የቀጠናው ተመልካች
رفتن به کانال در Telegram
በአለማችን ቀጠናዎች የሚከሰቱ ክስተቶችን ይዘግባል፣ ሳይቀዘቅዝ በትኩሱ። ለጥያቄና ለአስተያየቶች በኢሜል asuleyma246@Gmail.com ብላችሁ ፃፉልኝ።
نمایش بیشترکشور مشخص نشده استدسته بندی مشخص نشده است
4 308
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-227 روز
-8530 روز
آرشیو پست ها
4 307
🇮🇷⚡️🇺🇸 ኢራን እስራኤልን እንዳታጠቃ፣ አሜሪካ $12 ቢሊዮን ዶላር በምላሹ ልትሰጣት ፈልጋ እንደነበር፣ ነገር ግን ኢራን "ሞራሌን እና ወዳጆቼን በገንዘብ አልለውጥም" በማለት ውድቅ እንዳደረገች፣ የእስራኤሉ ቻናል 12 ዘግቧል።
በዘገባው፣ ገንዘቡ ለኢራን ቀርቦ የነበር ሲሆን፣ ወዲያው ኢራን አልፈልግም ማለቷ ተገልጿል።
4 307
🇺🇸🇮🇱🇱🇧🇮🇷 ⚡️ — ፕሬዚዳንት ትራምፕ ለAxios:
ቢቢ ለምን አባቱ ኢራንን እንዳጠቃ አላውቅለትም። በጣም ነው የተናደድኩት። አሳውቄዋለሁ። የእሱ (የብልግና ቃል) ማገናዘቢያው ተዘግቷል።ከጥቂት ሰዓታት በኋላ ይፈረማል የሚል ትልቅ ተስፋ አለኝ። ኢራን ሚሳዬል በአፀፋ እስራኤል ላይ እንዳትተኩስ እየተማፀንኳት ነው። አያስፈልገንም።
4 307
🇺🇸🇮🇷🇮🇱 ፕሬዚዳንት ትራምፕ፣ ዛሬ እስራኤል በሊባኖስ ላይ በሰነዘረችው ጥቃት እንዳዘነ እና መፈፀም የሌለበት እንደነበር ተናገረ። በዚህ ሁላችንም ስንጠብቀው በነበረው ትልቅ ቀን፣ የለፋንበት ሁሉ ጫፍ በደረሰበት፣ የእስራኤል ጥቃት መሆን ያልነበረበት ነው፣ ብሏል። አክሎም፣ ሁሉም አካላት በያሉበት እንዲረጋጉ እና ለቀጠናው ዘላቂ ሰላም ሊያመጣ ያለው ስምምነት እንዲፈረም አሳስቧል።
4 307
🇺🇸 ፕሬዝዳንት ትራምፕ፣ መልካም የ80 ዓመት የልደት በዓል ይሁንልዎ እላለሁ።
'መልካም ልደት' የሚለውን ሙዚቃ ስጋብዝዎ በደስታ ነው። ማርኮ ሩቢዮ ከዩትዩብ ላይ ሊያወርድልዎ ይችላል። ሊንኩን ልኬለታለሁ።
4 307
🇮🇷 የኢራን ደህንነት መስሪያ ቤት፣ 'የአሜሪካ እና የፅዮናዊያንን ዓላማ' ለማሳካት እና ሀገር ለማወክ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ 126 የወሃቢ/ተክፊሪ አመራሮችን በክትትል መያዙን እና ህቡዕ አደረጃጀታቸውን ማፍረሱን ተናገረ።
4 307
🇮🇱⚡️🇮🇷 እስራኤል ጦሯ በተጠንቀቅ እንዲሆን አሳስባለች። ከኢራን ባለስቲክ ሚሳዬሎች ይተኮሳሉ ብላም እየጠበቀች ነው። ዮርዳኖስ በበኩሏ፣ ለእስራኤል በማገዝ የኢራንን ሚሳዬል እስራኤል ከመድረሱ በፊት በአየሯ ለመታት ጦሯ እንዲዘጋጅ ትእዛዝ አውርዳለች።
4 307
🇮🇱🇮🇷⚡️የእስራኤል HAARETZ ጋዜጣ፡
"እስራኤል በስሌቷ ተሳስታለች፣ ማድረግ የነበረባትን ነው ያደረገችው። አፀፋውን ከኢራን ትጠብቅ።
4 307
🇷🇺⚡️🇺🇦 — እጅግ ግዙፍ የተባለ የዩክሬን የድሮን ጥቃት፣ ሪብኒስክ ሩሲያ ውስጥ በሚገኝ የነዳጅ ማጣሪያ፣ የማዳበሪያ ፋብሪካ እና የኬሚካል ኢንዱስትሪ ላይ፣ ዛሬ ንጋት መፈፀሙ ታውቋል። የፍንዳታው ጭስ መላውን ከተማና አካባቢውን ሸፍኖታል።
*-*-*
ሩሲያ ዓይናችን እያየ እየተበለተች ነው፣ አላወቀችውም እንጂ። ፑቲን፣ ሀገሩ እና ጦሩ፣ ያለውን እምቅ አቅም ተጠቅሞ ጨዋታውን በአንድ ጊዜ የሚቀይር እርምጃ እንዳይወስድ፣ እጅና እግሩን አሳስሮታል። ሩሪያንም እያስበላ ነው። ምን አስቦ ነው ግን? ይህ የኔ ምልከታ አይደለም፣ የብዙ የሩሲያዊያን ምልከታ ነው። ሰውዬው ፈርቷል!
4 307
🤝 — የሱማሌላን ፕሬዝዳንት አብዱራሕማን ሙሐመድ አብዱላሂ በኢየሩሳሌም፡
ዛሬ፣ ከሃርጌሳ እና ከሌሎችም ሥፍራዎች፣ የ6 ሚሊዮን ሙስሊሞችን ምስጋናና ክብር ለእስራኤል ለማቅረብ፣ በዚህ ተገኝቻለሁ።
4 307
🤝 — የእስራኤል ፕሬዝዳንት ሄርዞግ: ሻሎም፣ እንኳን ወደ እስራኤል በደህና መጣህ.
ሱማሌላንድ ፕሬዝዳንት አብዱራሕማን፡ ሻሎም፡ እስራኤላዊያን ለዘላለም ይኑሩ።
4 307
— 🤝የእስራኤል ፕሬዚዳንት፣ ይስሃቅ ሄርዞግ፣ የሱማሌላንድ ፕሬዝዳንት የሆኑትን፣ አብዱራሕማን ሙሐመድ አብዱላሂን፣ ዛሬ በኢየሩሳሌም በሚገኘው ቢሯቸው ተቀብለዋቸዋል።
4 307
🇺🇸🇮🇷⚡️ከፍተኛ የአሜሪካ ተደራዳሪ እና የዋይት ሃውስ ባለ ስልጣን ለ FOX NEWS:
የዛሬው የእስራኤል ጥቃት፣ ያለመታደል ሆን፣ ከኢራን ጋር ልንደርስበት ያልነው ስምምነት እንዳወሳሰበው አልጠራጠርም።
4 307
+3
🇮🇷⚡️🇺🇸🇮🇱 ሰበር ዜና፡ እስራኤል ደቡብ ቤሩትን መደብደቧ ተሰማ። የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፣ 'አሜሪካ ያበደ ውሻዋን (እስራኤልን) ለመቆጣጠር አቅም የላትም ወይም አትፈልግም' ሲል ተናግሯል። አክሎም 'ለዛሬ ቀጠሮ ተይዞለት የነበረው የፊርማ ሥነ ስርዓት ላይ ኢራን አትገኝም' ሲል ተናግሯል።
የኢራን ወታደራዊ ኮማንድ ፖስት፣ ኻቲመል አንብያ' በበኩሉ፣ የአካባቢውን የኃይል ባላንስ በማመጣጠን ላይ ተመርኩዞ፣ ጦሩ፣ ለዛሬው የእስራኤል ጥቃት አጸፋዊ ምላሽ እንደሚሰጥ ተናግሯል።
እስራኤል በበኩሏ፣ የዛሬውን ጥቃት ከመሰንዘሯ በፊት፣ ከአሜሪካ CENTCOM 'አረንጓዴ መብራት' እንዳገኘች ገልፃ፣ ካለ አሜሪካ ፈቃድ ያደረገችው እንደሌለ ተናግራለች።
*-*-*-
ይሄ፣ ትናንትም ሰሞኑንም ስንለው የነበረው ነው። እስራኤል በቀጠናው ከኢራን ጋር ሰላም አትፈልግም። አሜሪካንም ጨምሮ፣ ማንም ሀገር ከኢራን ጋር ሰላም እንዲያወርድ አትፈልግም። በቃ፣ ይሄ ልትለውጠው የማትችለው ተፈጥሮዋ ነው፣ ሳቦታጅ ማድረግ።
4 307
🇮🇷🇺🇸🇮🇱🇵🇰 እስራኤሎች፣ በስምምነቱ ከጨዋታ ውጭ ተደርገን ተበላን እያሉ ናቸው። ኢራኖችም፣ አደራዳሪዎቻችን ካልተሰቀሉልን አስበልተውናል እያሉ ናቸው። አሜሪካዎችም፣ ይህችን ታላቅ ሀገራችንን፣ ትራምፕ ተሸንፎ በድርድር አስበላን፣ እያሉ ናቸው።
እቺ ፓኪስታን የምትባል ሀገር ግን እኔ ገርማኛለች በበኩሌ። ስምምነቱን በእሽክርክር ቁልፍልፍ አድርጋ ነው በዙሪያ ጥምጥም የተበተበችባቸው። አይ ፓኪስታን አለ የሕንዱ ጠቅላይ ሚንስትር።
4 307
— የሱማሌላንድ ፕሬዝዳንት፣ አብዱራሕማን ሙሐመድ አብዱላሂ፣ ወደ እስራኤል ተጉዘው፣ የእስራኤል አቻቸውን ፕሬዝዳንት ይስሃቅ ሄርዞግን፣ ነገ፣ እሁድ፣ በኢየሩሳሌም በሚገኘው የፕሬዝዳንቱ ጽሕፈት ቤት እንደሚገናኙ ተገለፀ።
ፕሬዝዳንቱ በጉብኝታቸው፣ ከሌሎችም የእስራኤል ባለስልጣናት ጋር እንደሚገናኙ እና በርካታ ስምምነቶችንም እንደሚፈራረሙ ይጠበቃል ተብሏል።
*-*-*-
በፊት ድሮ፣ ኢትዮጵያ፣ የምሥራቅ አፍሪካ ስትራቴጂካል ሀገር ትባል ነበር፣ የባሕር በር ባለቤት በነበረች ጊዜ። ዛሬ አይደለችም።
ዛሬ፣ ኢትዮጵያ ምናልባት ከምሥራቅ አፍሪካ ቀጠና ውስጥ፣ ከሱማሊያ፣ ከሱማሌላንድ፣ ከጅቡቲ፣ ከሱዳን፣ ከኬንያ እና ከዑጋንዳ በታች፣ ተጽእኖ ፈጣሪነት ደረጃ ይኖራት ይሆናል።
እንደ ሀገር በዚህ ደረጃ የተፈጠፈጥነው፣ ዛሬ በስልጣን ያለው የኢትዮጵያ መንግሥት ወላጅ አባት የሆነው ሕወሓት፣ አንገታችንን (ኤርትራን) ቆርጦ ባሕራችንን በመሸጡ ነው።
ዛሬ በስልጣን ያለው መንግሥት ባሕራችንን ለማስመለስ ፍላጎት ያለው የሚመስላቸው የዋሆች ይኖራሉ። በፍፁም ስህተት ነው!
ለፖለቲካ ፍጆታ እና ለአጀንዳ ፈጠራ ባሕር አስመልሳለሁ ይላል፣ ይሄ ግን ከአንገት በላይ ለበጣ ነው። ቅንነት እና ውነተኝነት የጎደለው ነው። ያ ቢሆን፣ በቅድሚያ በሀገሩ ውስጥ ግድያዎችን አስቁሞ ሰላም በማውረድ እና ሀገሩን አንድ በማድረግ ፕሮሰሱን ይጀምር ነበር፣ እንዲያ ቢሆን የሕዝብ ድምፅ ሰምቶ ከብዙ ጥፋቱ ይታረም ነበር።
ስለዚህ ዛሬ፣ ኢትዮጵያ፣ በዓለም ታይቶ በማይታወቅ ድህነት ውስጥ የምትማቅቅ፣ ፖለቲካዋ እና ኢኮኖሚዋ የላሸቀ፣ መሪዎቿ በጦር ወንጀሎች እና በሕዝብ ፍጅቶች የሚፈለጉ፣ ያጣች እና የገረጣች፣ ስትራቴጂካል ደረጃዋን የተቀማች፣ የሚያበድራት ያጣች እና ፍርፋሪ ለቃቃሚ የሆነች ሀገር ሆናለች።
4 307
— የሱማሌላንድ ፕሬዝዳንት፣ አብዱራሕማን ሙሐመድ አብዱላሂ፣ ወደ እስራኤል ተጉዘው፣ የእስራኤል አቻቸውን ፕሬዝዳንት ይስሃቅ ሄርዞግን፣ ነገ፣ እሁድ፣ በኢየሩሳሌም በሚገኘው የፕሬዝዳንቱ ጽሕፈት ቤት እንደሚገናኙ ተገለፀ።
ፕሬዝዳንቱ በጉብኝታቸው፣ ከሌሎችም የእስራኤል ባለስልጣናት ጋር እንደሚገናኙ እና በርካታ ስምምነቶችንም እንደሚፈራረሙ ይጠበቃል ተብሏል።
*-*-*-
በፊት ድሮ፣ ኢትዮጵያ፣ የምሥራቅ አፍሪካ ስትራቴጂካል ሀገር ትባል ነበር፣ የባሕር በር ባለቤት በነበረች ጊዜ። ዛሬ አይደለችም።
ዛሬ፣ ኢትዮጵያ ምናልባት ከምሥራቅ አፍሪካ ቀጠና ውስጥ፣ ከሱማሊያ፣ ከሱማሌላንድ፣ ከጅቡቲ፣ ከሱዳን፣ ከኬንያ እና ከዑጋንዳ በታች፣ ተጽእኖ ፈጣሪነት ደረጃ ይኖራት ይሆናል።
እንደ ሀገር በዚህ ደረጃ የተፈጠፈጥነው፣ ዛሬ በስልጣን ያለው የኢትዮጵያ መንግሥት ወላጅ አባት የሆነው ሕወሓት፣ አንገታችንን (ኤርትራን) ቆርጦ ባሕራችንን በመሸጡ ነው።
ዛሬ በስልጣን ያለው መንግሥት ባሕራችንን ለማስመለስ ፍላጎት ያለው የሚመስላቸው የዋሆች ይኖራሉ። በፍፁም ስህተት ነው!
ለፖለቲካ ፍጆታ እና ለአጀንዳ ፈጠራ ባሕር አስመልሳለሁ ይላል፣ ይሄ ግን ከአንገት በላይ ለበጣ ነው። ቅንነት እና ውነተኝነት የጎደለው ነው። ያ ቢሆን፣ በቅድሚያ በሀገሩ ውስጥ ግድያዎችን አስቁሞ ሰላም በማውረድ እና ሀገሩን አንድ በማድረግ ፕሮሰሱን ይጀምር ነበር፣ እንዲያ ቢሆን የሕዝብ ድምፅ ሰምቶ ከብዙ ጥፋቱ ይታረም ነበር።
ስለዚህ ዛሬ፣ ኢትዮጵያ፣ በዓለም ታይቶ በማይታወቅ ድህነት ውስጥ የምትማቅቅ፣ ፖለቲካዋ እና ኢኮኖሚዋ የላሸቀ፣ መሪዎቿ በጦር ወንጀሎች እና በሕዝብ ፍጅቶች የሚፈለጉ፣ ያጣች እና የገረጣች፣ ስትራቴጂካል ደረጃዋን የተቀማች፣ የሚያበድራት ያጣች እና ፍርፋሪ ለቃቃሚ የሆነች ሀገር ሆናለች።
4 307
🤝 — የሱማሌላንድ ፕሬዝዳንት፣ አብዱራሕማን ሙሐመድ አብዱላሂ፣ ወደ እስራኤል ተጉዘው፣ የእስራኤል አቻቸውን ፕሬዝዳንት ይስሃቅ ሄርዞግን፣ ነገ፣ እሁድ፣ በኢየሩሳሌም በሚገኘው የፕሬዝዳንቱ ጽሕፈት ቤት እንደሚገናኙ ተገለፀ።
ፕሬዝዳንቱ በጉብኝታቸው፣ ከሌሎችም የእስራኤል ባለስልጣናት ጋር እንደሚገናኙ እና በርካታ ስምምነቶችንም እንደሚፈራረሙ ይጠበቃል ተብሏል።
*-*-*-
በፊት ድሮ፣ ኢትዮጵያ፣ የምሥራቅ አፍሪካ ስትራቴጂካል ሀገር ትባል ነበር፣ የባሕር በር ባለቤት በነበረች ጊዜ። ዛሬ አይደለችም።
ዛሬ፣ ኢትዮጵያ ምናልባት ከምሥራቅ አፍሪካ ቀጠና ውስጥ፣ ከሱማሊያ፣ ከሱማሌላንድ፣ ከጅቡቲ፣ ከሱዳን፣ ከኬንያ እና ከዑጋንዳ በታች፣ ተጽእኖ ፈጣሪነት ይኖራት ይሆናል።
እንደ ሀገር በዚህ ደረጃ የተፈጠፈጥነው፣ ዛሬ በስልጣን ያለው የኢትዮጵያ መንግሥት ወላጅ አባት የሆነው ሕወሓት፣ አንገታችንን (ኤርትራን) ቆርጦ ባሕራችንን በመሸጡ ነው።
ዛሬ በስልጣን ያለው መንግሥት ባሕራችንን ለማስመለስ ፍላጎት ያለው የሚመስላቸው የዋሆች ይኖራሉ። አይደለም! ለፖለቲካ ፍጆታ እና ለአጀንዳ ፈጠራ አስመልሳለሁ ይላል፣ ይሄ ግን ከአንገት በላይ ለበጣ ነው፣ እንጂ በቅንነት ወይም በውነተኛ መነሳሳት ለማድረግ በማሰብ አይደለም። ያ ቢሆን፣ በቅድሚያ በሀገሩ ውስጥ ግድያዎችን አስቁሞ ሰላም በማውረድ እና ሀገሩን አንድ በማድረግ ፕሮሰሱን ይጀምር ነበር፣ እንዲያ ቢሆን የሕዝብ ድምፅ ሰምቶ ከብዙ ጥፋቱ ይታረም ነበር።
ስለዚህ ዛሬ፣ ኢትዮጵያ፣ በዓለም ታይቶ በማይታወቅ ድህነት ውስጥ የምትማቅቅ፣ ፖለቲካዋ እና ኢኮኖሚዋ የላሸቀ፣ መሪዎቿ በጦር ወንጀሎች እና በሕዝብ ፍጅቶች የሚፈለጉ፣ ያጣች እና የገረጣች፣ ስትራቴጂካል ደረጃዋን የተቀማች፣ የሚያበድራት ያጣች እና ፍርፋሪ ለቃቃሚ የሆነች ሀገር ሆናለች።
4 307
🇮🇱⚡️🇮🇷🇺🇸 ቴል አቪቭ አሁን ባለው ሁኔታ የአሜሪካ-ኢራን ስምምነት ምንም እንኳን ቢፈረምም፣ ረጅም ጊዜ እንደማይቆይ ታምናለች።
አንድ ከፍተኛ የእስራኤል ባለስልጣን ለእስራኤል ህትመት Ynet እንዲህ ብሏል፡
"ይህ መጥፎ ስምምነት ነው። በእሱ ማንም አይረካም። ይህ ለእኛ ጥሩ እንዳልሆነ እና የእስራኤልን ጥቅም እንደሚጎዳ እንገነዘባለን። የሚያሳስበው ነገር፣ እስራኤል ተጽዕኖ ማሳደር አለመቻሏ እና ድምጿ አለመሰማቱ ነው።
ይህ በመሠረቱ 'የዓለም ዋንጫ ስምምነት ቢባል ይቀላል። የትራምፕን 80ኛ የልደት በዓል፣ እንዲሁም የአሜሪካን 250ኛ የምሥረታ በዓል፣ ኮሽ ሳይል ለማክበር፣ በዩኤስ ውስጥ ለሚከሰቱት ዋና ዋና ክስተቶች ሁሉ የተወሰነ ሰላም ለመግዛት፣ የሚደረግ ስምምነት ነው።
ይህ የጊዜ ፈተናን የሚቋቋም ስምምነት አይደለም" ሲል ለYnet ተናግሯል።
*-*-*-
እስራኤል ስምምነቱ ቢፈረምም ለማፍረስ ርቀትን ትሄዳለች፣ አልጠራጠም። ባሁኑ ሰዓት የኢራን ስስ ብልት ሊባኖስ ናት፣ ሊባኖስ በስምምነቱ ውስጥ ትካተታለች። ሊባኖስን በአንድም በሌላም መደብደቧን ትቀጥልና ኢራንን አስቆጥታ፣ 'ወጥቻለሁ' ልታስብላት ትችላለች። covert ኦፕሬሽኖችም ይኖሯታል።
ቴል አቪቭ፣ ቴህራን በዚህ መልኩ በመተዋ ልትደሰት አትችልም።
