Orthodox mezemur ኦርቶዶክስ መዝሙር
رفتن به کانال در Telegram
እኔ ግን በቸርነትህ ታመንሁ ልቤም በመድኃኒትህ ደስ ይለዋል የረዳኝን እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ ለልዑል እግዚአብሔር ስምም እዘምራለሁ ። መዝሙረ ዳዊት 13 : 5 - 6 o:-)- ለማንኛውም ጥያቄ በስር ባስቀመጥነው ሊንክ ሊጠይቁን ይችላሉ 👇👇 - @tan_flf -
نمایش بیشترکشور مشخص نشده استدسته بندی مشخص نشده است
283
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-17 روز
+2530 روز
آرشیو پست ها
የወደደኝ ጌታ
የወደደኝ ጌታ ምን አድርጌለት ነው
ብዘምርለትም ያንስበታል ይኸው
ከውድቀቴ አንስተህ ድካሜን ያገዝከኝ
ሰባራውን ድልድይ ገጥመህ ያሳለፍከኝ
አዝበኢያሪኮ መንገድ ስለምን ቁጭብዬ ብርሃን እጅግ ናፍቆኝ ከሰው ተገልዬ የብርሃን ጌታ ወደ እኔ መጣና ዓይኔን አበራልኝ በእጁ ዳሰሰና
አዝለብዙ ዘመናት አልጋ ላይ ተኝቼ የሚረዳኝ አጣሁ ጠሉኝ ዘመዶቼ የእኔ ጌታ አምላኬ ወደ እኔ መጣና አልጋህን ተሸከም አለኝ ፈወሰና
አዝአሥራ ሁለት ዓመት ደም የፈሰሰኝ ምራቅ እየተፋ ሁሉም ቢያንቋሽሹኝ የጌታዬ ልብሱን ጫፉን ብዳስሰው ኃይልም ከእርሱ ወጣ ደሜን ቀጥአረገው
አዝሰካራም ዘማዊ ወንበዴ ነበርኩኝ የአመጸኞች መሪ ደምን ያፈሰስኩኝ ዛሬ ግን ታሪኬን ጌታ ቀይሮታል ለኃያሉ ጌታ ምስጋና ይገባል ዘማሪ ዳግማዊ ደርቤ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
በእስራቴ አላፍርም
በእስራቴ አላፍርም እኔ የማርያም ነኝ
እሮማዊ አይደለሁ ፍጹም ክርስትያን ነኝ
ከመቤቴ ፍቅር የሚለየኝ ማነው
መከራ ነው ችግር ወይስ እስራት ነው /2/
አዝአንተ መዝሙረኛ ነብዩ ዳዊት እንድታሸበሽብ በታቦቱ ፊት ሜልኮም ብትንቅህ ሰገነት ላይ ሆና እግዚያብሔር አይትዋታል ሳትናገር ገና እኔስ ለመቤቴ እዘምራለሁ ፍቅርዋ በደሜ ውስጥ እንዳለ አውቃለሁ ስምዋን ለምን ጠራህ ተብየ ስተየቅ አድምጡልኝ መልሴን ድንግልን እኔ አለቅ በአማን /2/እረዳቴ ናት እመቤታችን
አዝየኤልዛቤት ጭፍሮች መጥተው ይዘውኝ ጭው ያለ በረሃ እስርቤት ጣሉኝ ስለ እስራቴ ጌታየ አይቶልኛል ሁሉን ተመልክቶ ተበቅሎልኛል ከዝምታየ የተነሳ እንደ ዲዳ ሆንኩኝ ለበጎ ነገርን እንኩዋ ዝምም ያልኩኝ በእኩለ ለሊት ሊያስፈራሩኝ መጥተው ሳህሊለነ ብዬ ብርታትን አገኘሁ በአማን /2/እረዳቴ ናት እመቤታችን
አዝእረበናት ዛሬም መስክረው ሀሰት ወደ ፍርድ ወሰዱኝ ከማላውቅበት ከሳሾችም ቀርበው ሲከራከሩኝ እውነተኛው ዳኛ አሰናብበተኝ የምስጋናም ዘውድም ጌታ ደፍቶልኛል ለድንግል ውዳሴን ላቀርብ ፈቅዶልኛል ባለምዋልናትና ለቅድስት ስላሴ እስከ መጨረሻው ታመስግናት ነፍሴ በአማን /2/እረዳቴ ናት እመቤታችን ዝማሬ በቀሲስ እንግዳወርቅ በቀ
ሰላም ለኪ እያለ
ሰላም ለኪ እያለ /2/
ሐርና ወርቁን ስታስማማ
የገብርኤል ድምፅ ተሰማ
ተሰማ የመልአኩ ድምፅ ተሰማ
ተሰማ የገብርኤል ድምጽ ተሰማ
አዝውሃ ስትቀጂ ክንፉን እያማታ ሊያበስርሽ የመጣው በታላቅ ደስታ ከሞገስሽ ብዛት /2/ ሲታጠቅ ሲፈታ አቅርቦልሽ ነበር የክብር ሰላምታ
አዝየምሥራቹን ቃል ምስጢር ተሸክሞ ገብርኤል ተላከ ሊያረጋጋት ደግሞ እርጋታን ተሞልታ/2/ ነገሩን መርምራ የመልአኩን ብሥራት ሰማችው በተራ
አዝይደሰታል እንጂ መንፈሴ በአምላኬ በምስጋና ሳድር ዘወትር ተንበርክኬ ሃሳቤ ለቅፅበት/2/ሌላ መች ያስባል ለእኔ ልጅን መውለድ እንዴት ይቻለኛል
አዝከአንቺ የሚወለደው ልዑል ነው ክቡር የተመሰገነ በሰማይ በምድር ምስጢሩ ኃያል ነው /2/ ይረቃል ይሰፋል ከአንቺ በቀር ይኼን ማን ይሸከመዋል
አዝእጹብ ነው ድንቅ ነው አንቺን የፈጠረ አንቺን በመውደዱ ሰውን አከበረ ዓለም ይባረካል /2/ በማሕፀንሽ ፍሬ ክብርሽን አልዘልቅም ዘርዝሬ ዘርዝሬ ሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ
መራሄ ብርሃን
መራሄ ብርሃን ረድኤትህ የበዛ
ወደ ግብፅ ስትሄድ ድንግል ልጇን ይዛ
አብረህ የተራዳህ መልዐከ ልዑል
የእግዚአብሄር አገልጋይ ቅዱስ ዑራኤል
አዝአበው ሠባስገል ዑራኤል ከምስራቅ ሲመጡ ዑራኤል ሆነህ ቆመህ የመራህ ዑራኤል አምሃ እንዲሠጡ ዑራኤል ህይወቴን አቅናልኝ ዑራኤል ከኃጥያት አውጣና ዑራኤል በብርሃን ምራኝ በፅድቅ ጎዳና
አዝፈጥነህ የምትደርስ ዑራኤል ስምህን ለጠራ ዑራኤል ፅዋህ አድርጎናል ዑራኤል ያጠጣህ ለዕዝራ ዑራኤል ጥበብ መንፈሳዊ ዑራኤል በውስጤ እንዲዘራ ዑራኤል በርሃናዊው መላክ ልቦናዬን አብራ
አዝለሔኖክ የገለፅክ ዑራኤል ረቀቀ ምስጢር ዑራኤል በገፀ ሰማይ ላይ ዑራኤል የፊደላት ቁጥር ዑራኤል ማስተዋል አግኝቼ ዑራኤል በፍቅር እንድሞላ ዑራኤል ምልጃህ አይለየን ሁነኝ ከለላ
አዝአምላክ ስለሰው ልጅ ዑራኤል ቀራንዮ ሲሰዋ ዑራኤል ደመ መለኮቱን ዑራኤል በብርሃን ፅዋ ዑራኤል ተቀብለህ ረጭተህ ዑራኤል አለምን የቀደስክ ዑራኤል ለምስጋና አንቃኝ በነግህና በሰርክ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
መራሄ ብርሃን
መራሄ ብርሃን ረድኤትህ የበዛ
ወደ ግብፅ ስትሄድ ድንግል ልጇን ይዛ
አብረህ የተራዳህ መልዐከ ልዑል
የእግዚአብሄር አገልጋይ ቅዱስ ዑራኤል
አዝአበው ሠባስገል ዑራኤል ከምስራቅ ሲመጡ ዑራኤል ሆነህ ቆመህ የመራህ ዑራኤል አምሃ እንዲሠጡ ዑራኤል ህይወቴን አቅናልኝ ዑራኤል ከኃጥያት አውጣና ዑራኤል በብርሃን ምራኝ በፅድቅ ጎዳና
አዝፈጥነህ የምትደርስ ዑራኤል ስምህን ለጠራ ዑራኤል ፅዋህ አድርጎናል ዑራኤል ያጠጣህ ለዕዝራ ዑራኤል ጥበብ መንፈሳዊ ዑራኤል በውስጤ እንዲዘራ ዑራኤል በርሃናዊው መላክ ልቦናዬን አብራ
አዝለሔኖክ የገለፅክ ዑራኤል ረቀቀ ምስጢር ዑራኤል በገፀ ሰማይ ላይ ዑራኤል የፊደላት ቁጥር ዑራኤል ማስተዋል አግኝቼ ዑራኤል በፍቅር እንድሞላ ዑራኤል ምልጃህ አይለየን ሁነኝ ከለላ
አዝአምላክ ስለሰው ልጅ ዑራኤል ቀራንዮ ሲሰዋ ዑራኤል ደመ መለኮቱን ዑራኤል በብርሃን ፅዋ ዑራኤል ተቀብለህ ረጭተህ ዑራኤል አለምን የቀደስክ ዑራኤል ለምስጋና አንቃኝ በነግህና በሰርክ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
እንዲህ በአራት ነጥብ
እንዲህ በአራት ነጥብ ሊዘጋ ምዕራፉ
እግዚአብሔር ሊያሸንፍ የእርሱ ሆኖ ሰልፉ
መልካም ለመናገር አፉ ባይታደል
ይህን እስኪያይ ጠላት ምን አለ ዝም ቢል/2/
አዝመልካሙን ደብቆ ክፉን እያሳየ ይለኝ ነበር ጠላት እግዚአብሔር ዘገየ ግን ሁሉን በጊዜው ውብ አግድጎ ሲሰራ አፍሮአል ለዘላላም ደንቆት የእርሱ ሥራ/2/
አዝበቃ ልጅ የለህም አትወልድም ሣራ ላይሰማህ እግዚአብሔር ጮኸ ብትጣራ እያለ ጠላቴ መስሎት ያሸነፈ ይስሃቅ ተወለደ ያ ቀንም አለፈ /2/
አዝፍፃሜዬን ሳያይ ገና ከጅምሩ ጠላት በእሱ ግምት ብዙ መናገሩ አስብሎታል ቴቄል ተቀይሮ ስሙ የዘገየ መስሎ ጌታ በመቅደሙ/2/
አዝድንጋይ ያሸከመን ውሃ ተሸከመ ለእኛ ቀን ወጣልን ለእርሱ ግን ጨለመ ገዳይ ቢዘገይም ሟች በመገስገሱ ፈረሰኛው ሞተ እስከነ ፈረሱ/2/
አዝቢመስለንም ሌሊቱ ፍፁም የማይነጋ ተቆልፎ የሚቀር በሩ እንደተዘጋ እርሱን ተስፋ አድርገው ባመንክበት ፅና ቀን አለው እግዚአብሔር ያደርግሃል ቀና/2/ ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
👆የቀጠለ
እኒኽም ቅዱሳን ይኽንን በሚነጋገሩበት ጊዜ በውስጡ አንገትን የሚቆለምም ልብንም የሚያቀልጥ ሆድን የሚሰነጥቅ ሥርን የሚበጣጥስ መሳሪያ ካለበት የብረት ጋን ውስጥ ጨመራቸው፡፡ ከዚህ በኋላ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል ከሰማይ ወረደና የብረቱን ጋን እሳት አጠፋው፡፡ ከቅዱሳኑም አንዳቸውንም ሳያቃጥላቸው የብረቱ ጋር ማቃጠሉና መፍላቱ ጸጥ አለ፡፡
ወንድሞቻችን ሆይ እንግዲህ በጭንቃቸው ጊዜ ገድላቸውን እስኪፈጽሙ ድረስ ይህ መልአክ ከሰማእታትና ከጻድቃን ጐን እንደማይለይ እወቁ ለኃጥአንም ኃጢአታቸውን ይቅር ይላቸው ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ይጸልይላቸዋል፡፡ እኛም የዚህ የሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል በዓሉን እያከበርን አማላጅና ወዳጅ እናድርገው። በዚህም በሚመጣውም ዓለም ሊረዳን ይችላልና፡፡
ዳግመኛም መስፍኑ ሐሳቡ ሳይሳካለት ስለቀረ 14 የሾሉና የጋሉ የብረት ችንካሮች አምጥተው ሰባቱን በእናቱ በኢየሉጣ አካል ሰባቱን በራሱ በቂርቆስ አካል ማለት ሁለቱን በጆሮዎቹ ሁለቱን በዐይኖቹ ሁለቱን በአፍንጫዎቹ አንዱን በልቡ ይቸነክራቸው ዘንድ ጭፍሮቹን አዘዘ፡፡ ዳግመኛም የህፃኑን የእራስ ቆዳ ገፈው እሳት ውስጥ ይጨምሩ ዘንድ አዘዘ፡፡
አሁንም መልአኩ መጥቶ ይህንን መከራ ከእርሱ አራቀለት፡፡ ቀጥሎም በመቃን ውስጥ ጨምረው በገመድ እንዲጎትቱት አዘዘ፡፡ በዚህም ጊዜ መልአኩ አዳነው፡፡ ሕዝቡም ይህንን ሁሉ ተአምር ባዩ ጊዜ እግዚአብሔርን አመሰገኑት ቅዱስ ገብርኤልንም አከበሩት፡፡ ቅዱስ ቂርቆስና ቅድስት እየሉጣ ብዙ መከራ ከተቀበሉ በኋላ ጥር 15 በሰይፍ ተመትተው ስማትነትን ተቀብለዋል።
የሊቀ መላእክት የቅዱስ ገብርኤል ፣ ቅዱስ ቂርቆስና የእናቱ የቅድስት እየሉጣ ተራዳኢነት ጸሎት አይለየን። ከዚህ በኋላ ሕፃኑን አስፈልገው ቢጠይቁት ነቢዩ ዳዊት የተናገረው ኃይለ ቃል መንፈስ ቅዱስ ተገልጾለት፤ ‹‹የአሕዛብ ጣዖታት የወርቅና የብር የሰው እጅ ሥራዎች ናቸው፡፡ የሚታመኑባቸውም ሁሉ እንደ እነርሱ ይሁኑ›› መዝ. ፻፴ በማለት ሲዘልፏቸው አገር ገዥው ሰምቶ ተቆጣና የብረት ጋን አስመጥቶ ውኃ ሞልቶ ከዕቶን እሳት ላይ ጥዶ ልዩ ልዩ ማገዶዎች በመጨመር ነበልባሉ ከመጠን በላይ ሆነ፡፡ የብረት ጋኑም ድምፅ እንደ ክረምት መብረቅና ነጎድጓድ እስኪያስፈራ ድረስ አስነድዶ ሕፃኑን ከነእናቱ ወስዳችሁ ጨምሩአቸው ብሎ አዘዘ፡፡
በዚህ ጊዜ ቅድስት ኢየሉጣ በጣም ፈራች፡፡ የእግዚአብሔር ሥራ እፁብ ድንቅ ግሩም ረቂቅ ነው፡፡ ገና አፉን ያልፈታ የሦስት ዓመት ሕፃን ‹‹እናቴ ሆይ! ገድላችን እንፈጽም ዘንድ ጨክኝ በርቺ›› አላት፡፡ ቅድስት ኢየሉጣም ‹‹ልጄ የነፍስ አባት ሁነኝ›› አለችው፡፡ ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስም ከዘመናቸው ሳይደርስ፣ ታሪካቸውን ሳይማር የሠለስቱ ደቂቅን ታሪክ መንፈስ ቅዱስ ገልጾለት ‹‹አናንያን፣ አዛርያንና ሚሳኤልን ያዳነ አምላክ ያድነናል›› ቢላት ፍርሃቱ ሊለቃት ባለመቻሉ፣ ወደ እግዚአብሔር እንዲህ ሲል ጸለየ፡፡
‹‹ጌታ ሆይ! የወይኑን ፍሬ ስትሻ ግንዱን ታጠፋለህን? እንደዚህስ ሁሉ እኔን አድነህ እናቴን ታጠፋታለህን?›› ብሎ በጸለየጊዜ መንፈስ ቅዱስ አደረባትና መንግሥተ ሰማያትን በዓይነ ሥጋ እንድታይ አደረጋት፡፡ ከዚህ በኋላ ፍርሃቱ ለቀቃትና ‹‹ልጄ ሆይ! ከዛሬ ጀምሮ መምህሬ፣ አባቴ፣ መካሪዬ እልሃለሁ እንጂ ልጄ አልልህም›› ብላ በጭካኔ ከልጅዋ ጋር ወደ ፈላው የብረት ጋን ገባችበት፡፡
በዚህ ጊዜ ሕፃኑ ቂርቆስ አናንያን፣ አዛርያንና ሚሳኤልን ያዳነ አምላክ ያድነናል ያለውን ቃል ለመፈጻም እግዚአብሔር አምላክ መልአኩ
ቅዱስ ገብርኤልን ላከላቸው፡፡ መልአኩም በትእምርተ መስቀል እሳቱን ቢባርከው እንደ በረዶ ቀዝቅዞላቸዋል፡፡ በመልካቸውም እንደ ፀሐይ አበራ፡፡ ከእግር ጥፍራቸው እስከ ራስ ጠሩራቸው አንድም ሳይጎዳቸው በደህና ወጡ፡፡
በመጨረሻም ሕፃኑ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ እንዲህ አለ፡፡ ይህን ያህል ገድል ተጋድዬ ምን ዋጋ ትሰጠኛለህ ቢለው፣ ጌታ በልብህ ያለውን ሁሉ እሰጥሃለሁ አለው፡፡ ዳግመኛም ሥጋህ በምድር ላይ እንዳይፈርስ እንዳይበሰብስ በኤልያስ ሠረገላ ላይ አኖርሃለሁ አለው፡፡
ስለሆነም በዚህ ዕለት ቤተክርስቲያናችን መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ለእናታችን ለቅድስት ኢየሉጣ እና ለሕፃኑ ለቅዱስ ቂርቆስ ያደረገውን ይህን ታላቅ ተአምር ድንቅ ሥራ በማሰብ ከዋዜማው ጀምራ እግዚአብሔርን ስታመሰግን ትውላለች ታድራለች፡፡
የመልአኩ የቅዱስ ገብርኤል በረከት ተራዳኢነት ከሁላችን ጋር ይኑር አሜን፡፡
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️
✞ድንግል ትንሳኤሽን✞
ድንግል ትንሳኤሽን እስከምናይ ድረስ
ገብተናል ሱባዔ በአንድነት በመንፈስ
ለእኛ እስከሚገለጥ ቶማስ ያየው እውነት
አንወጣም ከደጅሽ ኪዳነ ምህረት (፪)
ሞትን የረገጠ ልጅሽ ካንቺ ጋር ነው
ውጦ የሚያስቀርሽ የቱ መቃብር ነው
የዕርገትሽን ዜና ከቶማስ ሰምተናል
ትንሳኤሽ እውነት ነው ሰበንሽን አይተናል
ሞትማ በሞት ተሽንፏል በአንቺ ላይ እንዴት ኃይል ያገኛልአዝ= = = = = ልናየው ወደድን የቶማስን ክብር ለምን ተስወረን የትንሳኤሽ ምስጢር በራችንን ዘግተን በፀሎት ወድቀናል ተገልጠሽ አብሪልን ልጆችሽ ናፍቀናል
ሞትማ በሞት ተሽንፏል በአንቺ ላይ እንዴት ኃይል ያገኛልአዝ= = = = = መዝሙረኛ አባትሽ ዳዊት ጽፎልናል ሞትን የማያይ ስው ማን አለ ብሎናል ይህ እውነት በዘመን አንቺ ላይ ቢደርስም በሞት ተሽንፏል መቃብር አይኖርም
ሞትማ በሞት ተሽንፏል በአንቺ ላይ እንዴት ኃይል ያገኛልአዝ= = = = = ቶማስ ከደመናው ወርዶ ሲያናግረን ስለ ሆነው ነገር እጅጉን ተመሰጥን እኛም ይህን ክብር ተመኘን ለማየት ድንግል አሳስቢልን ኪዳነ ምህረት
ሞትማ በሞት ተሽንፏል በአንቺ ላይ እንዴት ኃይል ያገኛልመዝሙር በሊቀ መዘምራን ዲ/ን ቴድሮስ ዮሴፍ "እነሆ በፆማችሁ ቀን..." ኢሳ ፶፰ ፥ ፩-፲ ╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮ @Ortodoks_mezmur1 ╰══•ೋ•✧๑♡๑✧• ══╯
ይለይብኛል
ጠብቆ አሳድጎ ከልጅነቴ
አባት እየሆነኝ ሚካኤል አባቴ
ይለይብኛል ሚካኤል ይለይብኛል
በክንፉ ሸፍኖ በቤቱ አሳድጎኛል /2/
አዝአያምርብኝ ብዘነጋው ታሪኬን ሚካኤል ነው ያስጌጠልኝ ህይወቴን አልረሳብኝ እርሱ አትርሳብኝ ያልኩትን ለካስ ሰምቶኝ ኖሯል የልጅነት ጸሎቴን ሚካኤል ያን ሁሉ ዘመን የታገሰኝ ሚካኤል ፍሬ ጠብቆ ያልቆረጠኝ ሚካኤል የከፍታዬ መሰላል ሚካኤል መነሻዬ ሆነሀል
አዝእንዳይከፋኝ አንዳልደፋ አንገቴን እንዳላለቅስ እንዳላፈስ እንባዬን እንዳይርቀኝ ደስታ በመንፈሴ እንዳልዝል ካጠገቤ አይርቅም ያሳደገኝ ሚካኤል ሚካኤል ቀኔም ቀን አይሆን ሳልጠራህ ሚካኤል ና ድረስልኝ ሳልልህ ሚካኤል እንዳስጀመርከኝ ጅማሬዬን ሚካኤል አሳምረው ፍፃሜዬን
አዝውድቅ አረገው የጠላቴ ክፉ እቅድ አራመደኝ በከፍታዬ መንገድ ሊያስቀረኝ አልቻለም ሊጎትተኝ ባላጋራ ተጥሎ ስላለ በእግዚአብሔር ድንቅ ስራ ሚካኤል እሳታዊ ነው ነበልባል ሚካኤል ጠላቴ ፊትህ ይቀልጣል ሚካኤል ለኔ ኃይሌ ነው መከታዬ ሚካኤል የዘለዓለም ጠባቂዬ
ይለይብኛል
ጠብቆ አሳድጎ ከልጅነቴ
አባት እየሆነኝ ሚካኤል አባቴ
ይለይብኛል ሚካኤል ይለይብኛል
በክንፉ ሸፍኖ በቤቱ አሳድጎኛል /2/
አዝአያምርብኝ ብዘነጋው ታሪኬን ሚካኤል ነው ያስጌጠልኝ ህይወቴን አልረሳብኝ እርሱ አትርሳብኝ ያልኩትን ለካስ ሰምቶኝ ኖሯል የልጅነት ጸሎቴን ሚካኤል ያን ሁሉ ዘመን የታገሰኝ ሚካኤል ፍሬ ጠብቆ ያልቆረጠኝ ሚካኤል የከፍታዬ መሰላል ሚካኤል መነሻዬ ሆነሀል
አዝእንዳይከፋኝ አንዳልደፋ አንገቴን እንዳላለቅስ እንዳላፈስ እንባዬን እንዳይርቀኝ ደስታ በመንፈሴ እንዳልዝል ካጠገቤ አይርቅም ያሳደገኝ ሚካኤል ሚካኤል ቀኔም ቀን አይሆን ሳልጠራህ ሚካኤል ና ድረስልኝ ሳልልህ ሚካኤል እንዳስጀመርከኝ ጅማሬዬን ሚካኤል አሳምረው ፍፃሜዬን
አዝ
ውድቅ አረገው የጠላቴ ክፉ እቅድ አራመደኝ በከፍታዬ መንገድ ሊያስቀረኝ አልቻለም ሊጎትተኝ ባላጋራ ተጥሎ ስላለ በእግዚአብሔር ድንቅ ስራ ሚካኤል እሳታዊ ነው ነበልባል ሚካኤል ጠላቴ ፊትህ ይቀልጣል ሚካኤል ለኔ ኃይሌ ነው መከታዬ ሚካኤል የዘለዓለም ጠባቂዬ ዘማሪ ዲያቆን አቤል መክብብ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
✞እረድተሃልና✞
እረድተሃልና ባህራንን ሚካኤል
ጠብቀሃልና ትዮብስታን ሚካኤል
አስታርቀን አማልደን ሚካኤል
ከሰማያት ስትወርድ - - - ሚካኤል
ለሰው ልጆች ልትራራ - - - ሚካኤል
ከክብርህ የተነሳ - - - ሚካኤል
መላው ምድር አበራ - - - ሚካኤል
በመከራዬ ጊዜ - - - ሚካኤል
ፈጥነህ የደረስክልኝ - - - ሚካኤል
ከአምላኬ ተልከህ - - - ሚካኤል
ከጭንቅ የገላገልከኝ - - - ሚካኤል
አዝ= = = = =
አልተረዳሁትም - - - ሚካኤል
በእጄ ያለውን - - - ሚካኤል
የሞቴን ደብዳቤ - - - ሚካኤል
የሸሸኩትን - - - ሚካኤል
ልጨብጥ ስጣደፍ - - - ሚካኤል
የሰይፉን ስለት - - - ሚካኤል
የመላእክት አለቃ - - - ሚካኤል
አዳነኝ ከሞት - - - ሚካኤል
አዝ= = = = =
ገና ህፃን ሳለሁ - - - ሚካኤል
አሳድገኸኛል - - - ሚካኤል
በብዙ ፈተና - - - ሚካኤል
አንተ አድነኸኛል - - - ሚካኤል
አሁንም ጠብቀኝ - - - ሚካኤል
ቸል አትበልኝ - - - ሚካኤል
አባቴ ሚካኤል - - - ሚካኤል
ልጄ ሆይ በለኝ - - - ሚካኤል
መዝሙር
ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
@Ortodoks_mezmur1
ገድሉ ተዐምራቱ
ገድሉ ተዐምራቱ እጅግ ብዙ ነው
ጣዖትን አዋርዶ የተሸለመው
የተዋህዶ ኮከብ ተክለ ሐዋርያ
አባ ተክለሃይማኖት ዘኢትዮጵያ
አዝዳግማዊዉ ዩሐንስ ጠፍር የታጠቀ ንጽህ ባህታዊ ጠላት ያስጨነቀ የፀጋ ዘአብ ፍሬ ዛፍ ሆኖ በቀለ በደብረሊባኖስ መናኝ አስጠለለ
አዝደካማ መስሏቸው በአንድ እግሩ ሲያዩት ባለ ስድስት ክንፉ ተክልዬ የእኛ አባት እርሱስ አንበሳ ነው ትናገር ደብረ አስቦ ሌጌዮን ሲዋረድ እፍረት ተከናንቦ
አዝከካህናት መካከል ህሩይ ነው ተክልዬ መጣሁ ከገዳምህ ልሳለምህ ብዬ ኢትዮጵያዊው ቅዱስ አባ ተክለሃይማኖት ወልድ ዋህድ ብለህ ምድሪቷን ቀደስካት
አዝየባረከው ውሃ የረገጥከው መሬት ጥላህ ያረፈበት ሆኗል ፀበል እምነት ኑና ተመልከቱ ድውያን ሲፈቱ ይሰብካል ተክልዬ ዛሬም እንደ ጥንቱ @Qmamaaa
Repost from N/a
እግዚአብሔር ስራው ድንቅ ነው
እግዚአብሔር ስራው ድንቅ ነው
ለእኔ ያደረገው ብዙ ነው
እግዚአብሔር ስራው ድንቅ ነው
ለእኔ ያደረገልኝ ብዙ ነው
አዝእረዳት እርሱ ነው ከሰማያት እግዚአብሔር ጠባቂ የኔን ሕይወት ብርሃኑን በፊቴ የሚያበራ አምላኬ ድንቅ ነው የእርሱ ስራ
አዝበመንገዴ ሁሉ የሚመራኝ ስነሳ ስወድቅም የሚያስበኝ ማንም አልመጣልኝ ከወገኔ ከሁሉም ይበልጣል እርሱ ለኔ
አዝየእዳዬን ደብዳቤ ውድቅ አድርጎ ሕይወቴን መራልኝ ወደ በጎ ኧረ እንደእግዚአብሔር ማን ይሆናል እሱን ለሚፈሩት ይታመናል
አዝእንድ ቀን አስቤ ተጨንቄ ለመኖር አልቻልኩም ተጠንቅቄ ሁሉን ነገር ለእርሱ ትቼዋለሁ በምሕረቱ ጥላ እኖራለሁ ዘማሪ እንዳልካቸው 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
ቤዛዊት እያልን
በልጅነታችን ዛሬም ትልቅ ሆነን
ነጠላ ነጥለን ባንገታችን አስረን
ቃል በተዋህዶ ባንቺ ስላደረ
ቤዛዊት እያልን ዘመን ተቆጠረ
አዝየምድራዊው ዕ ውቀት የሰዎች አዕምሮ ፍጹሞ አይለካውም ሁሉም ተደምሮ ምን ብናስላስል የሆነውን ባንቺ ሌላ አማራጭ የለም አሜን ማለት እንጂ
አዝብፅዕት ብፅዕት ትአሁንም ብፅዕት ዘንዶው ቢደነፋም ለዘ'ላለም ክብርት የእሳት መጋረጃ በሆድሽ ተጋርዶ ከእኛ ተዛመደ ቃል በተዋህዶ
አዝአንቺ በ'ናትነት እኛ በልጅነት ቃልኪዳን አስረናል በእውነት ያለ ሐሰት የሕይወት እንጀራን ካንቺ ስላገኘን ድንግል ማርያም ሆይ እንወድሻለን
አዝቃል ከሰማይ ወርዶ እንዴት ሥጋ ሆነ አይመረመርም በመንፈስ ካልሆነ ትናንትናም ዛሬም ብፅዕት የምንለው ይሄ ታላቅ እውነት ስላስገደደን ነው ለልጅሽ ነግረሽው ውኃው ወይን ሆኗል ከዶኪማስ ጓዳ ጭንቀት ተወግዷል ልጅሽ በበረከት ከቤታችን ይግባ እንዲቆም ከምንጩ የሰቀቀን እንባ ሊቀ መዘምራን ቴድሮስ ዮሴፍ
