መጽሐፉ ይናገር | Official
رفتن به کانال در Telegram
መጽሐፉ ይናገር ክርስቲያናዊ አገልግሎት በወንጌላዊያን አማኞች የነገረ መለኮት ተማሪዎችና የቃሉ አገልጋዮች በ2013 ዓ.ም የተመሠረተ ተቋም ሲሆን አሁናዊ መስኮቹ፦ 🔘 የመጋቢያንና መሪዎች ስልጠና 🔘 የመጽሐፍ ቅዱስ ኮሌጅ (Gateway) 🔘 የቲቪ ፕ/ም በተስፋ TV ቅዳሜ 9-10 🔘 መጽሐፍ ቅዱሳዊ ኅብረቶች ሊንክ፦ @metsihafuyinager በውስጥ፦ @adfontess ☎️ +251947424046
نمایش بیشتر342
مشترکین
+124 ساعت
+27 روز
+1330 روز
آرشیو پست ها
ዝናቡን አሸንፈው የተገኙ ታማኝ እህት ወንድሞች በተገኙበት የዛሬውን እለት መርሓ-ግብር በጥሩ ሁኔታ አካኼድን። እግዚአብሔርም አገዘን።
በወንድም ፋኑኤል ብርሃነ፡ የቤተ ክርስቲያን ሁለቱ ገጽታዎች መካከል ያለ ተፈጥሯዊ ውጥረት! ገለጻ (presentation) ቀርቦ ተወያይተናል።
ሰሎሞን ከበደ፣ በርናባስ በቀለ እና ዓለም ታደሰ ገለጻውን ከተካፈሉ ቤተሰቦቻችን ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሾችን በማቅረብ የፋኑን Presentation አዳብረዋል።
ስለ ቤተ ክርስቲያን ይህ ሁሉ ከገባን ቀጥሎ ምን እናድርግ? ምን እንሥራ? ምን ታቅዷል? ከአንዷ ቤተሰባችን የቀረበ ሞጋች ጥያቄ ነበር።
- መጽሐፍትን መመርመር
- የተገለጠውን እውነት አጥብቆ መያዝ
- እውነቶቹን ወደ ብርሃን ማውጣት (መግለጥ)
- የአዲስ ማኅበረሰብ ግንባታ (Restoration)
ቤተ ክርስቲያንን በሚመለከት የሥራችን መንገዶች እንዲሆኑ ምላሽ ቀርቧል።
---------
ይህን እውነት ለሌሎች አጋሩልን።
የውስጥ መስመር፦ @adfontess
የእውነተኛዋ ቤተ ክርስቲያን መልክ!
-----🎻---------
ነገ (ሐምሌ 05/2018)!
ቤተ ክርስቲያን ሕያዊት ወይስ ተቋማዊት
(Organism Vs Organization)
------------------
መጽሐፉ ይናገር አጠቃላይ ቤተሰብና በጌትዌይ Community ወርሃዊ የአንድነት ጊዜ እርስዎም ተጋብዘዋል።
እለቱ፦ ነገ (ሐምሌ 05) 2018
ሰዓት ⏰ 9:00-11:30
ቦታ🔘 ልደታ GTC ማስተማሪያ
☎️ 0947424046
ቴሌግራም፦ @adfontess
ዛሬ በአያት Center!
የቆላስይስ መልእክት ጥናት በአያት ሴንተር ዛሬ ይጀመራል። አያትና በአካባቢው ያላችሁ መታደም ትችላላችሁ። ልክ 11:30 ይጀምርና 1:30 ያበቃል። በአቅራቢያው የሚኖሩ ወዳጆች ካሏችሁ እንዲቀላቀሉን ጋብዟቸው።
ቃለ እግዚአብሔርን የሚወድና የሕይወቱ መሠረት ያደረገ ትውልድ ለመፍጠር አብረን እንሥራ። ወደ አገልግሎቱ ለመምጣት የቴሌግራማችንን የውስጥ መስመር ይጠቀሙ።
👉 @adfontess
እንኳን አደረሰን!
በጥቂት የእግዚአብሔርን ቃል ከሚወዱና የሕይወታቸው መመሪያ ሊያደርጉ ከወሰኑ ሰዎች ጋር የተጀመረው ኅብረት እያደገ ለብዙዎች መጽናናት ሊሆን የሚችል ቤተሰብ ተገነባ።
አጥቢያ ቤተ ክርስቲያናትን በትምህርት ለማገዝ ታስቦ የተጀመረው የስልጠና ማዕከሉም ተወዳጅ የቃለ እግዚአብሔር ተማሪዎችን አፈራ፤ እነሆ በእግዚአብሔር ጸጋ በመታገዝ ሚኒስትሪያችን Officially ከተመሠረተ ዛሬ ሰኔ 30, 2018 አምስት አመት ሞላው።
ላለፉት አምስት አመታት አብራችሁን የቆያችሁ፣ ያገለገላችሁና በአንድም በሌላም ስለ አጠቃላዩ ቤተሰባችን ዋጋ የከፈላችሁ ሁላችሁ እንኳን ለዚህች ቀን አደረሳችሁ።
የፊታችን እሑድ ከሰዓት (ሐምሌ 05) ልደታ በሚገኘው የGTC ማስተማሪያ ስፍራችን የጋራ ጊዜ ይኖረናልና ቀጠሯችሁን ከወዲሁ አስተካክሉ። ለተጨማሪ መረጃ ጻፉልን!
የውስጥ መስመር፦ @adfontess
ዛሬ ከሰዓት በአያት ሴንተር!
----------------
የክርስቲያናዊ ኅብረት መሠረታዊያን (Foundations of Christian Fellowship)
▣ የእግዚአብሔር አሃዱ ስሉስነት የመጽሐፍ ቅዱሳዊ ኅብረት ጽኑ መሠረት!
▣ የፍጥረት ሕይወት ቀመርና መስተጋብር የእውነተኛው ኅብረት ሞዴል!
-----😊-------
ሰዓት፦ 9:00-11:30
ቦታ፦ አያት Shopping Mall
☎️ 0947424046
ቴሌግራም፦ @adfontess
በሐምሌ 05/2018 (ነገ ሳምንት/እሑድ) 9:00-11:30 ልደታ በሚገኘው የGTC ማስተማሪያ የጋራ ጊዜ ይኖረናል።
የእለቱ ይዘት ጭብጥ ሃሳብ፦ "የእውነተኛዋ ቤተ ክርስቲያን መልክ" ⛪ (መነሻ ሃሳብ ይቀርብና ወደ ውይይት ይኼዳል፤ በተወዳጁ ቡና የቤተሰብነት ጊዜው ይደምቃል!)😊
እለቱ፦ ሐምሌ 05/2018
አጀንዳ፦ የእውነተኛዋ ቤ/ክ መልክ
ቦታ፦ 📍ልደታ ፊሊንትስቶን ሕጻ አጠገብ
ሰዓት፦⌚ 9:00-11:30
☎️ 0947424046
ቴሌግራም፦ @adfontess
ነገ (28/102018) ይካኼድ የነበረው የአጠቃላዩ ማኅበረሰባችን የአንድነት ቀን ወደ ቀጣይ ሳምንት ሐምሌ 05/2018 ተሸጋግሯል።
እሑድ ከሰዓት ሁልጊዜ (ከአመታት በፊት በፒያሳ ኅብረት የተለመደው) ከ9:00-11:30 የBiblical Reflections እና የቤተሰብነት ጊዜ ይኖረናል።
በሳምንቱ ቀናት መካከል ደግሞ አንዱን ቀን (ለጊዜው ሐሙስ ምሽት ተመርጧል) ከ11:30-1:30 የቆላስይስ መጽሐፍ ይጠናል።
በዚህ አገልግሎት እዚያ ያለውን team join ማድረግ የምትፈልጉ በውስጥ መስመር ጻፉልን። ደውሉልን።
ቴሌግራም፦ @adfontess
☎️ 0947424046
በአዲስ አበባ አያት፣ CMC፣ ፍየል ቤት፣ ፊጋ፣ ጣፎ፣ 72፣ አራብሳና አርባ ዘጠኝ ያላችሁ ቤተሰቦቻችን በዚህ ማዕከል በአንድም በሌላም አብራችሁን መሥራት ትችላላችሁ።
ያለፈው እሑድ (ሰኔ 21/2018) አዲሱ ማዕከላችን በይፋ ሥራ ጀምሯል። የሚኒስትሪው መስራች አባላትና ከቢሮም ጥቂት ወንድሞች በተገኙበት የቤተሰብነት ጊዜ ተካኼዷል። የነበረንን ጊዜ ቆይታ ከታች ባለው ምስል አያይዘናል።
ነገ ከሰዓቱ 9:00-11:30 በአዲስ አበባ አያት አካባቢ Center በሚኖረን ኅብረት የውይይት መነሻ ሃሳቦች!
----------------------
▣ የክርስቲያናዊ ኅብረት መሠረት (Foundation of Christian Fellowship)
▣ በክርስትና የጋራ ማንነትና የአማኙ ሚና (Communal Identity of Christianity & role of the individual)
▣ ክርስቲያናዊ ኅብረትና መጽሐፍ ቅዱሳዊ የጋራ አምልኮ (Christian Fellowship & Corporate Worship)
-----------------
ኑ አብረን በቃሉ ማዕድ እንቀመጥ!
በእውነተኛ ወንድማማች መቆረስም ደስ ይበለን!
ለተጨማሪ መረጃ፦
☎️ 0947424046
ቴሌግራም፦ @adfontess
ከላይ በጠቀስናቸው 3 (ሦስት) የአገልግሎታችን የሥራ መስኮች አብራችሁን መሥራት የምትፈልጉ ወደ ቢሯችን ብቅ ማለት፣ በውስጥ መጻፍም ሆነ ደውላችሁ ስለ አገልግሎቱ ተጨማሪ መረጃዎችን ማግኘት ትችላላችሁ።
ቴሌግራም የውስጥ መስመር፦
👉 @adfontess
የቢሮ ስልክ፦
☎️ 0947424046
የነገረ መለኮት ኮሌጅ መረጃ፦
👉 @gatewayclass
➌ የሚዲያ አገልግሎት
ሚኒስትሪያችን አጥቢያ ቤተ ክርስቲያናትን ሊያግዝ በሚያስብባቸው አቅጣጫዎች የተዘጋጁ ይዘቶችን ወደ ሚዲያ ለማምጣት ይጥራል። ላለፉት አምስት አመታት በዚህ አቅጣጫ ብዙ ያልሠራንበት ቢሆንም በዚህኛው አመት (2018) ጀምሮ ግን የሚዲያውን ዘርፍ በይፋ ተቀላቅለናል።
የሚዲያ አገልግሎቱ ሁለቱንም የሚዲያ መስኮች (Mainstream Media & Social Media) ባካተተ መልኩ እንቅስቃሴዎችን ጀምሯል።
➢ የቴሌግራም የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት
@metsafuynager
➢ የተቋሙ የቴሌግራም official ገጽ
@metsihafuyinager
➢ መጽሐፉ ይናገር የfacebook ገጽ
➢ መጽሐፉ ይናገር Tiktok
➢ መጽሐፉ ይናገር TV በTesfa Broadcasting Corporation
- ቅዳሜ ከሰዓት 9:00-10:00
- ረቡዕ ምሽት በድጋሚ (2:00-3:00)
➋ ነገረ መለኮት /Gateway Theological College/ 🎓
ቤተ ክርስቲያንን ወደ ቀደመው መሠረቷ መጥራቱን ዓላማው አድርጎ የሚሠራው ተቋማችን ውጥኑን ከግብ ለማድረስ አጫጭር ስልጠናዎች ብቻ በቂ እንዳልሆኑ ስለተገነዘበ በመደበኛ ነገረ መለኮት ትምህርት በኩል ቤተ ክርስቲያንን ለማገዝ ይሠራል።
Gateway Theological College የዚህ ሚኒስትሪ እህት ተቋም ሲሆን ሚኒስትሪው ስለ እውነተኛ ተሐድሶና የቤተ ክርስቲያን ተልዕኮ ያለውን ጩኸት በወጥነት የሚያስተጋባበት ሌላኛው መድረክ ነው።
ጌትዌይ 2014 ዓ.ም የተጀመረ የነገረ መለኮት ተቋም ሲሆን ላለፉት አራት አመታት ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች በየካቲት 2018 በአዲስ አበባ አስመርቋል። ተማሪዎቹ ከተለያዩ ክፍለ ዓለማት፣ ቤተ እምነቶችና የሥራ መስኮች ሲሆኑ ከምሩቃኑ መካከል ሚኒስትሪው ይዞት የተነሳውን ሃሳብ (ሊያጠብ የሚፈልገውን ክፍተት) የግላቸው ጉዳይ ያደረጉ ጥቂት ተማሪዎች ቀጥለውም ከአገልግሎቱ ጋር ይሠራሉ።
ጌትዌይ በዚህ ጊዜ ከአንደኛ እስከ አራተኛ አመት ተማሪዎች ያሉት ሲሆን በየጊዜው አዳዲስ ተማሪዎችን እየተቀበለ ትውልዱን የማስታጠቅ ሥራውን ይቀጥላል።
በተግባር የሚሠሩ ሥራዎች ምን ምንድናቸው!?
------------
በዚህ ወቅት ተቋሙ በሦስት ዋና ዋና አቅጣጫዎች ይንቀሳቀሳል።
➊ የአጥቢያ ቤተ ክርስቲያን መጋቢያንንና መሪዎችን በትምህርትና ስልጠናዎች ማገዝ።
ይኸኛው አገልግሎት ነባሩን system ለማገዝ ተብሎ የታቀደ ሲሆን የአጥቢያ ቤተ ክርስቲያን መጋቢያንንና መሪዎችን በተለይም በክርስትና አስተምህሮ መሠረታዊያን ረገድ ማገዙ ላይ ትኩረቱን ያደርጋል።
በአንድ ወር አንዲት አጥቢያ ቤተ ክርስቲያንን የማገዝ እቅድ ይዞ የሚንቀሳቀሰው ተቋማችን ባለፉት አምስት አመታት በዚህም ረገድ ከቤተ ክርስቲያናት ጋር ሲሠራ ቆይቷል።
የአገልግሎቱ ራዕይ/ዓላማ ምንድነው?
በጤናማውን መጽሐፍ ቅዱሳዊ አጥብቆ በመያዝና በእውነተኛው ክርስቲያናዊ ወንድማማችነት መያያዝ ክርስቲያናዊ ተልዕኮውን የሚፈጽም ማኅበረሰብ ማየት።
"መጽሐፉ ይናገር ክርስቲያናዊ አገልግሎት" ምንድነው?
ይህ አገልግሎት በወንጌላውያን አቢያተ ክርስቲያናት ቤተ እምነቶች (ከነባሮቹ/ the mainlines) የተወጣጡ የመጽሐፍ ቅዱስ ተማሪዎች የተጀመረ ክርስቲያናዊ ተቋም ሲሆን ላለፉት አምስት አመታት በተለያዩ መንገዶች ቤተ ክርስቲያንን ሲያግዝ ቆይቷል።
ይህ የመጽሐፉ ይናገር ክርስቲያናዊ አገልግሎት ኦፍሴላዊ (official) የቴሌግራም ቻናል ነው። በሚቀጥሉት ቀናት ስለ አገልግሎቱ አጀማመር፣ አጠቃላይ እንቅስቃሴዎችና አሁን እየተሠሩ ስላሉ ሥራዎች ሰፋፊ መረጃዎችን እዚህ እናስቀምጣለን። እስከዚያው ቻናሉን ተቀላቀሉ! ለሌሎችም አጋሩ። እናመሰግናለን!
