Never give up
رفتن به کانال در Telegram
نمایش بیشتر
کشور مشخص نشده استدسته بندی مشخص نشده است
473
مشترکین
+124 ساعت
+107 روز
+930 روز
آرشیو پست ها
🔥💙 መቼ ትመጣለህ 💙🔥
ጊዜዉ ሲደምን ፀደዬች ሲረግፉ
ጨረቃ ጨልማ ከዋክብት ሲነጥፋ
ፀሀይ ስትከስም ብርሀኖች ሲጠፉ
መቼ ትመጣለህ 😑😑😑😑😑
መቼ ልጠብቅህ ምን ተንተርሼ
ለመልካም ምኞቴ ዉሀዉን አፍስሼ
ወይስ በድን ተስፋዬን ተመርኩዜ
መቼ ትመጣለህ 😐😐😐😐😐
ለምታዘግመዉ ጎዳና ስጨርስ አፈር ምሼ
እስከመቼ ልጠብቅህ በቀናት በአንዱ
ያንተ ወይ የኔ ዳናወቻችን ወዳንዳችን እስኪያንጋድዱ
እ .... ንገረኝ 😢
➖➖➖➖➖❤️➖➖➖➖➖
ሰው ብልኃተኛው፣ ምንኛ ዘየደ
ለጨለማ ቀኑ፣ ብርሐን ወለደ!
....እያልኩኝ አባቱን፣ በቃል ሳሞግሰው
በልጁ ውስጥ አየሁ፣
ብርሃን እየሰጠ፣ ቀን የጨለመው ሰው!
፣
የእድሜውን ማለዳ፣
ዘንግ እንደጨበጠ፣ ሳያውቀው መምሸቱን
መንገድ እየመራ፣
ከሁዋላ የሚቀር፣ እያየ ፊት ፊቱን
ጸዓዳ ልጅነቱን፣
ሳቁን ቡረቃውን፣ በሆድ የተቀማ
ምስኪን ህፃን አየሁ፣
ለአባቱ ብርሃን፣ ለራሱ ጨለማ፡፡
➖➖➖➖ 🤫 ተው 🤫 ➖➖➖➖
ማን ሲሞት ተደሰትክ
ማን ሲሞት አለቀስክ
ማንን በሳቅ ሸኘህ
ለማን እንባ አነባህ
ተው ይቅርብህ ህዝቡን አትመርዘው!
የሰው ደም አንድ ነው!
ቀይ ነው ቀለሙ ሲወጋ ሚፈሰው!
➖➖➖➖➖➖❤️➖➖➖➖➖➖
አገባህ ነበረ …………… 😂
ቆሎ 'የቆረጠምን እኖራለን ውዴ
ልጅ በልጅ ይሆናል ቤታችን መውደዴ
አንቺ ውሀ አጣጬ የእግዜር ባለ አደራ
እሺ በይኝ ላግብሽ ፍቅራችንም ይድራ::
አለኝ የኔ ሚስኪን..............
አገባህ ነበረ..................
ቆሎ ባልቆረጥም እርሀብ ባይደፋኝ
ሊያውም በዚ ዘመን..........
ቆሎ ያልከው ውዴ
ዝም ብለህ ስታየኝ የኤርፎራ ዶሮ እመስላለሁ እንዴ?
ጭራሹን.................
ልጅ በልጅ ሆኜልህ
አንዱን ከኃላዬ ሌላውን ከፊቴ
ገሚሱን በግራ ገሚሱን በቀኜ
እሪ እምቧ ሲሉብኝ መንምኜ መንምኜ
የድስት ፍቅፋቂ በጋራ ስንበላ
ጎረቤት ቢረበሽ ይደብራል ኃላ
እኔም ተማርሬ እግዜር ከሚከፋዉ
ቆሎህን ለብቻህ ተደብቅህ ብላው::
🐒 የዝንጀሮዋ እጅና የጠባቧ ማሰሮ
በአንድ ወቅት አዳኞች ዝንጀሮዎችን ለመያዝ የሚጠቀሙበት አንድ ብልህ ዘዴ ነበር። ጠባብ አፍ ያላት ማሰሮ መሬት ውስጥ ይቀብሩና በውስጧ ሙዝ ወይም ለውዝ ይጨምራሉ።
አንዲት ዝንጀሮ መጥታ እጇን በማሰሮዋ ጠባብ አፍ ውስጥ ትሰድና ሙዙን ትጨብጣለች። ነገር ግን እጇን ጨብጣ ለማውጣት ስትሞክር የጨበጠችው ሙዝ እጇን ስለሚያወፍረው በማሰሮዋ አፍ በኩል ሊወጣላት አይችልም። አዳኞቹ ሲመጡ ዝንጀሮዋ ለማምለጥ ትታገላለች፤ ነገር ግን የጨበጠችውን ሙዝ መልቀቅ ስላልፈለገች እጇ በማሰሮው ውስጥ እንደታሰረ ትያዛለች።
በሕይወት ጉዟችንም የያዝነው "ሙዝ" (ጊዜያዊ ደስታ፣ ቂም፣ ወይም መጥፎ ሱስ... ወዘተ) ነፃነታችንን ሊያሳጣን ይችላል። ዲስፕሊን ማለት አንዳንድ ጊዜ ነፃ ለመውጣት መያዝን ሳይሆን መተው መቻል ነው። ለትልቅ ስኬት ስንል ትናንሽና ጎጂ ፍላጎቶቻችንን እና ስሜቶቻችንን መልቀቅ ካልቻልን፣ በገዛ ምርጫችን የታሰርን ምርኮኞች እንሆናለን።
ነፃነታችንን ለማግኘት የጨበጥነውን ጎጂ ልማድ መልቀቅ መቻል የእውነተኛ ስኬታችን ቁልፍ ነው።
🔣🔣🔣🔣🔣🔣❣️🔣🔣🔣🔣🔣🔣
❣️ ጠብቂኝ አልመጣም ❣️
ከቀጠርሽኝ ቦታ ሂጂ ተገተሪ፣
ዛፉን ተጠልለሽ ግራ ቀኝ አማትሪ....
......ጠብቂኝ አልመጣም........
..አላፊ አግዳሚዉ ይጠቋቆምብሽ፣
የመንደሩ ዉርጋጥ ከበዉ ይሳቁብሽ፣
የተጠለልሽዉ ዛፍ አይቶ ይታዘብሽ....
.......ጠብቂኝ አልመጣም.........
...የእጅ አይበሉባሽን፣አስሬ አገላብጭዉ፣
ጉንጭሽን ሳብ አርገሽ፣ጊዜዉን ገላምጭዉ፣
በቀኝ መዳፍሽ ሰዓቱን አጋጭዉ....
.....ጠብቂኝ አልመጣም....
...በስንጣሪ እንጨት መሬቱን ቆፍሪ፣
ዉር ዉር ሚለዉን መኪና ቁጠሪ።
እሱ ሲሰለችሽ ጎርደድ ጎርደድ በይ፣
ግንባርሽን ይዘሽ አንጋጪ ወደላይ...
ጠብቂኝ አልመጣም......
ሀሩሩ ከሞቀሽ ጃኬትሽን አዉልቂዉ፣
በሁለት እጆችሽ ወገብሽን እነቂዉ፤
በቀኝ በግራ እግርሽ መሬቱን ደልቂዉ፣
ቀጥሮ መጠበቅን ህመሙን እወቂዉ....
....ጠብቂኝ አልመጣም.......
..የሚል ደብዳቤየን ከቀጠሮዉ ሰአት አስቀድሜ ፅፌ፣
እየጠበኩሽ ነዉ ከቀጠርሽኝ ቦታ ግንዱን ተደግፌ።
አያስችለኝ..... ☹️
⊶⊷⊶⊷❍ አንተ ነህ የገደልከኝ ❍⊶⊷⊶⊷
አይቶ ለማለፍ ፣ ላይቋጩት አይጀምሩት
❤️ በአንድ ወቅት ባል ጥዋት ተነስቶ ወደ ስራው ሊሄድ እየተሰናዳ ሳለ ሚስት ትመጣና ውዴ ሆይ ምነው ፊትህ ላይ ጥሩ ስሜት አይታየኝም ምን ሆነክብኝ ነው ብላ ትጠይቀዋለች??
ባልም፦ እንጃልኝ ማሬ ዛሬ ለሊቱን ሙሉ ሲያቃዠኝ ፡ እንቅልፍ ባይኔ ሳይዞር ነው ያደርኩት።
ድሮ ልጅ እያለው እናቴ በመኪና አደጋ ከመሞቷ አንድ ቀን በፊት ልክ እንደዛሬው ለሊት ሲያደርገኝ ስለነበር አሳስቦኝ ነውና ዛሬም ጥሩ ነገር ስለማይሸተኝ እባክሽ አንችም አንድ ነገር እንዳትሆኚብኝ ከስራ ቀርቼ አብሬሽ ልዋል ይላታል??
ሚስትም፦ ውዴ ሆይ አታስብ አትጨነቅ አንተ አብረሀኝ ዋልክም አልዋልክም ዛሬ ቀኔ ከሆነ ምንም የሚለወጥ ነገር አይኖርም ስለዚህ በቃ ወደስራህ ሂድ ትለዋለች።
ባልም፦ እየከበደውም ቢሆን በሚስቱ ሀሳብ ተስማምቶ ወደስራው ሄደ።
እኩለ ቀን ላይም ምሳ ለመብላት ወደ ክበብ ሄደ ምሳውንም ለመብላት ሲሰናዳ ክበብ ውስጥ ካለው ቴሌቪዥን ውስጥ አንድ #ሰበር ዜና ጆሮውን ገረፈው!!!
ዜናውም እንዲህ ይል ነበር፦ እሱ የሚኖርበት የጋራ መኖሪያ ሰፈር በከፍተኛ የመሬት መንቀጥቀጥ መመታቱን ያትታል።
በዚ ጊዜ ባል በከፍተኛ መሸበር እና መደናገጥ በፍጥነት ወደ ሰፈሩ በሩጫ አቀና።
አከባቢው ላይም ሲደርስ መንደሩ በፖሊሶች እና በነብስ አድን ሰራተኞች ተከቦ ያገኘዋል።
ወደ ውስጥም ዘልቆ ሊገባ ሲል ባከባቢው የነበሩ ፖሊሶች እንዳይገባ ይከለክሉታል።
እባካቹ አሳልፉኝ የልጅነት ፍቅሬ(ሚስቴ) ከውስጥ ነው ያለችው እያለ መማፀን ጀመረ??
ፖሊሶቹም ፦አፓርታማው በጣም ስለተጎዳና ሙሉ ለሙሉ ሊፈርስ ስለሚችል ለህይወትህ አደጋ ነው ስለዚህ ማለፍ አትችልም ይሉታል።
በዚ ጊዜ ባልም ከፈለጋቹ ተኩሳቹ ግደለኝ ይልና ፖሊሶቹን ጥሶ በከፊል ወደፈራረሰው አፓርታማ ዘልቆ ይገባል ።
ከብዙ ፍለጋና ልፋት በኋላም ሚስቱ በፍርስራሽ ተሸፍና ለመሞት እያጣጣረች ያገኛታል።
ሊያወጣት ቢሞክርም በላያ ላይ ያለውየብሎኬት እና የሲሚንቶ ፍርስራሽ ብዙ ስለነበር ሊያወጣት አልቻለም።
ሚስትም፦ እያቃሰተች የመጨረሻ ቃሏን እንዲህ ስትል ነገረችው፦ ውዴ አንተ የመኖሬ ምክንያት ዛሬ አንተ እውነተኛ አፍቃሪ እንደሆንክ በቃላት ድርደራ ሳይሆን በተጨባጭ በተግባር አሳይተህኛል።
ዛሬ አንተ ባትመጣ ኖሮ ሁለት ሞት እሞት ነበር።
አንድም በ#አካል ሁለትም #በመንፈስ ።
ነገር ግን አሁን አንተ ስለኔ ስትል ህይወትህን አደጋ ላይ ጥለህ ስለመጣህልኝ በመንፈስ ከመሞት ተርፌ በአካል ብቻ እሞታለው።
ውዴ፦ ጥዋት እንደነገርኩህ የፈጣሪ ትእዛዝ እስከሆነ ድረስ የመጣውን ሁሉ በፀጋ አለመቀበል ፈጣሪን መፈታተን ነው። ስለዚህ የእውነት የምትወደኝ ከሆነ ቀጥሎ የምልህን ነገር እህህህ ብለህ ስማኝ፦ እኔ ቀኔ ስለሆነ ለዘላለሙ ልሄድ ነው።
አንተ ግን ሌላ ሚስት አግባ ልጆችም ውለድ።
ነገር ግን ይሄን ቃሌን ጥሰህ በኔ ሀዘን ተቆራምተህና እኔን እያሰብክ ቀሪ ህይወትህን የምታበላሽ ከሆነ ዛሬ እኔን የገደለኝ የመሬት መንቀጥቀጡ አደጋ ሳይሆን # አንተ ነህ ብላ የዘላለም እንቅልፍ አሸለበች።
❤️ ተ 🔣ፈ 🔣ፀ 🔣መ ❤️
❤️ እውነተኛ ፍቅር መስዋእትነትን ይጠይቃል። ❤️
❤️ ጊዜና ሁኔታ(ደስታና መከራ) የማያናውጠው ፍቅር ይስጠን ። ❤️
ትወጂኛለሽ አለኳት? አይ ነበረ መለሷ
መሬቱን አያየች ተጣልታ ከራሷ
ጉንጯም አየቀላ አጇም ሲርበተበት
አልወድህም ብላኝ ስታየኝ በስስት
አልቻልኩም!!
ገፋኝ የሆነ ነገር !!
አቅፍ አረኩና ከንፈሮቿን ሳምኳት
አቦ አንዴት ጣፋጭ ናት!!!
ደረቴን
ደረቴን በአጇ አሩቅ ገፈተረችኝ
ተንደርድራ መጣች አጅግ ደነገጥኩኝ!!
አንዳላራቀችኝ ቀረበችኝ
አንዳልፈራችኝ ደፈረችኝ
መልሳ ሳመችኝ!!!
ያሰብኳትን ያችን ቁርጥ ሆነችብኝ
ቦታ ተቀያይረን ጭራሽ ትወደኛለህ አለቺኝ?
አይ ነበረ መልሴ መሬት እያየውኝ
አልወድሽም አልኳትኝ
አቦ በቃ ወንድ ልጅ አይደንግጥ
ከኔ በላይ ሆናብኝ እኮነው
➿➿➿➿➿➿🫥➿➿➿➿➿➿
የስጋዬ ክፋይ የደሜ ጠብታ፣
እየጠበኩህ ነው ከጧት እስከማታ።
የት ነህ ልጄ አለሜ...?
አንተን በመጠበቅ ዘመናት ነጎዱ፣
ስለአንተ ሳለቅስ ስንቶች ልጅ ወለዱ።
አይኔ ሟሙቶ አለቀ ጨለማ ጋረደው፣
ልቤም ሟሙቶ አለቀ ብሶት አነጎደው።
አባትህ ቦጋለም....
ጠላ ስጭኝ ብሎ ድንገት ቢጠይቀኝ፣
ከሳምንት በኋላ ሲናገር ደስ ብሎኝ።
ጠላ ለመበደር ከጎረቤት ሂጄ
ስመለስ ካልጋው ላይ በረዶ ነክቶ እጄ
ደግሜ በፍርሀት ጣቶቼን ብልክም፣
ያ ሞቃቱ ገላው እስትንፋሱ የለም።
እናም ልጄ ሆዴ...
እንደ እብድ እያረገኝ ደግሞ እንደወፈፌ፣
አለው ለብቻዬ...
ያባትህን በድን ሬሳ ታቅፌ😭
ከፍቅር እስከመቃብር ሁሌም የማልረሳው ክፍል!
ውዴ! ባንተ ያምራል😍
ስንቶች በማስመሰል ህይወቴነሽ ሲሉ፣
በፍቅር ስም ብለው በሀሰት ሲምሉ።
ከፊልም ከልቦለድ ከግጥም መድብሉ፣
በተዋሱት ቃላት እየሸነገሉ፣
ፍቅርን ቢናዘዙም ቃላት አሰማምረው፣
ያ'ንተ ሁለት ፊደል ትርጉሙ ረቂቅ ነው።
ውዴ....!
በዚች ቃል ስትጠራኝ ልቤን ሞላው ሀሴት፣
እኔ እስከሚመስለኝ ባለም ላይ ያለው ሴት።
እናም ዛሬም ተነስ ላዳምጥህ ምከረኝ፣
ያኔ ያልሰማውህ ዛሬ ላይ ፀፀተኝ።
ተይ ብለኸኝ ነበር....!
ፈጣሪን ማማረር ማጉረምረም ይቅርብሽ
የመከራ ሸክም ጠፍሮ እንዳይጭንሽ።
ያኔ ባልሰማህም ዛሬ እሰማሀለው፣
ተነስ ውዴ በለኝ የሚያምረው ባንተ ነው።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
............ ጪስ ጪስ ይላል ...........
መጨስ ማለት ማጨስ መስሎ የታያቸው
ብዙ ፍልጦች አሉ በየጉራንጉሩ መጨስ ፣
።።።።።። እና መንደድ የተምታታባቸው።
እዛጋ አንዲት ሴት እጨሳለው ብላ፣ ክብሪት የለኮሰች ፣
ማንነት የረሳች ፣
ታሪክ የሰረዘች ፣
በያዘችው ክብሪት እንዲው ነዳ ቀረች ።
አንዱ ደሞ እዛጋ ዲንጋይ ላይ ተቀምጦ ፣
በሱስ በናወዘ ባደፈ አምሮ ፣
እኔ ጪስ ነኝ ይላል ለመጨስ ሞክሮ።
ደሞ ከሱም ብሶ ሀገር ሀገር አትበል ፣
ፋራ አትሁንብኝ ፣
አድዋ ምኔ ነው ለኔ ምን ጠቀመኝ ፣
እያለ ይጮሀል ፣
ጪስነትን ሊከትብ' መርፌውን ይመዛል ፣
በመዘዘው መርፌ ታሪክ ይመርዛል ፣
ለማጨስም ብሎ ክብሪት ይለኩሳል ፣
በለኮሰው ክብሪት ሀገር ያቃጥላል ፣
ከሚጨሰው ሀገር ተመልከት ይልሀል ፣
አይኑን ጪስ አፍኖት ጭሱን ያሳይሀል፣
በጪሱ አፈና እራሱን የሳተ፣
ደሞ እንዲህ ያወራል ፣
"በቃ እኔ መሮኛል
ኢትዮጵያ ተሺጣ የድርሻዬን ስጡኝ "
ብሎ ይፎክራል ፣
ካመረራት መሬት ካቃጠላት ሀገር፣ ድርሻውን ሊካፈል ደሞ እጁን ይሰዳል ፣
በፈጠረው ቅዠት በሀሳቡ ያብዳል ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሀገር መሸጥ ,ማንነትን መርሳት ፣
ታሪክን ማንቋሸሽ
ከሆነ እርድና ከሆነ ጪስነት ፣
ላንዲቷ ሀገሬ ፣
ለውዷ እናቴ ለምዬ ኢትዮጵያ ፣
ስንቶች ለሞቱላት ደም ለፈሰሰባት፣
ባልጠቅማትም እንኳን ፋራ ልሁንላት ።
ሲመስለኝ ወዳጄ ሀገር ወዳድ ዜጎች፣
ታሪክ ጠባቂዎች አርበኞች ባሉባት፣
አምላክ ባላት ሀገር እጨሳለው ማለት፣
አንድም ለመቃጠል ወይ ነዶ ለመቅረት።
#ቆንጆ ነኝ
.
.
ስላንቺ ቁንጅና
ስላንቺ ቁመና
ከንፈር እና ዳሌ
ጥርስና ተረከዝ ፣ ፀጉር ገለመሌ
ለጡት ለወገብሽ ፣ ለፀባይሽ ጭምር
በግጥም በዝርው ፣ ባድናቆት ስዘምር
እስከዛሬ ድረስ...
ውበትሽን አግንኜ ፣ ሰርክ መለፈፌ
እኔ ስለራሴ ...
አንዳች ቀን እንኳን ፣ ግጥም አለመፃፌ
ሲትጠዪኝ ቆጨኝ
ቢሆንም ቆንጆ ነኝ፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
እርግጥ ነው ብዙዎች...
ስለኔ ሳወራ ፣ ድንገት ያኮርፉኛል
ያንተን ሌሎች ያውሩ ፣ ብለው ይነግሩኛል
እኔን ከኔ በላይ...
እርግጠኛ ሆኖ ፣ ሌላ እንዴት ያውቀኛል?!
።።።።፣፣
እናም እኔ ማለት...
ቁመቴ ከአክሱም ፣ በእጥፍ ይረዝማል
ጣፋጭ አንደበቴ...
መስማት ለተሳነው ፣ ለስልሶ ይሰማል
ውብ አረማመዴ...
እንኳን መንገደኛን ፣ መንገድን ያቆማል፡፡
፡፡፡፡፡፡
የከንፈሬ ወዙ ፣ ጥፍጥናው አያልቅም
ጥርሴ ሺ ገዳይ ነው!
ሺ ሟች ላለማየት ፣ ኗሪ ፊት አልስቅም፡፡
ከአይኔ ብሌን ውስጥ ፣ ብርሐን ይፈልቃል
አይኔን ያየ ሁሉ
ልቡን አሳውሮ ፣ በፍቅር ይወድቃል፡፡
፡፡፡፡፡
የገላዬ ጠረን ፣ ከሽቱ እጥፍ ነው
መልካም ጠረን ሁሉ...
አለ ባሉት ስፍራ ፣ እኔ አለሁ ማለት ነው፡፡
ፀባየ ትሁት ነኝ ፣ ምጡቅ ነው እውቀቴ
ግርማ ሞገሳም ነው ፣ ተክለ ሰውነቴ
ያየኝ ይወደኛል
የወደየኝ ሁሉ ፣ መቼም አይጠላኝም
ከዚ በላይ እንኳን...
ብዙም ስለራሴ ፣ የማውቀው የለኝም፡፡
እንደውም እንደውም...
አልጎርርም እንጂ ፣
ያፈር ሰውነቴን ፣ በቁንጅና አብየው
ቆንጆ ማየት ሲያምረኝ ፣ራሴን ነው ማየው፡፡
ብቻ ግን ቆንጆ ነኝ!!!😜😂
🌹።።።።።🌹የፍቅር ጅማሮ🌹።።።።🌹
አዳምና ሄዋን ፍቅራቸው ሲጀመር
ታሪኩ እንዲህ ነበር
ሄዋን ፍቅር ይዟት ተጨንቃ ተጠባ
ስትል ፈራ ተባ
ቆይታ ቆይታ
እንደዚ አለችው አዳምን ተጣርታ
"ምን ብዬ ልንገርህ
አዳም የኔ ፍቅር
ፍቅርህን እሻለሁ
በጣም እወድሃለሁ
መልሥህን ንገረኝ እባክህ በሞቴ
ፍቅሬን ተቀበለኝ አዳም አካላቴ"
በማለት ጠይቃው ልቧ ሲንሠፈሠፍ
"ምን አማራጭ አለኝ!" አላትና እርፍ
ከዚያን ጊዜ ወዲህ ምን በፍቅር ብታልቅ
ከሡ ይምጣ እንጂ እሷ ጠይቃ አታውቅ!
