝተን እየተጠጋን በሙላት እንኑር። ✍️ መክሊት አየለ 📆 June 12, 2026 #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional

9_Azeb_Hailu_6_Feligut(128k).m4a5.77 MB

🔐 #Our_Quality_Time_with_God ከአምላክ ጋር እንደመዋል፣ ከእግዚአብሔር ጋር እንደመቆየት፣ በእርሱ መገኘት ውስጥ ለመክረም ሁሉን ከመጣልና ወደ እርሱ ከመገስገስ ጋር የሚገናኝ ሌላ መልካም እድል የለም። ትናንትን፣ ከትናንት ወዲያን፣ አምናን አቻምናን ወደ ኋላ ዘወር ብለን አይተን ከእግዚአብሔር ጋር የነበርንበትን ጊዜ፣ ፊቱን የፈለግንበትን ወቅት ብንመረምር ብዙ የጸሎት ፍቅር፣ የማይረሳ የእግዚአብሔር መገኘት፣ በእግዚአብሔር ፊት ያለዝለት እንድንንበረከክ የሚያደርግ የፊቱ ረሃብ ሊኖረን ይችላል። ዛሬ ላይ ቆመን ራሳችንን ስናይ ግን ያ ያኔ የተነካንበት መነካት እግዚአብሔርን ደግሞ ላለመፈለግ በቂ ሆኖ ከፊቱ ሲያርቀን አላየንም፤ ይልቁንም ያ መነካት ሌላ እልፍ ረሃብ ወልዶ፣ ጥቂት የቀረብነው እግዚአብሔር ከምንም ነገር በላይ ልንቀርበው የተገባ ብቸኛው ክፍተታችን መሆኑን ተረድተን፣ ያለ እርሱ ህልውና መኖር ለነፍሳችን ክሳት መሆኑን አውቀን፣ ጸሎትና  የእግዚአብሔርን ፊት መፈለግ የማይለመድ ዋና ነገራችን መሆኑ ገብቶን በእግዚአብሔር እግር ስር አለን። የጸሎት ትልቁ ስራውና ዋና ጥቅሙ እኛን ከእግዚአብሔር ጋር ከማጣበቁ የተነሳ በእግዚአብሔር ፍቅር የተያዙ፣ ከመጸለይና ፊቱን ከመፈለግ ውጪ ሌላ አማራጭ የሌላቸው የእግዚአብሔር ወዳጆች ማድረጉ ነው። የዛሬው መቃተት፣ የዛሬው በእግዚአብሔር ፊት መቆየት ለነገው ፍለጋ አቅም የሚወልድ፣ የጸሎትን ረሃብ ዘር በልባችን የሚዘራ ትልቅ መነሻ ነውና ነገን በብዙ እግዚአብሔርን ለመፈለግ ዛሬን በእግዚአብሔር ፊት እንቆይ፤ ዛሬ ከጸለይን ነገን ሳንጸልይ መዋል ይከብደናል፣ የለመድነው የእግዚአብሔር ጠረን ሊያባክኑን ከሚጥሩ ብዙ ነገሮች መሃል አልፎ ስለሚሸተን ሁሉን ጥለን ወደ እርሱ፣ ወደ ፊቱ፣ ወደ ህልውናው ለመገስገስ አቅም ይሆነናል። እየጸለይን እንጸልይ!! ✍️ መክሊት አየለ 📆 November 10, 2023 #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional

የጸሎት ትልቁ ስራውና ዋና ጥቅሙ እኛን ከእግዚአብሔር ጋር ከማጣበቁ የተነሳ በእግዚአብሔር ፍቅር የተያዙ፣ ከመጸለይና ፊቱን ከመፈለግ ውጪ ሌላ አማራጭ የሌላቸው የእግዚአብሔር ወዳጆች ማድረጉ ነው። 📖 Hear. Obey. Practice. #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional t.me/hopministry10

📖 Hear. Obey. Practice. “ወደ እርሱ የሚመለከቱ ያበራሉ፤ ፊታቸውም ከቶ አያፍርም።” — መዝሙር 34፥5 (አዲሱ መ.ት) “ወደ እርሱ ቅረቡ ያበራላችሁማል፥ ፊታችሁም አያፍርም።” — መዝ
📖 Hear. Obey. Practice. “ወደ እርሱ የሚመለከቱ ያበራሉ፤ ፊታቸውም ከቶ አያፍርም።”   — መዝሙር 34፥5 (አዲሱ መ.ት) “ወደ እርሱ ቅረቡ ያበራላችሁማል፥ ፊታችሁም አያፍርም።”   — መዝሙር 34፥5 #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional t.me/hopministry10

ቤተልሔም_ወልዴ_አንተ_ብቻህን_በቂ_ነህ_Ante_Bchahin_Beki_Neh_Bethelihem_wolde.m4a4.78 MB

#ምስክርነቴ! እግዚአብሔር እንዴት ልጆቹን ማሳደግ እንዳለበት ያውቃል። የራሱ የሆነ መመሪያ (Manual)፣ ጥበብ፣ አሠራር፣ አመራር፣ ስርዓት፣ መግቦት፣ ምክር፣ ትምህርት፣ ተግሳጽ አለው። እርሱ ቤት ከመጣኹ፣ በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ልጁ ከሆንኹ ጀምሮ አቀማጥሎ ነው ያሳደገኝ፤ ከሚያስፈልገኝም ነገር አንዳች አላጎደለብኝም። እርሱን በግርግር መሃል፣ ብዙ ነገሮች በከበቡኝ ጊዜ አላወቅኹትም። የከበቡኝን ነገሮች ከዙሪያዬ ገለል አድርጎ ለብቻዬ ሲያስቀረኝ ግን በግል፣ በግልጥ አጊኝቼዋለሁ፣ አውቄዋለሁ። እኔ እና እርሱ ለብቻችን ሆነን ያሳየኝ ፍቅሩ፣ የገለጠልኝ ማንነቱ፣ እኔን የነካበት መንካት፦ እርሱ ጋር ተጠግቼ እንድኖር፣ በፍቅሩ ታስሬ እንድቀር አድርጎኛል። ያ ማንም ከእኔ ጋር በሌለ ሰዓት ያቀመሰኝ አብሮነቱ ከግርግር ገሸሽ እያልኹ በሬን እንድዘጋ፣ ልሰማውም በእግሮቹ ሥር እንድሆን ምክንያት ሆኖኛል። በዚህ መንገድ ከእርሱ ጋር ስኖር ሳለሁ ሰው ነኝና ቆይ እስት አሁን ደግሞ ወጣ ብዬ ውጪውን ልይ፣ አዲስ ነገር ካለ ልፈልግ፣ እንደዚህ #ችክ፣ #ግግም ብሎ እግዚአብሔር፣ እግዚአብሔር ማለቱን ገታ ላድርግ ብዬ በሬን ዘግቶ ከእርሱ ጋር መቀመጥ፣ ፊቱን ፊቱን ማለት ሳቆም ሁሉ ነገር ጨለማ ሲለብስ፣ አንድ እርምጃ ነው ብዬ የጀመርኹት #Walk  ጭልጥ አድርጎ ሲወስደኝ፣ ለብታ ላዬ ላይ ቤቱን ሲሰራ፣ መንፈሳዊ ረሃቤ ሲከስም፣ እግዚአብሔርን መፈለግ ዳገት፣ ሬት ሲሆንብኝ ራሴን አገኘሁ። እኔው ራሴ እስቲ ልየው፣ አንድ ቀን አይደል? ዛሬ ባልጸልይና ቃሉን ባላነብስ? ትንሽ አረፍ ብልስ? ብዬ የጀመርኹት ጉዞ ረሃቤንና በውስጤ ያለውን መሻት ሙጥጥ አድርጎ ጨርሶ አእምሮዬ ጊዜ የለኝም የሚለውን ውሸት እንዲቀበል፤ ለስንፍናዬም ምክንያት እንድደረድር አደረገኝ። በዚህ ሁሉ ውስጥ ሳልፍ የውስጥ ሰውነቴ በድካም ሲማቅቅ፣ እግዚአብሔርን አለመፈለጉና አለመጠጋቱ ልቤን ሲከነክነው ይሰማኛል። ከጉትጎታው ትንሽ ልረፍ ብዬ በእግዚአብሔር ፊት በርከክ ለማለት፣ ቃሉንም ገለጥ አድርጌ ለማየት ስሞክር ትልቅ ዓለት እንደተጫነው ሰው ሸክም ይሆንብኛል፤ ለመቀጠልም አቅም አጣ እና ትቼው እነሳለኹ። ይሄ አዙሪት ምርኮዬን በስንፍና እና በቸልታዬ እንዳስወሰድኹ፣ ለማስመለስም እንዳቃተኝ አምኜ እግዚአብሔር ፊት እስክመጣ፣ እንዳመመኝ፣ ለመፈወስና ለማገገምም በራሴ አቅም እንዳጣሁ ለእግዚአብሔር እስክነግረው ድረስ ቀጠለ። የልቤን ሕመም፣ የውስጤን ስብራት ለብቸኛው አካሚዬ የነገርኹት ዕለት ግን እርሱ በእውነት በፊቱ ለሚቀርቡ፣ ለሚመለሱ፣ ልባቸውን በትህትና፣ ሰብረው ለሚያቀርቡለት #ቅርብ መሆኑን ተማርኹበት። ሲረዳኝም አየሁት። አሁን የተወሰደውን ምርኮዬን ለማስመለስ፣ የደከመውን ጉልበቴን ለማበርታት፣ የደረቀ የውስጥ ሰውነቴን ለማለምለም፣ በፊቱም በደስታ ለመቅረብ ራሱ እግዚአብሔር አቅም ሆኖኛልና #ብረትን_በጋለበት ብዬ የፈረሰ መሰውያዬን ለማደስ፣ የተዳፈነ እሳቴን እንደገና ለማንደድ ከእግዚአብሔር ጋር እየሰራሁ፣ እየተጋሁ እገኛለሁ። በሬን ዘጋ አድርጌ ከእግዚአብሔር ጋር ክትት ለማለት፣ ቃሉን፣ የልቡንም አሳብ ለመስማት ሰከን፣ በእግሮቹ ሥር እርፍ ለማለት ኃይል ሆኖልኛል። ፍቅሩም በመንፈስ ቅዱስ በልቤ እየፈሰሰ ነውና አሁንም አሁንም እርሱን ያስናፍቀኛል፤ ከእርሱ ጋር ያለኝ የግል ጊዜም (Our quality time) ብዙ ነገር እየተጨዋወትንበት ነው። ከአባትዬ ጋር እንደ ልጅነቴ፣ እርሱን እንዳወቅኹበት የልጅነቴ ወራት በፍቅሩ ወድቅ! ለማለት፣ ከእርሱ ውጪ ሌላ ላለማየት ልቤን በፊቱ እያፈሰስኹ ነው። ድካሜን ሰምታችሁ፣ ከስብራቴ እንድትማሩ፤ እኔን የመታ እንቅፋት እንዳይመታችሁ፤ እኔን የረዳ፣ ዳግም መልሶ ያቆመኝ እግዚአብሔር እንደሚረዳ፣ ለእኛም ከእርሱ ውጪ ተስፋ፣ ሕይወት አለመኖሩን እንድታስተውሉ ስል ይህን ጻፍኹ። በእግዚአብሔር ፍቅር መውደቅ፤ ከፊቱ፣ ከእግሮቹ ሥር አለመጥፋት ዘወትር የምትመርጡት መልካም ዕድል ይሁንላችሁ!!! ጸጋ ይብዛላችሁ። ✍️ መክሊት አየለ 📆 June 11, 2026 #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional

በእግዚአብሔር ፍቅር መውደቅ፤ ከፊቱ፣ ከእግሮቹ ሥር አለመጥፋት ዘወትር የምትመርጡት መልካም ዕድል ይሁንላችሁ!!! ጸጋ ይብዛላችሁ። 📖 Hear. Obey. Practice. #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional t.me/hopministry10

በእድሜ መጎልመስ እንዲሁም በእግዚአብሔር ቤት ብዙ ጊዜ መቆየት እግዚአብሔርን ለማወቅ ያለንን መቃተት፣ መናፈቅ፣ መበርታት ሊያጠፋብን አይገባም።

ዛሬም ገና ያልያዝነው፣ ያወቅው ግን ደግሞ ተረድተን ያልጨረስነው እግዚአብሔር እንዳለ እናስተውል። 📖 Hear. Obey. Practice. #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional t.me/hopministry10

በእድሜ መጎልመስ እንዲሁም በእግዚአብሔር ቤት ብዙ ጊዜ መቆየት አንድ ነገርን ሊያጠፋብን አይገባም። እርሱም፦ እግዚአብሔርን ለማወቅ መቃተት፣ መናፈቅ፣ መበርታትን። የሁልጊዜ ስራችን እርሱን ለማወቅ መበርታት ከሆነ በእግዚአብሔር ላይ ሳናድግ ዘወትር እንደ ልጆች፣ እንደ ህጻናት የቃሉን ወተት እንመኛለን። ዋል አደር እያልን ስንሄድም ገና እንዳልያዝነው እየገባን ዱካውን መከታተል እናበዛለን። ዛሬም ገና ያልያዝነው፣ ያወቅው ግን ደግሞ ተረድተን ያልጨረስነው እግዚአብሔር እንዳለ እናስተውል። በዙሪያችን የሚሆነው ነገር፣ የሕይወት አዙሪት እየወጣ እየገባ፣ እየበላ እየጠጣ፣ እየተኛ እየተነሳ.... መደበኛ ኑሮው ላይ ብቻ ተጠምዶ የሚኖር #አማኝ፣ እግዚአብሔርን አዋቂ ነኝ ባይ ሰው ሊያደርገን የተጋ ነው። እኛ ግን በዚህ አዙሪት መሃል ቆም ብለን በየዕለቱ ልባችንን፣ አሳባችንን፣ ጊዜያችንን፣ ትኩረታችንን ልንሰጠው የሚገባ እግዚአብሔር እንዳለ ማሰብ፣ ማወቅም ይኖርብናል። እግዚአብሔር የየዕለት ነው፤ የሁሌ ነው፤ የዕለት እንጀራችን ነው። በሕይወት ለመሰንበታችን ወሳኙ መብል፣ መናም እርሱ ነው። ሌላው በዚህ እርሱን የማወቅ ፍለጋ ውስጥ መታደስ አለ። ይህም ለሕይወታችን እንዲሁም ለሕይወት ትርጉማችን (ስንኖር ልናደርገው ለተገባን ዓላማችን) ነው። ከጊዜ ብዛት ዘንግተነው ሕይወት ጣዕም ካጣብን እንኳን፤ ወደ እርሱ ቀርበን የልባችንን ስናወጋው፣ የልቡንም ስንጠይቀው፦ በልብ በነፍሱ ያለውን አሳቡን ሹክ ይለናል፤ የልቡን መሻት እንደገና ያስረዳናል። እኛ ብቻ ልንፈልገው፣ ልናውቀው፣ ልንከተለው እንበርታ እንጂ እርሱ እንደ ወገግታ ተዘጋጅቶ እንደምናገኘው ቃሉ ዋስትናችን ነው። “እንወቅ፤ እናውቀውም ዘንድ እግዚአብሔርን እንከተል፤ እንደ ወገግታም ተዘጋጅቶ እናገኘዋለን፤ እንደ ዝናብም ምድርንም እንደሚያጠጣ እንደ መጨረሻ ዝናብ ይመጣል።”   — ሆሴዕ 6፥3 1ኛ ጴጥሮስ 2 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ እንግዲህ ክፋትን ሁሉ ተንኰልንም ሁሉ ግብዝነትንም ቅንዓትንም ሐሜትንም ሁሉ አስወግዳችሁ፥ ²-³ ጌታ ቸር መሆኑን ቀምሳችሁ እንደ ሆነ፥ ለመዳን በእርሱ እንድታድጉ አሁን እንደ ተወለዱ ሕፃናት ተንኰል የሌለበትን የቃልን ወተት ተመኙ። ✍️ መክሊት አየለ 📆 October 2, 2025 #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional

ቤተልሄም_ተዘራ_Bethelhem_Tezera_የእግዚአብሔር_ጊዜ128k.m4a6.05 MB

📖 Hear. Obey. Practice. #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional t.me/hopministry10

#እኔ_እንደምፈልገው_ሳይሆን_አንተ_እንደምትፈልገው_ይሁን የሚለው ጸሎት እጅግ በጣም ቅልል ያለ፤ በምቹ ጊዜ፣ ጥቅማችን ባልጎደለ ሰዓት፣ የእኛ የምንለው ሁሉ ሳይነካ ብቻ የሚጸለይ ጸሎት ነው? ተግባሩስ እንደ ንግግሩ ቀላል ነው? ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይሄን ጸሎት የጸለየባት ወቅት ሁሉ ሊያበቃ ተቃርቦ፣ የሞት አፏፍ ላይ ቆሞ ነው። መከራን ሊቀበል እንደሆነ፣ ወደ ሞት እንደተቃረበ ያውቃል። #ቢቻል ይህ ጽዋ ከእርሱ ቢያልፍ ይሻል፤ ነገር ግን ብሎ ሲቀጥል ግን የአባቱን ፈቃድ መፈጸም የእርሱ ዋና ጉዳይ ነው። የትኛውንም ዋጋ ከፍሎ አባቱ የሚፈልገውን ነገር ማድረግ የእርሱ ደስታው፣ ምግቡም ነው። እርሱን ተመችቶት፣ እርሱ የሚፈልገው ሆኖ፤ ነገር ግን አብ ደስ ባይሰኝ፣ አብ የሚፈልገው ባይሆን የወልድ ልብ አያርፍም። የምሳሌያችን የእግዚአብሔር ወልድ ደስታና እረፍት ያለው፦ ፍላጎቱን ትቶ እግዚአብሔር አብ የሚፈልገውን በማድረግ ውስጥ ነበር። እያዘነ፣ እየተከዘ፣እየተጨነቀ፣ ነፍሱ እስከ ሞት ድረስ አዝና ቅድሚያ የሚሰጠው ለአባቱ ፈቃድ ነው። "  #እኔ_እንደምፈልገው_ሳይሆን_አንተ_እንደምትፈልገው_ይሁን" የማይቀየር ጸሎቱ ነው። እኛስ? አይደለም የሞት አፋፍ ላይ ቆመን በደህናው ጊዜ፣ አገር ሰላም በሆነበት ወቅት እንኳን ልባችን ለእግዚአብሔር ፈቃድ ምን ያህል ይገዛል? እኛና የእኛ ወደ ኋላ ቀርተን እግዚአብሔርን፣ የእግዚአብሔርን ለማስቀደም ምን ያህል ታዛዦች ነን? #እኔ_ልቅደም፣ #የእኔ_ይቅደም ከማለት ይልቅ እኔ እንደምፈልገው ሳይሆን አንተ እንደምትፈልገው ይሁን ብለን ሁሉን ለፈቃዱ ለመሰዋት ምን ያህል ቅርብ ነን? ጌታ ይርዳን!! ጸጋ ይብዛልን!! ማቴዎስ 26 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ³⁹ ጥቂት ዕልፍ ብሎ በግንባሩ በመደፋት፣ “አባቴ ሆይ፤ ቢቻል ይህ ጽዋ ከእኔ ይለፍ፤ ነገር ግን እኔ እንደምፈልገው ሳይሆን አንተ እንደምትፈልገው ይሁን” ብሎ ጸለየ። …  ⁴² እንደ ገና ለሁለተኛ ጊዜ ሄዶ፣ “አባት ሆይ፤ ይህ ሳልጠጣው የማያልፍ ጽዋ ከሆነ፣ ፈቃድህ ይፈጸም” ብሎ ጸለየ። …  ⁴⁴ ትቶአቸውም እንደ ገና በመሄድ ለሦስተኛ ጊዜ ቀደም ብሎ የጸለየውን ጸሎት ደገመ። ✍️ መክሊት አየለ 📆 February 19, 2025 #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional