The Legal Oracle(Ye_Hig Mahider)
رفتن به کانال در Telegram
Official channel of Almaw Wolie https://www.linkedin.com/in/almaw-wolie-82775183?utm_source=share_via&utm_content=profile&utm_medium=member_android
نمایش بیشترکشور مشخص نشده استدسته بندی مشخص نشده است
1 963
مشترکین
+2124 ساعت
+787 روز
+1 25830 روز
آرشیو پست ها
Delay_in_the_Performance_of_Contractual_Obligations_2nd_Edition.pdf8.04 MB
Owning_Intelligence_How_AI_is_Reshaping_Intellectual_Property,_Risk.pdf3.69 MB
General_Theory_of_Law_New_Challenges,_Current_Issues_and_Innovative.pdf3.97 MB
Hermeneutics_of_Law_From_Ancients_to_Contemporaries_Johann_Michel.pdf6.26 MB
አዲስ ጽሑፍ
"ከልሂቃን ውል እስከ ሕዝባዊ ውዴታ፦ የ1787ቱ የፊላደልፊያ ጉባኤና የዘመኑ የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር በንፅፅራዊ ሕገ መንግሥታዊ ዕይታ"
ውድ የቻናላችን ተከታዮች !
ከሁለት መቶ ዓመታት በፊት 55 ባለጸጋ ልሂቃን በተዘጋ ደጅ የአሜሪካን ሕገ መንግሥት ሲቀርጹ፣ ዛሬ ኢትዮጵያ ከ4,000 በላይ ልጆቿን ሰብስባ ስለ ነገዋ እየመከረች ነው። እነዚህ ሁለት ታሪካዊ ሂደቶች ምን ያመሳስላቸዋል? ምንስ ይለያያቸዋል?
በዚህ አጭር ጽሑፍ ውስጥ የሚከተሉትን ወሳኝ ጉዳዮች በሂሳዊ ዕይታ አቅርቤአለሁ፦
የአሜሪካ ሕገ መንግሥት አርቃቂዎች ማንነት፣ የአመራረጥ ሂደትና የተደበቀ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም፣ የ1787ቱ ጉባኤና የዛሬው የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ጎን ለጎን ንፅፅር፣ የአካታችነትና የስምምነት አስገዳጅነት ውጥረትየትኛው ነው ለዘላቂ ሰላም ወሳኙ?፣ ለኢትዮጵያ ተስማሚ የሆኑ የደቡብ አፍሪካና የስዊዘርላንድ የሕገ መንግሥት ማሻሻያ ሞዴሎች የሚሉት
ሙሉ ጽሑፉ ከላይ ተያይዞ ያገኙታል።
NB: ካነበቡ በኋላ አስተያየትዎን፣ ሂሳዊ ምልከታዎንና ጥያቄዎን ከታች ማጋራት አይርሱ—ውይይቱ ይቀጥል!
#ሕገመንግሥት #አገራዊምክክር #ኢትዮጵያ #ንፅፅራዊ_ጥናት
በኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 20(1) ሥር በተደነገገው "በምክንያታዊ ጊዜ ውስጥ የመዳኘት መብት" ጽንሰ-ሐሳብ እና በኢትዮጵያ የወንጀል ፍትሕ ሥርዓት ተጨባጭ እውነታዎች መካከል ባለው ሰፊ ክፍተት ላይ የሚያጠነጥን አጭር ትንተናዊ ጽሑፍ አጋርተናችኋል።
ይህ ጽሑፍ "ምክንያታዊ ጊዜ" (Reasonable Time) እና "ፈጣን ዳኝነት" (Speedy Trial) የሚሉትን መመዘኛዎች ፍልስፍናዊና ዶክትሪናዊ ልዩነት ከመፈተሽ ባለፈ፣ ረጅም የቅድመ-ፍርድ እስራትና ሥርዓታዊ የመዝገቦች መከማቸት በሕገ-መንግሥታዊ ዋስትናዎች ላይ የሚደቅኑትን ተግዳሮቶች በወፍ በረር ይዳስሳል። ጽሑፉ ለአገራችን የወንጀል ፍትሕ ሥርዓት መሻሻልና ለሰብዓዊ መብቶች መከበር መጠነኛ ምሁራዊ አስተዋጽኦ ያበረክታል የሚል ተስፋ አለን። የሕግ ምሁራን፣ ጠበቆች፣ ዳኞች፣ የሕግ ተማሪዎችና ጉዳዩ የሚመለከታችሁ ሁሉ ጽሑፉን ከላይ ከተያያዘው ላይ አውርዳችሁ እንድታነቡት፣ እንዲሁም ገንቢ አስተያየታችሁንና ሙያዊ ትንተናችሁን በኮሜንት መስጫው ላይ እንድታካፍሉን በአክብሮት እጋብዛለ።
መልካም ንባብ!
አልማው ወሌ
