የቀጠናው ተመልካች
رفتن به کانال در Telegram
በአለማችን ቀጠናዎች የሚከሰቱ ክስተቶችን ይዘግባል፣ ሳይቀዘቅዝ በትኩሱ። ለጥያቄና ለአስተያየቶች በኢሜል asuleyma246@Gmail.com ብላችሁ ፃፉልኝ።
نمایش بیشترکشور مشخص نشده استدسته بندی مشخص نشده است
4 307
مشترکین
-324 ساعت
-237 روز
-8630 روز
آرشیو پست ها
4 307
🇺🇸🇪🇹⚡️ — የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፣ በኢትዮጵያ የሰላም ጥረቶችን ያበላሻሉ ባላቸው የሕወሓት አመራሮች እና የቅርብ ቤተሰቦቻቸው ላይ የቪዛ ገደቦችን ጥሏል።
➡️ እርምጃዎቹ፣ በትግራይ ለተፈጠረው ቀውስ መፍትሄዎችን በማደናቀፍ ተጠያቂ ወይም ተባባሪ ናቸው ተብለው የሚታሰቡ ግለሰቦች ላይ ያነጣጠሩ ናቸው።
➡️ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ በሕወሓት ቡድን እና በኢትዮጵያ መንግስት መካከል ያለው ውጥረት በሰሜናዊ ኢትዮጵያ ግጭትን እንደገና ሊያነሳሳ እና የቀጠናውን ደህንነትን አደጋ ላይ ሊጥል እንደሚችል አስጠንቅቋል።
➡️ ኢትዮጵያ፣ ከጦርነት እና ግጭቶች መውጣት አልቻለችም፣ በመሆኑም ከዚህም በላይ ቀውሱ እንዳይባባስ በማለት፣ በሕወሓት አመራሮች ላይ የቪዛ እገዳ እርምጃ ለመውሰድ ተገዷል።
4 307
🇮🇱⚡️🇱🇧 አሜሪካ እስራኤልን አስጠነቀቀች፣ አርፈሽ ካልተቀመጥሽ በጥፊ ነው የምልሽ ብላታለች።
እስራኤል ምሽቱን በርካታ ድብደባዎችን በደቡብ ሊባኖስ አካሂዳለች። ድብደባው አሁንም እንደቀጠለ ነው። በዚህም፣ የኢራንን እና የአሜሪካንን ትዕግስት እየተፈታተነች እንደሆነ ተገልጿል።
እስራኤል፣ በሁለቱ ሀገሮች መካከል የተደረሰውን ስምምነት ለማደናቀፍ በብዙ እየሰራች ሲሆን፣ The Washington Post ምክትል ፕሬዝዳንት JD VANCEን ጠቅሶ አሁን እንደዘገበው፣ በእስራኤል ላይ የአሜሪካ ትዕግስት እየተሟጠጠ እንደሆነና ስምምነቱን በተመለከተ ከእስራኤል የሚሰነዘረው አላግባብ ትችት መቆም እንዳለበት አስጠንቅቋል፣ ብሏል።
JD VANCE በንግግሩ፣ "
እኔ እስራኤል ካቢኔ ውስጥ ብሆን፣ አንድ ያለችኝን አጋሬን አሜሪካን፣ ከመኮነን እቆጠብ ነበር። እስራኤሎች ስምምነቱን እና ፕሬዝዳንታችንን በመተቸት ጣልቃ ባይገቡብን የተሻለ ይሆናል"ብሏል።
4 307
🇮🇱⚡️🇱🇧 አሜሪካ እስራኤልን አስጠነቀቀች፣ አርፈሽ ካልተቀመጥሽ በጥፊ ነው የምልሽ ብላታለች።
እስራኤል ምሽቱን በርካታ ድብደባዎችን በደቡብ ሊባኖስ አካሂዳለች። ድብደባው አሁንም እንደቀጠሉ ነው። በዚህም፣ የኢራንን እና የአሜሪካንን ትዕግስት እየተፈታተነች እንደሆነ ተገልጿል። እስራኤል፣ በሁለቱ ሀገሮች መካከል የተደረሰውን ስምምነት ለማደናቀፍ በብዙ እየሰራች ሲሆን፣ The Washington Post ምክትል ፕሬዝዳንት JD VANCEን ጠቅሶ አሁን እንደዘገበው፣ በእስራኤል ላይ የአሜሪካ ትዕግስት እየተሟጠጠ እንደሆነና ስምምነቱን በተመለከተ ከእስራኤል የሚሰነዘረው አላግባብ ትችት መቆም እንዳለበት አስጠንቅቋል ብሏል።
JD VANCE በንግግሩ፣ "
እኔ እስራኤል ካቢኔ ውስጥ ብሆን፣ አንድ ያለችኝን አጋሬን አሜሪካን፣ ከመኮነን እቆጠብ ነበር። ስምምነቱን በመተቸት ጣልቃ ባይገቡብን የተሻለ ይሆናል"ብሏል።
4 307
🇺🇦🇷🇺 ሩሲያዎች ትራፊክ እያስቆሙ ሁላ ነበር ሞስኮ ውስጥ ዛሬ እንደ ቀላል የትከሻ ሚሳዬል ድሮኖች ላይ ሲተኩሱ የዋሉት።
በለው፣ ተኩሰው፣ ያውና፣ ተኩስ። እዛ ጋር ደግሞ የቆመው አጫፋሪ ቺቺኒያዊ ነው መሰል፣ ማሻላህ ይላል። አይ ፑቲን!
4 307
🇺🇦🇷🇺 ሩሲያዎች ትራፊክ እያስቆሙ ሁላ ነበር ሞስኮ ውስጥ ዛሬ እንደ ቀላል የትከሻ ሚሳዬል ድሮኖች ላይ ሲተኩሱ የዋሉት።
በለው፣ ተኩሰው፣ ያውና፣ ተኩስ
4 307
+5
🇺🇦🇷🇺 የሩሲያ ምንጮች፡ ትናንት ሌሊት ዩክሬን ወደ ሩሲያ ግዛት 1172 ድሮኖችን ልካለች፣ አብዛኞቹ ወደ ዋና ከተማዋ ሞስኮና አካባቢው።
ከእነዚህ ድሮኖች መካከል፣ የሩሲያ ኃይሎች 992 ድሮኖችን መትተው ጥለዋል (85% ስኬት)። የተቀሩት 180 ድሮኖች ግን፣ የአየር መከላከያ አጥሩን በጣጥሰው በመግባት ያደረሱትን ውድመት አድርሰዋል ብለዋል።
በG7 ስብሰባ ላይ፣ ምዕራባዊያ ተጨማሪ የመሳሪያ እርዳታ ያቀርቡ ዘንድ፣ ዘለንስኪ ማሳመን ነበረበት። ለፕሬዝዳንት ትራምፕ ጨምሮ፣ ለተሰብሳቢዎች በሙሉ፣ ዘለንስኪ፣ ዩክሬን ጦርነቱን እያሸነፈች እንደሆነና ከዚህ በኋላ የሚያስፈልገው ጥቂት ጊዜ መሆኑን ሰብኳል፣ ይላሉ እነዚሁ ምንጮች።
ከዚያ በተመለሰ በማግስቱ ነው፣ ለምዕራባዊያን "እያሸነፍን ነው" ያለውን መልዕክት ለማጉላት ሲል፣ ታይቶ የማይታወቅ ከፍተኛ ጥቃት በሞስኮ ላይ ያዘነበው።
ጥቃቱን የሩሲያ ኃይሎች በብዛት ያከሸፉት ቢሆንም፣ ጥሰው የገቡት ድሮኖች ያደረሱት ውድመት ግን የዓለምን የዜና አውታሮችን አየር ሊቆጣጠር ችሏል። ስለዚህ ዘለንስኪ የተሳካለት መስሏል፣ ብለዋል።
*-*-*
ሩሲያዎች፣ በሞስኮ እምብርት ላይ ዛሬ የደረሰባቸውን ውርደት ለማሳነስ እና ራሳቸውን ለማጥናናት እንዲህ ያሉ ብዙ መረጃዎችን እያወጡ ናቸው።
ሲጀመር በዚህ መጠንና ኃይል ዩክሬኖች ዋና ከተማውን መምታት መቻላቸው፣ ሩሲያ እየተዳከመች ለመምጣቷ ማሳያ ነው። 40 ፐርሰንቱን የሩሲያን የጋዝና የነዳጅ ኢንዱስትሪ በቦንብና በድሮን ማንኮታኮታቸውም፣ እንዲሁ፣ የሩሲያን መብረክረክ የሚያሳይ ነው።
ዩክሬኖች ከዋናው የጦር ግንባር አልፈው ነው፣ የመንግሥቱን መቀመጫ በሞስኮ እየመቱ ያሉት። ይህ ለዩክሬን ትልቅ ስኬት ነው።
ፑቲን፣ ካሁን በኋላ ቆፍጠን ብሎ ኃይል ለመጠቀም ካልደፈረ፣ ይገለብጡታል። የሩሲያ ታሪክ ቀልድ አያውቅም።
4 307
🇺🇦🇷🇺 የሩሲያ ምንጮች፡ ትናንት ሌሊት ዩክሬን ወደ ሩሲያ ግዛት 1172 ድሮኖችን ልካለች፣ አብዛኞቹ ወደ ዋና ከተማዋ ሞስኮና አካባቢው።
ከእነዚህ ድሮኖች መካከል፣ የሩሲያ ኃይሎች 992 ድሮኖችን መትተው ጥለዋል (85% ስኬት)። የተቀሩት 180 ድሮኖች ግን፣ የአየር መከላከያ አጥሩን በጣጥሰው በመግባት ያደረሱትን ውድመት አድርሰዋል ብለዋል።
በG7 ስብሰባ ላይ፣ ምዕራባዊያ ተጨማሪ የመሳሪያ እርዳታ ያቀርቡ ዘንድ፣ ዘለንስኪ ማሳመን ነበረበት። ለፕሬዝዳንት ትራምፕ ጨምሮ፣ ለተሰብሳቢዎች በሙሉ፣ ዘለንስኪ፣ ዩክሬን ጦርነቱን እያሸነፈች እንደሆነና ከዚህ በኋላ የሚያስፈልገው ጥቂት ጊዜ መሆኑን ሰብኳል፣ ይላሉ እነዚሁ ምንጮች።
ከዚያ በተመለሰ በማግስቱ ነው፣ ለምዕራባዊያን "እያሸነፍን ነው" ያለውን መልዕክት ለማጉላት ሲል፣ ታይቶ የማይታወቅ ከፍተኛ ጥቃት በሞስኮ ላይ ያዘነበው።
ጥቃቱን የሩሲያ ኃይሎች በብዛት ያከሸፉት ቢሆንም፣ ጥሰው የገቡት ድሮኖች ያደረሱት ውድመት ግን የዓለምን የዜና አውታሮችን አየር ሊቆጣጠር ችሏል። ስለዚህ ዘለንስኪ የተሳካለት መስሏል፣ ብለዋል።
*-*-*
ሩሲያዎች፣ በሞስኮ እምብርት ላይ ዛሬ የደረሰባቸውን ውርደት ለማሳነስ እና ራሳቸውን ለማጥናናት እንዲህ ያሉ ብዙ መረጃዎችን እያወጡ ናቸው።
ሲጀመር በዚህ መጠንና ኃይል ዩክሬኖች ዋና ከተማውን መምታት መቻላቸው፣ ሩሲያ እየተዳከመች ለመምጣቷ ማሳያ ነው። 40 ፐርሰንቱን የሩሲያን የጋዝና የነዳጅ ኢንዱስትሪ በቦንብና በድሮን ማንኮታኮታቸውም፣ እንዲሁ፣ የሩሲያን መብረክረክ የሚያሳይ ነው።
ዩክሬኖች ከዋናው የጦር ግንባር አልፈው ነው፣ የመንግሥቱን መቀመጫ በሞስኮ እየመቱ ያሉት። ይህ ለዩክሬን ትልቅ ስኬት ነው።
ፑቲን፣ ካሁን በኋላ ቆፍጠን ብሎ ኃይል ለመጠቀም ካልደፈረ፣ ይገለብጡታል። የሩሲያ ታሪክ ቀልድ አያውቅም።
4 307
🇪🇹 የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር፣ አቶ አብይ አሕመድ ዓሊ፣ እየተሰነዘረበት ላለው ዘለፋና ፌዝ፣ እርሱ ራሱ በብዕር ስም እንደፃፈው በሚታመን ሌላ ረጅም ጽሑፍ፣ ምላሽ መስጠቱን ቀጥሏል።
ጸሐፊው በጽሑፉ፣ የታወቁ ቲክቶከሮች የሆኑ ህፃናትና ወጣቶች፣ ከዑጋንዳ፣ ከዛንቢያ፣ ከቡርኪናፋሶ፣ ከአሜሪካ እና ከሌሎችም ሀገሮች እየመጡ፣ በተከልናቸው የከተማ መብራቶች እየተደመሙ ነው፣ ስለዚህ እኔም በዓለም ላይ ተጽእኖ እየፈጠርኩኝ ነው ብሏል።
4 307
🇺🇦❌🇷🇺 - አስደንጋጭ ምስል ከሞስኮ፡
ዛሬ ጠዋት በካፖትኒያ በሚገኘው የሞስኮ የነዳጅ ኢንዱስስትሪ ላይ የዩክሬን ድሮኖች ያደረሱትን ጥቃት ተከትሎ የነዳጅ ማጠራቀሚያ ጣሪያ ተገንጥሎ ወደ አየር ሲወጣ ታይቷል።
የዛሬው የዩክሬን ጥቃት፣ በክሬምሊን ላይ ከፍተኛ ድንጋጤ ፈጥሯል።
*-*-*-
ፑቲን ፈርቷል! ሀገሩን እና ጦሩን አሳስሮ ለእንግሊዝ እና ለዩክሬን አይሁድ ሃይሎች አሳልፎ እየሰጠ ይመስላል።
በጊዜ ከእንቅልፉ ይነቃል? ወይስ ጦሩ 'በቃህ!' ብሎ ያነቃዋል?
4 307
+1
🇪🇹 የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር፣ አቶ አብይ አሕመድ ዓሊ፣ በአሁኑ ሰዓት፣ በዓለም አቀፍ መድረኮች እና መገኘቶች ላይ Shadow Ban ተደርጎ በመገለሉ ምክኒያት፣ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የማህበረሰብ ክፍል እያላገጠበትና ዘለፋዎችን እየወረወረበት ይገኛል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ከሕዝቡ በማስተናገድ ላይ ላለው ዘለፋና ስድብ፣ ዛሬ፣ እራሱ በብዕር ስም እንደ ደረሳቸው በሚገመቱ ረጃጅም ጽሑፎች ምላሽ ሰጥቷል።
ከተለያዩ መሪዎች ጋር (የደቡብ ሱዳን፣ የጅቡቲ፣ የሱዳን፣ የግብፅ፣ የጊኒ ቢሳዎ፣ የሱማሊያ፣ የኡዝቤኪስታን እና እንደ ሕንድ፣ ቱርክ እና ሩሲያ ካሉ ታዋቂ ሀገር መሪዎች ጋር) ሲገናኝ የተነሳቸውን ፎቶዎችን ከአልበሙ እያወጣ ከጽሑፎቹ ጋር አያይዞ በመለጠፍ፣ 'እኔም ተጽእኖ ፈጣሪ' ሲል ተስተውሏል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ እና መንግሥቱ፣ በዓለም አቀፍ ተቋማት በብዙ የጦር ወንጀሎች፣ የሕዝብ ፍጅቶች፣ የእርስ በእርስ ጦርነቶች፣ ግድያዎች፣ እስራቶች እና እገታዎች የሚፈለጉ በመሆኑና በዚያ branded ስለሆኑ ከዓለም መድረክ እንደተገለሉ ይታወቃል።
4 307
🇺🇸🇮🇷 ፕሬዝዳንት ትሬምፕ ከኢራን ጋር የተደረሰውን ስምምነት የሚኮንኑትን ተችቷል።
ሞኞች፣ ምቀኞች እና ደደቦች ብቻ ናቸው የተደረሰውን ስምምነት፣ እየተንከባለለ በመውረድ ላይ ያለውን የነዳጅ ዋጋ እና ታሪካዊ ትርፍ የዛቀውን ገበያችንን የሚኮንኑትብሏል።
