መጽሐፉ ይናገር | Official
رفتن به کانال در Telegram
መጽሐፉ ይናገር ክርስቲያናዊ አገልግሎት በወንጌላዊያን አማኞች የነገረ መለኮት ተማሪዎችና የቃሉ አገልጋዮች በ2013 ዓ.ም የተመሠረተ ተቋም ሲሆን አሁናዊ መስኮቹ፦ 🔘 የመጋቢያንና መሪዎች ስልጠና 🔘 የመጽሐፍ ቅዱስ ኮሌጅ (Gateway) 🔘 የቲቪ ፕ/ም በተስፋ TV ቅዳሜ 9-10 🔘 መጽሐፍ ቅዱሳዊ ኅብረቶች ሊንክ፦ @metsihafuyinager በውስጥ፦ @adfontess ☎️ +251947424046
نمایش بیشتر340
مشترکین
+124 ساعت
+27 روز
+1330 روز
آرشیو پست ها
ለእውነተኛው ክርስቲያን የእምነቱ መሠረት ክርስቲያናዊ አስተምህሮ ነው። ክርስቲያናዊ ኅብረት በክርስቲያናዊ እምነት መሠረቶች ላይ ሊታነጽ ይገባል። ያለ አስተምህሮ ኅብረት ያለ አጥንት በሕያውነት ለመቆም የሚታገል ሥጋ ይመስላል። በመሠረታዊያን የክርስትና እውነቶች እንግባባ ዘንድ መጽሐፉን መመርመር አለብን። እጆቻችን ላይ ያሉ ልምምዶችን በቃሉ ብርሃን መፈተሽ አለብን። "መጽሐፉ ይናገር" ስንል ወደ ቀደመው መሠረት እንመለስ እያልን ነው።
------------
Join Us! & Share!!!
@metsihafuyinager
------------
ወደ ውስጥ፦ @adfontess
ዛሬ አያት በነበረን ጊዜ ቆላስይስ 1:1-2 ተመልክተናል። የዛሬው ጥናት ትኩረታችን ቁ2 የነበረ ሲሆን ይኸውም ጸሐፊው ስለ መልእክቱ ተቀባዮች ያስቀመጣቸው እውነቶች ናቸው።
➢ ቅዱሳን፣
➢ በክርስቶስ/ለክርስቶስ የታመኑ፣
የሚሉ የመልእክቱን ተቀባዮች ገላጭ ሃሳቦች በጥናት ክፍሉ ዐውድ ተብራርተዋል። በቆላስይስ (በከተማዋ) የሚገኙ ግን ለእግዚአብሔር የተለዩ ስለመሆናቸው የሚናገረው የመጀመሪያው ገላጭ ስለ positional Holiness የሚያወራ ስለመሆኑ ተነጋግረን ለክርስቶስ/በክርስቶስ የታመኑ (Faithful in Christ) የሚለው ሃሳብ ደግሞ የድነታቸውን practical aspect የሚመለከት ስለመሆኑ ተወስቷል።
"ወንድሞች" የሚለውም ሃሳብ በጥናት ክፍሉ ዐውድ ታይቷል። ይኸውም ጳውሎስ ነገረ ድነትን ከነገረ ቤተ ክርስቲያን ጋር የሚያቆራኝበትን ሃሳብ እንድንመለከት ረድቶናል።
ልንወያይባቸው የሚያስፈልጉ ጥያቄዎች ተነስተዋል።
➘ መቀደስ ይቀድማል መታመን?
➘ "በክርስቶስ ለታመኑት" ሲል ክርስቶስ ያመናቸው ናቸው ወይስ በርሱ ያመኑ (የታመኑ)?
➘ አንዳንድ ትርጉሞች "ታማኝ ወንድሞች" ሲሉ ጥቂት የእንግሊዝኛ ትርጉሞች "ወንድሞችና እህቶች" የሚሉት ለምንድነው?
➘ መቀደስ የእግዚአብሔር ድርሻ መታመን የአማኙ ነው ማለት ነው? ወይስ ሁለቱንም የሚሠራቸው እግዚአብሔር ነው?
➘ መታመን (ታማኝነት) እና "የደህንነት initial እምነት" መካከል ያለው ልዩነት ምንድነው?
እነዚህን ጥያቄዎች ወደፊት በአያት ሴንተር ሲያልፍም እዚሁ Online በVoice Chat እንነጋገርባቸዋለን። እናንተም Interested የሆናችሁባቸውን ጥያቄዎች አሳውቁንና እዚሁ እንወያያለን።
------------
Join Us! & Share!!!
@metsihafuyinager
------------
ወደ ውስጥ፦ @adfontess
ዛሬ ምሽት የሚኖረን የቆላስይስ መልእክት ጥናት እንደነበረ ነው። የጥናት ክፍሉ ቆላ 1:1-2 ያለው ክፍል ሲሆን ባለፈው የጥናት ቀን ያልተዳሰሱ የውይይት ጥያቄዎች (ጥያቄ ቁ3 እና 4) ውይይት ይደረግባቸዋል። ጥያቄዎቹ የተለጠፉበትን Post ከዚህ በመቀጠል pin እናደርጋለን። ከሥራ ሰዓት በኋላ 11:30 አያት Shopping Mall ላይ እንገናኝ።
ክርስቶስ ኢየሱስ ከእግዚአብሔር እቅፍ ወጥቶ ለቤዝዖቱ ሥራ መጣ፣ ከክርስቶስ ኢየሱስ ማንነትና ሥራ የድነት ወንጌል ወጣ፣ ከወንጌሉ ውስጥ መሲሓዊቷ ማኅበር (ቤተ ክርስቲያን) ወጣች፣ ከቤተ ክርስቲያን (በኩል) ሕያውነት ወደ ዓለሙ ይወጣል።
------------
Join Us! & Share!!!
@metsihafuyinager
------------
ወደ ውስጥ፦ @adfontess
"ክርስትና እንደ ዓለም መኖር ሳይሆን የዓለምን System እየተገዳደሩ መኖር ነው!"
----
Join Us! & Share!!!
@metsihafuyinager
------------
ወደ ውስጥ፦ @adfontess
ከ45 ደቂቃዎች በኋላ (3:00 ላይ) በቲክቶክ ገጻችን (መጽሐፉ ይናገር) የይሁዳ መልእክት ጥናት ይኖረናል። ዛሬ የምናየው ቁ17-21 ያለውን ክፍል ነው። በሰዓቱ እንገናኝ። ሌሎችም እንዲገኙ Share እናድርግ። ጸጋው ከቤተሰባችን ጋር።
------------
Join Us! & Share!!!
@metsihafuyinager
------------
ወደ ውስጥ፦ @adfontess
ዛሬ ምሽት በTiktok ገጻችን!
-------🔥------------
የይሁዳ መልእክት ጥናት! 📖
እለቱ፦ ማክሰኞ ምሽት
ሰዓቱ⏰፦ 3:00-4:30
ቤቱ፦ መጽሐፉ ይናገር
የጥናቱ ክፍል፦ ቁ17-21
ሁላችሁም በመገኘት እናትርፍ!!
------------
Join Us! & Share!!!
@metsihafuyinager
------------
ወደ ውስጥ፦ @adfontess
የጸጋ ስጦታ ሲጀመርም የጸጋ ነው። የመንፈስ ቅዱስ ስጦታም በመሆኑ የራሱ የእግዚአብሔር ነው። የሰውዬው ሳይሆን የአካሉ ነው። አንደውም ሰውዬው ራሱ የኛ ነው።
------------
Join Us! & Share!!!
@metsihafuyinager
------------
ወደ ውስጥ፦ @adfontess
"ጠቢብ በጥበቡ አይመካ፣
ኃያልም በኃይሉ አይመካ፣
ሁሉን ቻይ እግዚአብሔር
ጽድቅንና ፍርድን በምድር ላይ...
ማድረጉን ያወቀ በጌታ ይመካ!"
------------
Join Us! & Share!!!
@metsihafuyinager
------------
ወደ ውስጥ፦ @adfontess
የእግዚአብሔር መንግሥት አዕምሮ የቤቱ ማሰቢያ ማዕቀፍ (framework) ባልሆነበት፣ የክርስቶስ ማንነትና ሥራ ማዕከላዊነት ባልተረጋገጠበት፣ የቅዱሳት መጻሕፍት ባለ የበላይ ሥልጣንነት በተግባር ከማይታይበት ኅብረት ከመሆን የእግዚአብሔር ፈቃድ ያለበት ጭው በረሃና የለየት ብቸኝነት ይሻላል።
------------
Join Us! & Share!!!
@metsihafuyinager
------------
ወደ ውስጥ፦ @adfontess
እግዚአብሔር የጠራን ከርሱ ጋር ለሚኖረን እውነተኛው ኅብረትና ሕይወት እንጂ ለሩጫ (ለአገልግሎት) አይደለም። እርሱ በሚቸረን ጸጋ በመንግሥቱ ሥራ እንሮጣለን፣ ነገር ግን ከርሱ ጋር ያለንን ኅብረትና ሕይወት ከሁሉ ነገር እናስቀድማለን!!!
------------
Join Us! & Share!!!
@metsihafuyinager
------------
ወደ ውስጥ፦ @adfontess
ጳውሎስ፦
"በወንጌል አላፍርምና...." (ሮሜ 1:16)
እኛ፦ እንዴ Paul ለምን?
ጳውሎስ፦ "ለሚያምኑት ሁሉ የእግዚአብሔር ኃይል ለማዳን ነውና!" (የሚያድን መሆኑ 100% የተረጋገጠ ነውና!)
------------
Join Us! & Share!!!
@metsihafuyinager
------------
ወደ ውስጥ፦ @adfontessከነበረን ጊዜ እንደ ቅምሻ!
"በእግዚአብሔር ፈቃድ የክርስቶስ ኢየሱስ ሐዋሪያ የሆነ ጳውሎስ" (ቆላ 1:1)
ጳውሎስ ይህን እየጻፈ ያለው ከግሪኮ-ሮማን ዓለም በነበረው ደብዳቤ አጻጻፍ ስልት ተከትሎ ሲሆን ስለ ሐዋሪያነቱ ደግሞ ግልጽ Qualification ያስቀምጣል። ይህ የሚሆነው አንድም ለመልእክቱ (ቀጥሎ ለሚጽፋቸው ጉዳዮች) የስልጣኑን ምንጭ (source of authority) እየጠቀሰ ሲሆን የቆላስይስን አማኞች ፊት ለፊት አግኝቷቸው የማያውቅ እንደመሆኑ ደግሞ በትክክለኛው ተልኳዊ ማንነቱ እየተዋወቃቸው ነው። መልእክቱ የማንነቱን (የተላከበትን ስልጣን) የሚያህል ምላሽ የሚፈልግ ነውና።
በእግዚአብሔር ዘላለማዊ አቃጅነት በክርስቶስ ሿሚነት ጳውሎስ የአሕዛብ ሐዋሪያ ሆኗል። ከዕብራዊነት ስሙ "ሳውል" ይልቅ "ጳውሎስ" በተባለው ሮማዊ ስሙ የመልእክቶቹ መግቢያ መንበሽበሹም ሐዋሪያው ራሱን ከተልዕኮው ለይቶ የማያይ መሆኑን አመልካች ጭምር ነው። ጳውሎስ ሐዋሪያ የሆነው በDivine initiative (በእግዚአብሔር ፈቃድ) እንጂ በሰው እቅድ (human will) አይደለም። በእግዚአብሔር ፈቃድ የሆነ ሐዋሪያነቱን የተቀበለው ከክርስቶስ ኢየሱስ ነው። ክርስቶስ ኢየሱስ የእግዚአብሔር አድንሆታዊ ሥራ ማዕከልና አስፈጻሚ (agent) ነው። ይህን ስንል ታዲያ ለጊዜው ስለ Trinity economy እያወራን አይደለም። እንደርሱ የሚረዱ የቅዱሳት መጻሕፍት አጥኚዎች ቢኖሩም እኛ መጽሐፉ በራሱ ዐውድ ከተናገረ በኋላ systematize በማድረጉ እናምናለንና። እግዚአብሔር ለአናኒያ "የለየሁት እኔ ነኝ" ሲል ከመጽሐፉ ሰምተናል፤ ክርስቶስ ደግሞ በደማስቆ ሲሾመው (ሲልከው) በግልጽ ተነግሮናል።
ሐዋሪያትን የሚሾም (የሚሰጥም) ራሱ ክርስቶስ በመሆኑ ስለ ሐዋሪያነት ሹመት በዚህ ዘመን የሚነሱት ጥያቄዎች በጥንቃቄ ሊታዩ ይገባል። ይህ ሰው ክርስቶስ ከሾማቸው ሐዋሪያት የመጨረሻው ነውና። በኤፌሶኑም ሆነ በሌሎችም የአዲስ ኪዳን መልእክቶቹ (የጳውሎስ) ዐውድ አገልጋዮችን ለቤተ ክርስቲያን የሰጠ ራሱ ክርስቶስ ነው።
ጳውሎስ ይህን (የቆላስይስ) መልእክት እየጻፈ ያለው ከእግዚአብሔርና ከክርስቶስ በተሰጠው ስልጣንና ተልዕኮ ስር ሆኖ ነውና አንባቢዎቹም በዚሁ manner ማንበብ አለባቸው። አንብበው እንደ ሰው ምክርና ሃሳብ ሊያዩት አይገባም። በመልእክቱ ጳውሎስ ሲያዝ እግዚአብሔር እያዘዛቸው መሆኑን መገንዘብ አለባቸው። መጽሐፉን ማንበብ ያለባቸው በውስጡ ላለው እውነት ለመታዘዝ በተዘጋጀ ልብ ነው። በዚህም ዘመን ያለን አማኞች ለጳውሎስ መልእክታች ሞጋች እውነቶች የምንሰጣቸው ምላሾች (responses) ለራሱ ለእግዚአብሔር የምንሰጣቸው ናቸውና መልእክታቱን ስናነብ ለዚህ ስልጣን ልንታዘዝ መሆኑን እርግጠኞች እንሁን።
------------
Join Us! & Share!!!
@metsihafuyinager
@metsihafuyinager
------------
በውስጥ፦ @adfontess
የዛሬ ጥናት ክፍልና የውይይት ጥያቄዎች!
------------
ዋና ክፍል፦ የመልእክቱ መግቢያ (ቆላ 1:1-14)
ንዑስ ክፍል፦ ሰላምታ (ቆላ 1:1-2)
በእግዚአብሔር ፈቃድ የኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋሪያ የሆነ ጳውሎስ ጢሞቴዎስም ወንድሙ፣ በቆላስይስ ለሚኖሩ ቅዱሳንና በክርስቶስ ለታመኑ ወንድሞች፤ ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ሰላም ይሁን። (ቆላ 1:1-2)
የውይይት ጥያቄዎች፦
➊ "በእግዚአብሔር ፈቃድ የክርስቶስ ኢየሱስ ሐዋሪያ" በሚለው ሐረግ ጸሐፊው ሊነግረን የፈለገው ሃሳብ ምንድነው? ስለ ጳውሎስ ሐዋሪያነት እግዚአብሔርና ክርስቶስ በአንድነት የቀረቡት በምን sense ነው? ለምሳሌ፦ እግዚአብሔር ፈቃጅ፣ ክርስቶስ ላኪ? ወይስ ጳውሎስ የክርስቶስ ሐሪያ በመሆኑ የእግዚአብሔር ሐዋሪያ አይደለምን?
➋ "...ጳውሎስ ጢሞቴዎስም ወንድሙ" የሚለው አገላለጽ ሐዋሪያነቱ ጢሞቴዎስንም ይጨምራል ማለት ነው? ወይስ በዚህ ክፍል ጢሞቴዎስ የቀረበው ለምንድነው? በመልዕክቱ ታሪካዊ ዐውድ የዚህ ሰው መጠቀስ ያለው ፋይዳ ምንድነው? በሌሎች የጳውሎስ መልእክቶች የጳውሎስ የእምነት ልጁ እንደሆነ የምናውቀው ጥሞቴዎስ በዚህ ክፍል "ወንድም" ሆኖ የቀረበው በምን አግባብ ነው? ወይስ ይኸኛው ሌላኛው ጢሞቴዎስ ነው?
➌ "ቅዱሳንና በክርስቶስ ለታመኑ" የሚለው ሐረግ ስለ መልእክቱ ተቀባዮች የሚነግረን ምንድነው? "ቅዱሳን" የተባሉትና "በክርስቶስ ለታመኑት" የሚሉ ገላጭ ሃሳቦች የሚናገሩት ስለ አንድ ማኅበር ነው ወይስ ስለ ሁለት የተለያዩ ቡድኖች? "በክርስቶስ ለታመኑ" የተባሉት "ቅዱሳን" የተባሉት ራሳቸው ናቸው? ሁለቱም ገላጮች በመልእክቱ ዐውድ ትርጉማቸው ምንድነው?
➍ በቁ2 የምናነበው "ጸጋና ሰላም" እነዚህ ሁለቱ ቃሎች በራሳቸው ምንን የሚወክሉ ናቸው? በጳውሎሳዊ መልእክቶች (Pauline Epistles) ያላቸው ስፍራ (placement) ምንድነው? አንዱ ሌላኛውን ተከትሎ የሚመጣ ነው ወይስ ሁለቱም አንድ ላይ የሚከሰቱ? ስለ ሐዋሪያነቱ "እግዚአብሔርንና ክርስቶስን" በጠቀሰበት መልኩ ስለ ጸጋና ሰላምም ሀለቱንም እንደ ምንጭ አድርጎ የሚያቀርበው ለምንድነው?
➎ ከእለቱ ጥናታችን ለየእለት ሕይወት ምልልሳችን እግዚአብሔር ምን እያለን ነው? ምን እንተው? ምን እናንሳ? እንደ ግለሰብም ሆነ እንደ ክርስቲያን ማኅበር (ቤተ ክርስቲያን) ምን እናድርግ?
------------
ዛሬ በአያት ሴንተር
⏰11:30-1:30
📍Ayat Shopping Mall.
☎️ 0947424046
------------
Join Us!
@metsihafuyinager
@metsihafuyinager
------------
በውስጥ፦ @adfontess
"ደስ ደስ ይለኛል
እግዚአብሔርን ስጠራ፣
ደስ ደስ ይለኛል፣
ስለ ኢየሱስ ሳወራ፣
በምስጋና ኾኜ ከልቤ፣
ፍቅሩን ምህረቱን አስቤ።"
-------
Join Us!
@metsihafuyinager
@metsihafuyinager
-------
በውስጥ፦ @adfontess
ሰማዩ ዝም ያለ ሲመስለንና ነገረ ዓለሙ ግራ ገብቶን ስንዋትት እግዚአብሔር የነፍሳችን ማረፊያ ነው። እርሱ ልባችንን በሕያውነቱ የሚያሞቅ የደህንነታችን ምንጭ ነው። የሞት ሸለቆ በሚመስል ዝቅታ እያለፍን ያለን ሲመስለን እርሱ የዘላለሙ ከፍታችን ነው። ስለ ነገያችን አስበን እርግጠኝነት ሲጎድለን ዓለማትን በመግቦቱ የያዘው እርሱ መድን ዋስትናችን ነው።
-------
Join Us!
@metsihafuyinager
@metsihafuyinager
-------
በውስጥ፦ @adfontess
የተወደዳችሁ በቲክቶክ (መጽሐፉ ይናገር ገጽ) የሚኖረን የይሁዳ መልእክት ጥናት እንደተጠበቀ ነው። ዛሬ ምሽት ከቁ 17 ጀምሮ ያለውን ሃሳብ የምናይ ይሆናል። ልክ ከምሽቱ 3:00 እዚያ እንገናኛለን።
"ኃይል ያስፈልገናል!"
"የማወራችሁ ስለ ኃይል ነው! ኃይል ያስፈልገናል! ኃይል ስላችሁ የማወራው መሬት ላይ ጥሎ እንደ ትል ስለሚያንፈራፍረው ኃይል አይደለም፤ የማወራው መርሴዲስ ቤንዝ (Mercedes benz) ለመንዳት አዋጅ እንድናውጅ ስለሚያደርገን ኃይል አይደለም፤ የማወራው ያልተፈወሰውን ተፈወሰ ስለሚያስብለው የውሸት ኃይል አይደለም። የማወራው የክርስትናን ሕይወት በሚገባ እንድትኖሩ ስለሚያስችለው ኃይል፤ እውነተኛ በሆነ ፍቅር ስለሚያራምድ ኃይል፤ ስለ ጸሎት ኃይል፤ ወንጌል-መስካሪ ስለሚያደርግ ኃይል ነው። ይህ ኃይል ነው የሚያስፈልገን።"
መጋቢ ፖል ዎሸር
(Paul Washer)
-------
Join Us! 🔥
@metsihafuyinager
@metsihafuyinager
የወስጥ መስመር፦ @adfontess
"የቤተ ክርሰቲያን መታደስን ስናስብ ኤሊቶችን (የዘርፉ ምሁራንን) ሰብስበን የምንሠራው ሥራ እንደሆነ ማሰብ የለብንም። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ራሱ መንግሥቱን ለመመስረት እንደርሱ አላደረገምና። እርሱ (ክርስቶስ) አሳ አጥማጆችን፣ ቀራጮችንና በሰውኛ በታችኛው የማኅበረሰብ ክፍል ያሉትን ሰብስቦ አስተምሯቸው በማብቃት የመንግሥቱ ወኪሎች ካደረገ እኛም መከተል ያለብን የእርሱን ሞዴል ነው።
ይህ እውቁ መምህር John Stot የጻፈውን ሳነብ ሰሞኑን በጣም የተሞገትኩበት ሃሳብ ነው። አገልግሎታችን መጽሐፉ ይናገርም በዚህ ወቅት በgrassroot level (መሬት በወረደ አካኼድ) በሰዎች ላይ የሚሠራውን ሥራ መቀጠል አለበት። እመኑኝ እግዚአብሔር ልትልልቅ የተሐድሶ ፕሮጀክቶቹ የሚጠቀመው ተራ የተባሉ ሰዎችን ነው። እንበርታ። የጀመርነውን እንቀጥል!"
(ወንድማችን አሳየኸኝ ለገሠ ከሰሞኑ አሰላስሎቱ በጠዋቱ ያካፈለን ሞጋች እውነት!)
---------
አብራችሁን ሥሩ! ለሌሎችም አጋሩ።
@metsihafuyinager
የእናንተንም Daily Reflections ላኩልን።
የውስጥ መስመር፦ @adfontess
