LOGOS
رفتن به کانال در Telegram
🎯የቻናሉ ዓላማ:LOGOS የሚለው ቃል ከGreek የመጣ ሲሆን፦ትርጉሙም ቃል፣ ምክንያት፣ክርስቶስ (የእግዚአብሔር ቃል ዮሐ 1፥1) በዚህ ቃል እውቀታችንን አሳድገን በኑሮ እንድንተገብር ነው
نمایش بیشترکشور مشخص نشده استدسته بندی مشخص نشده است
247
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
+27 روز
+1330 روز
آرشیو پست ها
247
የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክነት (መለኮትነት) ክፍል_❺
የኢየሱስ መጠሪያ ስሞች
1.እግዚአብሔር (Theos) (ዮሐ 3:1-3)
➧ይህ ቃል ፍፁም መለኮት ለሆነ ለእግዚአብሔር የምንጠቀምበት ቃል ነው ።
“ቴዎስ” የሚለው ቃል በታች ባሉት ተጠቅሶ የሚናገኘው ለኢየሱስ ነው።
(ዮሐ 1:1, 20:28 , ሮሜ 9:5, ቲቶ 2:13, ዕብ 1:8 2ጴጥ 1:1)
➧የብሉይ ኪዳን ትንቢቶችም እርሱ አምላክ መሆኑን በግልጽ አሳይተዋል (ኢሳ 9:6, መዝ (110):1 (45):6, (102):2 )
2.ጌታ (kyrios)
➧በዕብራይስጡ ያህዌህ/ጄሆቫህ ለሚለው ለአምላክ ስም ምትክ ሆኖ ያገለግላል
➧ኪሪዮስ በግሪኩ ብሉይ ውስጥ ጌታ እግዚአብሔር ለሚለው ስያሜ #6814# ጊዜ ተጠቅሷል ።
ይኸው #ኪሪዮስ ጌታ ኢየሱስ የሚጠራበት “ጌታ” የሚለው ቃል ነው። ስለሆነም ማንኛውም ግሪካዊ አንባቢ “ጌታ” ኢየሱስ የሚለውን ቃል የሚረዳው የሁሉ ነገር ፈጣሪና ፣ የፍጥረቱ ሁሉ መጋቢ እና አስተዳደር አድርጎ ነው
(ሉቃ 2:11, ማቴ 3:3 ኢሳ 40:3, ማቴ 22:44, 1ቆሮ 8:6 ,12:3)
247
የኢየሱስ ክርስቶስ #አምላክነት (መለኮትነት)
#ክፍል_❹
አምላክ ብቻ ሊያደርጋቸው የሚችላቸውን ነገሮች በማድረግ:-
ለዚህ ጥሩ ምሳሌ የሚሆነን ኢየሱስ ኃጢዓትን ይቅር የማለት ችሎታ እንዳለው ማሳየቱ ነው (ማርቆስ 2፡1-12)፡፡ ከአምላክ በስተቀር ኃጢዓትን ይቅር ሊል የሚችል ማነው?
ለአብ የሚገባው ክብር ሁሉ ለእርሱም እንደሚገባ በመናገር:-
“ሰዎች ሁሉ አብን እንደሚያከብሩት ወልድን ያከብሩት ዘንድ፥ ፍርድን ሁሉ ለወልድ ሰጠው እንጂ አብ በአንድ ሰው ስንኳ አይፈርድም፡፡ ወልድን የማያከብር የላከውን አብን አያከብርም (ዮሐንስ 5፡22-23)፡፡” አብን የምናከብረው እርሱን በማምለክ ነው፡፡ ኢየሱስንም አብን እንደምናከብረው ማክበር የምንችለው ለአብ የምንሰጠውን ክብር ሁሉ ስንሰጠው ነው፡፡
ወደ እርሱ እንድንጸልይ እና እርሱም ደግሞ የምንለምነውን በሙሉ እንደሚያደርግልን በመናገር:-፡፡
“እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ በእኔ የሚያምን እኔ የማደርገውን ሥራ እርሱ ደግሞ ያደርጋል፤ ከዚህም የሚበልጥ ያደርጋል፥ እኔ ወደ አብ እሄዳለሁና፤ አብም ስለ ወልድ እንዲከበር በስሜ የምትለምኑትን ሁሉ አደርገዋለሁ፡፡ ማናቸውንም ነገር በስሜ ብትለምኑ እኔ አደርገዋለሁ (ዮሐንስ 14)፡፡” ኢየሱስ የሁሉን ሰው ጸሎት ለመስማት በሁሉም ስፍራ መገኘት እና ሁሉን ማወቅ መቻል አለበት፤የምንለምነውን ሁሉ ለማድረግ ደግሞ ሁሉን ቻይ መሆን አለበት፡፡ ከአንዱ አምላክ በስተቀር ፀሎታችንን ሰምቶ የምንለምነውን ሁሉ ማድረግ የሚችል ማነው? ኢየሱስ ግን ይህንን ማድረግ እንደሚችል ነግሮናል ስለዚህ አምላክ መሆኑን ተናግሯል፡፡
247
የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክነት(መለኮትነት)
#ክፍል_➌
መሲህ መሆኑን (ክርስቶስ መሆኑን) በመናገር፡-
ኢየሱስ በብሉይ ኪዳን ትንቢት የተነገረለት መሲህ መሆኑን በተደጋጋሚ ተናግሯል
(ማቴዎስ 16፡13-17፣ ዮሐንስ 4፡25-26፣ 26፡1-3 ማርቆስ 14:1-2፣ 12:35-37፣ 13፡26-27 ሉቃስ 24፡13-15፣ 24፡ 25-27፣ 24፡44-49 ይመልከቱ)፡፡
👉የብሉይ ኪዳን ትንቢቶች መሲሁ አምላክ መሆኑን ይናገራሉ:-
“ሕፃን ተወልዶልናልና፥ ወንድ ልጅም ተሰጥቶናልና አለቅነትም በጫንቃው ላይ ይሆናል ስሙም ድንቅ መካር፥ #ኃያል አምላክ፥ የዘለዓለም አባት፥ የሰላም አለቃ ተብሎ ይጠራል፡፡ ከዛሬ ጀምሮ እስከ ዘለዓለም ድረስ በፍርድና በጽድቅ ያጸናውና ይደግፈው ዘንድ በዳዊት ዙፋንና በመንግሥቱ ላይ አለቅነቱ ይበዛል፥ ለሰላሙም ፍፃሜ የለውም፡፡ የእግዚአብሔር ቅንዓት ይህን ያደርጋል፡፡” ትንቢተ ኢሳይያስ 9፡6-7
“#አምላክ ሆይ፥ ዙፋንህ ለዘለዓለም ነው የመንግሥትህ በትር የቅንነት በትር ነው፡፡ ጽድቅን ወደድህ ዓመፃንም ጠላህ ስለዚህ ከባልንጀሮችህ ይልቅ እግዚአብሔር አምላክህ የደስታ ዘይትን ቀባህ፡፡” መዝሙረ ዳዊት 45
ኢየሱስ በብሉይ ኪዳን ትንቢት የተነገረለት መሲህ መሆኑን ተናግሯል፡፡ በብሉይ ኪዳን ትንቢቶች መሠረት መሲሁ 👉አምላክ ነው፡፡ ስለዚህ ኢየሱስ #አምላክ መሆኑን ተናግሯል፡፡
ይቀጥላል ...
247
መሲህ መሆኑን (ክርስቶስ መሆኑን) በመናገር፡-
ኢየሱስ በብሉይ ኪዳን ትንቢት የተነገረለት መሲህ መሆኑን በተደጋጋሚ ተናግሯል
(ማቴዎስ 16፡13-17፣ ዮሐንስ 4፡25-26፣ 26፡1-3 ማርቆስ 14:1-2፣ 12:35-37፣ 13፡26-27 ሉቃስ 24፡13-15፣ 24፡ 25-27፣ 24፡44-49 ይመልከቱ)፡፡
የብሉይ ኪዳን ትንቢቶች መሲሁ አምላክ መሆኑን ይናገራሉ:-
“ሕፃን ተወልዶልናልና፥ ወንድ ልጅም ተሰጥቶናልና አለቅነትም በጫንቃው ላይ ይሆናል ስሙም ድንቅ መካር፥ #ኃያል አምላክ፥ የዘለዓለም አባት፥ የሰላም አለቃ ተብሎ ይጠራል፡፡ ከዛሬ ጀምሮ እስከ ዘለዓለም ድረስ በፍርድና በጽድቅ ያጸናውና ይደግፈው ዘንድ በዳዊት ዙፋንና በመንግሥቱ ላይ አለቅነቱ ይበዛል፥ ለሰላሙም ፍፃሜ የለውም፡፡ የእግዚአብሔር ቅንዓት ይህን ያደርጋል፡፡” ትንቢተ ኢሳይያስ 9፡6-7
“#አምላክ ሆይ፥ ዙፋንህ ለዘለዓለም ነው የመንግሥትህ በትር የቅንነት በትር ነው፡፡ ጽድቅን ወደድህ ዓመፃንም ጠላህ ስለዚህ ከባልንጀሮችህ ይልቅ እግዚአብሔር አምላክህ የደስታ ዘይትን ቀባህ፡፡” መዝሙረ ዳዊት 45
ኢየሱስ በብሉይ ኪዳን ትንቢት የተነገረለት መሲህ መሆኑን ተናግሯል፡፡ በብሉይ ኪዳን ትንቢቶች መሠረት መሲሁ አምላክ ነው፡፡ ስለዚህ ኢየሱስ አምላክ መሆኑን ተናግሯል፡፡
ይቀጥላል ...
247
#የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክነት #(መለኮትነት)_ክፍል_❷
ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ምድር የመጣው አምላክነቱንና ጌትነቱን ለማወጅ አልነበረም፡፡ የኢየሱስ ተልዕኮ ራሱን በማዋረድ ነፍሱን ለብዙዎች ቤዛ አድርጎ መስጠት እንጂ መለኮታዊ ክብሩን በማወጅ ሰዎች እንዲያውቁት ባለመሆኑ በየስፍራው እየዞረ አምላክነቱን ቢያውጅ ከተልዕኮው ጋር የሚጣጣም አይሆም፡፡
ጌታችን የራሱን ክብር ፍለጋ እንዳልመጣ በተደጋጋሚ ተናግሯል (ዮሐንስ 8:50፣ ማቴዎስ 20:28)፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም ይህንን ሐሳብ ልብን በሚነካ መንገድ ገልፆታል (ፊልጵስዩስ 2፡5-10)፡፡
ኢየሱስ በእርሱና በአብ መካከል ያለውን የአካል ልዩነት ግልፅ ሳያደርግ ‹አምላክ ነኝና አምልኩኝ› የሚሉትን ቃላት ቢናገር አይሁዶች ግራ ይጋቡ ነበር፡፡ አይሁዶች ስለ እግዚአብሔር ሦስቱ አካላት፣ ማለትም ስለ ሥላሴ ግንዛቤ ስላልነበራቸው ኢየሱስ ‹አምላክ ነኝና አምልኩኝ› የሚሉትን ቃላት ቢናገር ‹አብ ነኝ› የሚል ስለሚመስላቸው እንዲህ ብሎ መናገሩ ግርታን ከመፍጠርና በእርሱ ላይም ተቃውሞን ከማስነሳት የዘለለ ጠቀሜታ ሊኖረው አይችልም ነበር፡፡ ስለዚህ ሁልጊዜ አምላክነቱን የሚያሳዩ ስራዎችን እየሰራ እና በትምህርቶቹም ውስጥ ጥበብን በተሞላ መንገድ እየነገራቸው ሰዎች አምላክ መሆኑን ወደማወቅ ደረጃ እንዲመጡ መርቷቸዋል፡፡ ነገር ግን ይህንን ሲያደርግ ሁል ጊዜ ከአብ ጋር ያለውን የአካል ልዩነት ግልፅ በማድረግ ነበር፡፡
ኢየሱስ በምድር ላይ ይመላለስ በነበረበት ዘመን ከሌሎች ሰዎች የተለየ መልክ አልነበረውም፡፡ ዛሬ አንድ ሰው ወደ እኛ መጥቶ ‹አምላክ ነኝና አምልኩኝ› ቢለን እንደማንቀበለው ሁሉ ኢየሱስም በዘመኑ ይህንን ቢል ኖሮ ተቃውሞን ከማትረፍ ውጪ ምንም ጠቀሜታ አይኖረውም ነበር፡፡ ‹አምላክ ነኝና አምልኩኝ› ከሚለው መንገድ ይልቅ በተግባር አምላክ መሆኑን መግለጥ የተሻለ በመሆኑ ይህንኑ አድርጓል፡፡ ሰዎች ደግሞ ሥራውን በማየት አምላክነቱን ወደ ማወቅ ሲመጡና ለአምላክ የሚገባውን ክብር ሲሰጡት በመስማማት ሲያረጋግጥላቸው እንጂ አንድም ጊዜ ሲቃወማቸው አልታየም (ዮሐንስ 21:24-29)፡፡
➧ብዙ ጥቅሶችን እያነሳን በሚቀጥለው ክፍል እናያለን ።
ይቀጥላል ...
247
“የኢየሱስ ክርስቶስ ማንነት”
#የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክነት (መለኮትነት )_ክፍል_❶
አንዳንድ ወገኖች ከሚያነሷቸው ጥያቄዎች መካከል “ኢየሱስ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እኔ አምላክ ነኝና አምልኩኝ በማለት የተናገረበትን ቦታ አሳዩን” የሚለው አንዱና ዋነኛው ነው፡፡
ይህ አግባብ የሆነ ጥያቄ ቢመስልም ነገር ግን የኢየሱስ ክርስቶስን ተልዕኮ በትክክል ካለመረዳትና የመጽሐፍ ቅዱስን ቋንቋ በትክክል ካለማወቅ የመነጨ ጥያቄ ነው፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ ለመሆን የግድ እኔ አምላክ ነኝና አምልኩኝ በማለት መናገር ያስፈልገዋል የሚለው እሳቤ ምክንያታዊ አይደለም፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ኢየሱስ የእግዚአብሔር አንድያ ልጅ ስለመሆኑ፣ ስለስቅለቱ፣ ስለሞቱና ስለትንሳኤው የተናገረባቸው በርካታ ቦታዎች ይገኛሉ፡፡ እለዚህ ወገኖች እነዚህን እውነታዎች አለመቀበላቸው ኢየሱስ “አምላክ ነኝና አምልኩኝ” ያለበትን ቦታ ብናሳያቸው ሊቀበሉ እንደማይችሉ ያሳያል፡፡ ታድያ የጥያቄቸው ትክክለኛው ነጥብ ምንድነው?
እነዚህ ወገኖች በብሉይ ኪዳን ውስጥ እግዚአብሔር እርሱ እውነተኛ አምላክ መሆኑን የተናገረባቸውን ቦታዎች በመጥቀስ ኢየሱስ በምድር ላይ በነበረበት ጊዜ በተመሳሳይ መንገድ መናገር ነበረበት ይሉናል፡፡ ነገር ግን የብሉይ ኪዳን እና የአዲስ ኪዳን ዘመናት ልዩነት እንዳላቸው አይገነዘቡም፡፡ እግዚአብሔር በሁሉም ዘመናት በተመሳሳይ መንገድና ሁኔታ ራሱን መግለጥ የግድ አያስፈልገውም፡፡ ጥያቄያችን ሊሆን የሚገባው ኢየሱስ ክርስቶስ አምላክነቱን በምን ዓይነት መንገድ ነው የገለጠው? የሚል እንጂ “እኛ በምንፈልገው መንገድ ስላልተናገረ አምላክ አይደለም” በማለት መደምደም ትክክል አይደለም፡፡
በአዲስ ኪዳን ውስጥ ኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ መሆኑን በማያሻማ ሁኔታ ገልጧል፡፡ ነገር ግን ይህ መንገድ “አምላክ ነኝና አምልኩኝ” የሚሉትን እነዚህን ቃላት በመናገር ላይሆን ይችላል፡፡ ስለዚህ “እኔ ባልኩት መንገድ ካልተናገረ በስተቀር አምላክነቱን አልቀበልም” በማለት ሌሎች ማስረጃዎችን መካድ ጠያቂው መልስ ፈላጊ ሳይሆን ክርክር ፈላጊ መሆኑን ያሳያል፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ በምድር ላይ ይመላለስ በነበረበት ዘመን “አምላክ ነኝና አምልኩኝ” የሚሉትን እነዚህን ቃላት መናገር ያላስፈለገበትን የተወሰኑ ምክንያቶች መጥቀስ ይቻላል፡፡ ይህንን ስንል ግን ኢየሱስ ክርስቶስ አምላክነቱን ክዷል፣ ሸሽጓል ወይንም ደግሞ በምንም አይነት መንገድ አልተናገረም ማለታችን አይደለም፡፡
ይቀጥላል ...
247
...incarnation (ክፍል ➐)
"የኢየሱስ ክርስቶስ ፍጹም ሰው የመሆኑ አስፈላጊነት”
❺.የሕይወት አርዓያና ምሳሌ ሊሆነን፦
በምድር እያለን ከብዙ ሰዎች ልንማር ይገባል ግን ምሳሌያችን ሊሆን የሚገባው አንድ ብቻ ነው። እሱም ኢየሱስ ነው ።
የብሉይ ኪዳን አባቶቻችን ምሳሌዎች ሊሆኑን ይችላሉ ነገር ግን የየራሳቸው ጉድለት ነበራቸው ።
👉 አብርሃምን ብናነሳ ፦ አብርሃም በእግዚአብሔር ላይ ያለው እምነት እጅግ ጥልቅ ቢሆንም ፤ እግዚአብሔር በአደባባይ ይስሃቅን አዘጋጅቶ ፤ እሱ ያለ እግዚአብሔር እቅድ በጓዳ ወደ አጋር ገብቶ እስማኤልን ወልዷል።
👉ዳዊትንም ብናነሳ ፦ ዳዊትም በፍጹም እግዚአብሔርን የሚወድ ቢሆንና እግዚአብሔርም የልቤ ሰው እንኳ እግዚአብሔር የራሱን እቅድ በእሱ ላይ ልፈፅም ቢፈልግም ቤርሳቤህ ከጓዳው ነበረች።
💯 ግን ፍፁም ሰው እና ፍፁም አምላክ የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ ፤ ምንም እንኳ እንደ እኛ ቢፈተንም ፈፅሞ ኃጢአት የማያውቀው ብቸኛው ምሳሌያችን ነው ።
ሐዋርያው ዮሐንስም ፣ “ማንም በእርሱ እኖራለሁ የሚል፣ ኢየሱስ እንደ ተመላለሰ ሊመላለስ ይገባዋል”(1 ዮሐንስ 2:6) ብሎ ይነግረናል ። ቀጥሎም “ ወዳጆች ሆይ፤ እኛ አሁን የእግዚአብሔር ልጆች ነን፤ ወደ ፊት ምን እንደምንሆን ገና አልተገለጠም። እርሱ በሚገለጥበት ጊዜ እናየዋለን፤ እርሱን እንደምንመስልም እናውቃለን”(1 ዮሐንስ3:2)
👉ጳውሎስም ፣ “የእርሱን መልክ እንድንመስል... እንለወጣለን...”(2 ቆሮንቶስ 3:18)
👉ጴጥሮስም ፣ “የተጠራችሁትም ለዚሁ ነው፤ ምክንያቱም ክርስቶስ ስለ እናንተ መከራን የተቀበለው የእርሱን ፈለግ እንድትከተሉ ምሳሌን ሊተውላችሁ ነው”(1 ጴጥሮስ 2:21) ነው ይላል ።
🎯 ከኃጢአተኞች ወይም እግዚአብሔርን ከማያውቁ ሰዎች ፣ በሚደርስብን ጥላቻና ተቃውሞ ተስፋ ከቆረጥን “ እንግዲህ ዝላችሁ ተስፋ እንዳትቈርጡ፣ ከኀጢአተኞች የደረሰበትን እንዲህ ያለውን ተቃውሞ የታገሠውን እርሱን አስቡ” (ዕብራውያን 12:3)።
🎯 ኢየሱስ በሞቱም ምሳሌያችን ነው ።
የጳውሎስ ዓላማ ፣ “ በሞቱም እርሱን እንድመስል እመኛለሁ ” (ፊልጵስዩስ 3:10) በሞቱም ኢየሱስን መምሰል ነው።
🎯በሕይወት ዘመናችን ሁሉ እስከ እለተ ሞታችን ድረስ ክርስቶስንና እግዚአብሔርን በፅናት ታምነን እስከ ሞት ድረስ መታዘዝ ፣ በሌሎች ሰዎች ዘንድ ደግሞ በፍቅርና በይቅርታ መመላለስ ግባችን መሆን አለበት ።
247
#ክፍል_6 የኢየሱስ ክርስቶስ ሰው መሆን (incarnation)
❤“የኢየሱስ ክርስቶስ ፍጹም ሰው የመሆኑ አስፈላጊነት”❤
❸.በእግዚአብሔርና በሰው መካከል አማላጅ መሆን ፦
በኃጢአት ምክንያት ከእግዚአብሔር ተለይተን ስለነበር በእግዚአብሔርና በእኛ መካከል ገብቶ ወደ እግዚአብሔር የሚመልሰን ሰው አስፈለገን ።
🚩በእግዚአብሔር ፊት እኛን የሚወክልና በእኛ ፊት እግዚአብሔርን የሚወክል አማላጅ አስፈለገን።
💯ለዚህም መመዘኛውን የሚያሟላ አንድ ሰው ብቻ ( 🚧 አንድ ሰው ብቻ!🚧 አንድ ሰው ብቻ! ) ተገኘ።
(...“አንድ እግዚአብሔር አለና፤ ደግሞም በእግዚአብሔርና በሰዎች መካከል አንድ አስታራቂ አለ፤ እርሱም ሰው የሆነው ክርስቶስ ኢየሱስ ነው...” 1 ጢሞቴዎስ 2:5)
🛑ኢየሱስ ይህን የአማላጅነት ተግባር ለመፈጸም ፍጹም ሰውና ፍጹም አምላክ መሆን ነበረበት ።
🛑በሰውነቱ ብዙ የተፈተነ ስለሆነ ሁልጊዜ ድካማችንን ይራራል (ዕብ 2:8, 4:15-16)
❤ ዛሬም በአባቱ ቀኝ ሆኖ ስለ እኛ ይታያል ፤ በሰማያት ያለ የእኛ ሰው ነው ። የእኛ የእለት ተእለት ኑሮ ፣ የእኛ ፀሎት የእኛ ብርታት አይደለም ወደ ያቀረበን የፅድቅ ልብሳችን የሆነው የሁልጊዜ ድፍረታችን የሆነው አማላጃችን ኢየሱስ ነው። ደከመኝ ብለን ጉዞ ስናቆም ፤ ደከመኝ ብሎ ምልጃውን የማያቆም አማላጃችን ፣ ሊቀ-ካህናችን በሰማይ የእኛ ሰው ኢየሱስ ስሙ ይመስገን 🙏
🎶🎶🎶🎶🎶🎶🎶🎶🎶🎶
🎶 የመዳን ቀንዴ ጌታዬ 🎶
🎶 አምላኬ ያስነሳው ለእኔ 🎶
🎶 ከአብ ጋር ያስተራረቀኝ 🎶
🎶 ዘወትር ሚማልድልኝ 🎶
🎶 ውዴ የመዳን ቀንዴ (4x)🎶
🎶🎶🎶🎶🎶🎶🎶🎶🎶🎶🎶🎶
🎶ሊቀ-ካህን ሆኖልኛል ሊቀ-ካህን (2x)🎶
🎶አማላጄ ለዘለዓለም ነው ወዳጄ (2x)🎶
🎶ሊቀ-ካህን ሆኖልኛል ሊቀ-ካህን (2x)🎶
🎶አማላጄ ለዘለዓለም ነው ወዳጄ (2x)🎶
🎶🎶🎶🎶🎶🎶🎶🎶🎶🎶🎶🎶
❹ሰው ፍጥረትን በበላይነት ያስተዳድር ዘንድ የነበረውን የእግዚአብሔርን እቅድ/ዓላማ ከግብ ለማድረስ።
ሰው የእግዚአብሔር እንደራሴ/ተወካይ ሆኖ ምድርን እንድገዛትና በበላይነት እንዲያስተዳድራት እግዚአብሔር በምድር ላይ አስቀመጠው ። ነገር ግን ሰው በኃጢአት ሰለወደቀ ፣ ይህን ዓላማ ልፈጽም አልቻለም።
🚩ሁሉ ነገር በሰው ቁጥጥር ስር እንዲሆን እግዚአብሔር አቅዶ እንደነበር የዕብራውያን ፀሐፊ ይገነዘባል ፤ ዳሩ ግን ፤ “... ይሁን እንጂ በአሁኑ ጊዜ ሁሉም ነገር ተገዝቶለት አናይም።”
ኢየሱስ ሰው ሆኖ በመጣ ጊዜ ለእግዚአብሔር መታዘዝ ቻለ ፤ በዚህም እንደ ሰው ፍጥረትን በበላይነት ለማስተዳደር መብት ተሰጠው ፤ እግዚአብሔር ሰውን በምድር ላይ ሲያስቀምጥ የነበረውን የመጀመሪያ ዓላማም ከፍፃሜው አደረሰው ።
(.የክብርና የምስጋና ዘውድ ተጭኖለት እናየዋለን።ዕብ 2:9)
“ስልጣን ሁሉ በሰማይና በምድር” ለኢየሱስ ተሰጥቶታል (ማቴ 28:18) ...
(ኤፌ 1:22, 3:21 ሉቃ 19:17:19 1ቆሮ 6:3)
247
##ክፍል_⓹ ❤የኢየሱስ ክርስቶስ ሰው መሆን (incarnation)
📌ዛሬ በጣም አስፈላጊውን እና ኢየሱስ ሰው በመሆኑ ለእኛ ያመጣልንን ጥቅም እናያለን
🚩“የኢየሱስ ክርስቶስ ፍጹም ሰው የመሆኑ አስፈላጊነት”🚩
❶.ተተኪ ታዛዥ ለመሆን /በምትክነት ለመታዘዝ(For representative obedience )፦
ኢየሱስ ምትካችን በመሆን አደም ሳይታዘዝ የቀረውን ትዕዛዝ ታዞልናል።
📌ይህንንም በኢየሱስ ፈተናና (ሉቃ 4:1-13) በዔድን ገነት ለአዳምና ለሔዋን በተሰጠው የፈተና ጊዜ ( ዘፍ 2:15-3:7) መካከል ከነበሩት ጉድኝቶች ማስተዋል እንችላለን ።
📌ይህም በአዳምና በክርስቶስ መካከል ስለ አዳም አለመታዘዝ እና ስለ ክርስቶስ መታዘዝ ጳውሎስ በሮሜ 5 ካቀረበው ሀሳብ መረዳት እንችላለን ።
“ ሮሜ 5:18-19
18 ከእንግዲህ በአንድ ሰው መተላለፍ የተነሣ ኵነኔ በሁሉ ሰው ላይ እንደ መጣ፣ እንዲሁም በአንዱ የጽድቅ ሥራ ለሰው ሁሉ ሕይወትን የሚሰጥ ጽድቅ ተገኘ።
19 በአንዱ ሰው አለመታዘዝ ብዙዎች ኀጢአተኞች እንደ ሆኑ፣ በአንዱ ሰው መታዘዝ ደግሞ ብዙዎች ጻድቃን ይሆናሉ።”
📌በሌላም ቦታ ሐዋርያው ጳውሎስ ስናገር ኢየሱስ ክርስቶስ የመጨረሻው አዳም እንደሆነ ይናገራል ፤ “የመጨረሻው አዳም” (ሮሜ 5:18-19) ብሎ ሲጠራው ፤
አዳምን ደግሞ “የመጀመሪያው ሰው” ፤ ደግሞም ክርስቶስን “ሁለተኛ ሰው”(1ቆሮ 15:47) ብሎ ይጠራዋል ።
❤ኢየሱስ እኛን ተክቶ በእኛ ፈንታ ይታዘዝ ዘንድ ሰው ሆኖ፤ እኛም በእርሱ ምክንያት በአብ ዘንድ ታዛዦች ተብለን ተቆጠርን!
❷.በምትክነት ለመሞት እና ተተኪ መስዋዕት ለመሆን፦
ኢየሱስ ሰው ባይሆን ኖሮ፣ በእኛ ፈንታ ሞቶ ያለብንን ቅጣት መክፈል ባልቻለ ነበር። ( ...እርሱ የመጣው #መላእክትን ለመርዳት ሳይሆን፣ የአብርሃምን ዘር ለመርዳት እንደ ሆነ ግልጽ ነው።
17 ስለዚህ በሁሉም ነገር #ወንድሞቹን መምሰል ተገባው፤ ይህንም ያደረገው መሓሪና ታማኝ ሊቀ ካህናት ሆኖ፣ እግዚአብሔርን ለማገልገልና ለሕዝቡ የኀጢአትን ስርየት ለማስገኘት ነው። (ዕብ 2:16-17) )
❤ከአብ ጋር ሊያስታርቀን እኛን መሰለ። ለእኛ የቀረብክልን መስዕዋት ኢየሱስ ሆይ ስም ይመስገን 🙏
●➧በመሆኑም ኢየሱስ የሞተው በራሱ ምክንያት ሳይሆን በሰዎች ምክንያት በመሆኑ የእርሱ ሞቱ የምትክነት ሞት(Substitutionary death) ይባላል ።
ሰው ሁሉ ንፁህ ሆኖ እኔ ግን ቢቆሽሽ
በምድር ላይ እኔ ብቻ በኃጢአት ቢበላሽ
መሞት የሚገባኝ እኔ ብቻ ቢሆን
ኢየሱስ ለብቻዬ ይመጣልኝ ነበር
እንደ ኢየሱስ በምድር ላይ
ፈልጌ አጣው እሱን መሳይ
ስለዚህ እኔ አመልካለሁ
ቀር ዘመኔ የኢየሱስ ነው
ይቀጥላል...
247
#ክፍል_4 የኢየሱስ ክርስቶስ ሰው መሆን (incarnation)
ሐ.“ኃጢአት አልባነት” (ኢየሱስ ክርስቶስ ኃጢአት ፈጽሞ የሌለበት ብቸኛው ሰው ነው) ፦
📌 አድስ ኪዳን ፣ ኢየሱስ ልክ እንደኛ ሙሉ በሙሉ ሰው መሆኑን ቢናገርም ፣ ግን በአንድ ጠቃሚ ነገር የተለየ እንደሆነም ያረጋግጣል ፤ ይኸውም ኃጢአት አልባነት መሆኑ ነበረ ፤ በህይወት ዘመኑ ሁሉ ከቶ ኃጢአት አልሰራም።
📌አንዳንዶች ኢየሱስ ኃጢአት ካልሰራማ አማናዊ(እውነተኛ) ሰው አልነበረም ማለት ነው ፤ ሰው ሁሉ ኃጢአት ይሰራልና በማለት ይከራከራሉ ። ሆኖም ግን እግዚአብሔር ሰውን በመጀመሪያ በፈጠረው ጊዜ ሰው ኃጢአተኛ አልነበረም ነገር ግን ሰው ፍፁም ሰው ነበረ።
ስለሆነም ኢየሱስ እንደመጀመሪያው ሰው ከኃጢአት ነፃ የሆነ ፍፁም ሰው ነው ማለት ነው።
📌የኢየሱስ ኃጢአት- አልባነት በይበልጥ ግልጽ ሆኖ የሚገኘው በዮሐንስ ወንጌል ነው። “እኔ የአለም ብርሃን ነኝ” (ዮሐ 8:12) አስደናቂ አዋጅ ተናገረ ። ብርሃን እውነትንና ግብረ ገባዊ ንፅህናን እንደሚወክል ከተረዳን ፣ እዚህም ላይ ኢየሱስ በአለም ሁሉ የእውነት ፣ የግብረገባዊ ንፅህና የቅድስና ምንጭ መሆኑን እየገለፀ ነው።
📌ኢየሱስም በጲላጦስ ፊት በአይሁድ በተከሰሰ ጊዜ አይሁድ ክስ ቢያቀርቡበትም እንኳ ጲላጦስ “ እኔ የሚያስከስስ በደል አላገኘሁበትም ” (ዮሐ 15:10 ) በማለት ጉዳዩን ተቋጭቷል ።
📌በኃጢአተኛ ስጋ ምሳሌ እንጂ ኃጢአተኛ ሆኖ አልተገለጠም (ሮሜ 8:3)
📌ኃጢአት አያውቀውም ነበረ (2ቆሮ 5:21) ኢየሱስ ቢፈተንም ኃጢአትን ከቶ አላደረገም (ዕብ 4:5) እርሱ በክፉ አይፈተንምና (ያዕ 1:13)
📌ኢየሱስ ፦ “ቅዱስ ነቀፈ የሌለበት ንፁህ ከኃጢአተኞች የተለየና ከሰማያት በላይ የከበረ እንደዚህ ያለ ሊቀ ካህናት ነው”(ዕብ 7:26)
📌ጴጥሮስ በቀጥታ ፦ “ 1 ጴጥሮስ 2:22
22 “እርሱ ኀጢአት አላደረገም፤
በአፉም ተንኰል አልተገኘበትም።” ይላል።
📌ኢየሱስ ቅዱስና ነውር አልባ ነው (1ጴጥ 1:19, 3:18 1ዮሐ 2:1, 3:5)
📌የመፈተኑ አስፈላጊነት እኛን ይረዳን ዘንድ ነው(ዕብ 2:18)
247
##ክፍል_4 የኢየሱስ ክርስቶስ ሰው መሆን (incarnation)
ሐ.“ኃጢአት አልባነት” (ኢየሱስ ክርስቶስ ኃጢአት ፈጽሞ የሌለበት ብቸኛው ሰው ነው) ፦
📌 አድስ ኪዳን ፣ ኢየሱስ ልክ እንደኛ ሙሉ በሙሉ ሰው መሆኑን ቢናገርም ፣ ግን በአንድ ጠቃሚ ነገር የተለየ እንደሆነም ያረጋግጣል ፤ ይኸውም ኃጢአት አልባነት መሆኑ ነበረ ፤ በህይወት ዘመኑ ሁሉ ከቶ ኃጢአት አልሰራም ። 📌አንዳንዶች ኢየሱስ ኃጢአት ካልሰራማ አማናዊ(እውነተኛ) ሰው አልነበረም ማለት ነው ፤ ሰው ሁሉ ኃጢአት ይሰራልና በማለት ይከራከራሉ ። ሆኖም ግን እግዚአብሔር ሰውን በመጀመሪያ በፈጠረው ጊዜ ሰው ኃጢአተኛ አልነበረም ነገር ግን ሰው ፍፁም ሰው ነበረ።
ስለሆነም ኢየሱስ እንደመጀመሪያው ሰው ከኃጢአት ነፃ የሆነ ፍፁም ሰው ነው ማለት ነው።
📌የኢየሱስ ኃጢአት- አልባነት በይበልጥ ግልጽ ሆኖ የሚገኘው በዮሐንስ ወንጌል ነው። “እኔ የአለም ብርሃን ነኝ” (ዮሐ 8:12) አስደናቂ አዋጅ ተናገረ ። ብርሃን እውነትንና ግብረ ገባዊ ንፅህናን እንደሚወክል ከተረዳን ፣ እዚህም ላይ ኢየሱስ በአለም ሁሉ የእውነት ፣ የግብረገባዊ ንፅህና የቅድስና ምንጭ መሆኑን እየገለፀ ነው።
📌ኢየሱስም በጲላጦስ ፊት በአይሁድ በተከሰሰ ጊዜ አይሁድ ክስ ቢያቀርቡበትም እንኳ ጲላጦስ “ እኔ የሚያስከስስ በደል አላገኘሁበትም ” (ዮሐ 15:10 ) በማለት ጉዳዩን ተቋጭቷል ።
📌በኃጢአተኛ ስጋ ምሳሌ እንጂ ኃጢአተኛ ሆኖ አልተገለጠም (ሮሜ 8:3)
📌ኃጢአት አያውቀውም ነበረ (2ቆሮ 5:21) ኢየሱስ ቢፈተንም ኃጢአትን ከቶ አላደረገም (ዕብ 4:5) እርሱ በክፉ አይፈተንምና (ያዕ 1:13)
📌ኢየሱስ ፦ “ቅዱስ ነቀፈ የሌለበት ንፁህ ከኃጢአተኞች የተለየና ከሰማያት በላይ የከበረ እንደዚህ ያለ ሊቀ ካህናት ነው”(ዕብ 7:26)
📌ጴጥሮስ በቀጥታ ፦ “ 1 ጴጥሮስ 2:22
22 “እርሱ ኀጢአት አላደረገም፤
በአፉም ተንኰል አልተገኘበትም።” ይላል።
📌ኢየሱስ ቅዱስና ነውር አልባ ነው (1ጴጥ 1:19, 3:18 1ዮሐ 2:1, 3:5)
📌የመፈተኑ አስፈላጊነት እኛን ይረዳን ዘንድ ነው(ዕብ 2:18)
247
ኢየሱስ ክርስቶስ መልስ ሆኖን ካላረፍንበት ጥያቄ ሆኖ እንወዘወዝበታለን። በመልስነቱ ብንገፋው በጥያቄነቱ ይሞግተናል።
ዲ. አ. መ.
ኢየሱስ የሁልጊዜ ጥያቄያችን ነው ደግሞ የሁል ገዜ መልሳችን ነው ።
“የኢየሱስ ክርስቶስን ማንነት” እያጠናን ክፍል 3 ደርሰናል ዛሬ ክፍል 4 እንቀጥላለን
247
#ከፍል_3 የኢየሱስ ክርስቶስ ሰው መሆን (incarnation )
ለ.##የሰውነት_ባህሪያት_(የሰው ድክመትና_ውስንነት)...
1.ኢየሱስ እንደ እኛ ያለ አካል እንደነበረው መፅሐፍ ቅዱሳችን ብዙ ቦታ ይናገራል
📌ማንኛውም ህፃን እንደሚወለድ ተወለደ( ሉቃ 2፡52) እንደልጆች በጥበብ ፣በዕውቀት ፣ በቁመት ያድግ ነበረ (ሉቃ 2:40,52)
📌↖️ ይደክመው ነበረ (ዮሐ 4:6)
ልክ እኛን እንደሚደክመን እርሱንም ይደክመው ነበረ ፤
↖️ ይርበው ነበረ(ማቴ 4:2)
↖️ይጠማው ነበረ( ዮሐ 19:28)
↖️መላእክት ያገለግሉት ነበረ( ማቴ 4:11)
↖️ነፍሱን በእግዚአብሔር አጅ አደረ ሰጠ (ሉቃ 23:46)
📌ከሞትም ሲነሳ ሰብዓዊ አካሉ በሙሉ በትንሣኤ አካል ተነስቷል ። ስለሆነም ስጋና አጥንት ያለው አካል እንጂ መንፈስ አልነበረም ( ሉቃ 24:39)
በፊታቸውም ምግብ በልቷል (ሉቃ 24:42, ዮሐ 20:17,20,27 ዮሐ 21:9,13)
↗️ኢየሱስ በዚው አካል ሰማይም ይኖራል ።
2.ኢየሱስ ሰብዓዊ አዕምሮ ነበረው ፦
“ኢየሱስ በጥበብ.. አደገ”(ሉቃ 2:52) ኢየሱስ እንደ እኛው በመማር ህዳት እንዳሳለፈ ይህ ክፍል ይናገራል ።
እንዴት እንደሚበላ ፣ እንዴት እንደሚናገር ፣ እንዴት እንደሚያነብ ፣ ለወላጆቹ እንዴት እንደምታዘዝ (ዕብ 5:8)
3.ኢየሱስ ሰብዓዊ ነፍስና ፤ ሰብዓዊ ጥልቅ ስሜት ነበረው፦
ኢየሱስ ሰብዓዊ ነፍስ እንደነበረው የሚያመላክቱ ብዙ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች አሉ ።
↗️ነፍሱ ትታወክ ነበረ (ዮሐ 12:27),
↗️በመንፈሱ ይታወክ ነበረ ( ዮሐ 13:21)
↗️ነፍሱ ታዝን ነበረ (ማቴ 26:38)
↗️ይደነቅ ነበረ (ማቴ 8:10)
↗️ያዝንና ያለቅስ ነበረ (ዮሐ 11:35)
↗️በመራራ ጩኸትና እንባ ይፀልይ ነበረ (ዕብ 5:7)
📌ነፍስ 3 ክፍሎች አሏት 1.ስሜት
2.ፈቃድ
3.ዕውቀት
ክፍል 4 ይቀጥላል ... ✍️ወንድም አሻግሬ
247
እግዚአብሔርን #በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ብቻ ማወቅ ሳይሆን ፣ ራሳችንንም የምናውቀው #በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ብቻ ነው ፤ ህይወትና ሞትንም የምናውቀው #በኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ ነው ።#በኢየሱስ በኩል ካልሆነ በቀር የሕይወታችንንም ሆነ የሞታችንን ምስጥር ፤ የራሳችንንም ሆነ የእግዚአብሔርን ማንነት ለማወቅ አንችልም ። ”
(✍️ብሌይዝ ፓስካል )
“እግዚአብሔርን ማን እንደሆነ ለማወቅ ከፈለጋችሁ ኢየሱስን ተመልከቱ። ሰው መሆን ምን ማለት እንደሆነ ለማወቅ ከፈለጋችሁ #ኢየሱስን ተመልከቱ ። ፍቅር ምን እንደሆነ ለማወቅ ከፈለጋችሁ #ኢየሱስን ተመልከቱ። ሐዘን ምን እንደሆነ ለማወቅ ከፈለጋችሁ #ኢየሱስን ተመልከቱ።
( ✍️ ኤን ቲ ራይት )
ይሄን ጣፋጭ የሆነውን ኢየሱስን ማጥናት(እርሱን ማወቅ) ነፍስን ያሳርፋል ፤ ነፍስን ማሳረፍ ብቻ ሳይሆን ነፍስን ያሰፋል
#ኢየሱስ_ጣፋጭ_ነህ_እለት_እለት_ልብለህ🤲 ትላንት ##ክፍል_2 "የኢየሱስ ሰው መሆን"(incarnation ) የሚለውን ርዕስ ጀምረን ነበር ዛሬም እንቀጥላለን ...
247
#ክፍል 2 የኢየሱስ ክርስቶስ ሰብዓዊነት ( incarnation) ወይም “ሰው መሆን”
📌ሀ.ከድንግልና መወለዱ ፦ ስለ ክርስቶስ “ሰው” ወይም “incarnation” ስንናገር #ከድንግል መወለዱን ከግንዛቤ በማስገባት ብንጀምር በጣም ይጠቅማል ።
#ኢየሱስ ያለ ምንም ሰብዓዊ አባት አባት በመንፈስ ቅዱስ በመንፈስ ቅዱስ ተዓምራዊ ስራ በእናቱ በማርያም ማሕፀን እንደ ተፀነሰ መፅሐፍ ቅዱስ በግልጽ ያረጋግጣል ። (...እናቱ ማርያም ለዮሴፍ ታጭታ ሳይገናኙ፣ በመንፈስ ቅዱስ #ፀንሳ ተገኘች።ማቴዎስ 1:18)
👉ይገርማል! ግን በሰው አዕምሮ የማይተሰብ ነገር ሆነ ፣ ኢየሱስ #ከድንግል ተወለደ፤ #ድንግል እንዴት ትወልዳለች !
ይሄንን ስላለመኑ ነው የአለም ጠቢባን ሞኞች ሆነው የቀሩት ፤ እኛ ለአለም ሞኞች ሆነን ፤ በእግዚአብሔር ጥበብ ስላመንን (ድንግል መውለዷን ስላመንን) ጠብባን ሆንን !
📌 ኢየሱስ ##ከድንግል መወለዱ ለትምህርታችንም ለሕይወታችንም ትልቅ ጠቀሜታ አለው ( ሶስት ዋና ዋና ነገሮች)
1.#ደህንነት ከቶ ፣ በፍጹም በሰው ጥረት እንደማይመጣ ፤ የእግዚአብሔር ስራ ብቻ እንደሆነ እንረዳለን ! እግዚአብሔር፦ የሴቲቱ “ዘር” (ዘፍ 3፡15) በመጨረሻ የእባቡን ዘር እንደሚያጠፋ ቃል በገባው መሠረት ፣ በሰው ጥረት ሳይሆን በገዛ ኃይሉ እውን አደረገው።
የክርስቶስ ከድንግል መወለድ ፣ #ድነት #የእግዚአብሔር የራሱ ስራና ፣ የእኛ እጅ ያልታከለበት ፣ ከቶ በሰው ጥረት እንዳልሆነ የሚያሳስብ ብርት ትምህት ነው።
🚨ድነታችን በእግዚአብሔር መለኮታዊ ስራ ብቻ የሚፈፀም ነው ። ( ...ነገር ግን የተወሰነው ዘመን በደረሰ ጊዜ፣ እግዚአብሔር #ከ“ሴት” የተወለደውን፣ ከሕግም በታች የተወለደውን ልጁን ላከ፤
5 ይህም የሆነው #የልጅነትን መብት እናገኝ ዘንድ ከሕግ በታች ያሉትን ለመዋጀት ነው።ገላትያ 4:4-5)
2. ኢየሱስ ከድንግል መወለዱ #ፍፁም #አምላክነትና #ፍፁም #ሰውነት በአንድ አካል እንዲዋሐዱ አደረገ። እግዚአብሔር ልጁን ወደ አለም ለመላክ የተጠቀመበት ዘዴ ይህ ነበር ( ዮሐ 3፡16 ገላ 4፡4)
#ኢየሱስ ያለ ምድራዊ ወላጅ(ያለ ማርያም)ከሰማይ ስጋ እንደለበሰ ሙሉ ሰው ሆኖ ቢገለጥ እንደኛ ያለ ፍፁም ሰው መሆኑን #ማረጋገጥ አይቻልም ።
#ኢየሱስ ከእናትና ከስጋ አባት እንደኛ የተወለደ ቢሆን ፍፁም አምላክ መሆኑን ፈጽሞ #ማረጋገጥ አይቻልም ።
3.የክርስቶስ ከድንግል መወለዱም "የውርስ ኃጢአት" ሳይኖርበት እውነተኛ ሰው እንዲሆን ያስችለዋል ።
+ ኢየሱስም ሌሎች ሰዎች ከአዳም እንደተገኙ በተመሳሳይ ከአዳም አልተገኘም ፣ የስጋ አባት የለውም። ይህም የሰው ሁሉ ሕጋዊ በደልና ብልሹ ግብረገብ ክርስቶስ እንዳልወረሰ ያስረዳል ።
+ በተጨማሪ በማርያም ማህፀን ውስጥ መንፈስ ቅዱስ የሰራውን ስራ ማየትም ጠቃሚ ነው (ሉቃ 1፡35)።
ለ.የሰውነት ባህሪያት ( የሰው ድክመትና ውስንነት)...
ይቀጥላል ...
247
#ክፍል 2 የኢየሱስ ክርስቶስ ሰብዓዊነት ( incarnation) ወይም “ሰው መሆን”
📌ሀ.ከድንግልና መወለዱ ፦ ስለ ክርስቶስ “ሰው” ወይም “incarnation” ስንናገር #ከድንግል መወለዱን ከግንዛቤ በማስገባት ብንጀምር በጣም ይጠቅማል ።
#ኢየሱስ ያለ ምንም ሰብዓዊ አባት አባት በመንፈስ ቅዱስ በመንፈስ ቅዱስ ተዓምራዊ ስራ በእናቱ በማርያም ማሕፀን እንደ ተፀነሰ መፅሐፍ ቅዱስ በግልጽ ያረጋግጣል ። (...እናቱ ማርያም ለዮሴፍ ታጭታ ሳይገናኙ፣ በመንፈስ ቅዱስ #ፀንሳ ተገኘች።ማቴዎስ 1:18)
👉ይገርማል! ግን በሰው አዕምሮ የማይተሰብ ነገር ሆነ ፣ ኢየሱስ #ከድንግል ተወለደ፤ #ድንግል እንዴት ትወልዳለች !
ይሄንን ስላለመኑ ነው የአለም ጠቢባን ሞኞች ሆነው የቀሩት ፤ እኛ ለአለም ሞኞች ሆነን ፤ በእግዚአብሔር ጥበብ ስላመንን (ድንግል መውለዷን ስላመንን) ጠብባን ሆንን !
📌 ኢየሱስ ##ከድንግል መወለዱ ለትምህርታችንም ለሕይወታችንም ትልቅ ጠቀሜታ አለው ( ሶስት ዋና ዋና ነገሮች)
1.#ደህንነት ከቶ ፣ በፍጹም በሰው ጥረት እንደማይመጣ ፤ የእግዚአብሔር ስራ ብቻ እንደሆነ እንረዳለን ! እግዚአብሔር፦ የሴቲቱ “ዘር” (ዘፍ 3፡15) በመጨረሻ የእባቡን ዘር እንደሚያጠፋ ቃል በገባው መሠረት ፣ በሰው ጥረት ሳይሆን በገዛ ኃይሉ እውን አደረገው።
የክርስቶስ ከድንግል መወለድ ፣ #ድነት #የእግዚአብሔር የራሱ ስራና ፣ የእኛ እጅ ያልታከለበት ፣ ከቶ በሰው ጥረት እንዳልሆነ የሚያሳስብ ብርት ትምህት ነው።
🚨ድነታችን በእግዚአብሔር መለኮታዊ ስራ ብቻ የሚፈፀም ነው ። ( ...ነገር ግን የተወሰነው ዘመን በደረሰ ጊዜ፣ እግዚአብሔር #ከ“ሴት” የተወለደውን፣ ከሕግም በታች የተወለደውን ልጁን ላከ፤
5 ይህም የሆነው #የልጅነትን መብት እናገኝ ዘንድ ከሕግ በታች ያሉትን ለመዋጀት ነው።ገላትያ 4:4-5)
2. ኢየሱስ ከድንግል መወለዱ #ፍፁም #አምላክነትና #ፍፁም #ሰውነት በአንድ አካል እንዲዋሐዱ አደረገ። እግዚአብሔር ልጁን ወደ አለም ለመላክ የተጠቀመበት ዘዴ ይህ ነበር ( ዮሐ 3፡16 ገላ 4፡4)
#ኢየሱስ ያለ ምድራዊ ወላጅ(ያለ ማርያም)ከሰማይ ስጋ እንደለበሰ ሙሉ ሰው ሆኖ ቢገለጥ እንደኛ ያለ ፍፁም ሰው መሆኑን #ማረጋገጥ አይቻልም ።
#ኢየሱስ ከእናትና ከስጋ አባት እንደኛ የተወለደ ቢሆን ፍፁም አምላክ መሆኑን ፈጽሞ #ማረጋገጥ አይቻልም ።
3.የክርስቶስ ከድንግል መወለዱም "የውርስ ኃጢአት" ሳይኖርበት እውነተኛ ሰው እንዲሆን ያስችለዋል ።
+ ኢየሱስም ሌሎች ሰዎች ከአዳም እንደተገኙ በተመሳሳይ ከአዳም አልተገኘም ፣ የስጋ አባት የለውም። ይህም የሰው ሁሉ ሕጋዊ በደልና ብልሹ ግብረገብ ክርስቶስ እንዳልወረሰ ያስረዳል ።
+ በተጨማሪ በማርያም ማህፀን ውስጥ መንፈስ ቅዱስ የሰራውን ስራ ማየትም ጠቃሚ ነው (ሉቃ 1፡35)።
ለ.የሰውነት ባህሪያት ( የሰው ድክመትና ውስንነት)...
ይቀጥላል ...
247
እስቲ አንዴ አፍቅራችሁ የሚታውቁና የፍቅር ደብዳቤ የደረሳችው ሰዎች እጃችሁን አንሱ😁 ምን አይነት ስሜት አንዳለው ያው በደምብ ታውቃላችሁ 😁 ...
አሁን ደግሞ ሳታፈቅሩ ያፈቀራችሁን ፣ ሳትወዱት የወደዳችሁን ፤ የኢየሱስ ክርስቶስን እናጥና። አስቡ እስቲ ያፈቀራችሁ ሰው የሰጠውን ደብዳቤ ሳታነቡ ማስቀመጥ ትችላላችሁ ?🤔
የትላንቱ ክፍል ሁለት ዛሬ እንቀጥላለን 🫡
247
፨ #ክፍል 1 “የክርስቶስ ማንነት ”
📌ኢየሱስ፦ የግሪክ ቃል ሲሆን “መድኃኒት ፣ አዳኝ ” ማለት ነው።
በዕብራይስጥ “የሹዋህ” Yeho-shuah ትርጉሙ “ያህዌ” አዳኝ ነው “እግዚአብሔር አዳኝ ነው” ማለት ነው። (ማቴ 1፡21)
👉 በዚህ ስም ነው መዳን የሆነልን
📌ክርስቶስ፦ የተቀባ ፣ የተሾመ ማለት ነው ፣ ይህም የተላከበትን ዓላማና ስራ ሁሉ ለመፈጸም ስልጣን እንዳለው የሚገልጥ ማረጋገጫ የስልጣን ስም ነው ።
ክርስቶስ ከስምነት ይልቅ የኢየሱስን ማዕረግ እና ስልጣንን ይገልጣል ። (ማቴ 16፡16 ሐዋ 2፡36)
📌አማኑኤል፦ ትሥጉትን(አምላክ በስጋ መገለጡን) ወይም incarnation የሚለውን የሚያሳይ እና በሕዝቡ መካከል መኖሩን ስም ነው ። ትርጉሙም እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ማለት ነው ( ኢሳ 7፡14 , ማቴ 1፡23)
📌የእግዚአብሔር ልጅ፦ ዘላለማዊ የእግዚአብሔር የባህርይ ልጁ ፣ ማለትም ፍፁም አምላክ መሆኑን የሚገልጥ መጠሪያ ነው። ( ማቴ 16፡16) ዮሐ 20፡31)
📌የሰው ልጅ፦ በስጋ መገሉጡንና ፣ በስጋና በደም ከእኛ ጋር የተካፈለበትን ፍፁም ሰውነቱን የሚገልጥበት መጠሪያ ነው ። ( ማር 10፡45, ማቴ 26፡64)
📌ጌታ፦ በግሪኩ ኩሪዮስ የሚለው ቃል የተተረጎመው ላለና ለነበረው ለአምላክ ስም ያህዌህ ለሚለው ሲሆን በግሪኩ መጽሐፍ ቅዱስ ፈጣሪና ፣ ፍጥረቱን መጋቢ ለሆነ አምላክ ለሆነ አምላክ የሚቀጸል መጠሪያ ነው
📌👑ንጉስ፦ በዳዊት ዙፋን ላይ የሚቀመጥበት ፣ በያዕቆብ ቤት ሁሉ ላይ ፣ በኢየሩሳሌም በታላቁ ንጉስ ከተማ የሚነግስበት ስልጣኑን የሚያሳይ መጠሪያ ነው ( ማቴ 2፡1-11, 27፡37)
📌የዳዊት ልጅ፦ እግዚአብሔር ለዳዊት በዙፋኑ ላይ ለዘላለም የሚቀመጥ ልጅ እንደሚያስነሳለት ተስፋ ሰጥቶታል እናም አይሁድ ሁሉ ተስፋ የሚያደርጉት ንጉሳቸው መሆኑን የሚገልጥ መጠሪያ ነው ( መዝ 89፡28-37 ማቴ 10፡48)
ይቀጥላል ...
247
መግቢያ
“የክርስቶስ ማንነት ”
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሥጋን ለብሶ ከተወለደበት ጊዜ ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ ሰዎች በእርሱ ማንነት ላይ የተለያየ ዓይነት ገለጻ ሲሰጡ ይስተዋላሉ፡፡ በማንነቱ ላይ በነበራቸውም አልመግባባት ብዙ የኃይማኖት ተቋማት ሊመሠረቱ ችለዋል፡፡ እንዲህ ዓይነቱ ግራ መጋባት የተጀመረው ዛሬ ሳይሆን ከጥንት ነው፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋሪያቱን ሦስት ዓመት ተኩል ካስተማራቸው በኋላ አንድ ወሳኝ ጥያቄ ይጠይቃችኋል፤እንዲህ በማለት፡- ''ሰዎች የሰውን ልጅ ማን እንደ ሆነ ይሉታል?'' አላቸው (ማቴ 16፡13)፡፡ በእርግጥ ሐዋሪያቱ የተጠየቁት ጥያቄ በጣም ከባድ እንደሆነ ግልጽ ነው፡፡ ምክንያቱም ለሦስት ዓመት ተኩል የተማሩት ትምህርና የወሰዱት ሥልጠና በዚህ ጥያቄ ልቋጭ ነውና፡፡ እነርሱም፡- ''አንዳንዱ መጥምቁ ዮሐንስ፥ ሌሎችም ኤልያስ፥ ሌሎችም ኤርምያስ ወይም ከነቢያት አንዱ ነው ይላሉ አሉት'' (ማቴ 16፡14)። ኢየሱስም መልሶ ''እናንተስ እኔን ማን እንደ ሆንሁ ትላላችሁ? አላቸው'' (ማቴ 16፡15)። ከመካከላቸውም ጴጥሮስ ኢየሱስን እንዲህ አለው፡- ''አንተ ክርስቶስ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ነህ አለው'' (ማቴ 16፡15)። ዳሩ ግን ለጴጥሮስ ይህን መልስ የገለጠው እግዚአብሔር አብ ነበር (ማቴ 16፡17)፡፡ እግዚአብሔር አብ እስካልገለጠ ድረስ ወልድን ሊያውቅ የሚችል ከቶ የለምና (ሉቃ 10፡22)፡፡
📚 Android Application so called ‹‹መሠረታዊ የክርስትና አስተምህሮ›› is developed by Fantahun Beyene.
247
ወገኖች (በክርስቶስ ወንድሞችና እህቶቼ ) ፀጋና ሰላም ይብዛላችሁ ።
ሳምንቱን( በተከታታይ) የክርስቶስ ማንነት በሚል ሀሳብ እያጠነው ስለሆነ ...
ሌላ እቅድ የሌላችሁ ማታ ማታ (3፥00) ከእኔ ጋር ማጥናት ትችላላችሁ (ያጣናውትን በትንሹ አካፍላችዋለሁ)
reference (ማጣቃሻ መፅሐፍት የሚሆኑት )📚
📚(systematic theology.✍️“Wayne grudum”
📚የእግዚአብሔር ልጅ ✍️“ጳውሎስ ፈቃዱ”
📚የመዳን እውቀት ✍️“ተስፋኹን ነጋሽ ”
📚knowing God✍️J.I. packer
📚This Android Application so called ‹‹መሠረታዊ የክርስትና አስተምህሮ›› is developed by Fantahun Beyene.
ከነዚህ መፅሐፍት ይሆናል መፅሐፍቶቹን ካገኛችሁ እንድታነቡት ነው ስማቸውን እና ደራስዎቹን mention ያረኩት!
ግን እንግሊዝኛውን የት አባቱ ብዬ ገና እያሞከርኩ ነው😁
